ዳጉ-ጆርናል/Dagu-Journal


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic


The best fiction is far more true than any journalism
📢 ተዓማኒ የመረጃ ምንጭ ፤ ለሙያው ስነምግባር ተገዢ በሆኑ ጋዜጠኞች ብቻ
👉 በፌስቡክ ገፆቻችን https://www.facebook.com/simon.dereje.56
👉 https://www.facebook.com/mik0Man


Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Statistics
Posts filter


የኢትዮ ቴሌኮም ሰራተኛ በስራ ላይ እያለ በኤሌክትሪክ አደጋ ህይወቱ አለፈ

በትላንናው እለት እሁድ ግንቦት 20 ቀን 2015 ዓ.ም በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ወረዳ 1 ዓለም ባንክ እየተባለ በሚጠራዉ አካባቢ በኤሌክትሪክ አደጋ የአንድ ሰዉ ህይወቱ ማለፉን የእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አስታወቀ።

አደጋዉ ያጋጠመዉ ወጣት እድሜዉ 28 ዓመት የሆነ የኢትዮ ቴሌኮም ሰራተኛ ሲሆን በስራ ላይ ሆኖ ባለገመድ የስልክ መስመር በመዘርጋት ላይ እያለ ከከፍተኛ የኤሌክትሪክ መስመር ጋር ተገናኝቶ የሞት አደጋ መድረሰን የእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን የህዝብ ግንኙነት ባለሙያ አቶ ንጋቱ ማሞ ለብስራት ሬድዮ ተናግረዋል።

የእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን የአደጋ ጊዜ ሰራተኞች የወጣቱን አስከሬን  አዉርደዉ ለፖሊስ አስረክበዋል።

በተመሳሳይ ዓርብ ግንቦት 18 ቀን 2015 ዓ.ም በቦሌ ለሚ ኢንዱስትሪ ፖርክ ሰራተኛ በስራ ላይ እንዳለ በኤሌክትሪክ አደጋ ህይወቱ ማለፉ  ብስራት ሬዲዮ መዘገቡ ይታወሳል።

በሳምራዊት ስዩም
#ዳጉ_ጆርናል


በሩሲያ አንድ ካፌ ከእናቱ ጡት ወተት የሚዘጋጅ ማኪያቶ ማቅረብ ሊጀምር መሆኑን አስታወቀ

በሩሲያ ፐርም ከተማ የሚገኝ አንድ ካፌ የእናት የጡት ወተት የተቀላቀለበት ማኪያቶ ለማቅረብ ማቀዱን ካስታወቀ በኋላ ከፍተኛ ትኩረት አግኝቷል። መቀመጫውን በፐርም ላይ ላፕ ያደረገውና በርካታ ቅርንጫፎች ያሉ ኮፊ ስማይል እንደ ማኪያቶ እና ካፑቺኖ ላሉ አቅርቦቶቹ የሰው ልጅ የጡት ወተት እንደ ግብአት ለመጠቀም መወሰኑን አስታውቋል።

አዲሱን ንጥረ ነገር የሚያስተዋውቅ ፖስተሮች በከተማዋ የተለያዩ ስፍራዎች ተለጥፈዋል። የኮፊ ስማይል ባለቤት ማክሲም ኮቤሌቭ  ካፌዎቹ ልዩ በሆነ መልኩ እውነተኛ የጡት ወተት ይጠቀማሉ ሲሉ ተናግረዋል። ከእናት ጡት ወተት ለሚዘጋጅ ማኪያቶ 650 የራሺያ ሩብልስ ወይም 8 የአሜሪካን ዶላር ዋጋ ተቆርጦለታል።

በስምኦን ደረጄ
#ዳጉ_ጆርናል


🇹🇷አጫጭር መረጃዎች በቱርክ ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ዙሪያ

🇹🇷ሬሴፕ ጣይብ ኤርዶጋን ፕሬዝዳንታዊ ምርጫውን አሸንፈው በድጋሚ የቱርክ ፕሬዝዳንት ሆነው መመረጣቸውን የቱርክ ጠቅላይ ምርጫ ምክር ቤት (YSK) ኃላፊ ተናግረዋል።የምክር ቤቱ ሊቀመንበር አህመት የነር የምርጫውን ውጤት በይፋ ያስታወቁ ሲሆን ኤርዶጋን 52.14% የመራጮችን ድምጽ በማግኘት የስልጣን ዘመናቸውን አራዝመዋል።

🇹🇷ኤርዶሃን 11 ዓመታትን በጠቅላይ ሚኒስትርነት 9 ዓመታትን በፕሬዝዳንትነት ቱርክን አገልግለዋል።ለተጨማሩ አምስት ዓመታት በምሽቱ ድል ስልጣናቸውን አራዝመዋል።

🇹🇷በቱርክ ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ፕሬዝዳንት ኤርዶሃን ማሸነፋቸውን ተከትሎ በኢስታንቡል ኡስኩዳር ወረዳ ባደረጉት ንግግር "ቱርክ በምርጫው ብቸኛ አሸናፊ መሆኗን" ተናግረዋል። ድሉ "የቱርክ ክፍለ ዘመን" በር ተከፍቷል ሲሉ አክለዋል።

🇹🇷ይፋዊው የምርጫው ውጤት እንደሚያሳየው ኤርዶጋን ከተፎካካሪያቸው ከማል ኪሊዳሮግሉ በ4 በመቶኛ አብላጫ ድምጽ አግኝተዋል።

🇷🇺የሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን እንኳን ደስ አላችሁ በማለት የቱርክ ህዝብ ለኤርዶጋን አስተዳደር  እና እራሱን የቻለ የውጭ ፖሊሲ አድናቆት እንዳለው የሚያሳይ የምርጫ ውጤት ነው ሲሉ ተናግረዋል።

🇻🇪የቬንዙዌላ ፕሬዝዳንት ኒኮላስ ማዱሮ "የወንድሜ እና የጓደኛዩ" ኤርዶጋን "ድል" ሲሉ የደስታ መልዕክት ልከዋል።

🇮🇷የኢራን ፕሬዝዳንት ኢብራሂም ራይሲ ኤርዶጋንን በድጋሚ በመመረጣቸው እንኳን ደስ አላችሁ በማለት "ለቱርክ ህዝብ ቀጣይነት ያለው ጥቅም " በማለት ድሉን ጠርተውታል።

🇸🇰🇵🇸🇦🇿የሰርቢያ ፣ፍልስጥኤምና አዘርባጃን መሪዎች የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።

🇹🇷የቱርክ ተቃዋሚ ብሄራዊ የአይዋይአይ ፓርቲ መሪ የሆነችው ሜራል አክሴነር ኤርዶጋን በፕሬዚዳንታዊ ምርጫው ድል በማግኘታቸው እንኳን ደስ አላችሁ ብላለች።በአንካራ ንግግር ያደረጉት አክሴነር በምርጫ ውጤቱ ኤርዶጋን ትልቅ ትምህርት ያገኙበት እንደሆነ ያሳያል ብላለች።


🇹🇷የቱርክ ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ ዕጩ ኪሊዳሮግሉ ለዴሞክራሲ የሚያደርጉትን ትግል እንደሚቀጥሉ በመግለፅ ደጋፊዎቻቸው ትግላቸውን እንዲቀጥሉ ጠይቀዋል። ኪሊዳሮግሉ የምርጫውን ሂደት በአመታት ውስጥ እጅግ ኢ-ፍትሃዊ ነበር ብለዋል።


🇶🇦🇭🇺🇫🇷የኳታር አሚር ታሚም ቢን ሃማድ በትዊተር ገፃቸው ላይ "ውድ ወንድሜ ረሲፕ ጣይብ ኤርዶሃ፣ ስላገኘህው ድል እንኳን ደስ ያለህ፣ በአዲሱ የስልጣን ዘመንህ ስኬታማ እንድትሆን እመኛለሁ" ሲሉ ጽፈዋል። የሃንጋሪው ጠቅላይ ሚኒስትር ቪክቶር ኦርባን “አጠያያቂ ያልሆነ” ድል ሲሉ አድንቀዋል።የፈረንሳዩ ፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮን የእንኳን ደስ አለህ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።

በስምኦን ደረጄ
#ዳጉ_ጆርናል




ነባር መንደሮችን በማፍረስ የሚከናወኑ የልማት ስራዎች የተጠኑ እና የከተሜነት መርህን የተከተሉ አይደለም ተባለ

መንግስት በኮንዶሚኒየም ግንባታ እና በሌሎች የልማት ፕሮጀክቶች በተለይም በአዲስአበባ እና በዙሪያዋ ነባር መንደሮችን በማፍረስ የሚከናወኑ ስራዎች የከተማ ልማት መርህን የተከተሉ አለመሆናቸውን የፍሊንት ስቶን ሪልስቴት ም/ል ስራ አስኪያጅ አቶ ብሩክ ሽመልስ ለብስራት ራዲዮ ተናግረዋል።

ፍሊንት ስቶን ፤ ከአመታት በፊት በተለይም በአዲስአበባ የሚገኙ ነባር መንደሮችን በዘመናዊና የከተማዉን ደረጃ በሚጠብቅ መልኩ አፍርሶ ነዋሪዉ ከቀዬዉ ሳይፈናቀልና ወፈ ሌላ ቦታ ሳይዘዋወር ግንባታ ለማድረግ እቅድ ይዞ የነበረ ቢሆንም በአዲስአበባ ከተማ መስተዳድር በኩል ትብብር ባለማግኘቱ ተግባራዊ ሳይደረግ መቆየቱን ገልጸዋል።

ከተማዋን ማስተዳድሩ ከስርዓት ስርዓት ቢለዋዋጥም አሁንም በአዲስአበባ የሚሰሩ ፕሮጀክቶች ነዋሪዉን ወደ ሌላ አካባቢ እንዲፈናቀል የሚያስገድዱ ሆነዉ ዘልቀዋል። በተለይም በመኖሪያ ቤት ግንባታ ላይ ይህ ችግር በስፋት ይስተዋላል። ይህንንም እቅድ ተግባራዊ ለማድረግ ከግንባታ ፈቃድ ጋር በተያያዘ በአንድ ካርታ ላይ ብቻ ግንባታ መፈቀዱ እና ተጨማሪ መመሪያዎች በማስፈለጋቸዉ ፣ የቀበሌ ቤቶች ባለቤትነት ፣ በግል የመሬት ይዞታ ላይ የቀበሌ ቤቶች መገኘታቸዉ ዉስብስብ እንዳደረገዉና እቅዱን ተግባራዊ ለማድረግ መቸገሩን አንስተዋል።

እንደ አቶ ብሩክ ገለጻ ፤ ከተማ ፈርሶ ነዋሪዉም አንዲበተን ሲደረግ የማህበረሰቡ ማንነትን የሚያጠፋ እና የከተማዉን መገለጫ የሚያሳጣ መሆኑን ጠቅሰዋል። ለዚህም ምክኒያቱ  የከተማ አመሰራረትና ግንባታ ላይ መሰረታዊ ግንዛቤ የጎደለዉ አካሄድ ነዉ ብለዋል።

ፍሊንት ስቶን ፤ በአዲስአበባ ተግባራዊ ለማድረግ ያልቻለዉን እቅድ ወደ በኦሮሚያ ፣ አማራ እና ትግራይ ክልሎች ከተማና ከተሜነትን ተግባራዊ ለማድረግ የራሱን እቅድ አሰናድቶ በተለይም በገጠሩ ክፍል የሚገኘዉን ሰፊ የገበሬ ማህበረሰብ በማዘመንና የግብርና ስራዉን ጎን ለጎን እንዲያስኬድ የሚያስችል መንገድ ቢቀይስም ብቻዉን ግን ተግባራዊ ሊያደርገዉ አልቻለም ሲሉ ጨምረዉ ለብስራት ራዲዮ ተናግረዋል።

በበረከት ሞገስ
#ዳጉ_ጆርናል


በሲ.ኤም.ሲ ሚካኤል ከአያት አ.ማ

የግንባታ ደረጃቸው ከ 80% በላይ የደረሱትን ከረጂም አከፋፋል በተጨማሪ በ500,000 ብር ጀምሮ በቀላሉ የቤት  ባለቤት የሚሆኑበትን እድል አመቻችተናል ዛሬ ነገ ሳይሉ ቤቶን መርጠው አሁኑኑ ይያዙ  ከአያት ጋር ያሰቡት ይሳካል


ብሩክ ሠጠኝ
የገበያና ሽያጭ ባለሙያ
አያት አ.ማ

⏱📞 ☎️ +251912898237
👉
@Bruk23

Telegram join
@Bruk_Sales_consultant


የናይጄሪያ ሰንደቅ ዓላማ ያረፈበት ንብረትነቱ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የሆነ አውሮፕላን ወደ አቡጃ በረራ ማድረጉ ተገለጸ


ባሳለፍነው አርብ ግንቦት 18/2015 የናይጄሪያ ሰንደቅ ዓላማ ያረፈበት እና ንብረትነቱ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ነው የተባለ አውሮፕላን፤ ከቦሌ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ በመነሳት ወደ ናይጄሪያ ዋና ከተማ አቡጃ በረራ ማድረጉ ተገልጿል፡፡

ዴይሊ ትረስት ባወጣው ልዩ ዘገባ፤ ለውጭ ገበያ ክፍት ሆኖ ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ጋር ለዓመታት ድርድር ሲያደርግ የቆየው የናይጄሪያ አየር መንገድ በይፋ ሥራ መጀመሩን አስመልክቶ የተጠቀመበት ቦይንግ 737-800 አውሮፕላን ባለቤትነቱ የኢትዮጵያ አየር መንገድ መሆኑን አረጋግጫለሁ ብሏል፡፡

በዚህም አርብ ምሽት አቡጃ በሚገኘው ናምዲ አዚኪዌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ጣቢያ ያረፈው አውሮፕላኑ፤ እስከባለፈው እሁድ ድረስ ለዋናው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ሲያገለግል እንደነበር ተጠቁሟል፡፡

የትላንቱ በረራ በኹለቱ አየር መንገዶች በኩል ከፈረንጆች 2016 ጀምሮ ሲካሄድ የነበረው ድርድር ማብቃቱን ማሳያ ነው የተባለ ሲሆን፤ በሚቀጥሉት አምስት ዓመታት 35 አውሮፕላኖች እንደሚኖሩትም ተመላክቷል፡፡

በሥነ ስርዓቱ ላይ የታደሙት የናይጄሪያ አቪዬሽን ሚኒስትር ሃዲ ሲሪካ፤ ከረዥም እና ፈታኝ ጉዞ በኋላ በናይጄሪያ አየር መንገድ እድገት መታየቱን ገልጸዋል፡፡

49 በመቶ በኢትዮጵያ አየር መንገድ የገበያ ድርሻ የተያዘው የናይጄሪያ አየር መንገድ፤ በቀጣዮቹ አምስት ዓመታት ውስጥ የአንድ ቢሊዮን ዶላር ገንዘብ ባለቤት እንደሚሆንም ነው የተጠቆመው፡፡

የኢትዮጵያ አየር መንገድ በናይጄሪያ አቬሽን ዘርፍ የሚያደርገው ተሳትፎ ቀጣይነት እንዲኖረው የናይጄሪያ መንግሥት የ15 ዓመት የግብር እፎይታ እንዲሰጠውና ሌሎች ድጋፎችንም እንዲያደርግለት መጠየቁ ይታወሳል፡፡

ከአፍሪካ ግዙፍ አየር መንገዶች ቀዳሚ መሆኑ የሚነገርለት የኢትዮጵያ አየር መንገድ፤ የናይጄሪያ አየር መንገድ ዋነኛ ባለድርሻ መሆኑን ተከትሎ የናይጄሪያ አየር መንገዶችን እና ሠራተኞችን ከሥራ ውጭ ያደርጋል በሚል ተቃውሞ ሲነሳበት እንደነበር የአዲስ ማለዳ ዘገባ ያሳያል፡፡

#ዳጉ_ጆርናል




በሙስና ወንጀል በተከሰሱ በ49 ግለሰቦች ላይ የፍርድ ውሳኔ ተላለፈ

በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን በሙስና ወንጀል ከተከሰሱ 53 ግለሰቦች መካከል በ49 ተከሳሾች ላይ የፍርድ ውሳኔ መተላለፉን የሰሜን ሸዋ ዞን አቃቢ ህግ አስታዉቋል ።ተከሳሾች ከሙስና ጋር በተያያዘ ስልጣንን  ያለ አግባብ በመጠቀም ወንጀል በመንግሥት ገቢ ታክስ እና በመሬት አስተዳደር በተፈፀመ ወንጀል ጥፋተኛ ተብለዋል ።

ውሳኔ የተላለፈባቸው 49 ግለሰቦች ከ16 ሚሊዮን ብር በላይ ለግል ጥቅማቸው ለማዋል ሲሞክሩ በቁጥጥር ስር የዋሉ ሲሆን በዚህም ጥፋታቸው ከሁለት ዓመት እስከ ሰባት አመት እስራት ተቀጥተዋል። በገንዘብ መቀጮ ረገድ ከ10 ሺ እስከ 40 ሺ ብር እንዲቀጡ መወሰኑን የሰሜን ሸዋ ዞን አቃቢ ህግ ጽ/ት ቤት ሀላፊ  ዳአ/ቶ ጎሹ ለገሰ ለብስራት ራዲዮ ተናግረዋል ።

ግለሰቦቹ 16 ሚሊዮን ብር ለግል ጥቅማቸው ለማዋል የተደራጀ የሙስና ተግባር ውስጥ ገብተው እንደነበር የተገለፀ ሲሆን በተቋቋመው የፀረ ሙስና ኮሚቴ መሰረት በተደረገ የኦዲት ምርምረ ውጤት 44 ሚሊዮን የመንግስት ገንዘብ ከብክነት ማዳን ተችሏል ። 

ከዚህም ውስጥ ከመንግሥት ካዝና ወጥቶ ያለ አግባብ እንዲከፈል የተወሰነ 30 ሚሊዮን ብር ሳይከፈል በቁጥጥር ስር የዋለ ሲሆን ከስንቄ ባንክ ያለ አግባብ በብድር የወጣ 15 ሚሊዮን ብር ተመላሽ እንዲሆን ተደርጓል ።

ከመሬት ጋር በተያያዘ ከ 50 ሺ በላይ ካሬ ሜትር ቦታ ያለ አግባብ ሊከፋፈል ሲል በተደረገ ምርመራ ተደርሶበት ለመንግሥት ገቢ ሆኗል ። በተጨማሪ 660 ካሬ ሜትር ቦታ ላይ የተሰራ መኖሪያ ቤት በቁጥጥር ስር መዋሉ አ/ቶ ጎሹ ጨምረው ለብስራት ራዲዮ ተናግረዋል ።

በአበረ ስሜነህ
#ዳጉ_ጆርናል


ጠቅላይ ምክር ቤቱ በመንግሥት ዉስጥ ሆነው ሕዝብንና መንግሥትን የሚያጋጩ አካላት ተገቢው እርምጃ እንዲወሰድባቸው ጥሪ አቀረበ!

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት መንግሥት ኢስላም ጠል የሆኑ እና በመንግሥት መዋቅር ዉስጥ በተለያዩ እርከኖች ያሉትን አካላት በመገምገም እና በማጥራት ሕዝብንና መንግሥትን ሆነ ብለው ለማጋጨትና አገሪቷን ወደ ለየለት ቀውስ ለመውሰድ እየሰሩ ያሉ አካላትን ፈትሾ ተገቢውን እርምጃ በመውሰድ መዋቅሩን እንዲያጠራ ጥሪ አቀረበ።

ጠቅላይ ምክር ቤቱ ትናንት ግንቦት 18/2015 በአዲስ አበባ አንዋር መስጂድ በአዲሱ ሸገር ከተማ አስተዳደር እየተከናወነ የሚገኘውን የመስጂዶች ፈረሳ እንዲቆም ለማሳሰብ ሰላማዊ ሰልፍ በወጡ የእስልምና ዕምነት ተከታዮች እና በመንግስት የጸጥታ ሀይሎች መካከል በተፈጠረ ግጭት የሰዎች ሕይወት መጥፋቱን ተከትሎ፤ በዛሬው ዕለት በጠራው አስቸኳይ ጠቅላላ የምክክር ጉባኤ ባለ አስራአንድ ነጥብ የአቋም መግለጫ አውጥቷል።

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ያወጣው አቋም መግለጫ ሙሉ ቃል እንደሚከተለው ቀርቧል፦

እኛ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ም/ቤት በግንቦት 19/2015 በጠራው አስቸኳይ ጠቅላላ የምክክር ጉባኤ ላይ የተሳተፍን የጠቅላላ ጉባኤ አባላት፥ የዑለማ ምክር ቤት እና የክልል የእስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ም/ቤት አባላት በወቅታዊ የህዝበ ሙስሊሙ ጉዳዮች ላይ ባደረግነው ምክክር የሚከተለውን የአቋም መግለጫ አውጥተናል።

1. በሸገር ከተማ እየተደረገ ካለው የመስጂድ ፈረሳ ሂደትን አስመልክቶ በትናንትናው ዕለት በአዲስ አበባ ከተማ በአንዋርና ኑር መስጊዶች ዙሪያ የመስጂድ ፈረሳውን በሚቃወሙ ሙስሊሞች ላይ በተፈጸመው ጥቃት ሕይወታቸውን ላጡ ንጹኃን ሙስሊሞች አላህ በሸሂድነት(ሰማዕትነት) እንዲቀበላቸው፥ ለቤተሰባቸውና ለወዳጅ ዘመዶቻቸው መጽናናትን አላህ እንዲሰጣቸው እንማጸነዋለን። በግጭቱ ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኖቻችን  በቶሎ መሻርን አላህ እንዲለግሳቸው እንማጸነዋለን።

2. በትናንትናው ዕለት በአዲስ አበባ በአንዋርና ኑር መስጊድ የተፈጠረው ክስተት እንዴት እንደተፈጠረና የደረሰውን ሞትና ጉዳት መንስኤዎች የሚያጣራ ከመንግሥትና የእስልምና ጉዳይ ም/ቤት በጋራ ያሉበት ገለልተኛ አጣሪ ቡድን በአስቸኳይ እንዲቋቋም እንጠይቃለን።

3. በኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት በሸገር ከተማ ኢስላምንና ሙስሊሞችን በናቀ መልኩ በመስጂዶች ላይ እየተደረገ ያለው የጅምላ ፈረሳ ሂደት በአስቸኳይ እንዲቆም፥ እንዲሁም ለፈረሱት መስጊዶች የክልሉ መንግስት ምትክ ቦታ በመስጠት በአስቸኳይ ተመልሰው እንዲገነቡ በማድረግ ሕዝበ ሙስሊሙን በይፋ ይቅርታ በመጠየቅ እንዲክስ እናሳስባለን።

4. በኦሮሚያ ክልልም ሆነ በሌሎች የአገራችን ክልሎች ለእምነት ቦታዎች ተገቢውን ክብርና ጥበቃ እንዲደረግ፥ እንዲሁም ለመስጂዶች ካርታ በመከልከልና ሆነ ብሎ ቢሮክራሲውን በማንዛዛት ሕዝቡን ላማረሩ ዘርፈ ብዙ ችግሮች መንግስት ተገቢውን ትኩረት በመስጠት በአፋጣኝ እንዲፈታቸው እናሳስባለን።

5. በሕገ መንግሥቱ እውቅና የተሰጣቸው የእምነት ነጻነትን በመጻረር በአገራችን አንዳንድ አከባቢዎች በተለይም በጉራጌ ዞን በጉንችሬ ሙስሊም ተማሪዎችን ለይቶ ከትምህርት የማባረር ሂደት በአስቸኳይ እልባት እንዲሰጠበት። መሰል ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታትም በኢስላም ጠልነት ምክንያት በሙስሊሞች ላይ የሚደርሱ ጥቃቶችን በዘላቂነት የሚያስቀርና ለሃይማኖታዊ መብቶቻችንን የሚጥሱ አካላትን የሚቀጣ ሕግን መንግስት እንዲያወጣ እንጠይቃለን።

6. ሕዝበ ሙስሊሙ ከመሪ ተቋሙ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ም/ቤት ጎን በመቆም ሃይማኖታዊ መብቶችን ለማስከበር የሚደረገውን ጥረት በሕጋዊ እና ሰላማዊ መንገድ ብቻ እንዲያደርግ ጥሪ እናደርጋለን።

7. የሃይማኖታችንን ክብር ብሎም የአላህ ቤት የሆነውን መስጂድ መድፈርና ማዋረድ እጅግ ዉስጥን የሚያደማ ብሎም ስሜታዊ የሚያደርግ መሆኑን የመንግስት የጸጥታ አካላት በመገንዘብ ወደ ሕብረተሰቡ ከመተኮስ እንዲቆጠቡ እናሳስባለን።

8.ሕዝበ ሙስሊሙ የመብት ጥያቄዎቹን ለማስከበር ከመሪ ተቋሙ መጅሊስ ጎን በመቆም በሚያደርገው ህጋዊ ትግል ለራሳቸው የፖለቲካ ፍላጎት ሕዝበ ሙስሊሙን መረማመጃና መጠቀሚያ ሊያደርጉ ከሚችሉ አካላት የማባባስና ግጭትን የማስፋፋት ቅስቀሳና ሴራ ራሱን እንዲጠብቅ ጥሪ እናደርጋለን።

9.የሕዝበ ሙስሊሙን የመብት ጥያቄዎች የምናስከብረው በአንድነትና በመደማመጥ በመቆም ሕዝበ ሙስሊሙ በየእርከኑ ካሉ የእስልምና ጉዳዮች ም/ቤቶች ጎን በመቆም አንድነቱን በማጠናከር ለመብቱ ትግል ስኬት በአንድነት እንዲቆም ጥሪ እናደርጋለን።

10. መንግሥት ኢስላም ጠል የሆኑ እና በመንግሥት መዋቅር ዉስጥ በተለያዩ እርከኖች ያሉትን አካላት በመገምገም እና በማጥራት ሕዝብንና መንግሥትን ሆነ ብለው ለማጋጨትና አገራችንን ወደ ለየለት ቀውስ ለመውሰድ እየሰሩ ያሉ አካላትን ፈትሾ ተገቢውን እርምጃ በመውሰድ መዋቅሩን እንዲያጠራ ጥሪ እናደርጋለን።

11. በአገራዊ የምክክር ሂደት ላይ ሕዝበ ሙስሊሙ በንቃትና በስፋት በመሳተፍ ለዘመናት ሲንከባለሉ የቆዩ የሕዝበ ሙስሊሙ ችግሮችን፥ ጥያቄዎችንና አጀንዳዎችን በማንሳት ኹሉንም ኢትዮጵያውያንን በፍትሃዊነትና በእኩልነት የምታስተናግድ አገር ለመግንባት በሚደረገው ጥረት የበኩላችንን ጥረት እንድናደርግ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን።

  ግንቦት 19/2015
አዲስ አበባ

#ዳጉ_ጆርናል


ክፍት የስራ ማስታወቂያ

Telegram join 👇👇
https://t.me/Bruk_Sales_consultant

በሀገራችን  የሪል እስቴትገቢያ እና ሽያጭ  መሰረታዊ  የፍላጎቶችን ለማድረስ እና የሚታዩ  ችግሮችንም  በቀላሉ ለመቅረፍ የሚስችል ከመሆኑም በላይ ለራስዎም መልካም የስራ እድል በመፍጠር  በቂ ልምድ  እውቀት እና ክህሎት ካላቸው  የሪል እስቴት ገቢያ እና ሽያጭ አማካሪዎች  ጋር ለመስራት የሚስችልዎትን  እድል አመቻችተናል ።

ስራዎት ሳይበደል ጊዜ ሳይባክን ከ25ሺ  እሰከ 100ሺ ብር ማግኘት የሚስችለዎትን የኮሚሽን ስራ  አዘጋጅተናል ። አሰፈላጊ የሆነ የሪል እስቴት ስልጠናወችንም እንሰጣለን ። ከዚህ በፌት የሪል እስቴት የስራ ልምድ ያላችሁም ከሆነ በደስታ እንቀበላለን ።
ይግዙ ይሽጡ ያማክሩ ያለዎትን ሪሶርስ በቀላሉ ይጠቀሙበት ።
መረጃ እውቀትም ገንዘብም  ነው ።
ጊዜ ወርቅ ነው ።

ይደውሉ

ብሩክ ሠጠኝ
የገበያና ሽያጭ ባለሙያ/አማካሪ

⏱📞 ☎️ +251912898237


Telegram join 👇👇
https://t.me/Bruk_Sales_consultant


ዘመን ባንክ አቶ ኤርሚያስ አመልጋን ጨምሮ ለባንኩ እና ለህንጻ ግንባታዉ ትልቅ አስተዋጽኦ ላበረከቱ ሰዎች እዉቅና ሰጠ

ዘመን ባንክ ከምስረታዉ ጀምሮ ለባንኩ የህንጻ ግንባታ ትልቅ አስተዋጽኦ ላበረከቱ ሰዎች እዉቅና ሰጥቷል።

በባንኩ ምስረታ ስማቸዉ የሚነሳዉ አቶ ኤርሚያስ አመልጋ በዘመን ባክን አርማ የተሰራ 20 ግራም ወርቅ ሽልማት እንደተበረከተላቸው ብስራት ራዲዮ ሰምቷል።

በተጨማሪም የባንኩ የመጀመሪያ ፕሬዚዳንት አቶ ተክሌ አለምነህ ፣ የባንኩ ሁለተኛ እና የመጀመሪያዋ ሴት ፕሬዚዳንት ወ/ሮ ብሪክታዊት ዳዊት ፣ ባንኩን ለ ስድስት አመታት በዋና ስራ አስፈጻሚነት የመሩት አቶ ጸጋዬ ተጠምቀ ፣ በህንጻ ግንባታዉ ወቅት ትልቅ አበርክቶ ነበራቸዉ የተባሉ ኢንጂነር ቴድሮስ ከበደ እና ዋና መሀንዲስ ኢንጂነር እዬቤድ ምርዬ የባንኩ አርማ ያረፈበት የ15 ግራም ወርቅ ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።

በተጨማሪም በህንጻዉ ግንባታ በአማካሪነትና በሌሎች ሚናዊች ሀላፊነታቸውን ለተወጡ ሰዎች የገንዘብና የዋንጫ ሽልማት ባንኩ አበርክቷል።

#ዳጉ_ጆርናል


የኢትዮጵያ አየር መንገድ የአፍሪካ የአመቱ አስተማማኝ የጭነት አገልግሎት ሰጪ ሽልማትን አሸነፈ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ በሚሰጠው የጭነት አገልግሎት የአፍሪካ የአመቱ አስተማማኝ የጭነት አገልግሎት ሰጪ ሽልማትን አሸነፈ።

አየር መንገዱ በቱርክ ኢስታንቡል በዘርፉ የተሰማሩ ዓለም አቀፍ ድርጅቶች፣ ተገልጋዮች እና መራጮች በሰጡት ድምጽ ነው አሸናፊ የሆነው።

በአጋሮች እና ተገልጋዮች በሚሰጠው የጭነት አገልግሎት ቀዳሚ ሆኖ በመመረጡ የተሰማውን ደስታ ገልጿል።

በቀጣይም በጭነት አገልግሎት ያለውን ቀዳሚ ሚና እና ለደንበኞቹ የሚሰጠውን ውጤታማ አገልግሎት  እንደሚያስቀጥልም አስታውቋል።

#ዳጉ_ጆርናል


ዘመን ባንክ መቄዶንያን ጨምሮ ለበርካታ የበጎ አደራጎት ድርጅቶች በህምጻ ምርቃት ስነስርዓቱ የገንዘብ ድጋፍ አደረገ

ዘመን ባንክ ያስገነባውን የዋና መስሪያቤት ህንጻ ምርቃት ስነስርዓት በማስመልከት ለተለያዩ የበጎ አድራጎት ድርጅቶች የገንዘብ ድጋፍ አድርጓል።

ባንኩ ለመቄዶንያ የ 3 ሚሊዮን ብር ፣ በቀድሞ የኢፌዴሪ ጠ/ሚ አቶ ሀይለማርያም ደሳለኝ እና ቀዳማዊት እመቤት ሮማን ስም ለተመሰረተዉ ሀይለማርያም እና ሮማን ፋዉንፌሽን የ 2 ሚሊዮን ብር፣ ለልብ ህሙማን ህጻናትል ማዕከል 2 ሚሊዮን ብር ፣ ቀይመስቀል ማህበር 2 ሚሊዮን ብር ፣ ጌርጌሴኖን የአእምሮ ህሙማን ማዕከል 2 ሚሊዮን ብር እንዲሁም ለሀይሌ ማናስ አካዳሚ የ2 ሚሊዮን ብር ድጋፍ አድርጓል።

በተጨማሪም ፕሮጀክት ሀረር ለተሰኘ የግብረ ሰናይ ተቋም 1 ሚሊዮን ብር ፣ የፓርኪንሰን ህሙማን ማዕከል 500 ሺህ ብር ፣ነኸሚያ ኦቲዝም ማዕከል 500 ሺህ ብር ፣ ጎጆ ህሙማን ማረፊያ 500 ሺህ ብር ፣ ፍሬገነት ኪዳን ለህጻናት ማዕከል 250 ሺህ ብር ፣ የወደቁትን አንሱ የነዳያን መርጃ ማህበር 125 ሺህ ብር እና ሰሊሆም የአምሮ ህሙማን መርጃ ማዕከል 125 ሺህ ብር ድጋፍ አድርጓል።

በነገዉ እለት ረፋድ ለአቅመ ደካሞች የማዕድ ማጋራት በዋና መስሪያቤቱ እንደሚኖር የባንኩ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ደረጄ መናገራቸውን ብስራት ራዲዮ ሰምቷል።

በበረከት ሞገስ
#ዳጉ_ጆርናል


ዘመን ባንክ በ 1.5 ቢሊዮን ብር ያስገነባዉ ባለ 36 ወለል ህንጻዉን አስመረቀ

ዘመን ባንክ በ 1.5 ቢሊዮን ብር ገደማ ወጪ ያደረገበትን ባለ 36 ወለል ህንጻ በዛሬዉ እለት የብሔራዊ ባንክ ገዢ አቶ ማሞ ምህረቱ በተገኙበት አስመርቋል።

ባንኩ ከ 15 አመታት በፊት በ 87.2 ሚሊዮን ብር የተከፈለ ካፒታል ተመስርቶ ዛሬ ላይ 1መቶ ገደማ ቅርንጫፎች ባለቤት መሆኑን የባንኩ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ደረጀ ዘነበ መናገራቸውን ብስራት ራዲዮ ሰምቷል።

ህንጻዉ ለሰራተኞቹ የህጻናት ማቆያ ፣ የስፖርት ማዘዉተሪያ ጂምናዚየም ፣ መዝናኛ ክበቦች እና የስራ ማስኬጃ ቢሮ ያለዉ ነዉ። 5 ወለሎቹ እና ከወለል በታች በድምሩ ከ 2 መቶ በላይ መኪናዎች ማቆም ይችላል በተባለለት ህንጻ በተጨማሪም ከወለል በታች አስተማማኝ የገንዘብ እና  የከበሩ ማድናት ማስቀመጫ እንዲሁም የሰነድ ክፍል እንደሚኖረዉ ተገልጿል። በተጨማሪም ለቀጣዮቹ አምስት አመታት ባንኩ የሚጠቀምበትን አስተማማኝ የተባለ የመረጃ ቋት እንዳለዉም ተነግሯል።

አምስት አመት የፈጀዉ ግንባታ በቻይና መንግስት ተቋራጭ ድርጅት ግንባታዉ መከናወኑ ተገልጿል።

አዲስ ባስመረቀዉ ህንጻ ባንኩ ከዚህ ቀደም ለኪራይ ህንጻ በየአመቱ 40 ሚሊዮን ብር ወጪ ያደርግ እንደነበርና ይህንን እንደሚያስቀርለትም አቶ ደረጀ ገልጸዋል።

በበረከት ሞገስ
#ዳጉ_ጆርናል


በደቡብ ኮሪያ በረራ ወቅት የአውሮፕላን በር የከፈተዉ ተሳፋሪ በቁጥጥር ስር ዋለ

በደቡብ ኮሪያ በማረፍ ሂደት ላይ የነበረዉን የኤዢያና አየር መንገድ አውሮፕላን የአደጋ ጊዜ በር የከፈተዉ ግለሰብ በፖሊስ በቁጥጥር ስር ውሏል።በአዉሮፕላኑ ዉስጥ የነበሩ 194ቱ መንገደኞች በሰላም የተረፉ ቢሆንም በዛሬዉ እለት አዉሮፕላኑ በዴጉ አየር ማረፊያ ዉስጥ ሲያርፍ በሩ ክፍት እንደነበር ተመላክቷል፡፡

አንዳንድ ተሳፋሪዎች ራሳቸውን የሳቱ ሲሆን ሌሎች ደግሞ የአተነፋፈስ ችግር ገጥሟቸዉ ወደ ሆስፒታል መወሰዳቸውን የሀገር ውስጥ መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል።ድርጊቱን የፈጸመዉ በ30ዎቹ ዕድሜ ክልለ ውስጥ የሚገኘው ግለሰብ ለማስቆም የበረራ አስተናጋጆች ቢሞክሩም እንዳልተሳካላቸዉ የዓይን እማኞች ለሃገር ውስጥ መገናኛ ብዙሃን ተናግረዋል።

የበረራ ቁጥሩ ኤ 321-200 ኤር ባስ ዛሬ ከጄጁ ደሴት ተነስቶ ከአንድ ሰአት በረራ በኃላ በማረፍ ላይ እያለ ድርጊቱ ተፈጽሟል፡፡ ግለሰቡን የድንገተኛ መዉጫ በሩን ሲከፍተዉ አውሮፕላኑ ከመሬት 250 ሜትር ርቀት ነበረዉ፡፡በማህበራዊ ሚዲያ ላይ በተሰራጨ የቪዲዮ ምስል እንዳመላከተዉ በአውሮፕላኑ በግራ ክፍል በኩል የተቀመጡ ተሳፋሪዎች ከንፋስ ጋር ሲታገሉ ያሳያል።

ሰውዬው በሩን ከፍቶ ከአውሮፕላኑ ለመዝለል ሞክሮ እንደነበርም የዓይን እማኞች አክለዋል፡፡አንድ የ44 ዓመት ተሳፋሪ ለደቡብ ኮርያ የዜና ወኪል ዮንሃፕ እንደተናገረው “ለበሩ ቅርብ የነበሩ ሰዎች አንድ በአንድ የሚዝሉ ይመስል ነበር እናም የበረራ አስተናጋጆች ዶክተሮችን ሲጠሩ የነበረዉ ትርምስ ከፍተኛ እንደነበር" ገልጿል።

ፖሊስ እስካሁን ተጠርጣሪው ድርጊቱን ለምን እንደፈጸመ ምንም አይነት ማብራሪያ አልሰጠኝም በተያዘበት ጊዜ ሰክሮ አልነበረም ሲል ተናግሯል፡፡አሁን ላይ ከእርሱ ጋር መደበኛ ውይይት ማድረግ አስቸጋሪ ነው የወንጀሉን መንስኤ መርምረን እንቀጣዋለን ሲል አክሏል።

በስምኦን ደረጄ
#ዳጉ_ጆርናል




በፊንጫኣ ስኳር ፋብሪካ ላይ በተፈጸመ ጥቃት 14 ሰዎች ሲገደሉ ፋብሪካዉ ስራ ለማቆም ተገዷል 

በኦሮሚያ ክልል ሆሮ ጉድሩ ወለጋ ዞን በሚገኘው ፊንጫኣ ስኳር ፋብሪካ ላይ ታጣቂዎች ባደረሱት ጥቃት፤ 11 የፋብሪካው ሰራተኞች እና ሶስት የአካባቢው ነዋሪዎች እንደተገደሉ ማረጋገጡን የኢትዮጵያ ስኳር ኢንዱስትሪ ግሩፕ ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” አስታወቀ። ፋብሪካው በተፈጸመበት በዚሁ ጥቃት እና ዘረፋ ምክንያት ስራ ማቋሙም ተገልጿል።

ከአዲስ አበባ በ 350 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የሚገኘው የፊንጫኣ ስኳር ፋብሪካ ላይ ጥቃቱ የተፈጸመው ባለፈው ሳምንት ቅዳሜ ግንቦት 12 ፤ 2015 መሆኑን የኢትዮጵያ ስኳር ኢንዱስትሪ ግሩፕ የህዝብ ግንኙነት እና ተሳትፎ ክፍል ኃላፊ አቶ ረታ ደመቀ ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናግረዋል። ፋብሪካው ባለፈው 2014 ዓ.ም እና በዚህ ዓመት ተመሳሳይ ጥቃቶችን ቢያስተናግድም፤ የአሁኑ ከዚህ ቀደም ከነበሩት “ከበድ ያለ” እንደሆነ  ተነግሯል።

የፊንጫኣ ስኳር ፋብሪካ እና በስሩ ያለው የሸንኮራ አገዳ እርሻ፤ በአጠቃላይ በ67 ሺህ ሄክታር ይዞታ ላይ ያረፈ ነው። የቀደሙት ጥቃቶች ይበልጥኑ ኢላማ የሚያደርጉት የፋብሪካው እርሻ ላይ እንደነበር የሚናገሩት አቶ ረታ፤ ታጣቂዎቹ “የአገዳ እና የእርሻ ማሽነሪዎችን የማቃጠል” ድርጊት ይፈጽሙ እንደነበር ያስታውሳሉ። የአሁኑ ከዚህ ቀደም ከነበሩት የሚለየው፤ ታጣቂዎቹ ወደ ፋብሪካ ጭምር በመግባት ጥቃቶቹን በመፈጸማቸው እንደሆነ ያስረዳሉ።

የኢትዮጵያ ስኳር ኢንዱስትሪ ግሩፕ ጥቃቱን እንዲመረምር ያቋቋመው ግብረ ኃይል፤ በጥቃቱ 11 የፋብሪካው ሰራተኞች እና ሶስት የአካባቢው ነዋሪዎች እንደተገደሉ ማረጋገጡን ኃላፊው አስታውቀዋል። ሰኞ ዕለት ወደ አካባቢው የተሰማራው ይኸው ግብረ ኃይል፤ “እንደ ልብ ተዘዋውሮ ለመስራት የሚያስችል ሁኔታ ባለመኖሩ” የደረሱ ሌሎች ጉዳቶችን እስካሁን ሙሉ ለሙሉ ለማረጋገጥ አለመቻሉንም ጠቅሰዋል።

#ዳጉ_ጆርናል




በዛሬዉ እለት በመርካቶ ከነበረዉ ተቃዉሞ ጋር በተያያዘ መንግስት ለህዝበ ሙስሊሙ ጥያቄ የሠጠው ኃይልን የቀላቀለ ምላሽ አሳዝኖኛል ሲሊ ኢዜማ አስታወቀ

የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) በአዲሱ የሸገር ከተማ አስተዳደር እየተካሄደ ካለው የመስጂድ ፈረሳ ጋር ተያይዞ በዛሬው ዕለት በአዲስ አበባ የተለያዩ መስጂዶች በህዝበ ሙስሊሙ የታየውን ተቃውሞ ተከትሎ መንግስት ለጥያቄው የሠጠው ኃይልን የቀላቀለ ምላሽ እንዳሳዘነው ይገልፃል፡፡

ይህን መሰል የህዝብ ጥያቄ መመለስ ያለበት የዜጎችን ደህንነት በጠበቀና ዘላቂ ሰላምን በሚያረጋግጥ መልኩ ብቻ መሆን ይኖርበታል፡፡ እንዲህ አይነት ጥያቄዎች ሊፈቱ የሚገባቸው በሰለጠነ መንገድ በእርጋታና በማስተዋል ሊሆን ይገባል ብለን እናምናለን፡፡ በመሆኑም መንግስት ወሳኝ ኃላፊነት እንዳለበት አካል ለጥያቄዎቹ ተገቢውን መልስ እና ማብራሪያ ሊሰጥ የሚገባው ችግሮች ከመሰከሰታቸው አስቀድሞ መሆን እንዳለበት አበክረን ለመግለፅ አንወዳለን፡፡

በዛሬው ዕለት በአዲስ አበባ የተለያዩ መስጂዶች ለቀረበው ጥያቄና የተፈጠረውን ችግር አስመልክቶ መንግስት ትክክለኛውን መረጃና ማብራሪያ በመስጠት ጉዳዩ ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ እልባት እንዲያገኝ በአፋጣኝ እንዲሰራ በአፅንኦት እንጠይቃለን ብሏል ፓርቲው፡፡

#ዳጉ_ጆርናል

20 last posts shown.