TGStat
TGStat
Type to search
Advanced channel search
  • flag English
    Site language
    flag Russian flag English flag Uzbek
  • Sign In
  • Catalog
    Channels and groups catalog Search for channels
    Add a channel/group
  • Ratings
    Rating of channels Rating of groups Posts rating
    Ratings of brands and people
  • Analytics
  • Search by posts
  • Telegram monitoring
ዳጉ-ጆርናል/Dagu-Journal

24 Jan, 12:28

Open in Telegram Share Report

በትናንትናው እለት ምሽት 4፡48 ላይ በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ህንፃ ላይ የደረሰውን አደጋ ተከትሎ የፖሊስ ምርመራ እንደሚጀመር የከንቲባ ጽ/ቤት አስታወቀ፡፡

ጽ/ቤቱ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የአገልግሎት አሰጣጡን ለማዘመንና ሌብነትን ለመከላከል የዲጂታይዜሽን ስርዓትን ለመተግበር በርካታ ስራዎችን እያከናወነ እንደሚገኝ አስታውሷል::

በተለይም በለሚ ኩራ ክ/ከተማ የነበረውን ብልሹ አሰራር ሌብነትን ለማስተካከልና መልካም አስተዳደርን ለማስፈን ይረዳ ዘንድ የዘመናዊ የቢሮ ግንባታና የተቋማዊ ሪፎርምና የዲጂታል ቴክኖሎጂ በመተግባር በከንቲባዋ አስተባባሪነት የኢትዮ ቴሌኮም ፤ የአርቴፊሻል ኢንተልጀንስ ፤የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት ተቋማት የተሳተፉበት የዲጂታል አገልግት መስጠት የሚያስችል ስራ የፊታችን ቅዳሜ ለምረቃ የሚያበቃ ስራ በትጋት ተሰርቶ እንደነበር ጠቁሟል፡፡

ነገር ግን በትናንትናው እለት ምሽት 4፡48 ላይ የተዘጋጀው ከፍተኛ ቴክኖሎጂና ግብዓት የፈሰሰበት የክ/ከተማው አስተዳደር ህንፃ የእሳት አደጋ ደርሶበት መሰረተ ልማቱ ወድሟል ብሏል፡፡

የአደጋው ምክንያት እና መንስኤ በፖሊስ ምርመራ እየተካሄደበት ሲሆን ምርመራው እንዳለቀ ለህዝብ ይፋ የሚደረግ ይሆናል ሲልም በማህበራዊ ትስስር ገፁ አስታውቋል፡፡የአካባቢው ማህበረሰብም መንግስት የጀመረውን ጥረት ለመደገፍ ከዚህ አደጋ ጋር ተያይዞ ማንኛውንም መረጃዎች በመስጠት የተለመደ ትብብሩን እንዲያደርግ ጥሪ አቅርቧል፡፡

#ዳጉ_ጆርናል

4.1k 0 8 18
Catalog
Channels and groups catalog Channels compilations Search for channels Add a channel/group
Ratings
Rating of Telegram channels Rating of Telegram groups Posts rating Ratings of brands and people
API
API statistics Search API of posts API Callback
Our channels
@TGStat @TGStat_Chat @telepulse @TGStatAPI
Read
Blog Telegram Research 2019 Telegram Research 2021
Contacts
Support Email Jobs
Miscellaneous
Terms and conditions Privacy policy Public offer
Our bots
@TGStat_Bot @SearcheeBot @TGAlertsBot @tg_analytics_bot @TGStatChatBot