በማስተዋል ዘምሩ ✨


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic
Category: not specified


⚠️ Contact us through our bot: 💬 @zemeru_bot
⚠️ Chat Group: https://t.me/bemastewalzemeru

Related channels  |  Similar channels

Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Category
not specified
Statistics
Posts filter


WARA BETHEL 2025


የመሐል ሲዳማ ቅርጫፍ ሰበካን ልዩ ከሚያደርጉት አንዱ ከመላ አገሪቱና ከአለም ዙሪያ የሚመጡ ምዕመናን የሚሳተፉበት ታላቁ አለም አቀፍ ጉባኤ የሚካሄድበት ሰፊው የዋራ ሜዳ የሚገኝበት መሆኑ ነው። የኢትዮጵያ ሐዋርያዊት ቤተክርስቲያን በዚያ ሜዳ ላይ በብሎኬት የታጠረ ሰፊ ቦታ አላት፤ በቦታው የኮንፍራንስ ማዕከል ተገንብቶ አለም አቀፍ ጉባኤ ከ1984 ዓ.ም ጀምሮ በየአመቱ እየተካሄደ ይገኛል።

ያዕቆብ ከቤርሳቤህ ወጥቶ ወደ ካራን ሲሄድ ድንጋይ ተንተርሶ የተኛበትን "ሎዛ" የምትባለውን ስፍራ እግዚአብሔር ተገልጦለት ካነጋገረው ቦኃላ ይህ የእግዚአብሔር ደጅ ነው ስል "ቤቴል" ብሎ እንደጠራት፣ እንዲሁ በዋራ አከባቢ እግዚአብሔር እራሱ እንዲመለክበት በደሙ ለዋጃት ቤተከርስቲያን አሳልፎ ሰጥቶ በዚያ ስፍራ እውነቱን ስላበራ ቤተክርስቲያን "ዋራ ቤቴል" ብላ ጠራችው።

የዋራ ኮንፍረንስ ማዕከል በኢየሩሳሌም ከተማ ምሳሌ የተሰራ ቅጥርና መሰረት አለው። ቅጥሩ አራት ማዕዘን ቅርጽ ያለው ሆኖ በአራቱም አቅጣጫ እያንዳንዱ ሶስት ሶስት በሮች በድምሩ አስራ ሁለት በሮች አሉት። የዋራ ቤቴል የኮንፍራንስ ማዕከል 12 ትላልቅ ሼዶች የተገነቡለት የተንጣለለ ሰፊ ሜዳ ነው።

ከመጋቢት 5 ቀን 1984 ዓ.ም ጀምሮ ህዝቡን በበረከትና በምህረት እየጠበቀና እየጎበኘ፣ በድንቅና የሰው ልብና አዕምሮ ልገምተው ከምችለው በላይ ብዙ አስደናቂ ነገሮችን ያከናወነበት ዋራ ቤቴል የአምላካችን የእግዚአብሔር ተአምራት የሚገልጽ ነው።

ዋራ ሜዳ ላይ የማያቋርጥ ሃሌሉያና እልልታ በሽብሸባ ታጅቦ አስተጋባ። ግማሹ ይሰግዳል፣ ግማሹ ያመሰግናል፣ ሌላው ኢየሱስ እያለ ይጮሃል፤ እጆቹ ተዘርግተው ሞትን ለዘላለም የዋጠውን ኢየሱስን ያመሰግናሉ። ከኢየሱስ ፈውስ፣ በረከትንና ምህረትን የሚሹ ሁሉ ኢየሱስን ዝቅ ብለው፣ ሜዳ ላይ ተንበርክከው እንዲሰማቸው ይማጸኑታል።

በዚህ የሰው ልጅ ብቻ ሳይሆን የሰማይ መላዕክት ጭምር በተገኙበት ቢሾፕ ተክለማርያም ገዛኸኝ "ኢየሱስ በመካከላችን ነውና ምስጋናን አታቋርጡ" ብሎ ሲናገር የመንፈስ ቅዱስ ኃይል በዋራ ቤቴል ፈሰሰ። በህመም ስሰቃዩ የነበሩ ተፈቱ፣ "አምላኬ ዛሬስ አያልፈኝም የእስራቴን ገመድ ይበጥሳል" ብለው የሚጠብቁ ነፍሳት ዘመናትን በአጋንንት እስራት ያሳለፉ ተፈትተው ለምስጋና እጃቸው ሲዘረጉ ታየ።

እግዚአብሔር የጠራው ጉባኤ ለመሆኑ መንፈሱን እያፈሰሰ በደዌና በሕመም የታሰሩትን እየፈታ በዋራ ቤቴል አምላካችን በሕዝቡ መካከል እንደነበረ መሰከረ።

በብሉይ ኪዳን ዘመን የእግዚአብሔር ህዝብ አንድም ሳይቀር በእግዚአብሔር ፊት ሊታይ ከነቤተሰቡ ይወጣ እንደነበርና እግዚአብሔርም ለህዝቡ ህጉን ያስተምርና ይባርክ እንደነበር መጽሐፍ ቅዱስ ይመሰክርልናል።

ዛሬም በአዲስ ኪዳን የአብርሃም፣ የይስሐቅና የያዕቆብ አምላክ ሕዝቡን በጉባኤ ሰብስቦ መንፈስ ቅዱስ እያፈሰሰ ሲባርክና የደመና ዓምድ ሲያወርድ የሚታይበት ጉባኤ አዘጋጅቷል።

ከሰሜን፣ ከደቡብ፣ ከምስራቅና ከምዕራብ የሃገሪቱ ክፍሎች የተሰበሰቡ በደሙ የተዋጁ የጌታ የኢየሱስ ክርስቶስ ልጆች በዚህ ዓለም ብቻ ሳይሆን ሊመጣ ባለው ዓለም ደግሞ ከሚጠራበት ስም ሁሉ በላይ የሆነውን የታላቁን የአምላካችንን የኢየሱስ ክርስቶስን ስም እየጠሩ በፊቱ ሲሰግዱና ሲዘምሩ፣ በደዌና በአጋንንት የታሰሩ ሲፈቱ፣ ያየንበት፣ ከዚህ ጨለማ ዓለም አንዱን አምላክ ከምያስክድ ክፉ ትምህርት ሰዎች በንስሐ ሲመለሱ የታየበት ድንቅ ጉባኤ ነው።

ብቻውን በዙፋኑ ላይ ተቀምጦ ያለውን አንዱን አምላክ በአንድ ልብና በአንድ መንፈስ ከተሰበሰበ ህዝብ ጋር ማምለክ ምንኛ መታደል ነው! ህዝቡም በአንድ ልብ እጁን ዘርግቶ በመካከሉ ያለውን አምላክ ሲያመሰግን ማየትም ነፍስን በሃሴት የሚሞላ ድንቅ ትዕይንት ነው። እግዚአብሔር የሚገለጥበት ጉባኤ!!

ለ34ኛው ዋራ ቤቴል አለማቀፍ ኮንፍረንስ እንኳን ጌታ ኢየሱስ በሰላም በጤና አደረሰን! ጉባኤም ከመጋቢት 5-7/2017 ዓ.ም ይካሄዳል። ሁላችሁም በክርስቶስ ኢየሱስ ፍቅር ተጋብዛችኋል።

@zemeru
@zemeru
በማስተዋል ዘምሩ Telegram Channel JOIN US for more Updates!

611 0 10 3 22



ኤልዛቤል የእግዚአብሔርን ነቢያት ባስገደለች ጊዜ 100 የእግዚአብሔርን ነቢያትን በዋሻ ደብቆ በየእለቱ እንጀራና ውሃ እየሰጠ እነዚያን የእግዚአብሔርን ነቢያትን የመገበ የአክዓብ የቤቱ አዛዥ፣ ያ እግዚአብሔርን የሚፈራ ሰው ማን ይባላል?
Poll
  •   አብድዩ
  •   አቤሜሌክ
  •   ባሮክ
  •   አቤኔር
6 votes


ጢሞቴዎስ ማን ነው?


◉ ጢሞቴዎስን ለመጀመሪያ ጊዜ የሚናገኘው በሐዋ 16፡1-5 ነው፤ ያደገው ደግሞ ልስጥራን በምትባል ከተማ ነው፡፡

◉ አባቱ የግሪክ ሰው፣ እናቱ አይሁዳዊት ነበረች። በእናቱ ኤውንቄና በአያቱ ሎይድ በኩል የብሉይ ኪዳንን ተምሯል (2ኛ ጢሞ 1፡ 5፤ 2ኛ ጢሞ 3፥14-15)፡፡

◉ ጢሞቴዎስ የጳውሎስ አጋዥ ነበር፡፡ ለ15 ዓመታት ከጳውሎስ ጋር አብሮ ሲያገለግል ነበር፡፡

◉ ጢሞቴዎስ ወጣት ቢሆንም እንኳ ጠንካራ የቤተ ክርስቲያን መሪ ሊሆን እንደሚችል ጳውሎስ ስለተረዳ ይዞት ለመዞር ፈለገ፡፡ ሆኖም ጢሞቴዎስ በእናቱ ምክንያት አይሁዳዊ ቢሆንም፤ ካልተገረዝ በቀር በአይሁዶች ዘንድ ተቀባይነት ስለማይኖረው ገረዘው፡፡

◉ ጢሞቴዎስ ቤተ ክርስቲያንን እንዲያጽናና በመጀመሪያ ወደ ተሰሎንቄ ተላከ (1ኛ ተሰ 3፥2)። ከዚያም ወደ መቄዶንያና ወደ ቆሮንቶስ ተላከ (1ኛ ተሰ 3፥4-7)። ከዚያም የተሰበሰበውን የእርዳታ ገንዘብ ይዞ ከጳውሎስ ጋር ወደ ኢየሩሳሌም ሄደ (ሐዋ 20፡4)፡፡

◉ ጳውሎስ የፊልጵስዩስንና የቄላስያስን መልዕክቶች ሲጽፍ ጢሞቴዎስ አብሮት ነበረ (ፊል 1፥1፤ ቄላ 1፥1)፡፡

◉ ጳውሎስ ሁለቱን መልዕክቶችን ለጢሞቴዎስ ሲጽፍ እርሱ በኤፌሶን ቤተ ክርስቲያን ውስጥ እያገለግል ነበረ (1ኛ ጢሞ 1፡3)፡፡

◉ ጢሞቴዎስ ባልታወቀ ጊዜ ታስሮም ነበር (ዕብ 13፡23)

◉ ጢሞቴዎስ የጳውሎስ ታማኝ ረዳት በመሆን እስከ መጨረሻው ጸንቶ የክርስቶስን ወንጌል በታማኝነት አብሮት አገለገለ፡፡

@zemeru
በማስተዋል ዘምሩ Telegram Channel JOIN US for more Updates!


የአሞን ልጆችን በእጄ አሳልፈህ ከሰጠኸኝ ወደ ቤቴ ስመለስ መጀመሪያ የሚያገኘኝን ለእግዚአብሔር እሰዋለሁ ብሎ ተስሎ ውጊያውን አሸንፎ ስመለስ አባቷን ለመቀበል ከበሮ ይዛ የወጣቺውን የሚወዳትን ልጁን ለእግዚአብሔር ቃል ስለገባ የሠዋት የእስራኤል መስፍን ማን ይባላል?
Poll
  •   ሳምሶን
  •   ጌዴዎን
  •   ናዖድ
  •   ዮፍታሔ
54 votes


ንጉሱ ሰለሞን የተናገራቸው ምሳሌዎች ምን ያህል ነበሩ?
Poll
  •   1,500
  •   3,000
  •   1,050
  •   3,500
62 votes


#Confirmed

34ኛው ዋራ ቤቴል አለማቀፋዊ ኮንፍረንስ ከመጋቢት 5-7/2017 ዓ.ም ይካሄዳል። ስንቶቻችሁ ተዘጋጅታችኋል?

@zemeru


ኢየሱስ ይወደው የነበረው ደቀመዝሙር፣ ሌሎቹ ኢየሱስን ለመጠየቅ የሚፈሩትን ጥያቄ እንኳ እስከ ደረቱ ድረስ በመጠጋት የሚጠይቅ ደቀመዝሙር ማነው?
Poll
  •   ጴጥሮስ
  •   ዮሐንስ
  •   ያዕቆብ
  •   ጳውሎስ
81 votes


ንጉሱ ዳዊት ለኢዮአብ ደብዳቤ ልኮ በጦር ሜዳ ያስገደለው ኦርዮ ከንጉሱ ሰላሳ ሰባት (37) ሃያላን መካከል አንዱ ነበር።
Poll
  •   እውነት
  •   ሀሰት
17 votes


ንጉሱ ሰለሞንና ልጁ ሮብአብ እንደ አባታቸው እንደ ዳዊት አምላካቸውን ፈጽሞ ባለመከተላቸው ምክንያት እግዚአብሔር ከእስራኤል አስሩን ነገድ ቀድዶ ለማን ነበር የሰጠው?
Poll
  •   ለአኪያ
  •   ለኢዮርብዓም
  •   ለባኦስ
  •   ለአሳ
19 votes


የእስራኤል ልጆች ከግብጽ ከወጡ ከስንት አመት በኃላ ነው ንጉሱ ሰለሞን የእግዚአብሔርን ቤት ለመስራት የተነሳው?
Poll
  •   400 አመት
  •   450 አመት
  •   480 አመት
  •   520 አመት
62 votes


ጥያቄ ኢየሱስ የተሰቀለበት ቦታ ማን ተብሎ ይጠራል ?
Poll
  •   ሀ) ሰማሪያ
  •   ለ) ናዝሬት
  •   ሐ) ጌቴሴማኔ 
  •   መ) ቤተልሔም 
  •   ሠ) ጎሎጎታ
70 votes


ጥያቄ ሁለቱን እስራኤላውያን ሰላዮች በኢያሪኮ የደበቀችው ሴት ማን ትባላለች? 
Poll
  •   ሀ) ሩት 
  •   ለ) ረዓብ 
  •   ሐ) አስቴር 
  •   መ) ዲቦራ 
84 votes


#መልዕክት

የእግዚአብሔር ሰው ወንጌላዊ ተዎድሮስ አልታዬ በአንድ ጉባኤ ካስተላለፉት መልዕክት የተወሰደ!


ሕዳር, 2017 ዓ.ም

@zemeru
በማስተዋል ዘምሩ Telegram Channel JOIN US for more Updates!


አገልጋዩ... በርሃብ በጥማቱ መታረዝና ስደቱ፣ መገፋቱ አንዳች ሳይገደው ለወንጌል የሚጋደለው፣ ቤቴን ልጆቼንም ሳይል ሁሉን ስላንተ የጣለ፣ እርሱ ነው ያንተ አርበኛ በመንግስትህም አንደኛ።


Let us share our deepest love to our Father 🙏🩷

@zemeru


QUESTION! እግዚአብሔር ሰማይና ምድርን በስንት ቀን ፈጠረ ?
Poll
  •   ሀ) 3
  •   ለ) 6
  •   ሐ) 7
  •   መ) 10
48 votes

1.7k 0 10 14 30

ግጥም


ህዝቤን በመሻቴ ስጠኝ
በእህት ስጦታ ደጀኔ

በንግስት አስቴር ሕይወት ዙሪያ ያጠነጠነ መንፈሳዊ ግጥም! ሳያዳምጡ አይለፉ! ተባረኩ!


@zemeru
@zemeru
በማስተዋል ዘምሩ Telegram Chennel JOIN US for more Updates!


New Single Song


ተሻገርኩበት
ወ/ም ሹሜ ኤልያስ

ዘንድሮን እንኳን አልሻገርም
በህያዋን ምድር በቃ አልኖርም
ብዬ ተስፋዬን በቆረጥኩበት
ምህረትህ በዝቶ ተሻገርኩበት
ለኔ ድልድይ መሸጋገርያ
በፍርሀት ቀኔ ለኔ መመኪያ
ኢየሱስ ሁሌ የልቤ ሙላት
ምተማመንህ የኔ ውድ አባት

አፌ ያቀርባል ምስጋና
አድርገኸኛልና ቀና ቀና
ክብር እልልታ ቤትህን ይሙላ
አሻግረኸኛል ሆነኸኝ ጥላ

በጥማት መሬት በምድረበዳ
በጠላት ቀስቶች ነፍሴ ተሰዳ
ረዳት የለዉም ህዝብ ሁሉ ሲለኝ
ከሰማይ ነበር እኔን ሚረደኝ

ልቤ በፍርሀት በሀዘን ተሞልቶ
የሚይዘውን ስያጣ ተስፍ ተሟጦ
ለካስ ሚረዳኝ ችግረን ሁሉ
መቶ አፅናኝ ኢየሱስ በቃሉ

ምስጋናን እንጂ ምን እከፍላለዉ
ያለኝን ይዤ ፊትህ እቀርባለዉ
የደስታን መዝሙር ልቤ አፍልቆ
ያመሰግንሀል ወጥመድ ተሰብሮ

@zemeru
@zemeru
በማስተዋል ዘምሩ Telegram Chennel JOIN US for more Updates!


Message

Bishop Degu Kebede
በህሊና ወቀሳ ልምትቸገሩ

...ዳዊት እጅግ ተጨነቀ፤ ዳዊት ግን በአምላኩ በእግዚአብሔር ልቡን አበረታ። 1ኛ ሳሙኤል 30፥6

@zemeru
በማስተዋል ዘምሩ Telegram Chennel JOIN US for more Updates


Call For Conference


በኢትዮጵያ ሐዋርያዊት ቤተክርስቲያን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ሰበካ አመታዊ ኮንፍረንስ ከየካቲት 6-9/207 ዓ.ም በሆሳዕና እናት አጥቢያ ጊቢ ውስጥ ይካሄዳል።

ሁላችሁም በክርስቶስ ኢየሱስ ፍቅር ተጋብዛችኋል!

@zemeru
@zemeru

20 last posts shown.