Addis Ababa Education Bureau


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic
Category: not specified


ይህ ቻናል የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የቴሌግራም ቻናል ሲሆን በከተማ አስተዳደሩ እስከ ትምህርት ቤት ድረስ የተከናወኑ እንዲሁም ሀገራዊ ፣ አህጉራዊ እና አለማቀፋዊ የትምህርት መረጃዎች ተደራሽ የሚደረጉበት ነው፡፡

Related channels  |  Similar channels

Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Category
not specified
Statistics
Posts filter




በከተማ አስተዳደሩ የሚገኙ መምህራንን አጠቃላይ መረጃ ወደ ኢ-ስኩል ሲስተም ለማስገባት በሚያስችል አሰራር ዙሪያ ውይይት ተካሄደ፡፡


(ጷጉሜ 1/2016 ዓ.ም) በውይይቱ ርዕሳነ መምህራንን ጨምሮ የቢሮውና የክፍለከተማ የአይ ሲቲ ቡድን መሪዎችና ባለሙያዎች የተሳተፉ ሲሆን ሲስተሙን ባበለጸገው ትሪያ ትሬዲንግ አማካይነት የመምህራኑን መረጃ እንዴት ወደ ሲስተም ማስገባት እንደሚቻል ገለጻ ተደርጉዋል፡፡


የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የሶፍት ዌርና ሲስተም ልማት ቡድን መሪ ወይዘሮ ሰላም ተስፋዬ የመምህራኑ አጠቃላይ መረጃ ወደ ሲስተም መግባቱ ወጥ የሆነ እና ተአማኒነት ያለው መረጃ ለሚመለከተው አካል ተደራሽ ለማድረግ እንደሚረዳ አስታውቀዋል፡፡


ቡድን መሪዋ አክለውም ቢሮው የኢ-ስኩል ሲስተሙን በመጠቀም በከተማ አስተዳደሩ በሁሉም የመንግስት ትምህርት ቤቶች የ2017 ዓ.ም የተማሪዎች ምዝገባን ኦን ላይን ማካሄዱኑ ጠቁመው በቀጣይ የመምህራኑን መረጃ ወደ ሲስተም የማስገባትም ሆነ ኦን ላይን የተመዘገቡ ተማሪዎችን በየክፍሉ የመመደብ ስራ በአጭር ጊዜ ውስጥ የሚከናወን መሆኑን ገልጸዋል፡፡




አጠቃላይ ትምህርት የምዘና ረቂቅ መመሪያ ዙሪያ በባለድርሻ አካላት ውይይት ተካሄደ፡፡


(ጷጉሜ 1/2016 ዓ.ም) በመርሀ ግብሩ የክፍለከተማ የሁለቱ ስርአተ ትምህርት አስተባባሪዎች፤ የትግበራ ቡድን መሪዎች እና የፈተና ባለሙያዎችን ጨምሮ ከተመረጡ ትምህርት ቤቶች የተውጣጡ የመንግስትና የግል ትምህርት ቤቶች ርዕሳነ መምህራን እንዲሁም የክፍለከተማና ክላስተር ሱፐርቫይዘሮች ተሳታፊ ሆነዋል፡፡


የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የአጠቃላይ ትምህርት ምዘና ፈተና ዝግጅትና አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ዲናኦል ጫላ ረቂቅ መመሪያው በሁሉም የትምህርት እርከኖች የሚማሩ ተማሪዎችን በአግባቡ ለመመዘን እንዲቻል ታስቦ መዘጋጀቱን ጠቁመው ምዘናው የስርአተ ትምህርቱን ይዘት መሰረት አድርጎ የሚሰጥ እንደመሆኑ የተማሪዎቹ ለቀጣዩ የትምህርት እርከን በአግባቡ ዝግጁ እንዲሆኑ ታስቦ መመሪያው መዘጋጀቱን አስታውቀዋል፡፡


ዳይሬክተሩ አያይዘውም ከውይይቱ ተሳታፊዎች የሚነሱ ሀሳቦችን እንደ ግብአት በመጠቀም መመሪያውን የማሻሻል ስራ እንደሚሰራ ገልጸው በቀጣይ ከቢሮው የማኔጅመንት እና የአጠቃላይ ካውንስል አባላት ጋር በረቂቅ መመሪያው ዙሪያ ውይይት ተካሂዶ መመሪያው ተግባራዊ እንዲሆን የሚሰራ መሆኑን አስገንዝበዋል፡፡


በውይይቱ የቢሮው የአጠቃላይ ትምህርት የፈተና ዝግጅት አስተዳደር ቡድን መሪ ወይዘሪት መሰረት ኩማ የረቂቅ መመሪያውን ይዘት አቅርበው ተሳታፊዎች የተለያዩ አስተያየቶችን እና ጥያቄዎችን ያቀረቡ ሲሆን ለቀረቡ ጥያቄዎች መመሪያውን ባዘጋጁ አካላት ምላሽ ተሰቱዋል፡፡


Video is unavailable for watching
Show in Telegram
ግንባታው የተጠናቀቀው የለሚኩራ ክፍለከተማ የካ ቦሌ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት G+4 ሕንፃ


(ጷጉሜ 1/2016 ዓ.ም)


መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

Imo: - https://s.channelcom.tech/vlWdNr?from=TG
What Sapp: - https://whatsapp.com/channel/0029VaHFiBpA2pLF0lLslK2D
flickr :- https://www.flickr.com/photos/197652854@N04/
You Tube: @addisababaeducationbureau9728' rel='nofollow'>https://www.youtube.com/@addisababaeducationbureau9728
TikTok፡- @aaeducationbureau' rel='nofollow'>https://www.tiktok.com/@aaeducationbureau
Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau
Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc
Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication
Blog: - http://www.aacaebc.wordpress.com/
Instagram: - https://www.instagram.com/aacaeb/
Website: - aaceb.gov.et
Email;- aacaebc@gmail.com


ከአፍሪካ ከተሞች ፎረም ጎን ለጎን ከናሚቢያዋ ዋና ከተማ ዊንድሆክ ከንቲባ ኦማግኖ ካማቲ ጋር በጋራ ተጠቃሚነት ላይ ውይይት በማድረግ የእህትማማች ስምምነት ተፈራርመናል።


(ጷጉሜ 1/2016 ዓ.ም) የውይይት ቆይታችን ወሳኝ የትብብር ጉዳዮች ላይ ያተኮረ የስምምነት ሰነድ ያካተተ ሲሆን በተለይም በፍሳሽ አወጋገድና በውሃ አቅርቦት፣ በከተማ ፕላን፣ በንግድ፣ በኢንቨስትመንት፣ በቱሪዝም፣ በማኑፋክቸሪንግ፣ በኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ፣ በቴክኒክና ሙያ እንዲሁም በአቅም ግንባታ ስራዎች ዙሪያ ዘላቂ ትብብር መፍጠር የሚያስችል እና በሁለቱ ከተሞች መካከል ጠንካራ ግንኙነት የሚፈጥር ይሆናል።



ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ህዝቦቿን ይባርክ


ከንቲባ አዳነች አቤቤ


መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

Imo: - https://s.channelcom.tech/vlWdNr?from=TG
What Sapp: - https://whatsapp.com/channel/0029VaHFiBpA2pLF0lLslK2D
flickr :- https://www.flickr.com/photos/197652854@N04/
You Tube: @addisababaeducationbureau9728' rel='nofollow'>https://www.youtube.com/@addisababaeducationbureau9728
TikTok፡- @aaeducationbureau' rel='nofollow'>https://www.tiktok.com/@aaeducationbureau
Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau
Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc
Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication
Blog: - http://www.aacaebc.wordpress.com/
Instagram: - https://www.instagram.com/aacaeb/


Video is unavailable for watching
Show in Telegram
ለክቡራንና ለክቡራት ተገልጋዮቻችን እንኳን ለጷጉሜ ቀናት አደረሳችሁ እያልን በጷጉሜ 2 በሪፎርም ቀን አገልግሎት_የምንሰጥ መሆኑን እናሳውቃለን፡፡


(ጷጉሜ 1/2016 ዓ.ም) ለክቡራንና ለክቡራት ተገልጋዮቻችን እንኳን ለ2016 ዓ.ም የጷጉሜ ቀናት አደረሳችሁ እያልን የሪፎርም ቀንን (ጷጉሜ 2) ምክንያት በማድረግ በእለቱ (ቅዳሜ) ለክቡራን ተገልጋዮቻችን አገልግሎት የምንሰጥ መሆኑን እናሳውቃለን።


በድጋሜ እንኳን አደረሳችሁ!


መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

Imo: - https://s.channelcom.tech/vlWdNr?from=TG
What Sapp: - https://whatsapp.com/channel/0029VaHFiBpA2pLF0lLslK2D
flickr :- https://www.flickr.com/photos/197652854@N04/
You Tube: @addisababaeducationbureau9728' rel='nofollow'>https://www.youtube.com/@addisababaeducationbureau9728
TikTok፡- @aaeducationbureau' rel='nofollow'>https://www.tiktok.com/@aaeducationbureau
Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau
Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc
Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication
Blog: - http://www.aacaebc.wordpress.com/
Instagram: - https://www.instagram.com/aacaeb/
Website: - aaceb.gov.et
Email;- aacaebc@gmail.com


እዚህ የደረስነው ብዙ ነገሮችን ተሻግረን ነው። ያልተመዘዘ ሰይፍ፣ ያልተሰበቀ ጦር፣ ያልተተከለ ወጥመድ፣ ያልተሤረ ሤራ፣ ያልተቆፈረ ገደል አልነበረም። በፈጣሪ ርዳታ ሁሉንም እየተሻገርነው ነው።


(ጷጉሜ 1/2016 ዓ.ም) ጦርነትን፣የኮሮና ወረርሽኝን፣ ግጭትን፣ የአንበጣ መንጋን፣ የሕዳሴ ግድብ ውጣ ውረድን፤ ተሻግረናቸዋል። ሌሎችንም እየተሻገርን ነው።


ተሻጋሪዎች ነን። አሻጋሪያችንም የማይሰበር ነው። ከማዶ አንቀርም። በመሐልም አንወድቅም። በድል እንደምንሻገር ቅንጣት ጥርጥር የለንም።


ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)



መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

Imo: - https://s.channelcom.tech/vlWdNr?from=TG
What Sapp: - https://whatsapp.com/channel/0029VaHFiBpA2pLF0lLslK2D
flickr :- https://www.flickr.com/photos/197652854@N04/
You Tube: @addisababaeducationbureau9728' rel='nofollow'>https://www.youtube.com/@addisababaeducationbureau9728
TikTok፡- @aaeducationbureau' rel='nofollow'>https://www.tiktok.com/@aaeducationbureau
Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau
Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc
Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication
Blog: - http://www.aacaebc.wordpress.com/
Instagram: - https://www.instagram.com/aacaeb/
Website: - aaceb.gov.et
Email;- aacaebc@gmail.com


በመርሀ ግብሩ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የስርአተ ትምህርት ማበልጸግና ትግበራ ባለሙያው አቶ ምህረቱ ዋሌ የስራ ክፍሉን የ2017 ዓ.ም እቅድ አቅርበው ተሳታፊዎች ውይይት አካሂደዋል፡፡


መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

Imo: - https://s.channelcom.tech/vlWdNr?from=TG
What Sapp: - https://whatsapp.com/channel/0029VaHFiBpA2pLF0lLslK2D
flickr :- https://www.flickr.com/photos/197652854@N04/
You Tube: @addisababaeducationbureau9728' rel='nofollow'>https://www.youtube.com/@addisababaeducationbureau9728
TikTok፡- @aaeducationbureau' rel='nofollow'>https://www.tiktok.com/@aaeducationbureau
Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau
Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc
Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication
Blog: - http://www.aacaebc.wordpress.com/
Instagram: - https://www.instagram.com/aacaeb/
Website: - aaceb.gov.et
Email;- aacaebc@gmail.com


የስርአተ ትምህርት ማበልጸጊያና ትግበራ ዳይሬክቶሬት የዘርፉን የ2016 ዓ.ም አፈጻጸም እና የ2017 ዓ.ም እቅድ ገመገመ፡፡

(ነሀሴ 30/2016 ዓ.ም) በመርሀ ግብሩ የክፍለከተማ የስርአተ ትምህርት ትግበራ ቡድን መሪዎችና ባለሙያዎችን ጨምሮ የወረዳ ስርአተ ትምህርት ትግበራ ባለሙያዎች ተሳታፊ ሆነዋል፡፡


የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የስርአተ ትምህርት ማበልጸጊያና ትግበራ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ጌታቸው ታለማ ውይይቱ በ2016 ዓ.ም ስርአተ ትምህርቱ በአግባቡ ተግባራዊ እንዲሆን የተከናወኑ የድጋፍና ክትትል ተግባራት አፈጸጸም ምን ደረጃ ላይ እንደሚገኝ በመገምገም በአፈጻጸም የተስተዋሉ ጠንካራ ጎኖችን በማስቀጠልም ሆነ በሂደት ያጋጠሙ ክፍተቶችን በማረም በ2017ዓ.ም የተሻለ ስራ ለመስራት ታስቦ መዘጋጀቱን አስታውቀዋል፡፡


ዳይሬክተሩ በ2016 ዓ.ም በዘርፉ የተከናወኑ ዋና ዋና ተግባራትን የተመለከተ ሪፖርት ያቀረቡ ሲሆን የተማሪዎች የመማሪያ መጽሀፍና የመምህር መምሪያ ብቃትን በማረጋገጥ ለትምህርት ቤቶች እንዲሰራጭ መደረጉን ፤በተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች የአቅም ማጎልበቻ ስልጠናዎች መሰጠታቸውን፤የመምህራንን እለታዊና አመታዊ እቅድ አዘገጃጀት እና የቤተ ሙከራ አደረጃጀትን በተመለከተ በየትምህርትቤቱ የድጋፍና ክትትል ስራ መሰራቱን እንዲሁም በሁሉም የመንግስትና የግል ትምህርትቤቶች ስርአተ ትምህርቱ በአግባቡ ተግባራዊ መደረጉን በቼክሊስት የማረጋገጥ ስራ መሰራቱን በሪፖርታቸው ከተጠቀሱ ነጥቦች መካከል የተወሰኑት ናቸው፡፡


Biiroo barnootaa Finfinneetti Daayireektoreetiin qophiifi raawwii sirna barnootaa Afaan Oromoo gamaggama karoora bara 2017fi galmee barattootaa taasisee jira.


gaggeeffame kana irratti waajjira barnootaa kutaalee magaalaa irraa dursitoonni garee sirna barnootaa Afaan Oromoofi Ogeeyyii sirna barnootaa kutaalee magaalaafi aanaalee hirmaatanii jiru.


Biiroo barnootaa Finfinneetti Daayireektarri Daayireektoreetii qophiifi raawwii sirna barnootaa Afaan Oromoo Obbo Tashoomaa Qanaasaa baniinsa marichaa irratti haasaa taasisaniin hojiilee gurguddoo biiroo barnootaa bulchiinsa magaalichaatin hojjatamaniin bu'aaleen jajjabeessan galmeeffamanii jiru. Isuma kana itti fufsiisuun gabinaan hojjachuun barbaachisaa akka ta'u hubachiisanii jiru. Daayireektarichi itti aansuun qormaata sadarkaa magaalaatti qophaa'een qabxiin jajjabeessaa ta'e galmeeffamuu isaa kaasanii, qabxiin barattootaa herreegaafi Afaan Ingiliziikutaa kutaa 6ffaafi 8ffaa haga yaadame waan hintaaneef fuulduratti xiyyeeffannoon barbaachisaa kennamuufi akka qabu hubachiisanii jiru.


Hirmaattonni marii sanadoota dhiyaatan irratti yaada adda addaafi gaafii kaasanii deebiin kennameefii jira.


መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

Imo: - https://s.channelcom.tech/vlWdNr?from=TG
What Sapp: - https://whatsapp.com/channel/0029VaHFiBpA2pLF0lLslK2D
flickr :- https://www.flickr.com/photos/197652854@N04/
You Tube: @addisababaeducationbureau9728' rel='nofollow'>https://www.youtube.com/@addisababaeducationbureau9728
TikTok፡- @aaeducationbureau' rel='nofollow'>https://www.tiktok.com/@aaeducationbureau
Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau
Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc
Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication
Blog: - http://www.aacaebc.wordpress.com/
Instagram: - https://www.instagram.com/aacaeb/
Website: - aaceb.gov.et
Email;- aacaebc@gmail.com


የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የአፋን ኦሮሞ ስርአተ ትምህርት ማበልጸግና ትግበራ ዳይሬክቶሬት የ2017 ዓ.ም እቅድ እና የተማሪ ቅበላ አፈጻጸምን ገመገመ።


(ነሀሴ 30/2016ዓ.ም) በመርሀ ግብሩ የክፍለ ከተማ ትምህርት ጽህፈት ቤት የአፋን ኦሮሞ ስርአተ ትምህርት ትግበራ ቡድን መሪዎች እና ባለሙያዎችን ጨምሮ የወረዳ የአፋን ኦሮሞ ስርአተ ትምህርት ትግበራ ባለሙያዎች ተሳታፊ ሆነዋል።


የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የአፋን ኦሮሞ ስርአተ ትምህርት ማበልጸግና ትግበራ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ተሾመ ቀናሳ በውይይቱ መክፈቻ ባስተላለፉት መልዕክት በከተማ አስተዳደሩ የአፋን ኦሮሞ ስርአተ ትምህርትን ተደራሽ ለማድረግ በተከናወኑ የተለያዩ ተግባራት በየጊዜው አበረታች ውጤት እየተመዘገበ እንደሚገኝ ጠቁመው ለ2017 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የአፋን ኦሮሞ ትምህርትን ተደራሽነት ለማሳደግ ከተማሪ ቅበላ ጀምሮ የተለያዩ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን በመጥቀስ የተማሪ ቅበላ አፈጻጸሙ አሁን ካለበት ደረጃ ከፍ እንዲል በየደረጃው የሚገኙ ባለድርሻ አካላት በትኩረት መስራት እንደሚገባቸው አስገንዝበዋል።


ዳይሬክተሩ አያይዘውም በ2016ዓ.ም የተማሪዎችን ውጤት ለማሳደግ በተከናወኑ የተለያዩ ተግባራት በ6ኛ እና 8ኛ ክፍል ተስፋ ሰጪ ውጤት መመዝገቡን ጠቁመው በሒሳብና እንግሊዘኛ የትምህርት አይነቶች ግን የተማሪዎች ውጤት በሚጠበቀው ደረጃ ባለመሆኑ በቀጣይ ትኩረት ማድረግ እንደሚገባ አስገንዝበዋል።


የውይይቱ ተሳታፊዎም በቀረቡ የመወያያ ሰነዶች ዙሪያ የተለያዩ አስተያየቶችን እና ጥያቄዎችን ያቀረቡ ሲሆን ለቀረቡ ጥያቄዎች በስራ ክፍሉ ምላሽ ተሰቷል።


Video is unavailable for watching
Show in Telegram
የጷጉሜ ቀናት


(ነሀሴ 30/2016 ዓ.ም)



መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

Imo: - https://s.channelcom.tech/vlWdNr?from=TG
What Sapp: - https://whatsapp.com/channel/0029VaHFiBpA2pLF0lLslK2D
flickr :- https://www.flickr.com/photos/197652854@N04/
You Tube: @addisababaeducationbureau9728' rel='nofollow'>https://www.youtube.com/@addisababaeducationbureau9728
TikTok፡- @aaeducationbureau' rel='nofollow'>https://www.tiktok.com/@aaeducationbureau
Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau
Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc
Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication
Blog: - http://www.aacaebc.wordpress.com/
Instagram: - https://www.instagram.com/aacaeb/
Website: - aaceb.gov.et
Email;- aacaebc@gmail.com





15 last posts shown.