Veronica Melaku


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic
Category: Blogs


ይህ የቴሌግራም ቻናል ነሐሴ 18/2013 ተከፈተ!

Related channels  |  Similar channels

Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Category
Blogs
Statistics
Posts filter


እናርጅ እናውጋ!
በአማራ ክልል እናርጅ እናውጋ ውስጥ በአብይ ቡድን የተፈፀመው ጭፍጨፋ የሚነግረን በጣም ብዙ ነገር አለ፡፡ ዋናው መልእክት የንፁሃኑ ጭፍጨፋ መጪውን እጅግ አስከፊ ዘመን የሚያሳይ መሆኑ ነው፡፡ ከዚህ በላይ ጭፍጨፋና ከዚህ በላይ ግፍ እየመጣ እንደሆነ የሚያረጋግጥ ነው፡፡ ንፁሃንን ጨፍጭፈው “ፅንፈኛ ተደመሰሰ” እንደሚሉ የሚያረጋግጥ ነው፡፡ ንፁሃንን አግተው የታገተ ሰው እየለም እያሉ እንደሚክዱ፣ አማሮችን በገፍ አስረው ግፍ እየፈፀሙ ግፍ የተፈፀመበትና የሚፈፀምበት ሰው የለም እያሉ እንደሚናገሩ፣ ይህንን ፕሮፓጋንዳቸውን ደግሞ ህዝብ እስኪሰለች በማቅረብ ለማሳመን እንደሚሞክሩ የሚያሳይ ነው፡፡

የቡድኑ መመሪያ ዳንኤል ክብረት በአፋሪካ አመራር አካዳሚ የብልፅግናን ካድሬዎች ሰብስቦ ሲያሰለጥን የተናገረው ነው፡፡ “በዚህ ድህረ እውነት አለም ማሸነፍ የሚቻለው አንድን ጉዳይ ደግሞና ደጋግሞ በተቀናጀ ሁኔታ በማቅረብ ነው፡፡ አንድን ጉዳይ ዳጋግመን ስናቀርበው ህዝቡ ‹አሁንስ በዛ!› ካለ ገብቶታል ዓላማችንም ተሳክቷል ማለት ነው” ብሎ ነበር፡፡ የብልፅግና የኮሙኒኬሽን ስትራቴጂ ይህ ነው፡፡ የአብይ ቡድን ብርቱካን በተባለች እህታችን ላይ ያደረገውን እርብርብ እና የእኛን ምላሽና ሽንፈት ልብ ይሏል፡፡ እንደ መሳይ መኮነን ያሉ የኮሙኒኬሽን ስትራቴጂ ያልገባቸው ሰዎች “አሁንስ አበዛችሁት! አሁንስ እጅ እጅ አላችሁ!” እያሉ ሲጽፉ ስናይ የነዳንኤል ክብረት ስትራቴጂ ምን ያህል እንደሰራ እንገነዘባለን፡፡ መሳይ መኮነንን በስም ጠቀስነው እንጅ ሁላችንም ከዚያ የተሻለ ስራ አልሰራንም፡፡ አጀንዳውን ሙጭጭ ብለን መያዝ ሲገባን አስረክበን ቤታችን ገብተናል፡፡ በዚህም ምክንያት ቀጣይ ብዙ አማራ ቢያልቅና ብንዘግበው ያንንም አጀንዳ ውሸት ነው ብሎ እንደሚያስጥለን የሚያሳይ ነው፡፡ አሳፋሪ አክቲቪዝም!
የአብይ ቡድን ስራውን እየሰራ ነው፡፡ መጪው ጭፍጨፋ ከእናርጅ እናውጋ እየበለጠ እንደሚሄድ መጠራጠር አይገባም፡፡ የጅምላ እስሩና ስቃዩ፣ ስደቱ፣ አንገት መድፋቱ ሁሉ እየመጣ ነው፡፡ ይህን እጅግ አስቀያሚ ሁኔታ መቀልበስ ግን ይቻላል፡፡ የችግሩም ሆነ የመፍትሄው ምንጮች ደግሞ እኛው ነን፡፡ ሌላ ቦታ ማንጋጠጥ አይገባም፡፡
መፍትሄው በየእለቱ የሚጠቃው ህዝባችን ጥቃትና ውርደት ተሰምቶን ለህዝባችን ስንል፣ ከእርስ በእስር መጠፋፋት፣ ከእርስ በእስር ጥላቻ፣ ከቂምና ከበቀል መራቅ እና “ያለፈው አለፈ” ብሎ መተባበር ብቻ ነው፡፡ መፍትሄው “እኔ ብቻ ነኝ ትክክል፣ የእኔ መንገድ ብቻ ነው ትክክሉ” ከሚል ከንቱና ፍሬ ቢስ አስተሳሰብ እርቆ ለህዝብ ህልውናና ጥቅም ሲባል መተባበር ነው፡፡ መፍትሄው ለጋራ አሸናፊነት ሲባል መሸነፍ ነው፡፡ መፍትሄው ራስን ከከፋፋይ አክቲቪስት ማራቅ ነው፡፡ መፍትሄው ራስን፣ ትግሉንና የጠላትን ሁኔታ በየጊዜው መገምገምና ሁኔታው የሚጠይቀውን ስትራቴጂ መቅረጽ ነው፡፡ መፍትሄው በእቅድ መመራት ነው፡፡ ከሁሉም በላይ ዋናውና ቁልፉ መፍትሄ በአማራ ብሄርተኝነት ርእዮት መመራት ነው፡፡
ከንቱዎች እንደሚሉትና እንደሚመስላቸው ከትግሉ ሜዳ እስክንድር ነጋ ባይኖር ወይም ሌሎች ከንቱዎች እንደሚመስላቸው ዘመነ ካሴ ቢወጣ የሚመጣ አንዳችም ለውጥ የለም፡፡ የአማራ ትግል ችግር ከእነዚህ ግለሰቦች በላይ በመሆኑ የእነዚህ ግለሰቦች መኖር አለመኖር ጋር ሊያያዝ አይችልም፡፡ ስለሆነም ከግለሰቦች ራስ ወርዶ (ከማሞገስና ከማኮሰስ ተቆጥቦ) በድርጅት ግንባታ ላይ ማተኮር ነው፡፡ እንደ ህዝብ የእኛ ትልቁና ቋሚው ድክመታችን የድርጅት ግንባታ ችግር ነው፡፡ ይህን ፈተና ሳናልፍ የምናመጣው አንዳችም ለውጥ የለም፡፡ ስለሆነም ከዋናው ጠላት በላይ ግለሰቦችን ዋነኛ ኢላማ በማድረግ ጎራ ለይቶ መጠፋፋቱ የጋራ ውድቀትን ካልሆነ በስተቀር የሚያስገኘው አንዳችም ውጤት የለምና ከዚህ የጥፋት ጎዳና መውጣት ይጠበቅብናል፡፡ ኋላቀርነት ይብቃ! ከጠላት ይልቅ በጠላት ላይ መጨከን ይብቃ!

ይህ ሳይሆን ቀርቶ የፋኖ ትግል አሁን ባለበት የእውር-ድንበር ጎዳና የሚቀጥል ከሆነ ግን እንኳን ህዝብን ነፃ ሊያወጣ የራሱንም ህልውና መጠበቅ አይችልም፡፡ ከመንቦጅቦጅ ወጥቶ የሰከነ የትግል ምህዋር ውስጥ መግባት ግዴታ ነው፡፡

የወገኖቻችንን መስዋእትነት ወደ ሞት እንዳንቀይረው እንጠንቀቅ!

ለገባንበት መቀመቅ ዋነኛዎቹ ተጠያቂዎች እኛው ራሳችን መሆናችንን እንቀበል!

አማራ ብሄርተኝነት ይለምልም!!!


ሻለቃ መንበሩ ተሰዋ ነው የምትሉኝ!? 😭


😖


በመዘናጋትና በእንዝላልነት ከምንፈጥራቸው ለድሮን ጥቃት ምቹ ሁኔታዎች እራሳችን እናርቅ!


👆 መልሱ ከፍያለው ደሴ
በፋሽስት ወራሪ ኦህዴድና በጀግናው የጎንደር ክፍለ ሃገር 206ኛ ኮር ሰራዊት መካከል በመድፍና በሮኬት የተደገፈ ውጊያ እየተካሄደ መሆኑ ከጋይንት ግንባር ያገኘሁት መረጃ ያመለክታል:: ጀግናው የ206ኛ ኮር ዋና አዛዥ ኮሎኔል አዲሱ ደባልቄና በሜጀር ጀኔራል ከፍያለው ደሴ የአማራ ፋኖ ጎንደር ጠቅላይ ግዛት ዕዝ ምክትል ወታደራዊ አዛዥ የሚመራው ሰራዊት በጀግንነት የፋሽስት ወራሪ ኦህዴድን መንጋ እየደመሰሰው መሆኑ የሚወጡ ዘገባዎች ያመለክታሉ:: በጋይንት አውራጃ ታች ጋይንት ወረዳ ልዩ ስሙ አጋጥ ሚካኤል በሚባል አካባቢ የጠላት ሰራዊት በከፍተኛ ደረጃ ተደምስሶ ወደመጣበት አርብ ገበያ ከተማ መመለሶን ከሰራዊቱ ኢንዶክትሪነሽን መምሪያ ያገኘሁት መረጃ ያመለክታል።

March 13/2025 የተለጠፈ ነበር


በነገራችን ላይ በ2015 ሀምሌ መጨረሻ የአማራ ፋኖ የኦሮሙማውን አገዛዝ ለመፋለም አሐዱ ብሎ ውጊያ የጀመረው አርበኛ ከፍያለው ነበር። በታች ጋይንት እና በፋርጣ ወረዳ ቆላማ አካባቢዎች ያደራጃቸውን ፋኖዎች በመያዝ ወደ ደብረታቦር ከተማ በመምጣት የ6 ቀን ውጊያ በማደረግ የትግሉን ችቦ የለኮሰው እርሱ ነበር!! ከፍያለውን ተከትሎ በባህርዳር፣ ጎንደርና ሌሎች አካባቢዎች ትግሉን ተቀላቀሉ!!!!

ይሔን የመሰለ ጀግና የህዝብ አለኝታ በክህደት ሲገደል ትግሉ አደጋ ላይ እንዲወድቅ ሁኗል!!!


ጥያቄ
የአማራ ህዝብ መጨፍጨፍና መራቆት በቃ ብሎ የኦሮሙማው ሀይል ላይ #የመጀመሪያዋን ምላጭ የሳበ ፋኖ ማን ይባላል??

መልሱን ቀጣይ አያይዛለሁ


ለምጣዱ ብየ አይጧ  ትለፍ አልልም!! በጭራሽ!
ዛሬ በእናርጅና እናውጋ ወረዳ የፋኖ ታጣቂዎች በምን ምክንያት እንደተሰባሰቡ ለጊዜው ማረጋገጥ ባልችልም በአሳዛኝ ሁኔታ በድሮን ተጨፍጭፈዋል  😭

የአማራ ፋኖ በጎጃም ደግሞ እውነቱን ክዶ የሀሰት ፕሮፖጋንዳ እየሰራ ይገኛል። ከ120 በላይ ተጨፈጨፉ ይልና ምክንያቱ ደግሞ

ቤት ለመስራት እንጨት በደቦ የተሸከሙ
ለፋሲካ በዓል ዝግጅት ሲያደርጉ የነበሩ

ይላል!

ባይሆን የሚመስል ፕሮፖጋንዳ ስሩ፤ የትግሉ ሰማዕታትም አታራክሱ!!

ማስታወሻ
የህልውና ትግል የሀሰት ፕሮፓጋንዳ አያስፈልገውም!!


ያሳዝናል!!
አገዛዙ እስከዛሬ በአማራ ምድር ካደረጋቸው የድሮን ጥቃቶች ሁሉ የዛሬ ስኬታማ እንደነበር የወጣው ሪፖርት ያሳያል!! እንዴት ሊሆን ቻለ? ፋኖዎች እንዴት በዚህ መጠን ተሰባስባው ለድሮን ጥቃት ተጋላጭ ሆኑ!?
የወንድምክን ስብዕና ገደላ ትተህ፣ ግልገል አምባገነን የመሆን አምሮትክን ገተህ፣ ከመሰሎችህ ጋር ተቀምጠህ ካልመከርክና ካልተገማገምክ መጨረሻህ በድርድር ሰበብ ለአገዛዙ እጅ ትሰጣለህ፤ ትደመሰሳለህ ወይም ጥሻ ለጢሻ ትቆያለህ!! በዚህ ሁሉ ሒደት አማራው ዋጋ ይከፍላል!!


የአብይ አህመድ ቡድን!
የአብይ አህመድ ቡድን ምርጫ ያካሂዳል፡፡ የተወሰኑ ወንበሮችን ለአጋሮቹ ይለቅና በከፍተኛ ድምጽ ማሸነፉን ያውጃል፡፡ ምርጫውን ተከትሎ እሱን በሚጠቅም መልኩ የህገ መንግስት ማሻሻያ ያካሂዳል፡፡ የአማራ ህዝብ ጥያቄዎች ተካተዋል እንዲባል አንዳንድ የአማራ ህዝብ ወሳኝ ጥያቄዎች ያልሆኑ እንደ ሰንደቅአላማ ያሉ ጉዳዮችም ይሻሻላሉ፡፡ በአዲስ አበባ ዙሪያ የኦሮሞ ብሄርተኞች ተጨማሪ ጉዳዮችን ያካትታሉ፤ ኦሮምኛ ቋንቋን የስራ ቋንቋ ያደርጋሉ ወዘተ። የኮሪደር ልማቱና ሌላው የህዝብን ቀልብ ሊገዛ የሚችል ብልጭልጭ፣ ግን ደግሞ የተወሰነ ቡድንን የሚያከብር “ልማት” ተጠናክሮ ይቀጥላል፡፡ አብይ የአረንጓዴ ልማት አርበኛ ተብሎ እንዲሸለም ሎቢ ይደረጋል፡፡ ገንዘብ ተከፍሎም ሆነ በሌላ መንገድ ሽልማቱም ይመጣል፡፡ "ህዝቡ ነፃነት ተሰጥቶት ነፃነትን ማስተዳደር አልቻለም” ተብሎ የአብይን ቡድን አሜን ብሎ እንዲቀበል ይደረጋል…

የፋኖ ትግል አሁን በተያዘው የእውር-ድንብር መንገድ የሚቀጥል ከሆነ በራሱ በፋኖው ድክመትና በዲያስፖራው መጋለብ ምክንያት ይሽመደመዳል፡፡ ግሽበት ክሽፈትን ይወልዳል፡፡ የተወሰነው የፋኖ ታጋይ እጁን ይሰጣል፡፡ የሚታሰረው ይታሰራል፤ ፍርፋፊ የሚሰጠው ይሰጠዋል፡፡ የተወሰነው ይሰደዳል፡፡ የተወሰነው እያንገራገረ በጫካዎች ውስጥ ይንቀሳቀሳል፡፡ የሚያመጣው ጠብ የሚል ለውጥ ግን አይኖርም፡፡ ከፋኖው ትግል መዳከም ጋር ተያይዞ አብዛኛው አክቲቪስት ነኝ ባይም ጥጉን ይይዛል፡፡

በዚህ ሂደት በአማራ ህዝብ ዘንድ ከፍተኛ ተስፋ መቁረጥና ቁዘማ ይነግሳል፡፡ ብዙዎች ራሳቸውን ከፖለቲካ ያገላሉ፡፡ ብዙዎች ጥቅመኛ የሆነ የአካባቢ ወይም የሃይማኖት ፖለቲካ ሊያራምዱ ይችላሉ፡፡ “የአማራ ብሄርተኝነት አይድንም፤ የአማራ ፖለቲካ አልቆለታል” ብሎ ተስፋ የሚቆርጠው ነፋስ አመጣሽም ብዙ ነው፡፡ ለውድቀቱ ሁሉም ተጠያቂነት ያለበት ቢሆንም መካሰሱ ተጠናክሮ ይቀጥላል፡፡ ሁሉም ራሱን ከተጠያቂነት ለማዳን ሌሎችን መክሰሱን ይቀጥልበታል፡፡ መካሰሱና መጠፋፋቱ በሌላ መልክ ይቀጥላል፡፡

ለማንኛውም የአማራ ህዝብ መከራ መራዘሙ እርግጥ ነው፡፡ ይህም በጠላት አቅም ሳይሆን በእኛው በራሳችን ውድቀት ምክንያት የመጣ ነው፡፡ ዋነኛው ውድቀታችን በኤሊት ደረጃ ስር ከሰደደው የእውቀት ድህነት ጋር የተያያዘ ነው፡፡ የእውቀት ድህነት የወለደው እልህ፣ መጠፋፋት፣ ጥቅመኝነትና ህዝበኝነት የትግሉ ነቀርሳ ነው፡፡
የብሄርተኝነት ምንነትና ኃያልነት የገባቸው ጀግኖች ግን ጸንተው በትግላቸው ይቀጥላሉ፡፡ የፋኖ ትግል የአማራ ብሄርተኝነት አንዱ ገጽታ እንጂ የአማራ ብሄርተኝነትን እንደማይተካ የሚገነዘቡ ብሄርተኞች ጸንተው ይቀጥላሉ፡፡ ዛሬ በነፋስ አመጣሽ ተውጠው የሚሰቃዩት ጽኑዎቹ የአማራ ብሄርተኞች ይበልጥ ይጠናከራሉ እንጂ አይዳከሙም፡፡ የፖለቲካን ተቀያያሪ ባህሪ ስለሚገነዘቡ ደቅድቅ ጨለማ የመሰለው የዛሬው ሁኔታ በትግል እንደሚቀየር ይረዳሉ፡፡ ስለሆነም ከቶም ተስፋ አይቆርጡም፡፡ የእስካሁኑን ሂደት ገምግመው አዳዲስ የጥናት መጽሔቶችን (ጆርናሎችን) ይፈጠራሉ፡፡ አዳዲስ ሲቪክ ማህበራትን ይገነባሉ፡፡ አዳዲስ የአማራ ተቋማትን ያብባሉ፡፡ አሁን ያሉትና በአረም የተዋጡት ተቋማት እንዲጠሩና እንዲታረሙ ይደረጋል፡፡ የማይድነው ተፈጥሯዊ ሞቱን ይሞታል፡፡ መሞቱም ጥቅም እንጂ ጉዳት የለውም፡፡
በአለም ታሪክ “ሞቢሊላይዝድ” ሆኖ እንደገና የከሰመ ብሄርተኝነት የለም፡፡ ስለሆነም የአማራ ብሄርተኝነት በየጊዜው ከሚገጥሙት ፈተናዎች እየተማረ በትውልዶች ቅብብል እያደገና እየጎመራ ይሄዳል እንጂ አይሞትም፡፡ ስለሆነም ይህን ሃቅና መጪውን የጭቆና ዘመን የተገነዘቡ የአማራ ልጆች ከወዲሁ ቦታ ቦታቸውን መያዝ አለባቸው፡፡ የመጀመሪያ ዲግሪ፣ የማስተርስና የዶክትሬት ዲግሪ መመረቂያ ጽሁፋቸውን በአማራ ታሪክ እና በአማራ ብሄርተኝነት ላይ ማድረግ አለባቸው፡፡ በአማራ ጥናት ዙሪያ በታወቁ መጽሄቶች ላይ ማሳተም ይጠበቅባቸዋል፡፡ አመታዊ የአማራ ጥናት ጉባኤዎችን በየአሁጉሩ ማካሄድ ይገባቸዋል፡፡ በብሄርተኞች የሚመሩ አዳዲስ የጥናትና ምርምር፣ የሰብአዊ መብት፣ የሎቢ፣ የባህል እና የፖለቲካ ተቋማትን ማቋቋም ያስፈልጋል፡፡

የኤርትራ ብሄርተኞች ለድል የበቁት ከ30 አመት በላይ ታግለው መሆኑን መገንዘብ ያስፈልጋል፡፡ አልቆለታል ተብሎ ሞቱ የታወጀው ኦነግም በሌላ መልክ ለድል የበቃው ከ40 አመት በኋላ መሆኑን መረዳት ይገባል፡፡ አይሪሾች እንዴትና ለስንት ዘመን ታግለው ለድል እንደበቁ፤ እስራኤሎች እንዴትና ለስንት ዘመን ታግለው ለድል እንደበቁ፤ ፍልስጤማዊን ተስፋ ሳይቆርጡ ለ75 አመታት እየታገሉ እንደሚገኙ የሚገዘቡ የአማራ ብሄርተኞች በትግላቸው ጽንተው ይቀጥላሉ፡፡ ድልም ያደርጋሉ!

የአማራ ብሄርተኝነት ይለምልም!!!

(ጽሁፉን ከአመት በኋላ አብረን እንገመግመዋለን)




የነ አጅሬ ሹመት ፍንትው አድርጎ የሚያረጋግጠው የፖለቲካ እውነታ አለ፡፡ መማር ለሚችል ብዙ ትምህርት ሊቀሰምበት የሚገባው አስገራሚ ክስተት ነው፡፡ ጌታቸው ረዳ እና ክንደያ ገ/ሂወት ሲንቁት፣ ሲያጣጥሉትና ሲያዋርዱት በነበረው አብይ አህመድ ተረቱ፡፡ ጫማ ልሰው ተሾሙ፡፡ መማር ለሚችል የእነዚህ ሰዎች ሁኔታ ለአማራ ትግል ከፍተኛ ትምህርት የሚሰጥ ነው፡፡ ግለሰቦች ለስልጣን፣ ለዝና፣ ለገንዘብ፣ ለወሲብ ወዘተ ወዘተ ብለው የህዝብን ጥቅም ሊሸጡ እንደሚችሉ ፍንተው አደርጎ የሚያሳይ ነው፡፡ እልህ፣ ግለሰባዊ አልሸነፍም ባይነትና መጠቃቃት የግለሰቦችን አቋም ሊያሽመደምድ እንደሚችል የሚያረጋግጥ ነው፡፡ በግለሰቦች ላይ መተማመን እጅግ አደገኛ መሆኑን የሚያረጋግጥ ነው፡፡ ዋናው የትግል ሞተር የነቃ፣ የተደራጀና ለመብቱ መስዋእትነት ለመክፈል ዝግጁ የሆነ ህዝብ መሆኑን የሚያረጋጥ ሃቅ ነው፡፡

በግለሰቦች ላይ በመንጠልጠል የሚታወቀው የአማራ የፖለቲካ ባህል ከመሰረቱ መቀየር አለበት፡፡ በዲሞክራሲያዊነት፣ በፍትሃዊነት እና በእኩልነት መርሆዎች የሚመሩ የፖለቲካ፣ የሲቪክና የሚዲያ ተቋማትን መፍጠር ካልተቻለ አንዳችም ለውጥ አይመጣም፡፡ ትግል የሚባለው ሁሉ ድክ ድክ ሆኖ እንደሚቀርም አያከራክርም፡፡
እስክንድ ነጋ ከትግሉ ቢወጣ ትግሉ የሚሳካ የሚመስለው አለ፡፡ መሰረት የሌለው እይታ ነው፡፡ ዘመነ ካሴ ከትግሉ ቢወጣ ትግሉ የሚሳካ የሚመስለው አለ፡፡ ይህም መሰረት የሌለው እሳቤ ነው፡፡ እከሌ ቢገባ፣ እከሌ ቢወጣ ብሎ ነገር ፍሬ የለውም፡፡ በግለሰቦች ላይ መንጠልጠል የከንቱ ከንቱ ነው፡፡ በግለሰቦች መውጣት ወይም መግባት የሚመጣ መሰረታዊ ለወጥ የለም፡፡ የአማራ ፈተናዎች ከግለሰቦች በላይ ናቸው፡፡ በጠራ ብሄርተኝነት ርእዮት የሚመሩ የፖለቲካ፣ የሲቪክና የሚዲያ ተቋማት እስካልተመራ ድረስ አሁን በተያዘው መንገድ ጠብ የሚል ለውጥ አይመጣም፡፡ ጠንካራ ድርጅቶች ካሉ ግለሰቦች ትግሉን ልጥለፍ ቢሉ እንኳ አይሳካላቸውም፡፡
ስለዚህ ወደ ውጭ ማማተሩን ማቆም ያስፈልጋል፡፡ ሌሎችን መክሰሱን መግታት ይገባል፡፡ ሌሎችን መግፋት መገፋትን እንደሚያስከትል በደንብ መገንዘብ ያስፈልጋል፡፡ የሌሎችን ስብእናም ሆነ አካላቸውን ለማጥፋት መሞከር መጠቃትን እንደሚጋብዝ በደንብ መገንዘብ ይገባል፡፡ ሌሎችን አጥንትን በሚሰብር ቃላት መቀጥቀጥ፤ አጥንት በሚሰብር ቃላት መቀጥቀጥን ይጋብዛል፡፡ ሄዶ ሄዶ ውጤቱ ደግሞ የጋራ ውድቀት ነው፡፡ ስለሆነም ወደ ሌሎች መጠቆሙን ትቶ ወደ ውስጥ መመልከት ያስፈልጋል፡፡ እልሁን፣ መካሰሱንና መጠፋፋቱን ወደ ጎን ብሎ የትግሉን አካሄድ መገምገም ይገባል፡፡ አሁን በተያዘው መንገድ የጋራ ውድቀትና ውርደት ካልሆነ በስተቀር ድል ብሎ ነገር እንደማይታሰብ በደንብ መገንዘብ ያስፈልጋል፡፡ መጪው ጊዜ ካለፈው ሁሉ የበለጠ ፈታኝ ነው፡፡ አርቆ አሳቢዎችን፣ አሰባሳቢዎችን፣ ጽኑዎችን ይፈልጋል!

ስህተት ያልሰራና የማይሰራ የለም፡፡ ውድቀት የሚመጣው ከስህተትና ከድክመት አለመማር ሲገነግን በመሆኑ አካሄድን በሃቅ መገምገም ያስፈልጋል፡፡ ጊዜው የግምገማ ነው!

የአማራ ብሄርተኝነት ይለምልም!!!

የግርጌ ማስታወሻ
ከ1,000,000,000 መንጋ 1 አሰላሳይ ይበልጣል!


ሺ ውሸት አንድ እውነትን አያሸንፍም! በህልውና ትግል ሒደት "ለምጣዱ ሲባል አይጧ ትለፍ::" አይነት አባባል አይሰራም!! አካፋን አካፋ ዶማን ዶማ ማለት ግድ ነው! በሀሰት ፕሮፖጋንዳ አማራው ነፃ አይወጣም!!


ፎተሊካ በጎጃም ሸማይ ስር 😂
የርዕዮተ አለም ልዩነት ነው ያለን ሲሉ አልነበር እንዴ? ከመቼው አበልፅገውት አረፉ

ልብ በሉ!
1. እነዚህ አካላት ከአርበኛ እስክንድር ነጋ ጋር ድርጅት ለመመስረት አብረው መክረው መሪ መምረጥ ጀምረው ነበር!! ታዲያ ያኔ እስክንድር አልበለፀገም ነበር ማለት ነው?
2. ሜ/ጄኔራል ከፍያለው ደሴን የገደልነው እኛ ነን እያሉ መሆኑ ነው፤ ይመዝገብ!

3. ብልፅግና የሰራውን sound cloning ማስረጃ በማድረግ መንጋው እያደናገሩ ነው!! በሚስጥር የተደረገ ምክክር public ሲወጣ አይታያችሁም!


ቀጣዩ መጠፋፋት!
የሚበዛው የአማራ አክቲቪስት የፖሊቲካ ድንክ ነው፡፡ በረጅሙ አቅዶ በጽናት መታገል እንዳለበት አይገባውም፡፡ ሃይል ማሰባሰብ ብሎ ነገር አያውቅበትም፡፡ መገፋፋትና መጠፋፋት የተለመደ ክፉ መገለጫው ነው፡፡ ከጠላት ይልቅ የራሱን ወገን ሲታገልና ሲያጠፋ የሚውል ነው፡፡
አማራ አሁን ለሚገኝበት አዘቅት የተዳረገው በብዙ ዘመናትና በተከታታይ መንግስታት መሆኑን መገንዘብ ያስፈልጋል፡፡ ስለሆነም ከዚህ ጥልቅ አዘቅጥ ለመውጣት ብዙ መስዋእትነት፣ ብዙ ጊዜና የተቀናጀ ትግልን ይጠይቃል፡፡ የአማራ አክቲቪስትና ታጋይ ነኝ ባይ ግን ይህ ሃቅ አይገባውም፡፡ መገለጫው መጋለብ ነው፡፡ መገለጫው መንቦጅቦጅ ነው፡፡ እንቅስቃሴው ሁሉ ስር የለውም፡፡ ፖለቲካን ከሃይማኖት ጋር ያቀላቅላል፡፡ ከድርጅት ይልቅ ግለሰቦችን ያመልካል፡፡ የሃይል አሰላለፍና የወዳጅ ጠላት ትንተናውም በጣም ደካማ ነው፡፡
የአብይ ቡድን የምክክር ኮሚሽኑን በመጠቀም ስልጣኑን በማደላደል ለብዙ ዘመናት በፍፁም አምባገነናዊ ስርአት ለመግዛት የተቀናጀ ስራ ላይ ነው፡፡ ብዙው ነገርም እየተሳካለት ነው፡፡ በእሱ ጥንካሬ ሳይሆን በአማራው ድክመት፡፡ የአብይን ቡድን በማንበርከክ ጥቅምን ለማስከበር የግድ የመሰባሰብ አስፈላጊ ነው፡፡ የግድ ሃይል ማሰባሰብ ግዴታ ነው፡፡ የአማራ አክቲቪስትና ታጋይ ነኝ ባይ ግን ይህ አይገባውም፡፡ ግማሹ አንዱን የፋኖ ቡድን ደግፎ በሌላው ላይ ሲዘምት ይውላል፡፡ ሌላው ተቀራኒውን ቡድን ደግፎ ሲባክን ይታያል፡፡ ከንቱ የእውር ድንበር ጉዞ!

መፍትሄው አንድና አንድ ብቻ ነው፡፡ መፍትሄው የአማራ ፋኖ ትግል በድርጅት ካልተመራ ለውጤት እንደማይበቃ ተገንዝቦ ከግለሰቦች ይልቅ ድርጅቶች እንዲጠናከሩ መስራት ነው፡፡ መፍትሄው አንዱን ደግፎ በሌላው ላይ መዝመት ሳይሆን ልዩነቶቻቸውን እንዲያቻችሉ አድርጎ አንድነትን መፍጠር፣ አሰባሳቢ የሆነ ጠንካራ ድርጅት ወይም ደርጅቶች እንዲገነቡ ማድረግ ነው፡፡ የሚፈጠሩት ድርጅቶች ከአንድ በላይ ከሆኑ በመካከላቸው መጠፋፋት እንዳይኖር መንገድ ማበጀት ነው፡፡
አሁን በአማራ ፖለቲካ ውስጥ የሚታየው ያዋከቡት ነገር ምእራፍ አያገኝም እንደሚባለው ነው፡፡ ግለሰቦችን አዋክቦ ማጥፋት መጠፋፋትን ይጋብዛል፡፡ በመጨረሻም ጠላትን ድል እንዲያገኝ አድርጎ የዘላለም ባርነት መቀበል ብቻ ይሆናል፡፡ መጋለብ ይብቃ፡፡ ከንቱ መንቦጅቦጅ ይብቃ፡፡ አሁንም ጊዜ አለ፡፡ “እነ እከሌ ካልተወገዱ ይህ ትግል አይሰምርም” ብሎ የገዛ ወገኖችን የሚያሳድድ አካል በመጨረሻም ራሱ ተሳዳጅ ይሆናል፡፡ ለድል ሊበቃ አይችልም!
ፋኖ አደገኛ እጥፋት ላይ ይገኛል፡፡ ድርጅት ከመፍጠር ይልቅ በግለሰቦች ላይ ተንጠልጥሎ የቆየው ትግል እድገቱ የኋሊት ሆኗል፡፡ ቆም ብሎ ማሰብ ያስፈልጋል፡፡ አካሄድን መገምገም ግዴታ ነው፡፡ በተማሩ የአማራ ልጆች የተዋቀረ የፖለቲካ ድርጅት የማይመራ የትጥቅ ትግል የትም ሊደርስ አይችልም፡፡ ጠንካራ ድርጅት ሊፈጠር የሚችለው ደግሞ በዲሞክራሲ፣ ፍትሃዊነትና በእኩልነት መርህ ብቻ ነው፡፡ ሽፍታነትን አስወግዶ አርበኝነት ማንበር የሚቻለው በዚህ መንገድ ብቻ ነው፡፡ አላማ የለሽ ሽፍታና የጦር አበጋዝ ምንም አይነት የህዝብ አጀንዳ ሊያሳካ አይችልም፡፡

ከመጠፋፋት መውጣት፣ በብሄርተኛ ርእዮትና በጠንካራ ድርጅት መመራት፣ የሽፍታና የጦር አበጋዝ አዝማሚያዎችን አጥብቆ መታገል የግድ አስፈላጊ ነው፡፡ ሁሉንም የአማራ አካባቢዎች በፍትሃዊነት ያልወከለ ድርጅትና ትግል የትም እንደማይደርስ በደንብ መገንዘብ ያስፈልጋል፡፡ ይህን ሃቅ ያልተገነዘበ አክቲቪስትና ታጋይ ነኝ ባይ መጠፋፋቱን ያስቀጥለዋል፡፡ መጨረሻውም የባሰ ውርደትና ውድቀት ይሆናል!
አሁን ጊዜው የግምገማ ጊዜ ነው፡፡ ከመንቦጅቦጅ ወጥቶ የትግሉን ሁኔታና አካሄድ በሚገባ መገምገም የሚያስፈልግበት ጊዜ ነው፡፡ ራስን ከማጥፋት ተቆጥቦ በልበ ሰፊነት ማሰብና ራስን እንደገና መልሶ ማደራጀት የሚያስፈልግበት ጊዜ ነው፡፡

የአማራ ብሄርተኝነት ይለምልም!!!!

የግርጌ ማስታወሻ
ከ1,000,000,000 መንጋ 1 አሰላሳይ ይበልጣል!


እውነቱን ለህዝቡ መግለፅ እንዳለብኝ ይሰማኛል! በተለያዩ ጊዜያት በተዘዋዋሪ መልዕክቶችን ሲጋራ ሀሳብና አቋሜንም ስገልፅ ቆይቻለሁ!! አንዳንድ ሰዎች ግን አኝከህ ካላጎረስካቸው አይውጡምና በቀጥታ መናገር ያሻል?
በጥያቄ ልጀምር በጨዋ ደንብ መልሱ!

1.በአማራ ፋኖ መካከል የርዕዮተ ዓለም ልዩነት አለ ብላችሁ ታስባላችሁ? ርእዮት ዓለም ማለትስ ምን ማለት ነው? ካለ ሁለቱንም ግለፁ?

2. አሁን ካሉት የፋኖ ጎራዎች የትኛው የተሻለ የድርጅት ቅርፅ ይዟል? ርዕዮተ ዓለሙን በሰነድ አስተዋውቋል?

3. በየትኛው ጎራ ላይ ያሉ አመራሮች ላይ የበለጠ character assassination (በአገዛዙና በአማራ ጠላቶች) ተፈፅሟል?

4. በየትኛው የፋኖ ጎራ ያሉትን የሚዲያ አውታሮች አገዛዙ ተከታትሎ ያዘጋል?

5. በየትኛው ጎራ ያሉ የፋኖ አመራሮች ሲሰው አገዛዙ የበለጠ ይፈነጥዛል?

6. የትኞቹው ጎራ ከብልፅግና ጋር ይሰራል? ከህውሃት ጋር ይሰራል? ተብሎ propagate ይደረጋል?

7. የትኛው ጎራ ለዴሞክራሲያዊ ሒደት ፈቃደኛ አልሆነም?

8. የትኛው የፋኖ ቡድን በድፍረት፣ በጭካኔ የራሱን ወንድም ይገድላል?

9. የትኛው ጎራ መጠነ ሰፊ የሀሳት ፕሮፖጋንዳ ይነዛል?

10. የህውሃትና የብልፅግና ተላላኪዎች በየትኛው ጎራ በዝተው ይገኛሉ!?

........ይቀጥላል

የግርጌ ማስታወሻ
ከ1,000,000,000 መንጋ 1 አሰላሳይ ይበልጣል!


አሁንም ቢሆን ጊዜ አለን!! ህዝቡ ስለሁኔታው ያሰላስል! ወጣቱ influencer ዎች እና የsocial media ጡረተኞች መስማት አቁሞ መረጃ ቀጥታ ከትግል ሜዳ ይከታተል!!

የህውሃት ቅጥረኛ
የብአዴን ቅጥረኛ
ለአብይ የሚሰሩ
ለውጭ ጠላት የሚሰሩ
ለስልጣንና ሐብት ለማካበት የገቡ እና በአጠቃላይ ለአማራ ህዝብ ብለው ወደ ትግል ሜዳ ያልገቡ ቅይጥ ታጣቂዎች ስላሉ እነርሱን የመለየትና ድርጅታዊ መልክ እንዲይዙ አወንታዊ ሚና መጫወት ከእኛ ይጠበቃል!!
ያ ሳይሆን ከቀረ ግን ለአማራ ብሎ የወጣ ወጣት በጠላት ተሰልቦ በሁለት ጎራ እርስ በርዕሱ መጠፋፋቱ አይቀሬ ነው!!


ጋሽ አሰግድ
ጀኔራል ውባንተ
ኮሎኔል ታደሰ እሸቴ
አርበኛ አሰቻለው ደሴ
...ይቀጥላል!!

የሚነደው መንጋ ወደ ገደል የሚጨመርበት ሰሀት ላይ እየደረስን ነው!! አንድ ሁኑ፤ ድርጅት ፍጠሩ የምንለው ተነጋግሮ አንድ ለመሆን ስለሚጠቅም አልያም በፊናቸው የራሳቸውን ትግል እንዲያደርጉ፤ መዋቅር እንዲጠራ (ሰርጎ ገብን ለመከላከል) ስለሚጠቅም ነበር። አሁን ባቡሩ ሀዲዱን እየለቀቀ ይመስላል!! መሪዎቻችን ይገዳደላሉ፤ መንጋው ይነታረካል፤ ጠላት ቤንዚን ያርከፈክፋል!!!


የህልውና ትግሉ አላማም ልክም ይህ አይደለም!

የህልውና ትግሉ ልክ "አንድ አማራ ለሁሉም አማራ፤ ሁሉም አማራ ለአንድ አማራ" ነው! ነበርም። አሁን የትግሉ አላማ ለህልውና አልሆነም። ወደ ስልጣን ትግል ወርዷል።

"አንድ አማራ ለሁሉም አማራ፤ ሁሉም አማራ ለአንድ አማራ" ብለው የተነሱት የአብን ወንድሞቻችን ሳይቀሩ ወዲያና ወዲህ ሆነው በፌስቡክ ሲቧቀሱ ከርመዋል። መሳሪያ ይዘው ቢገናኙ አባላትና አመራር የነበሩት አይታኮሱም ሊባል አይችልም።

አገዛዙ ጦርነት ሲከፍት የአማራን ህልውና እናስጠብቃለን ብለው የተነሱ ፋኖዎች በሁሉም የአማራ አካባቢዎች መሳሪያ አንስተው ተሞካክረዋል። የሚያሳዝነው ይህ ሲሆን አንዱን ደግፎ ሌላውን ይሰቀል እያለ የሚያወግዝ የህልውና ትግሉ ያገባኛል የሚል ከተራ ፌስቡከኛ ፖለቲካ አውቃለሁ እስከሚል ድረስ በየቀኑ ታያላችሁ።

የታጠቁ የአማራ ልጆች መካከል ምህረት የሌለው ማለያየትና እርስ በእርስ የማታኮስ ስልት ላይ የከረመው ብዙ ነው። ሚሊሻ አባት ፋኖ ልጁን፣ ፋኖ ልጅ ሚሊሻ አባቷን ገድለው ጀግና ሲባሉ ከረሙ። አንድ አማራ ለሁሉም አማራ ብቻ ሳይሆን አባትና ልጅን ማገዳደል የህልውና ትግል አስመስሎ ሲያቀርብ የከረመ የትግል ሀዲዱን መዛነፍ የማያውቀው በርካታ ነው። ግን ተዛንፏል። መስመር ከተሳተ ቆይቷል።

የአማራ ህዝብ የፋኖና ሚሊሻ፣ የካድሬ ወዘተ ተብሎ ከግለሰብ ያለፈ ደም መመላለስ ውስጥ እንዲከርም ተደርጓል። አሁን የፋኖ እዞች እርስ በእርስ ጦርነት እየገጠሙ፣ በሚዲያ በየፊናቸው እንደ ጀብዱ ሲያስነግሩ እየዋሉ ነው። እንዲህ የሚያደርጋቸው የህልውና ትግሉ አላማ አይደለም። ፈፅሞ። የህልውና ትግሉ የአማራን ሞት ማዳን እንጅ አገዛዙ ካደረገው በተጨማሪ አማራን የጦር ቀጠና አድርጎ እርስ በእርስ መዋጋት አይደለም።

ለዚህ ከህልውና ትግሉ ያፈነገጠ የእርስ በእርስ ግጭትና ውረድ እንውረድ ምክንያቱ ስልጣን ነው። ይህ መራራው ሀቅ ነው። ደግሞ በየስልጣኑ የፋኖ አደረጃነት ስልጣን እንጅ የአገረ መንግስት ስልጣን ይዞ ለህዝብ የሚጠቅም ነገር አመጣለሁ ከሚል አይደለም።

በዚህም በዛም ያለ ኃይል "አንድ ሁናችሁ ተደራደሩን" ስለሚል ነው ወንድም በወንድሙ ላይ እየተኮሰ ያለው። ይህ ደግሞ የህልውና ትግሉ ደረጃም፣ ቀለምም አላማም የለውም።

በስሜት ሲነዳ የሚውል ደጋፊ ቀጣዩን የአማራ መከራ ማየት አልቻለም። ይህን ያህል አቅም የገነባን ፋኖ ለምን እና እንዴት መጠቀም እንዳለበት አላወቀም። አገዛዙ በዚህ ከልክ በላይ ደስተኛ ሆኗል። የአማራ ህልውና ጉዳይ እጅግ አሳሳቢ ከነበረበት ከክልል ውጭ ወደ ክልሉ ገብቶ ህዝብ ፍዳውን እያየ ነው። አሁን የአማራን ህልውና እናስጠብቃለን ብለው የወጡ ፋኖ አደረጃጀቶች አንዱ የአንዱን ህልውና ማጥፋት ሆኗል አላማቸው። የአማራ ህልውና ትግል ተረስቷል።

ይህ የህልውና ትግሉ አላማ አልነበረም። አይደለምም። በአስቸኳይና በግፊት ይህ አደገኛ አካሄድ ካልተስተካከለ የአማራን የህልውና ትግል ተረት ተረት አስመስለው ያስቀሩታል። የአማራን ህልውና እናስጠብቃለን እየተባለ የአማራን የህልውና ትግል መዘባበቻ እንዲሆን እየተሰራ ነው።

የህልውና ትግል እንደሆነ የሚያምን የሚዲያ ኃይል የህልውና ትግልን ያህል ጉዳይ እያለ እርስ በእርሱ በሀሰት ሲካሰስ፣ በሀሰት ሲዘምት አይውልም!

የህልውና ትግል እንደሆነ የሚያምን ፖለቲከኛ በአደባባይ እርስ በእርስ ሲገጥም አይውልም!

የህልውና ትግል እንደሆነ የሚያምን የታጠቀ ኃይል እርስ በእርስ ሲታኮስ፣ አንዱ በሌላው ላይ ሲዘምት አይውልም!

እየሆነ ያለው ግን ሌላ ነው። እርስ በእርስ መዘማመት ጀብዱ ሆኗል። ማህበራዊ ሚዲያው የሀሰት መካሰሻ፣ ስም መጠፋፊያ ሆኗል። የህልውና ትግሉን ስለዘነጋ ነው!

ሚዲያው የፖለቲከኞች መነታረኪያ ሆኗል። የህልውና ትግሉ ሳይሆን የስልጣንና የቡድነኝነት ጉዳይ ስለቀደመ ነው። ጥቅም ማጋበስ ተጨምሮበታል።

የፋኖ እዞች ከአገዛዙ ጋር ከሚያደርጉት ጦርነት ያላነሱ በራሳቸው ወንድሞች ላይ የሚያደርጉት ዘመቻ በድል ዜና ሲነገር ከርሟል። የህልውና ትግሉ መስመርን ስለሳቱት ነው።

የህልውና ትግሉ አላማ የአማራን አንድነት፣ ህይወትና ክብር ማስጠበቅ እንጅ ይህ አሁን የምናየው ትርምስ አይደለም! የህልውና ትግሉ በጋራ ሆኖ የትም የሚኖር አማራን ህልወትና ክብር ማስጠበቅ እንጅ በየአካባቢው እርስ በእርስ ጦርነት ማወጅ፣ መገዳደል አይደለም።
©Getachew Shefraw


ሲነግሩት የማይሰማ ከሆነ ምን ታደርጉታላችሁ?


የአማራ እናቶች፣ ህፃናት እና አረጋዊያን በዚህ መልኩ በኦሮሙማው ሀይል ይጨፈጨፋሉ!
እኛ አንድነት ከብዶን እንነታረካለን!!
😭

20 last posts shown.