Posts filter


ምዕራባውያን_ኤምባሲዎች እና የ አውሮፓ_ሕብረት አባል ሀገራት በትግራይ ውስጥ ያለውን ወቅታዊ ሁኔታ እና እየጨመረ የሚገኘውን ውጥረት እየተከታተሉ መሆናቸውን አስታወቁ

የምዕራባውያን ኤምባሲዎች እና የአውሮፓ ህብረት አባል ሀገራት በትግራይ ክልል ውስጥ ያለውን ወቅታዊ ሁኔታ እና እየጨመረ ያለውን ውጥረት እየተከታተሉ መሆናቸውን ዛሬ መጋቢት 4 ቀን 2017 ዓ.ም ባወጡት የጋራ መግለጫ አስታውቀዋል።

መግለጫውን ያወጡት የዩናይትድ ስቴትስ፣ የእንግሊዝ፣ የኒው ዚላንድ፣ የጃፓን፣ የኖርዌይ፣ የቤልጂየም፣ የቡልጋሪያ፣ የቼክ ሪፐብሊክ፣ የዴንማርክ፣ የጀርመን፣ የአየርላንድ፣ የግሪክ፣ የስፔን፣ የፈረንሳይ፣ የጣሊያን፣ የሉክዘምበርግ፣ የሃንጋሪ፣ የኔዘርላንድስ፣ የኦስትሪያ፣ የፖርቱጋል፣ የሮማኒያ፣ የስሎቬኒያ፣ የፊንላንድ፣ የስዊድን ኤምባሲዎች እና የአውሮፓ ህብረት ልዑካን ናቸው።

ሃገራቱ በመግለጫቸው እ.ኤ.አ. ህዳር 2022 ለተፈጸመው ዘላቂ ግጭት የማቆም ስምምነት ሙሉ ድጋፍ እንደሚሰጡ ገልጸው፤ ሁሉም ወገኖች አስቸኳይ ውይይት በማድረግ ውጥረቱን በማርገብ ስምምነቱን እንዲጠብቁ አሳስበዋል።

በቅርቡ በህወሓት ውስጥ ክፍፍሎች እና የስልጣን ሽኩቻዎች እየተባባሱ መምጣታቸውን ተከትሎ በክልሉ ያለው አለመረጋጋት እየጨመረ መጥቷል።

በጌታቸው ረዳ የሚመራው የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ረቡዕ መጋቢት 3 ቀን 2017 ዓ.ም የቅርብ ጊዜውን ውጥረት በመጥቀስ  "አንዳንድ ወታደራዊ አካላት" በክልሉ የሰላም ስምምነትን ለማዳከም "መፈንቅለ መንግሥት ሙከራ" አድርገዋል ሲል ከሷል።

https://t.me/voa_amharic1
https://t.me/voa_amharic1


አርቲስት አንዱአለም ጎሳ በቀነኒ ሞት ተጠርጥሮ ፍርድ ቤት ቀረበ


አርቲስት አንዱአለም ጎሳ በእጮኛው ቀነኒ አዱኛ ሞት ተጠርጥሮ ከታሰረ ከሁለት ቀናት በኋላ ፍርድ ቤት መቅረቡን ጠበቃው ለቢቢሲ አፋን ኦሮሞ ገልጿል።

ፖሊስ እስካሁን አሻራ ማንሳቱን፣ አስከሬኑን ወደ ሆስፒታል በመላክ፣ የአስከሬን ምርመራ ማድረጉን ገልጾ የሰው ማስረጃዎችን በማሰባሰብ ላይ እንደሚገኝ ተናግሯል።

"አሁን ፎቶግራፎችን ከመዝገቡ ጋር ለማያያዝ፣ የሰዎች ምስክርነት ለመስጠት እና የአስከሬን ምርመራው እስኪመጣ ድረስ ለማጣራት 14 ቀናት ያስፈልገኛል ብሏል።

የአንዱአለም ጠበቃ በበኩሉ የዋስ መብት ይሰጥ ብሎ ቢጠይቅም ፍርድ ቤት የአስክሬን ምርመራ እንስኪደርስ በማለት 13 ቀናት ድምፃዊው በማረሚያ ቤት እንዲቆይ ወስኗል።

https://t.me/voa_amharic1
https://t.me/voa_amharic1


Attention‼️

የኢትዮጵያ የምግብ እና መድኃኒት ባለስልጣን አምስት የገበታ ጨው አይነቶች  ህብረተሰቡ እንዳይጠቀም አሳሰበ

የኢትዮጵያ የምግብ እና መድኃኒት ባለስልጣን
የተለያዩ የገበታ ጨው ምርት ዓይነቶች በሚመለከተው አካል የደረጃ ምልክት የመጠቀም ፈቃድ ሳይኖራቸው በመገኘታቸው ህብረተሰቡ እንዳይጠቀማቸው አሳስቧል።

ባለስልጣኑ በቅርቡ ገበያ ላይ ባደረገው ቁጥጥር  አምስት የተለያዩ የገበታ ጨው ምርቶች የብሔራዊ የደረጃ ምልክት የመጠቀም ፈቃድ ሳያገኙ ምልክቱን ለጥፈው ገበያ ላይ ውለው መገኘታቸውን የባለስልጣኑ የህዝብ ግንኙነት  እና ኮሙኒኬሽን ዋና ዳይሬክተር አቶ አበራ ደመቀ  ተናግረዋል።

በመሆኑም እነዚህ ምርቶች ጥራታቸውና ደህንነታቸው ያልተረጋገጡ በመሆናቸው ህብረተሰቡ እንዳይጠቀማቸው ባለሰልጣኑ አሳስቧል፡፡

ጥቅም ላይ እንዳይውሉ የተባሉት ምርቶች ሊኑ የገበታ ጨው፣ታሪክ የገበታ ጨው ፣ቤይ የገበታ ጨው፣ሺማ አዮዳይዝድ እና ጂ.ኤም ኤዳይዝድ ጨው በሚባል የምርት ስም የሚጠሩ መሆናቸውን አቶ አበራ ደመቀ ጨምረው ተናግረዋል።

https://t.me/voa_amharic1
https://t.me/voa_amharic1


በዶክተር ደብረፂዮን የሚመራው የህወሃት ቡድን በመቀሌ ከተማ የህዝብ አገልግሎት መስጠት ጀመሩን አስታወቀ።

እንደሚታወሰው በመቀሌ በጊዜያዊ አስተዳደሩ የተሾመና በነደፂ የተሾመ ሁለት ከንቲባ ነበሩ።

ክልሉን የተቆጣጠረው የነደፂ ቡድን ለመቀሌ ከተማ የመደብኳቸው ከንቲባ በዛሬው ዕለት ቢሯቸው ገብተው የህዝብ አገልግሎት መስጠት ጀምረዋል ብሏል።

https://t.me/voa_amharic1
https://t.me/voa_amharic1


"እኔ የዉጪ ሰዎችንም ሰማለሁ የፌደራል መንግስቱ ለምንድነዉ ዝም ያለዉ? ይላሉ...አላቅም ይዋጣላቸዉ ብሎ ሊሆን ይችላል እላለሁ...ማለት የፌደራል መንግስቱ ዝም ብሎ ያየዉ ቦታ ሁሉ እየገባ ጦርነት የመክፈት አባዜ ያለዉ አይመስለኝም።እንደዛ ሊሆን ይችላል እላቸዋለሁ። "

"ከጠ/ሚኒስትሩ ጋር በሚኖረኝ ዉይይት ልምድ ያለዉ ድርጅት ነዉ (ህወሓት) ተመልሶ ወደጦርነት ትገባላችሁ የሚል እምነት የለንም በዉስጣችሁ ፍቱ... ትግራይ ላይ አላስፈላጊ ጣልቃገብነትን ስለማንፈልግ ነዉ ይላሉ ፤ ይሄንንም እቀበላለሁ። ግን ዝም ማለት የለበትም የፌደራል መንግስት እኔ ያዝምት እያልኩ አይደለም ትግራይ ዉስጥ ራሱ የፌደራል መንግስት ተቋማት አሉት እንዲሰሩ ማስቻል አለበት።የትግራይን ድንበር መጠበቅ መቻል አለበት ካልቻለም outsource ይደረግ ከተባለ ቁርጣችንን አዉቀን እናድርገዉ።" አቶ ጌታቸዉ በመግለጫው ከተናገሩት የተወሰደ

https://t.me/voa_amharic1
https://t.me/voa_amharic1


Update❗️❗️

ጊዜያዊ አስተዳደሩ ከፌደራል መንግስት “ድጋፍ” መጠየቁን ተከትሎ #ህወሓት “የሶስተኛ ወገን ጣልቃ ገብነት ጥሪ ተቀባይነት የለውም" ሲል ተቃወመ

የ #ትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር የፌዴራል መንግስት “አስፈላጊውን ድጋፍ” እንዲያደርግለት መጠየቁን ተከትሎ ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) "በቀጥታና በተዘዋዋሪ ሶስተኛ ወገን ትግራይ ውስጥ እጁን እንዲያስገባ የሚያደርገው ጥሪ በፍፁም ተቀባይነት የለዉም" ሲል ተቃወመ።

ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) ትናንት 03 መጋቢት 2017 ዓ.ም ባወጣው መግለጫ፤ በጊዜያዊ አስተዳደሩ አራት የሰራዊት ከፍተኛ አመራሮች መታገዳቸው “ከሃላፊነት ውጪ የተደረገና ተፈፃሚነት የሌለው ውሳኔ ነው” ሲል ገልጿል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ ትናንት የጊዜያዊ አስተዳደሩ ፕሬዝዳንት ጌታቸው ረዳ ከአሜሪካ፣ ጀርመን፣ ፈረንሳይ፣ ጣሊያን፣ አውሮፓ ህብረት እና እንግሊዝ የተወጣጡ አምባሳደሮች በትግራይ ውስጥ ስለተፈጠሩ ክስተቶች እና አስተዳደሩ ስላጋጠሙት ፈተናዎች ገለፃ ማድረጉን በኤክስ ገጻቸው ገልፀዋል።

https://t.me/voa_amharic1
https://t.me/voa_amharic1


#Update

- ኃፍረት የማይታይባቸው ናቸው በጥቂት ግለሰቦች ጥቅም ሲባል የትግራይ ህዝብ መጎዳት የለበትም
የትግራይ ህዝብ ወደ ባሰ መከራ ለማስገባት ርብርብ ላይ ናቸው።

- ትግራይ ህዝብ ሰላም ነው የሚሻው ድጋሚ ጦርነት አይፈልግም። የአለም አቀፍ ማህበረሰብ ጣልቃ እንዲቀባ ጠይቀዋል።

- ይህ ቡድን ጠቅላይ ሚንስትር ጋር ቀን ከለሊት አየደወሉ ስልጣን የሚለምኑ ኃይል ነው።

"ለምንድን ነው ከትግራይ የምሸሸው? . . . እመለሳለሁ" አቶ ጌታቸው ረዳ

ጌታቸው ረዳ ከትግራይ ሽሹ ስለተባለው የሰጡት ምላሽ :


ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ጋር ያለኝን ስበሰባ ማጠናቀቅ አለብኝ። በሚቀጥሉት ቀናት ሌሎች ስብሰባዎችም አሉኝ። በሚቀጥለው ሳምንት መጀመሪያ [ወደ ትግራይ] እመለሳለሁ። ዕቅዴ እሱ ነው።

ትላንት [ማክሰኞ] ከሰዓት ከሕዝብ ጋር ውይይት እያደረግኩ ነበር። የጊዜያዊ አስተዳደሩ አጋር የሆነው የፌዴራል መንግሥቱ ስልክ ደወለልኝ።

እርግጥ ነው ሁኔታው የሚያሳስብ ነው። ፌዴራል መንግሥቱ ትግራይን የሚያስተዳድሩ ሰዎችን ስብሰባ ጠርቶ የማናገር መብት አለው።

ነገር ግን ይህ የሚባለው ነገር እንደኛው የህወሓት ክፍል ብዥታ መፍጠር ካለው ዓላማ ነው። ለውጥ ማምጣት የሚሹ ሰዎችን እኔን ጨምሮ ከትግራይ እየወጡ ነው ይላሉ።

ነገር ግን ትግራይን ሸሽቶ ወጥቷል የሚባለው ሐሰት ነው። ሕዝቡን ግራ ለማጋባት ያሰራጩት ወሬ ነው።

https://t.me/voa_amharic1
https://t.me/voa_amharic1


የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ አዲስ አበባ ይገኛሉ።

ፕሬዝዳንቱ በአሁን ሰዓት አዲስ አበባ ሸራተን አዲስ ሆነው ስለ ክልሉ ሁኔታ ጋዜጣዊ መግለጫ እየሰጡ ናቸው።

https://t.me/voa_amharic1
https://t.me/voa_amharic1


የየካቲት ወር የሀገሪቷ  አጠቃላይ የዋጋ ግሽበት 15 በመቶ መሆኑን አገልግሎቱ አስታወቀ

የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ባወጣው መረጃ መሰረት የየካቲት ወር አጠቃላይ የዋጋ ግሽበት 15 በመቶ ደርሷል።

ይህ አሀዝ ከጥር ወር ጋር ሲነጻጸር የ0.5 በመቶ ቅናሽ ያሳየ ሲሆን፣ በየካቲት ወር ከተመዘገበው የዋጋ ግሽበት መካከል የምግብ ነክ እቃዎች የ14.6 በመቶ ድርሻ ሲይዙ፣ ምግብ ነክ ያልሆኑ እቃዎች ደግሞ 15.6 በመቶ ድርሻ እንዳላቸው ተጠቁሟል ።

https://t.me/voa_amharic1
https://t.me/voa_amharic1


❗️ጌታቸው ረዳ በትግራይ ወቅታዊ ጉዳይ ከ አሜሪካ እና አውሮፓ አምባሳደሮች ጋር መነጋገራቸውን አሳወቁ

የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት ጌታቸው ረዳ፣ በትግራይ እያሽቆለቆለ የመጣውን ኹኔታ መቀልበስ በሚቻልበት ኹኔታ ዙሪያ በኢትዮጵያ ከአሜሪካ፣ ብሪታንያ፣ ጣሊያን፣ ፈረንሳይ፣ ጀርመንና አውሮፓ ኅብረት አምባሳደሮች ጋር ትናንት መወያየታቸውን አስታውቀዋል።

ጌታቸው፣ ውይይቱ የፕሪቶሪያ የግጭት ማቆም ስምምነት ባለድርሻዎች ዳግም በትግራይ ጦርነት እንዳይቀሰቀስ ማድረግ ባለባቸው ጥረቶች ዙሪያ ጭምር እንደኾነ በኤክስ ገጻቸው ላይ ገልጸዋል።

በትግራይ ዳግም ጦርነት ከተቀሰቀሰ፣ ሥውርና አፍራሽ ዓላማ ያላቸው በርካታ የቀጠናው ኃይሎች ሊገቡበት የሚችሉበት እድል እንዳለ ጌታቸው ጠቁመዋል።

https://t.me/voa_amharic1
https://t.me/voa_amharic1


በመቀሌ ከተማ ያለው ሁኔታ ከቁጥጥር ውጭ ሆኗል።

ህወሓት በኃይል በመጠቀም ከተማዋን ሙሉ በሙሉ ተቆጣጥሯል ተብሏል።

የከተማው ነዋሪዎች ከፍተኛ ድንጋጤ ውስጥ የገቡ ሲሆን፣ ከቤታቸው ለመውጣት እንኳን እየተሳቀቁ ነው።

የደብረጽዮን ገብረሚካኤል ደጋፊዎች በስፋት በማህበራዊ ሚዲያ ላይ "ህወሓት ማለት የትግራይ ህዝብ ነው፣ የትግራይ ህዝብ ማለት ህወሓት ነው" የሚሉ መፈክሮችን እያስተጋቡ ነው።

ይህ ሁኔታ በከተማው ውስጥ ያለውን ውጥረት የበለጠ አባብሶታል።

በተጨማሪም፣ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ የፌዴራል መንግሥቱ በአስቸኳይ ጣልቃ እንዲገባ እና አስፈላጊውን ትብብር እንዲያደርግላቸው ጥሪ አቅርበዋል።

ይሁን እንጂ፣ የፌዴራል መንግሥቱ እስካሁን ድረስ በጉዳዩ ላይ ይፋዊ ምላሽ አልሰጠም።

https://t.me/voa_amharic1
https://t.me/voa_amharic1


የወንዝ ብክለት ፈጻሚዎች ላይ ከ6.7 ሚሊዮን ብር በላይ ቅጣት ተጣለባቸው

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን፣ ከአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ጋር በመተባበር፣ ፍሳሽ ቆሻሻ ወደ ወንዝ የለቀቁ 24 ድርጅቶችና 3 ግለሰቦች ላይ በአጠቃላይ 6,700,000 ብር (ስድስት ሚሊዮን ሰባት መቶ ሺህ ብር) የገንዘብ ቅጣት መጣሉን አስታውቋል ።

ቅጣቱ በተለያዩ ክፍለ ከተሞች የተጣለ ሲሆን፣ በተለይም አዲስ ከተማ፣ ንፋስ ስልክ ላፍቶ እና አራዳ ክፍለ ከተሞች ከፍተኛ ቅጣት ተመላክቷል።

https://t.me/voa_amharic1
https://t.me/voa_amharic1


ብሄራዊ ክህደት ተፈፅሞብናል-ህወሃት

"በትግራይ የጸጥታ ሃይሎች የተጀመረው ህገ መንግስታዊ እና የህግ የበላይነት የማስከበር ንቅናቄ የፕሪቶሪያን የሰላም ሂደት ያከብራል እንጂ የሚጥስ አይደለም።

ሰራዊቱ እና አመራሩ የፕሪቶሪያን ስምምነት በከፈሉት መስዋዕትነት ያመጡ ሲሆን አሁንም ለተግባራዊነቱ እየታገሉ ነው። ህወሓት፣ የትግራይ ህዝብና ሰራዊት፣ ጊዜያዊ አስተዳደሩ ተልእኮውን ለመወጣት እንዲችል በአዲስ መልክ ሊዋቀር ይገባል በማለት ወስኗል። ስለዚህ የብሄራዊ ክህደት ቡድኑ [የጌታቸው ረዳን ቡድን ነው] በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ  በትግራይ  ላይ የሶስተኛ ወገን/የፌደራል መንግሥቱ/ ጣልቃ እንዲገባ  ያቀረበው ጥሪ፣ ግልፅ ብሄራዊ ክህደት እና የፕሪቶሪያውን ስምምነት አደጋ ላይ የሚጥል በመሆኑ በፍጹም ተቀባይነት የለውም።"

በደብረጽዮን የሚመራው ሕወሓት ዛሬ ካወጣው መግለጫ

https://t.me/voa_amharic1
https://t.me/voa_amharic1


የኤርትራን ጣልቃ ገብነት እና የአካባቢውን ሰላምና መረጋጋት የሚፃረሩ የውጭ አካላት ሚናን ለመግታት አፋጣኝ እርምጃ መውሰድ ያስፈልጋል ሲሉ በትግራይ ክልል የሚንቀሳቀሱ ፓርቲዎች አስታወቁ

👉 ፓርቲዎቹ በጦር በመታገዝ የሚደረግ ይስልጣን ንጥቅያ ይቁም ሲሉም ተደምጠዋል።

የትግራይ ነፃነት ፓርቲ ፣ ባይቶናና ዓረና ትግራይ በጋራ ባወጡት መግለጫ የህወሓት ካድሬ ጄነራሎችና አጋሮቻቸው በህገወጥ መንገድ ስልጣን ለመንጠቅ እየሞከሩ ባሉበት ወቅት የክልሉ ሰላምና መረጋጋት መደ ቀወስ ውስጥ ከተውታል ብለዋል።

ፓርቲዎቹ በመግለጫቸው ህገወጥ የመፈንቅለ መንግስት ሙከራ መንግስታዊ መዋቅር ከታች እስከላይ በማፍረስ ክልሉ ወደ ከፍተኛ አለመረጋጋት እስገብተዋል ያሉ ሲሆን ይህ በግዴሌሽነት እየተፈፀመ ያለው የስልጣን ወረራ የተናጠል ተግባር ሳይሆን ከኤርትራ መንግስት ጋር በመቀናደት የተሰራ ነው ሲሉ አስታውቀዋል።

በዚህ መሰረትም አለም አቀፍ አካላትና ሁሉም የፕሪቶርያ ስምምነት ተዋናዮች በአስቸኳይ ጣልቃ እንዲገቡ እንጠይቃለን ያሉ ሲሆን ተጨማሪ ትርምስ ለመከላከልና እስከፊ ክልላዊ ቀውስን ለመከላከል ሲበላል የህግ የበላይነት መከበር አለበት ሲሉ ተደምጠዋል።

በመጨረሻም የኤርትራን ጣልቃ ገብነት እና የአካባቢውን ሰላምና መረጋጋት የሚፃረሩ የውጭ አካላት ሚናን ለመግታት አፋጣኝ እርምጃ መውሰድ ያስፈልጋል ብለዋል።

https://t.me/voa_amharic1
https://t.me/voa_amharic1


የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር መግለጫ ትርጉም የፌደራል መንግሥቱ ጣልቃ እንዲገባ ጠይቋል።

ከጥር 15 ቀን 2017 ጀምሮ አንዳንድ የትግራይ ሰራዊት ከፍተኛ አዛዦች የጠባቦችን የስልጣን ጥማት ለማርካት ግልጽ የሆነ መፈንቅለ መንግስት ለማድረግ ሲንቀሳቀሱ እንደነበር ይታወቃል።

በተመሳሳይ የሰሜን ምስራቅ እና ደቡብ ግንባር አዛዦች የሚመሩ ህገወጥ ድርጊቶች በዚህ ሳምንት ተጠናክረው ቀጥለዋል።

ይህንን አደገኛ መንገድ ለመግታት እና ህገ-ወጥ ድርጊቶችን ሁሉ ለማስቆም የካቲት 26 ቀን 2017 ዓ.ም ለትግራይ ጦር ዋና አዛዥ የተጻፈ ትዕዛዝ ቢሰጥም የጥፋት ድርጊቱ ለሰዓታት ቀጥሏል። ሁኔታው እልባት ባለማግኘቱ የግንባሩ አዛዦች በመንግስት እገዳ ተጥሎባቸዋል። የጸጥታው ቢሮ ኃላፊም ከኃላፊነታቸው ተነስተዋል።

ሆኖም በሰላማዊ ዜጎች ላይ ያነጣጠሩ ጥቃቶች አሁንም ቀጥለዋል። መንግስትን ከላይ እስከታች የማፍረስ ስራው ተጠናክሮ ቀጥሏል። የትግራይ ሰራዊት ከፍተኛ አዛዦች የኋለኛውን ቡድን ፍላጎት ለማስፈጸም መንግስትን በመበተን እና የፕሪቶሪያን ስምምነት በይፋ በመጣስ የትግራይን ህዝብ ወደ ሌላ ጥፋት እያመጡ ነው።

ያለፉትን ስህተቶች ከማረም ይልቅ ከትናንት ጀምሮ የግዚያዊ አስተዳደር አመራሮችን እያደኑ፣ እያፈኑ እና እያሰሩ ነው።

ይህም በማኅተም ስም መንግሥትን ለመጣል የሚያደርጉትን እንቅስቃሴ የበለጠ ያጠናክራል። ይህ ኋላ ቀርና ወንጀለኛ ቡድን ዕድሉን ካገኘ ማፈንና ማሰር ብቻ ሳይሆን የጊዚያዊ አስተዳደር አመራርን ለሶስተኛ ወገን እንደሚያስረክቡ መረዳት ያስፈልጋል።

በሰራዊቱ አዛዦች ስም የሚካሄደው ዘመቻ ሁኔታውን ከጊዚያዊ አስተዳደር ቁጥጥር ውጪ የሚያደርግ እና እንደ ህዝብ ራሳችንን እንድንዋጋ የሚያደርግ ሃላፊነት የጎደለው እና ተቀባይነት የሌለው ተግባር ነው። በአጠቃላይ የትግራይ ህዝብ ከውስጥም ከውጪም; የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር የትግራይ ወጣቶችና የትግራይ ሰራዊት ይህንን ሁኔታ በመረዳት አካባቢያቸውን እንዲጠብቁና በእነዚህ የሁለቱም ግንባሮች አዛዦች ላይ እንዲነሱ ጥሪውን ያቀርባል። የትግራይ ወጣቶች ባንተና በህዝባችሁ ላይ እየደረሰ ያለውን አደጋ ለመታገል በተደራጀ መልኩ አካባቢያችሁን ጠብቁ።

የትግራይ ሰራዊትም እንዲሁ የጥፋት ስርዓቱን አጥብቆ በመቃወም ህዝቦቻችሁን ከፊት ካለው ከባድ አደጋ መታደግ አለበት። የፌደራል መንግስትም በጸጥታ ሃይሎች ስም የሚንቀሳቀሱት ኋላ ቀር እና ወንጀለኛ ቡድን ተላላኪ እንጂ የትግራይን ህዝብና ጊዜያዊ አስተዳደር የማይወክሉ መሆናቸውን ሊረዳ ይገባል። የፕሪቶሪያ ስምምነት በዚህ መንገድ መፍረስ የለበትም የትግራይ ህዝብም ዝም አይልም። ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ በዚህ ቡድን እና አጋሮቹ ላይ ወንጀላቸውን ለመከላከል የፕሪቶሪያ ስምምነትን እየጣሱ በመሆኑ አስፈላጊውን ሁሉ ጫና እንዲያደርግ እንጠይቃለን። ይህ ካልተደረገ የትግራይ ህዝብ ማምለጥ ወደማይችልበት ሌላ የጥፋት ዙር ውስጥ ይገባል።

https://t.me/voa_amharic1
https://t.me/voa_amharic1


በትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር የተባረሩት የግንባሩ አዛዦች እና የህወሓት ምክትል ሊቀመንበር ፈትለወርቅ ገብረእግዚአብሔር (ሞንጄሪኖ) በመቀሌ ሰሜን ሆቴል ስብሰባ ተቀምጠዋል።

አጀንዳቸው ከፌደራል መንግስት ጋር ያለውን ግጭት ለመገምገም መሆኑን ምንጮቼ ገልፀዋል።

የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ፕሬዚዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ በትናንትናው ዕለት ወደ አዲስ አበባ ተጉዘዋል።

https://t.me/voa_amharic1
https://t.me/voa_amharic1


አባይ ባንክ ለመቄዶንያ የ10 ሚሊየን ብር ድጋፍ አደረገ

የባንኩ ፕረዜዳንት አቶ የኃላ እንደተናገሩ ባንኩ እንደ ባንክ ላለፉት ዓመታት ከመቄዶንያ ጎን አልጠፋም ዛሬም ይህንን እርዳታ ለማድረግ ስናስብ ሰራተኛውንም እናሳታፍ በማለት ከሰራተኛው 3 ሚሊዮን ብር ባንኩ 7 ሚሊዮን ብር በአጠቃላይ 10 ሚሊዮን ብር ድጋፍ ተደርጓል ብለዋል።

ድጋፉንም የተረከቡት ክቡር ዶክተር ቢንያም በለጠ፣ አርቲስትና ጋዜጠኛ ሰይፉ ፋንታሁን እና አርቲስት ይገረም ደጀኔ ናቸዉ።

የክቡር ዶክተር ቢንያም በለጠ ሌሎችም ተቋማት መሳተፍ እንዳለባቸው መልዕክት አስተላልፈዋል።

https://t.me/voa_amharic1
https://t.me/voa_amharic1


በዓዲጉዶምና በመቀለ ከተማ ዙርያ ንፁሀን ላይ በተከፈተ ተኩስ ጉዳት መድረሱ አቶ ጌታቸው ረዳ አስታወቁ

በተወሰኑ የጦር አዛዦች የተወሰነ የተሳሳተ ውሳኔና ህግን በጉልበት በማስፈፀም የመንግስት መዋቅር ለማፍረስ እየተደረገ ባለ ሙከራ ክልሉን አለመረጋጋት ውስጥ ከቶታል ያሉት ፕሬዝደንቱ፤ ይህንን የመንግስት መዋቅር ለማፍረስ የሚደረገውን ሙከራ በተቃወሙ ሰዎች ላይም ታጣቂዎች ተኩስ ከፍተዋል ሲሉ የትግራይ ጊዝያዊ አስተዳደር ፕሬዝደንት አቶ ጌታቸው ረዳ በኤክስ ገፃቸው ፅፈዋል።
ፕሬዝደንቱ በዓዲ ጉዶም ከተማና በመቀለ ዙርያ ድርጊቱን ለመቃወም በወጡ ንፁሓን ላይ በተከፈተ ተኮስ ጉዳት ደርሳልም ያሉ ሲሆን ድርጊቱ ህገወጡን የህወሓት ቡዱን ወደ ስልጣን የመመለስ እቅድ አካል መሆኑንም አስታውቀዋል። ይህም ከትግራይ ህዝብ ፍላጎትና ከፕሪቶርያ ስምምነት ተቃራኒ ነው ብለዋል።

https://t.me/voa_amharic1
https://t.me/voa_amharic1


ኤርትራ ለጄኔራል ፃድቃን ገብረትንሳኤ መልስ ሰጠች፡፡

ጄኔራል ፃድቃን በትላንትናው እለት በኢትዮጵያና በኤርትራ መካከል ጦርነት ሊነሳ ጫፍ ላይ እንደደረሰ ገልፀው በዚህም ትግራይ የጦር አውድማ መሆን እንደሌለባት ማስታወቃቸውን መዘገባችን ይታወሳል፡፡

ለዚህ አስተያየት የኤርትራ ማስታወቂያ ሚኒስትር አቶ የማነ ገብረመስቀል ዛሬ መልስ ሰጥተዋል፡፡

በመልሳቸው ያሰፈሩት የመጀመሪያው ነጥብ ጄኔራል ፃድቃን ከዚህ ቀደም ኤርትራን የመውረር አጀንዳ ደጋፊ መሆናቸውን ነው፡፡

በተለይም አሰብን በሀይል ወደኢትዮጵያ ስለመጠቅለል ጄኔራሉ በራሳቸው አንደበት የተናገሩትን አውስተዋል፡፡

በሁለተኝነት ያነሱት ነጥብ ደግሞ የኢትዮጵያና ኤርትራ ግንኙነት ጥሩ በነበረበት ወቅት ጭምር ኢትዮጵያ በአሰብ ላይ ይገባኛል ጥያቄ እንድታነሳ በሚስጥር ሲቀሰቅሱ እንደነበር ነው፡፡

አቶ የማነ ሲቀጥሉም "በኢትዮጵያና ኤርትራ ጦርነት ወቅት ኢትዮጵያ አሰብን ለመጠቅለል እድሉን ባለመጠቀሟ ጄኔራል ፃድቃን ተቆጭተዋል" ያሉ ሲሆን አሁን ደግሞ ሁለቱ አገራት የጦርነት ዝግጅት እንደጨረሱ አስመስለው መግለፃቸውን ጠቅሰዋል፡፡

የዚህ የትላንቱ አስተያየታቸው መነሻም የአዞ እንባ በማንባት የጦርነት አጀንዳ መቀስቀስ መሆኑን የገለፁት አቶ የማነ ይህም በኤርትራና በጎረቤቶቿ መካከል ጠላትነትን የመፍጠር ስሌት አካል ነው ብለዋል፡፡

https://t.me/voa_amharic1
https://t.me/voa_amharic1


ዩክሬን ከሩሲያ ጋር የ30 ቀን የተኩስ አቁም ስምምነትን ለመቀበል ዝግጁ መሆኗ ተሰማ

በሳውዲ አረቢያ ከአንድ ቀን የዩናይትድ ስቴትስ እና የዩክሬን ውይይት በኋላ በአሜሪካ የቀረበውን የ30 ቀን የተኩስ አቁም ስምምነት ዩክሬን ለመቀበል ዝግጁ መሆኗን ተናግራለች። የዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ ዋና ፀሀፊ ማርኮ ሩቢዮ ይህንኑ ሀሳብ ለሩሲያ እንደሚያቀርቡ እና " አሁን ኳሱ በእጃቸው ውስጥ ነው" ሲሉ ተደምጠዋል።የዩክሬኑ ፕሬዝዳንት ቮሎዶሚር ዘለንስኪ እንዳሉት ሩሲያ በ"አዎንታዊ" ሀሳብ እንድትስማማ የማሳመን ድርሻ የዩናይትድ ስቴትስ ብቻ ነው ብለዋል።

የማክሰኞው የጄዳ ንግግር በዜለንስኪ እና በአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በሞላላው የዋይት ሀውስ ቢሮ ውስጥ ከተፈጠረው ያልተለመደ ግጭት በኋላ በሁለቱ ሀገራት መካከል የመጀመሪያው ይፋዊ ውይይት ነው።በጋራ የሁለቱ ሀገራት ተወካዮች በሰጡት መግለጫ፣ ከዚህ ቀደም ታይቶ በማይታወቅ መልኩ የትራምፕ እና የዜለንስኪን ግጭት ተከትሎ ዋሽንግተን ያቋረጠችውን ለዩክሬን የስለላ መረጃ ልውውጥ እና የደህንነት ድጋፍ ወዲያውኑ እንደገና እንደሚጀምር ተናግራለች። የአሜሪካ እና ዩክሬን መግለጫ እንደሚያሳየው “ሁለቱም ልዑካን ቡድን ተደራዳሪ ቡድኖቻቸውን ለመሰየም መስማማታቸውን እና ዘላቂ ሰላም ለማምጣት የዩክሬን ደህንነትን ለማስፈን ድርድር ይጀምራሉ” ይላል።

ሩቢዮ ማክሰኞ ማምሻውን በጄዳህ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ሩሲያ ሃሳቡን እንደምትቀበል ተስፋ አደርጋለው ብለዋል። ዩክሬን " ተኩስ ለማቆም እና ለመነጋገር ዝግጁ ነች" ሲሉ አክለዋል። ሩሲያ የተኩስ አቁም ስምምነቱን ውድቅ ካደረገች " በሚያሳዝን ሁኔታ ሰላም ለማምጣት እንቅፋት የሆነው ማን እንደሆነ እናውቃለን" ብለዋል። "ዛሬ ዩክሬናውያን የተቀበሉትን ሀሳብ አቅርበናል ይህም የተኩስ ማቆም እና አፋጣኝ ድርድር ለማድረግ ነው።"፤ "ይህንኑ ለሩሲያውያን እናቀርባለን እናም ለሰላም አዎ እንደሚሉ ተስፋ እናደርጋለን፤ ኳሱ አሁን በእነሱ ግቢ ውስጥ ነው" ሲሉ ተደምጠዋል።

https://t.me/voa_amharic1
https://t.me/voa_amharic1

20 last posts shown.