ዝክረ ቅዱሳን ማኅበረ ቅዱስ ዳዊት - ዘብሔረ ጎንደር (ዲ/ዮርዳኖስ አበበ)


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic
Category: not specified


በዚህ ቻናል ዲ/ዮርዳኖስ የሚያስተምራቸው ወቅታዊ እና የነገረ ቅዱሳን (ዝክረ ቅዱሳን ትምህርቶችን ከእርሱ በመቀበል እናስተላልፋለን):: "ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን"::አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ /መጽሐፈ ምሥጢር/

Related channels  |  Similar channels

Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Category
not specified
Statistics
Posts filter




ዝክረቅዱሳን (ማኅበረ ቅዱስ ዳዊት)

" ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን"::/የቅዱሳንን ዜና(ታሪክ) እንድመሰክር ፍቅር ያስገድደኛል::
       አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ /መጽሐፈ ምሥጢር/

🛑በዩቲብለመከታተል👉https://www.youtube.com/@ZikereKedusan

🛑በቴሌግራም👉
https://t.me/zikirekdusn






✞✞✞ Annual feasts celebrated on the 1st of Megabit
1. St. Methuselah (The day he departed at the age of 969)
2. St. Narcissus of Jerusalem
3. St. Alexander/Alexandrus
4. St. Mercurius/Anba Marcura the Bishop
5. Abba Michael of Atrib and Abba John of Parallos (They prepared the Faith of the Fathers, the Lectionary and the Synaxarium.)

✞✞✞ Monthly Feasts
1. Nativity of the Virgin Mary, our Lady
2. Sts. Joachim and Anna
3. St. Raguel the Archangel
4. St. Bartholomew the Apostle
5. St. (Mar) Melki of Kuelzem (Full of Virtues)

✞✞✞ “And that, knowing the time, that now it is high time to awake out of sleep: for now is our salvation nearer than when we believed. The night is far spent, the day is at hand: let us therefore cast off the works of darkness, and let us put on the armour of light.”✞✞✞
Rom. 13:11-12

✞✞✞ Salutations to God ✞✞✞

(Translated by Mhr. Esuendale Shemeles with the permission of Dn. Yordanos Abebe)


Memhir Esuendale:
#Feasts of #Megabit_1

✞✞✞On this day we start the Month of Megabit, the beginning of the second half of the year, and commemorate our Father Methuselah and Saint Narcissus ✞✞✞

✞✞✞In the name of the Father, the Son and the Holy Spirit, one God. Amen!✞✞✞

✞✞✞The Month of Megabit✞✞✞
=>The Month of Megabit has days and nights that are 12hrs each. From today onwards, for the coming 6 months (186 days) let us prepare ourselves to follow the path of God, which is good, by keeping ourselves from useless discourse and by distancing ourselves from wickedness.

✞✞✞ Our Father Methuselah✞✞✞
=>Also on this day, is commemorated Methuselah our father who was the 8th descendant from Adam. St. Methuselah was the son of the Righteous Enoch and the father of the benevolent Lamech. And in Church History he was the father that lived the longest on earth (969 years). St. Methuselah is counted as one of the Ten Holy Fathers.

✞And the Ten Holy Fathers are;
-Our father St. Adam
- Seth
- Enos
- Cainan
- Mahalaleel
- Jared
- Enoch
- Methuselah
-Lamech and
-Noah.

✞✞✞ Saint Narcissus of Jerusalem✞✞✞
=>Also on this day, departed St. Narcissus the Bishop of Jerusalem. This father was appointed during the reign of Caesar Alexander who loved Christians and he kept his flock as the Apostles had, in a good manner.

✞A bit later, Caesar Alexander died and Caesar Maximianus became Emperor. He tortured Christians and killed most of them.

✞At the time, there were some that fled from their country. And this father also took to flight and entered into the desert. The people sought for him but were not successful.

✞Then, they appointed over him a Bishop named Dius and he departed within a few days. Again, they appointed another Bishop named Ghordinus/Gordius (some accounts mention of a Germanion before him).

✞And when the time of flight was over, St. Narcissus returned to Jerusalem from seclusion and found that they had appointed another bishop called Ghordinus/Gordius as mentioned earlier.

✞As he reached Jerusalem, the people were jubilant and Bishop Ghordinus/Gordius besought him to seat on the See once more. And after much plea, he sat on the See and lived with Ghordinus/Gordius for a year. Then, Ghordinus/ Gordius departed.

✞But Abba Narcissus lived until he was of very old age. And he implored his people to appoint another Bishop. However, they said no.

✞And in those days, there was a Bishop of Cappadocia named Alexander that had went to Jerusalem for prayer. And when he completed his want, and the days of the feast being celebrated were done, he wished to return to his country [as he had planned earlier].

✞Nonetheless, a voice was heard on the day of the Resurrection of the Holy Savior that said, “Go to the entrance of the City of Jerusalem to ‘such and such’ gate, there, seize the first person that enters and appoint him as a coadjutor-bishop so that he would aid Narcissus.”

✞Then, they went out and reached the gate of the city where they found Alexander. And without his will, made him a coadjutor-bishop to assist Narcissus. And he lived with the Saint until he (Narcissus) departed.

✞St. Narcissus lived, in total, for 117 years. He lived 81 years before he was appointed a Bishop and 36 years on the See. He passed away in peace after serving God.

✞✞✞Saint Alexander the Martyr✞✞✞
=>Also on this day, is commemorated St. Alexander the martyr. The Holy Marty was Roman and because he did not follow the orders of the apostate Emperor Maximianus and did not sacrifice to his idols, he sentenced him to much affliction.

✞He hung the Saint after fastening to his hands and legs heavy and great stones. He also ordered that he be whipped and that his sides to be cut and fire be lit upon his face.

✞And when he noticed that the Saint was not terrified, he ordered his beheading.

✞And so the Saint received the crown of martyrdom.

✞✞✞May the God of the Saints grant us the years of Methuselah for repentance!




✝✞✝ እንኩዋን ከተባረከ ወር መጋቢትና ከሁለተኛው መንፈቀ ዘመን የመጀመሪያ ዕለት በሰላም አደረሳችሁ ✝✞✝

=>ወርኀ መጋቢት መዐልቱና ሌሊቱ እኩል (12:00) ናቸው:: ከዛሬዋ ዕለት ጀምሮ ለሚቀጥሉት 6 ወራት (186 ቀናት) ከማይጠቅም ወሬ ተቆጥበን: ከክፋትም ርቀን መልካሙን የእግዚአብሔር ጐዳና ለመከተል ራሳችንን ልናዘጋጅ ይገባል::

=>በዚህ ዕለትም ከአዳም 8ኛ ትውልድ የሆነው አባታችን ማቱሳላ በዓሉ ይከበራል:: ቅዱስ ማቱሳላ የጻድቅ ሰው ኄኖክ ልጅ: የደጉ ላሜሕ አባት ሲሆን በቤተ ክርስቲያን ታሪክ ረዥም ዕድሜ (969 ዓመት) የቆየ ባለ ረዥም ዕድሜ አባት ነው:: ከአሥሩ ቅዱሳን አባቶች አንዱ ነው::

+10 ቅዱሳን አባቶች ማለት:-
*ቅዱስ አዳም አባታችን
*ሴት
*ሔኖስ
*ቃይናን
*መላልኤል
*ያሬድ
*ኄኖክ
*ማቱሳላ
*ላሜሕ
*ኖኅ ናቸው::

† ቅዱስ በርኪሶስ †

«« በዚች ቀን የኢየሩሳሌም አገር ኤጲስቆጶስ ቅዱስ በርኪሶስ አረፈ።ይህም አባት ክርስቲያኖችን በሚወዳቸው በቄሳር እለእስክንድሮስ ዘመነ መንግስት ተሹሞ ሳለ ሀዋርያት ሲጠብቋቸው እንደነበር በበጎ አጠባበቅ ህዝቡን ጠበቃቸው ።

«ከጥቂት ጊዜ በኃላ እለእስክንድሮስ ሞተ ከእርሱ በኃላ ቄሳር መክስሚያኖስ ነገሰ። ክርስቲያኖችውም በፅኑእ መከራ አሰቃያቸው ከእርሳቸውም ብዙዎችን ገደላቸው።

ሀገሮቻቸውን ትተው የተሰደዱም አሉ። ይህም አባት ሽሽቶ ወደ ገዳም ገባ ህዝቡም ፈልገው አጡት።

ከዚህም በኃላ ስሙ ዲዮስ የተባለ ሌላ ኤጲስቆጶስ በላያቸው ሾሙ። እርሱም በጥቂት ቀን አረፈ። ከዚህ በኃላ ስሙ አግርንዲኖስ የሚባል ሌላ ኤጲስቆጶስ ሾሙ።

የስደቱም ወራት በአለፈ ጊዜ ይህ አባት በርኪሶስ ወደ ኢየሩሳሌም ከተማ ተመለሰ ።አግርንዲኖስ የሚባል ሌላ ኤጲስቆጶስ ሹመው አገኛቸው።

ወደርሳቸውም በደረሰ ጊዜ ህዝብ በመምጣቱ ደስ አላቸው አግርንዲኖስም ተመልሶ በመንበረ ጵጵስናው ላይ እንዲ ቀመጥ ለመነው በታላቅ ድካምም በወንበሩ ላይ አስቀመጡት። ከአግርንዲኖስም ጋራ አንዲት አመት ኖረ አግርንዲኖስም አረፈ።

አባ በርኪሶስም እጅግ እስኪያረጅና እስኪያረጅና እስኪደክም ድረስ ኖረ ወገኖቹንም ሌላ ኤጲስ ቆጶስ በላያቸው እንዲሾሙ ለመናቸው እነርሱም አይሆንም አሉ።

በዚያም ወራት የቀጰዶቅያ ኤጲስቆጶስ ስሙ እለእስክንድሮስ የሚባል አንድ ሰው ነበር። እርሱም በውስጥዋ ሊፀልይና ወዳገሩ ሊመለስ ወደ ኢየሩሳሌም መጣ።ስራውንም በጨረሰ ጊዜ የበአሉም ቀኖች በተፈፀሙ ጊዜ ወዳገሩ ሊመለስ ወደደ።

በመድኃኒታችን ትንሳኤ በአል በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ወደ ኢየሩሳሌም ከተማ መግቢያ ወደ እገሌ ደጃፍ ውጡ ወደ ደጃፉ መጀመሪያ የሚገባውን ያዙት በጵጵስና ስራም ይረዳው ዘንድ ከበርኪሶስ ጋር አድርጉት የሚል ቃል እነሆ ተሰማ።

ወጥተውም ወደ ደጃፉ በደረሱ ጊዜ እለእስክንድሮስን አገኙት ይረዳውም ዘንድ ያለ ፈቃዱ ከአባት በርኪሶስ ጋራ አደረጉት። እስከሚአርፍበትም ጊዜ አብሮት ኖረ።

መላ የህይውቱ ዘመን አንድ መቶ አስራ ሰባት አመት ሆነ ኤጲስቆጶስነት ሳይሾም ሰማንያ አንድ አመት ኖረ በሹመቱም ላይ ሰላሳ ስድስት አምታትን ኖረ። እግዚአብሄርንም አገልግሎ በሰላም አረፈ።

† ቅዱስ እለእስክንድሮስ †

በዚችም እለት የሰማእቱ የቅዱስ እለእስክንድሮስ መታሰቢያው ነው። ይህም ቅዱስ ሰማእት የሮም ሀገር ሰው ነው ለእርሱ ባለመታዘዙና ለረከሱ ጣኦቶቹ ባለመሰዋቱ ከሀዲው መክስሚያኖስ ፁኑእ ስቃይን አሰቃየው።

እጅግ ከባድና ታላቅ የሆነ ደንጊያ በእጆቹና በእግሮቹ ላይ አስሮ ሰቀለው። ብዙ ግርፋትንም ገረፈው ጎኖቹንም ቀደደ በፊቱም ላይ የእሳት መብራት ጨመሩ።

ስቃዩንም ባልፈራ ጊዜ ራሱን በሰይፍ ይቆርጡ ዘንድ አዘዘ።
በመንግስተ ሰማያትም የሰማእታትን አክሊል ተቀዳጀ።

=>ዕድሜ ማቱሳላን ለንስሃ አምላከ ቅዱሳን ይስጠን!

=>መጋቢት 1 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት=
1.ቅዱስ ማቱሣላ (በ969 ዓመቱ ያረፈበት)
2.ቅዱስ በርኪሶስ ዘኢየሩሳሌም
3.ቅዱስ እለእስክንድሮስ
4.ቅዱስ መርቆሬዎስ
5.አባ ሚካኤል ዘሃገረ አትሪብና አባ ዮሐንስ ዘሃገረ ቡርልስ
(ሃይማኖተ አበውን: ግፃዌንና ስንክሳርን ያዘጋጁ ናቸው)

=>ወርኀዊ በዓላት
1.ልደታ ለማርያም ድንግል እግዝእትነ
2.ቅዱሳን ኢያቄም ወሐና
3.ቅዱስ ራጉኤል ሊቀ መላዕክት
4.ቅዱስ በርተሎሜዎስ ሐዋርያ
5.ቅዱስ ሚልኪ ትሩፈ ምግባር

=>+"+ ከእንቅልፍ የምትነሱበት ሰዓት አሁን እንደ ደረሰ ዘመኑን እወቁ:: ካመንንበት ጊዜ ይልቅ መዳናችን ዛሬ ወደ እኛ ቀርቧልና:: ሌሊቱ አልፏል: ቀኑም ቀርቧል:: እንግዲህ የጨለማውን ሥራ አውጥተን የብርሃንን ጋሻ ጦር እንልበስ:: +"+ (ሮሜ. 13:11)

>


✝እንኳን አደረሰነ!

☞ወርኀ የካቲት ቡሩክ፥ አመ ፴

✝ጾም ዐቢይ ዘመድኅን ክርስቶስ (አምላክነ)

❖ተፈጸመ ወርኀ የካቲት ቡሩክ (በሰላመ እግዚአብሔር)

✞ወበዓለ ቅዱሳን አበው፦

✿ተረክቦተ ርዕሱ ለዮሐንስ መጥምቅ (ጸያሔ ፍኖት ወነቢየ ልዑል)
✿ሚናስ ክቡር (ሊቀ ጳጳሳት)
❀ቄርሎስ መንፈሳዊ
❀ወአንያኖስ ዘሐምዳ

❖ወስብሐት ለእግዚአብሔር፤
ኪያነኒ ይምሐረነ በጸሎቶሙ።
ወበረከቶሙ ይብጽሐነ፤ ለዓለመ ዓለም አሜን፡፡

https://t.me/zikirekdusn


ዝክረቅዱሳን (ማኅበረ ቅዱስ ዳዊት)

" ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን"::/የቅዱሳንን ዜና(ታሪክ) እንድመሰክር ፍቅር ያስገድደኛል::
       አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ /መጽሐፈ ምሥጢር/

🛑በዩቲብለመከታተል👉https://www.youtube.com/@ZikereKedusan

🛑በቴሌግራም👉
https://t.me/zikirekdusn


"" ጦሬም አያድነኝም! "" (መዝ. ፵፫:፮)

"ዝክረ ቅዱስ ዳዊት - ዘወርኀ የካቲት"

(የካቲት 23 - 2017)

https://t.me/zikirekdusn


✝ ቅዱስነታቸው አቡነ ቄርሎስ ፮ኛ እና ግርማዊ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ✝

☞116ኛው የእስክንድርያ ፓትርያርክ፡፡
☞13ኛው ሐዋርያ (በግብጻውያን አበው አጠራር)፡፡
☞የቅዱስ ሚናስ ወዳጅና፡፡
☞ድንቅ አድራጊው አባት ያረፉት የካቲት 30, 1971 (1963) ነበር፡፡

(እንዳጋጣሚ ዛሬ አንድ ሰው የላከልኝን መጽሐፍ ስመለከት ስለርሳቸው ነው፡፡ በNabil Adly በዐረቢኛ ተጽፎ፤ በSamuel Bishara ወደ እንግሊዝኛ የተተረጎመ ነው፡፡ The Gate of Heaven ይላል፡፡ ከጀርባው ላይ ደግሞ የብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ሺኖዳ ፫ኛ አስተያየት አለበት)

"" በረከታቸው ይደርብን፡፡ ""

ዝክረቅዱሳን ማኅበረ ቅዱስ ዳዊት

"ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን"::/የቅዱሳንን ዜና(ታሪክ) እንድመሰክር ፍቅር ያስገድደኛል::
       አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ /መጽሐፈ ምሥጢር
በዩቲብለመከታተል👉https://www.youtube.com/@ZikereKedusan
በቴሌግራም👉
https://t.me/zikirekdusn


>

=>ቸሩ አምላካችን እግዚአብሔር ባለፉት 6 ወራት (180 ቀናት) ምንም እንኩዋ ኃጢአታችን ቢበዛ : ሰውነታችንም ቢከፋ ያጠፋን ዘንድ አልወደደም::

=>እስኪ ለዛሬ እንዲህ ብለን ራሳችን እንጠይቅ?

=>ባለፉት 6 ወራት (180 ቀናት) ምን በጐ ሥራ ሠራን?

=>ምንስ መልካም ፍሬ አፈራን?

=>ስንት ጊዜስ ንስሃ ገባን?

=>አሁንስ ለቀጣዮቹ 6 ወራት ምን አሰብን?

=>ቸሩ አምላካችን ተረፈ ዘመኑን የፍቅር : የበረከትና የንስሃ ያድርግልን::

=>+"+ ከእንግዲህ ወዲህ በሥጋ ልትኖሩ በቀረላችሁ ዘመን እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ እንጂ እንደ ሰው ምኞት እንዳትኖሩ . . . የአህዛብን ፈቃድ ያደረጋችሁበት . . . ያለፈው ዘመን ይበቃልና . . . ዳሩ ግን የነገር ሁሉ መጨረሻ ቀርቧል:: እንግዲህ እንደ ባለ አእምሮ አስቡ . . . +"+ (1ዼጥ. 4:2-7)



ዝክረቅዱሳን ማኅበረ ቅዱስ ዳዊት

"ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን"::/የቅዱሳንን ዜና(ታሪክ) እንድመሰክር ፍቅር ያስገድደኛል::
       አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ /መጽሐፈ ምሥጢር
በዩቲብለመከታተል👉https://www.youtube.com/@ZikereKedusan
በቴሌግራም👉
https://t.me/zikirekdusn


"መንግሥተ ሰማያት ቀርባለችና ንስሐ ግቡ::
(ማቴ ፫:፫
ሰላም ለሙሴ ዘተሰብሐ ገጹ፤
ወተለዓለ ድምጹ፤
ወዘሠነየ ምርዋጹ!


ብፁዕ አባ አቡነ ተክለሃይማኖት ዘኤለ ገዳማተ እምኀበ እግዚኡ ይነሣእ እሴተ ቦአ ሀገረ ደብረ ሊባኖስ በፍሥሐ ወበሰላም።

ማኅደረ ሰላምነ ቅድስት ደብተራ እሞሙ ለሰማዕት ወእኅቶሙ ለመላእክት ንዑ ንስግድ ኵልነ ኀበ ማርያም እምነ።

ልብኪ የዋህ ዘኢየአምር ተበቊሎ ለኃጥእ እምተኃጒሎ፡፡ ተሣሀልኒ ድንግል ዘልማድኪ ተሣሕሎ ምንተ እነግረኪ ዉስተ ልብየ ዘሀሎ፡፡ እስመ አንቲ ተአምሪ ኀዘንየ ኩሎ፡፡"

ብጹእ አንተ ወሠናይ ለከ ብእሴ እግዚአብሔር መርቆሬዎስ ሰማዕት ሰላመ ጸሊ ለርኁቃን ወዳኅና ለቅሩባን ሰአል ወጸሊ በእንቲአነ::

ሰላም ለክሙ እንጦንስ ወመቃርስ፤
አቢብ ሲኖዳ ገብረ መንፈስ ቅዱስ፤
ለባርኮትነ ንዑ ውስተ ጽርሐ ዛቲ መቅደስ፤
ተክለ ሃይማኖት አኖሬዎስ ኤዎስጣቴዎስ፤
ሳሙኤል ተክለ አልፋ በብኑዳ ኪሮስ፡፡

✝ 5 ነገሮችን በደንብ ያዙ።
    1, 🛑አላማ

    2 ,🛑እምነት

   3,🛑ጥረት

   4 🛑ጥንቃቄ
     5🛑ጽናት
=>እነዚህን ያዟቸው ተጠቀሙባቸዉ ኑሯቸው።
@9ኙ የቅድስና መንገዶች

፩👉ሃይማኖት
፪👉ጾም
፫👉ጸሎት
፬👉ስግደት
፭👉ምጽዋት
፮👉ፍቅር
፯👉ትህትና
፰👉ትዕግስት
፱👉የዋህነት

ንስሐ የተጣመመውን ያቀናል።በኃጥያት የቆሸሸውን ያነጻል፤ንስሐ ለሚገቡ ሁሉ የመላዕክት ንጹሕ ልብስ ይሰጣችኃል

ዝክረቅዱሳን ማኅበረ ቅዱስ ዳዊት

"ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን"::/የቅዱሳንን ዜና(ታሪክ) እንድመሰክር ፍቅር ያስገድደኛል::
       አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ /መጽሐፈ ምሥጢር
በዩቲብለመከታተል👉https://www.youtube.com/@ZikereKedusan
በቴሌግራም👉
https://t.me/zikirekdusn




This was because he was a hermit whose stamina was upright, whose beard came down like woven silk, whose hair was as dark as a raven, and who had an appearance that was complete and had an impression that triggered fear.✞He then immediately preached to the people to repent and baptized many unto repentance. And after six months in this ministry, our Lord came to him. St. John was alarmed when the Creator, Who holds heaven and earth with everything in them in His hands, came saying, “Baptize Me.” He [St. John] did not know where to go.

✞He said, “No my Lord! You baptize me.” However, the Lord responded with, “I have permitted it [for you St. John to baptize Me].” So, he baptized Him. And for this, he will always be called, “Metmeqe Melekot” (The Baptist). Finally, St. John rebuked Herod (Antipas). And the king led by a grudge imprisoned him for 7 days. 

✞And when Herod celebrated his birthday, the daughter of Herodias trapped him with music and persuaded him to make a vow. And he gave her the head of the great prophet in a charger, after decapitating him. The scholars say, “it was better for him if he had swallowed up [have not honored] his vow.” Then, while the decapitated head of St. John flew away, his disciples buried his body (Matt. 3:.1/ Mark 6:14/ Luke 3:1/ John 1:6).

✞The head of John the Baptist flew with wings of grace after the cursed Herod beheaded him and it bowed down before the Lord at Mt. Olive, where he was. The Holy Apostles astounded by what they saw, gave salutations to the Saint’s head.

✞After this, our Lord Jesus Christ, gave authority to St. John’s head to preach and sent it forth. Thence, it spent 15 years preaching all over the world and on this day it rested in Arabia.

+++ Names of St. John the Baptist +++
1. Prophet
2. Apostle
3. Martyr
4. Righteous
5. Priest
6. Hermit/Ascetic
7. Baptist [Metmeqe Melekot]
8. Forerunner
9. Virgin
10. Bridge (that joins the Old and the New)
11. Herald (The voice that crieth)
12. Teacher and Rebuker
13. Greater from All

✞✞✞May our Lord, the Holy Savior, in remembrance of St. John the Baptist forgive us. And may He indwell in us his grace, blessing and glory.

✞✞✞ Annual feasts celebrated on the 30th of Yekatit
1. St. John the Baptist (After the Great Prophet and Priest St. John the Baptist was brutally beheaded with a sword by the order of Herod, his head travelled and preached for 15 years and rested. And on this day is commemorated the day it was found in a clay vessel. And the feast is called “Terekbote Re’su” – “The Finding/Appearance of His Head.”)
2. Abba Minas the Archbishop

✞✞✞ Monthly Feasts
1. St. Mark the Apostle
2. Abba Shalusi the Honorable
3. St. Gregory the Theologian
4. St. Sophia Martyr

✞✞✞ “. . . Jesus began to say unto the multitudes concerning John . . . But what went ye out for to see? A prophet? Yea, I say unto you, and more than a prophet. . . Verily I say unto you, Among them that are born of women there hath not risen a greater than John the Baptist . . . For all the prophets and the law prophesied until John. And if ye will receive it, this is Elias, which was for to come. He that hath ears to hear, let him hear.”✞✞✞
Matt. 11:7-15

✞✞✞ Salutations to God ✞✞✞

(Translated by Mhr. Esuendale Shemeles with the permission of Dn. Yordanos Abebe)


Memhir Esuendale:
#Feasts of #Yekatit_30

✞✞✞On this day we commemorate the annual feast of the Great Prophet and Martyr Saint John the Baptist✞✞✞

✞✞✞In the name of the Father, the Son and the Holy Spirit, one God. Amen!✞✞✞

✞✞✞Saint John the Baptist✞✞✞

=>It is difficult to say that there is someone whose honor was mentioned as much as the family of Zacharias in the Gospel, except our Lady. St. Luke started his Gospel with this family and the Holy Spirit inspired him to write the following. “And they were both righteous before God, walking in all the commandments and ordinances of the Lord blameless.”(Luke 1:6)

✞ Let us leave ‘before mankind’, but how transcendent is it to live blameless before God? And to this, awe is appropriate!

✞These holy husband and wife, because they were barren, most of their days/ages were spent without bearing a child. And according to the Tradition of the Church, the age of Elisabeth was 90 and Zacharias had reached 100.

✞However, the Lord who saw their patience, sent the angel of annunciation, St. Gabriel, to give them [annunciate the birth of] a great prophet, who was greater than men and about whom a prophecy was foretold (Isa. 40:3/ Mal. 3:1).

✞St. Zacharias, because he was a human and argued from joy, was made dumb. But Saint Elisabeth conceived the great man on Meskerem 26 (October 6) and concealed herself for 6 months. And on the sixth month, when the Lord of all creation was conceived (assumed flesh [human nature]), the Queen of Heaven, our Lady the Virgin Saint Mary, came to Elisabeth through the hill country. The two Saints were daughters of sisters (cousins).

✞And when the Theotokos (Mother of God) reached and saluted them, the Holy Spirit descended upon the mother and child; hence Elisabeth praised and John, while in the womb, leaped (prostrated) with joy. Then, he was born on Sene 30 (July 7) and Zacharias, his father, was able to speak when he named him “John.” 

✞When St. John was 2 years and 6 months old, because the wise men came, Herod the ‘Great’ slaughtered the children that were found in Israel. Later, the Jews told Herod about St. John. They said, “Because there is a child who had shut his father’s mouth [before he was conceived] and opened it when he was born [miraculously]. Kill him as well.”

✞Thence, when St. Elisabeth, his mother, took him and fled, soldiers killed the priest Zacharias in the middle of the Temple. And the old woman, Elisabeth, raised the child and stayed in the Desert of Zifata for 3 (5) years. And when St. John was 5(7) years old, his mother passed away in the desert. Thus, Zacharias and Simeon descended from heaven and buried her.

✞And when the child John cried, the Virgin Mary heard him from far away as she was also in exile. She then went with the Lord upon a cloud and comforted him. Thereafter, she asked the Lord, “Shall we take him?” To which our Lord answered, “Until I call him for ministry, let him stay here.” After that she blessed, consoled St. John and they departed.

✞Afterwards, St. John, in that desert, lived in asceticism wearing a raiment of camel's hair and a leathern girdle about his loins. And for 25 (23) years, while living in purity, he did not see anyone except beasts of the field and heavenly hosts. He as well did not know the tang of this rebellious world.

✞Then, when he became 30, God spoke to him from heaven. And because the prophets had prophesized about it, He said to him, “Go! Pave the way for My Son” (Isa. 40:3/Mal. 3:1). Also Zacharias, his father, had said, “And thou, child, shalt be called the prophet of the Highest: for thou shalt go before the face of the Lord to prepare his ways” about his forerunning (Luke 1:76).

✞Hence, at that time, St. John, filled with the Power of the Holy Spirit, came hurriedly to Judea from the desert. And all those that saw him feared and respected him.




††† እንኳን ለታላቁ ነቢይና ሰማዕት ቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅ ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን። †††

††† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!†††

††† ቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅ †††

††† ቅዱስ ወንጌል ላይ ከእመቤታችን ቀጥሎ የነ ዘካርያስን ቤተሰብ ያህል ክብሩ የተገለጠለት ፍጡር ይኖራል ብሎ መናገሩ ይከብዳል:: ቅዱስ ሉቃስ ወንጌሉን የጀመረው በዚህ ቅዱስ ቤተሰብ ነውና መንፈስ ቅዱስ እንዲህ ሲል አጽፎታል::
"ዘካርያስ ካህኑና ቅድስት ኤልሳቤጥ በሰውና በእግዚአብሔር ፊት ያለ ነቀፋ የሚኖሩ ጻድቃን ነበሩ" ይላቸዋል:: (ሉቃ. 1:6)

*የሰውን እንተወውና በእግዚአብሔር ፊት ያለ ነቀፋ መኖር ምን ይረቅ? ለዚህ አንክሮ (አድናቆት) ይገባል!
እሊህ ቅዱሳን ባልና ሚስት ግን መካኖች በመሆናቸው ልጅ ሳይወልዱ ዘመናቸው አልፎ ነበር:: እንደ ቤተ ክርስቲያን ትውፊት ዕድሜአቸው የኤልሳቤጥ 90 የዘካርያስ ደግሞ 100 ደርሶ ነበር::

*ፍጹም መታገሳቸውን የተመለከተ ጌታ ግን በስተ እርጅናቸው ከሰው ሁሉ በላይ የሆነ: ትንቢት ለብቻው የተነገረለት (ኢሳ. 40:3, ሚል. 3:1) ታላቅ ነቢይን ይሰጣቸው ዘንድ መልአከ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤልን ላከላቸው::

*ቅዱስ ዘካርያስ ሰው ነውና ከደስታ ብዛት በመከራከሩ ድዳ ሆነ:: ቅድስቲቷ ግን መስከረም 26 ቀን ታላቁን ሰው ጸንሳ ለ6 ወራት ራሷን ሠወረች:: በ6ኛው ወር የፍጥረት ሁሉ ጌታ በተጸነሰ ጊዜ የአርያም ንግሥት ድንግል እመቤታችን ደጋ ደጋውን ወደ ኤልሳቤጥ መጣች:: ሁለቱ ቅዱሳት የእህትማማች ልጆች ናቸው::

*የአምላክ እናቱ ስትደርስና "ሰላም" ስትላቸው መንፈስ ቅዱስ በእናትና ልጅ ወርዶ ኤልሳቤጥ በምስጋና: ዮሐንስ ደግሞ ገና በማሕጸን ሳለ በደስታ ዘለለ (ሰገደ):: ከዚህ በሁዋላ ሰኔ 30 ተወልዶ: አባቱ ዘካርያስ "ዮሐንስ" ሲለው አንደበቱ ተፈትቶለታል::

*ቅዱስ ዮሐንስ ከተወለደ 2 ዓመት ከ6 ወር በሆነው ጊዜ ሰብአ ሰገል በመምጣታቸው በእሥራኤል ምድር የሚገኙ ሕጻናትን ሔሮድስ ቁዝ አስፈጀ:: ትንሽ ቆይቶም አይሁድ ለሔሮድስ ስለ ቅዱሱ ሕጻን ነገሩት:: "ሲጸነስ የአባቱን አንደበት የዘጋ: ሲወለድ ደግሞ የከፈተ 'ዮሐንስ' የሚባል ሕጻን አለና እሱንም ግደል" አሉ::

*እናቱ ቅድስት ኤልሳቤጥ ይዛው ስትሸሽ ካህኑን ዘካርያስን ግን በቤተ መቅደስ መካከል ገድለውታል:: አረጋይት ኤልሳቤጥም ሕጻኑን እያሳደገች በገዳመ ዚፋታ ለ3 (5) ዓመታት ቆይታለች:: ቅዱስ ዮሐንስ 5 (7) ዓመት ሲሞላው ግን እዚያው በበርሃ እናቱ ዐረፈች:: ከሰማይ ዘካርያስና ስምዖን ወርደው ቀበሯት::

*ሕጻኑ ዮሐንስ ሲያለቅስ ድንግል ማርያም ስንት አገር አልፋ ሰማችው:: እርሷም ስደት ላይ ነበረችና:: ከጌታ ጋር በደመና ሒደው ድንግል አቅፋ አጽናናችው:: ጌታንም "እንውሰደው ይሆን?" አለችው:: ጌታችን ግን "ለአገልግሎት እስክጠራው እዚህ ይቆይ" አላት:: ባርካው: አጽናንታውም ተለያዩ::

*ቅዱስ ዮሐንስ ከዚህ በሁዋላ በዚያ ቆላ የግመል ጠጉር ለብሶ: ጠፍር ታጥቆ ተባሕትዎውን ቀጠለ:: ለ25 (23) ዓመታትም በንጽሕና ሲኖር ከምድር አራዊትና ከሰማይ መላእክት በቀር ማንንም አላየም:: ይሕችን ዐመጸኛ ዓለምም አልቀመሳትም::

*ከዚህ በሁዋላ 30 ዘመን ሲሞላው እግዚአብሔር ከሰማይ ተናገረው:: "ሒድ! የልጄን ጐዳና ጥረግ" አለው:: ነቢያት ስለዚህ ነገር ተናግረው ነበርና:: (ኢሳ. 40:3, ሚል. 3:1) አባቱ ዘካርያስም "ወአንተኒ ሕጻን ነቢየ ልዑል ትሰመይ: እስመ ተሐውር ቅድመ እግዚአብሔር ከመ ትጺሕ ፍኖቶ" (ሉቃ. 1:76) ብሎ መንገድ ጠራጊነቱን ተናግሮ ነበርና::

*ቅዱስ ዮሐንስ በዚያ ጊዜ በኃይለ መንፈስ ቅዱስ እየገሰገሰ ከበርሃ ወደ ይሁዳ መጣ:: ያዩት ሁሉ ፈሩት: አከበሩት:: ቁመቱ ቀጥ ያለ: ጽሕሙ እንደ ተፈተለ ሐር የወረደ: ጸጉሩ የቁራ ያህል የጠቆረ: መልኩ የተሟላ: ግርማው የሚያስፈራ ገዳማዊ ነውና::

*ፈጥኖም ሕዝቡን ለንስሃ ሰበከ: ለንስሃም በርካቶችን አጠመቃቸው:: በዚህ አገልግሎት ለ6 ወራት ቆይቶ ጌታችን ወደ እርሱ ዘንድ መጣ:: ዮሐንስ ሰማይን ከነግሱ: ምድርን ከነልብሱ የያዘ ፈጣሪ "አጥምቀኝ" ብሎ ሲመጣ ደነገጠ:: የሚገባበትም ጠፋው::

*"እንቢ ጌታየ! አንተ አጥምቀኝ" አለው:: ጌታ ግን "ፈቅጄልሃለሁ" አለው: አጠመቀው:: በዚህ ምክንያት ይሔው እስከ ዛሬም "መጥምቀ መለኮት" ሲባል ይኖራል:: ቅዱስ ዮሐንስ በመጨረሻ ሔሮድስን ገሰጸው:: ንጉሡም ተቀይሞ ለ7 ቀናት አሠረው::

*ልደቱን ባከበረ ጊዜ ወለተ ሔሮድያዳ በዘፈን አጥምዳ አስማለችው:: እርሱም የታላቁን ነቢይ ራስ አስቆርጦ በወጪት አድርጐ ሰጣት:: አበው "እምሔሶ ለሔሮድስ ይብላዕ መሐላሁ - ሔሮድስ መሐላውን በበላ በተሻለው ነበር" ይላሉ:: የቅዱስ ዮሐንስ ራሱ በርራ ስትሔድ አካሉን ግን ደቀ መዛሙርቱ ቀብረውታል:: (ማቴ. 3:1, ማር. 6:14, ሉቃ. 3:1, ዮሐ. 1:6)*ርጉም ሔሮድስ አንገቱን ካስቆረጠው በሁዋላ የመጥምቁ ቅዱስ ዮሐንስ ራሱ የጸጋ ክንፍ ተሰጥቷት ጌታችን ወዳለበት ደብረ ዘይት ሔዳ በፊቱ ሰገደች:: ቅዱሳን ሐዋርያት በአዩት ነገር ተገርመው ራሱን እጅ ነሷት::

*ከዚሕ በሁዋላ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለቅዱስ ዮሐንስ ራስ የማስተማር ስልጣን ሰጥቶ አሰናበታት:: በመላው ዓለም ለ15 ዓመታት ስትሰብክ ኑራ ዓረቢያ ውስጥ ዓርፋለች::

††† አስማተ-ዮሐንስ መጥምቅ (የመጥምቁ ዮሐንስ ስሞች)
1.ነቢይ
2.ሐዋርያ
3.ሰማዕት
4.ጻድቅ
5.ካሕን
6.ባሕታዊ/ገዳማዊ
7.መጥምቀ መለኮት
8.ጸያሔ ፍኖት (መንገድ ጠራጊ)
9.ድንግል
10.ተንከተም (የብሉይና የሐዲስ መገናኛ ድልድይ)
11.ቃለ አዋዲ (አዋጅ ነጋሪ)
12.መምሕር ወመገሥጽ
13.ዘየዐቢ እምኩሉ (ከሁሉ የሚበልጥ)

††† ጌታችን መድኃኔ ዓለም መጥምቁ ዮሐንስን አስቦ ይቅር ይበለን:: ጸጋውን: በረከቱንና ክብሩንም ያሳድርብን::

††† የካቲት 30 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
1.ቅዱስ ዮሐንስ መጥምቀ መለኮት
(ታላቁ ነቢይና ካህን መጥምቁ ዮሐንስ ሔሮድስ በግፍ አንገቱን ካስቆረጠው በሁዋላ ቅድስት ራሱ ለ15 ዓመታት ዙራ አስተምራ አርፋለች:: በዚህ ዕለትም በልሑክት (በሸክላ ዕቃ) የተገኘችበት በዓል ይከበራል:: በዓሉም "ተረክቦተ ርዕሱ" በመባል ይታወቃል:: )
2.አባ ሚናስ ሊቀ ዻዻሳት

††† ወርኀዊ በዓላት
1.ቅዱስ ማርቆስ ዘአንበሳ (ሐዋርያ)
2.አባ ሣሉሲ ክቡር
3.ቅዱስ ጐርጐርዮስ ነባቤ መለኮት
4.ቅድስት ሶፍያ ሰማዕት

††† "ጌታ ኢየሱስ ለሕዝቡ ስለ ዮሐንስ ሊናገር ጀመረ . . . ምን ልታዩ ወጣችሁ? ነቢይን? አዎን እላችሁአለሁ ከነቢይም የሚበልጠውን . . . እውነት እላቹሃለሁ ከሴቶች ከተወለዱት መካከል ከመጥምቁ ዮሐንስ የሚበልጥ አልተነሳም . . . ነቢያት ሁሉና ሕጉ እስከ ዮሐንስ ድረስ ትንቢት ተናገሩ:: ልትቀበሉትስ ብትወዱ ይመጣ ዘንድ ያለው ኤልያስ ይሕ ነው::
የሚሰማ ጀሮ ያለው ይስማ::" †††
(ማቴ. 11:7-15)

††† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †††


✝እንኳን አደረሰነ!

☞ወርኀ የካቲት ቡሩክ፥ አመ ፳ወ፱

✝ጾም ዐቢይ ዘመድኅን ክርስቶስ (አምላክነ)
✝ወተዝካረ በዓሉ ለክርስቶስ እግዚእነ (ስቡሕ ወውዱስ)

✞ወበዓለ ቅዱሳን አበው፦

✿ፍቅርተ ክርስቶስ/እማ ምዑዝ (ጻድቅት፥ ወሰማዕት)
✿ደናግል ንጹሐት (ማኅበራኒሃ)
❀ዘርዓ ክርስቶስ ሰማዕት (ምታ)
❀ገብርኤል መነኮስ
❀ዘመለኮት ጳጳስ
✿ቢላካርዮስ አረጋዊ (ጳጳስ ወሰማዕት)

❖ወስብሐት ለእግዚአብሔር፤
ኪያነኒ ይምሐረነ በጸሎቶሙ።
ወበረከቶሙ ይብጽሐነ፤ ለዓለመ ዓለም አሜን፡፡

https://t.me/zikirekdusn

20 last posts shown.