Student News Channel ®


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic
Category: Education


ይህ የ ፈተና ውጤት መረጃዎችን የምታገኙበት 100,000 ተማሪዎች ያሉበት ትልቁ የተማሪዎች ቻናል ነው።
Request to join ሚለውን በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ መረጃዎችንም በፍጥነት ያግኙ። 👇👇

Related channels

Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Category
Education
Statistics
Posts filter


Forward from: ትምህርት በቤቴ®
#ጥቆማ  እድሉ አያምልጣችሁ 📣

የኢትዮጵያ መንግስት ከተባበሩት አረብ ኢምሬት ጋር በመተባበር በቀጣይ 3 አመታት 5ሚሊየን ፕሮግራመሮችን ለማፍራት እቅድ ይዘዋል ::

ይህ ስልጠና ሲጠናቀቅ አለም አቀፍ ተቀባይነት ያለው ሰርተፍኬት ያገኛሉ::ትምህርቱ የሚሰጠው በኦን ላይን ሲሆን ከርሰዎ የሚሰፈልገው ሞባይል ወይ ላበቶፕ እና ኢንተርኔት ብቻ ነው ::ትምህርቱን በኢንተርኔት ከቤተዎ ሁነው ይማራሉ::

የሚሰጡ ትምህርቶች:-
1. Android Kotlin Development Fundamentals
2. Data Science Fundamentals
3. Programming Fundamentals

ትምህርቱ እድሜ ፆታ አይገድበውም:: ከገጠር እሰከ ከተማ ያሉ ከልጆች እሰከ አዛውንቶች በዚህ እድል መሳተፎ አለባቸው::ምንም አይነት የትምህርት ደረጃ አይጠይቅም :: በማንኛውም ዘርፍ ላይ ብትሆኑ መማር ትችላላችሁ:: በተለይም ወላጆች ሀገራችን ላገኜችው ለዚህ ከፍተኛ እድል ልጆቻችሁን  አሰመዝግቡ ::


ለመመዝገብ ይህን ሊንክ ይጠቀሙ:-

https://ethiocoders.et/

#ለሌሎችም_ያጋሩ!

ለተጨማሪ መረጃ👇👇👇👇

❤️ @temhert_bebete
❤️ @temhert_bebete


"ከዚህ በኃላ በወረቀት የሚሰጠው የ12ኛ ክፍል ፈተና እየቀነሰ በበይነ መረብ የሚሰጠው ፈተና ቁጥር እየጨመረ የሚሔድ ይሆናል፡፡" - ትምህርት ሚኒስቴር

የዘንድሮው የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና በወረቀት እና በኦንላይን መሰጠቱ ይታወቃል፡፡ ለመጀመሪያ ጊዜ በኦንላይን በተሰጠው ፈተና 29,718 ተማሪዎች በበይነ መረብ መፈተናቸውም ተገልጿል፡፡

"የመሠረተ ልማት ሥራና የኮምፕዩተሮች አቅርቦትን አጠናክሮ በመቀጠል ወደፊት ሙሉ በሙሉ በበይነ መረብ ለመስጠት እየተሠራ እንደሚገኝ" ትምህርት ሚኒስቴር ገልጿል፡፡

የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተናን ከሦስት ዓመት በኋላ ሙሉ በሙሉ በበይነ መረብ ለመስጠት መንግሥት አቅዶ እየሰራ እንደሚገኝ ከዚህ ቀደም መግለፁ ይታወሳል፡፡

SHARE❤️
https://t.me/+QcLpbg9EiMllODhk
https://t.me/+QcLpbg9EiMllODhk


Forward from: ትምህርት በቤቴ®
✅ አጭር ምክር - ለ12ኛ ክፍል ተማሪዎች

✅ ከትንሽ ጊዜ በኃላ ዩኒቨርስቲ ምርጫ እንድትሞሉ ትጠየቃላቹ፡፡  ዓምና ውጤት ከመጣ በኃላ በድጋሚ ዩኒቨርስቲ ምርጫቸውን እንዲያስተካከሉ እድል ተሰቶዋቸው ነበር ፤ በዚህ ዓመት ከተቀየረ አናቅም፡፡

ዩኒቨርስቲ ለዓመታት የምትቆዩበት ስለሆነ ፤ ዩኒቨርስቲ ስትመርጡ እነዚህን ማወቅ አለባቹ:

1. የምትመርጧቸው ዩኒቨርስቲዎች የምትፈልጉት field/department እንደሚሰጡ ማወቅ አለባቹ ይሄ ዋነኛው ነው። መማር የምትፈልጉትን field/department  ካልወሰናቹ ካሁኑ shortlist አድርጓቸው፡፡

2. ስለዩኒቨርስቲው ትምህርት ጥራት በተለይ እናንተ መማር የምትፈልጉት field/department  በደንብ አጣሩ፡፡

3. የምትመርጧቸውን ዩኒቨርስቲዎች እና ከተማውን youtube ላይ እዩ ፤ እዛ ዩኒቨርስቲው ውስጥ የሚማር ተማሪ ሰው በሰው ጠይቁ፡፡ ዩኒቨርስቲ የሚማሩ ወንድም / እህት ካላቹ ከእነሱ ጋር High school አብረው የተማሩ ሌላ ጊቢ የደረሳቸው ተማሪዎች ስለሚኖሩ እነሱ ሊያጠያይቁላቹ ይችላል፡፡

4. እንደ አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ (AAU) በጣም ሀሪፍ የሚባሉ ዩኒቨርስቲዎች ውስጥ በጣም ተፈላጊ የሆኑ department እንደ Medicine, Software Engineering መግባት በጣም ከባድ ነው፡፡ ውጤት በደንብ ካልሰራቹ በስተቀር በጣም ተፈላጊ የሆነ department የማግኘታቹ እድል ጠባብ ነው፡፡ የመጀመሪያ ምርጫቹ ያልሆነ department ውስጥ ልትመደቡ ትችላላቹ፡፡

5. ዩኒቨርስቲ ምርጫ ስትሞሉ ከክፍል ጓደኞቻቹ ወይም ዩኒቨርስቲ ከሚማር ወንድም/እህታቹ ጋር አብሯቹ ሙሉ። የምትሞሉት ዩኒቨርስቲ እንደየፍላጎታቹ እና እንደምታገኙት ውጤት ሊለያይ ይችላል። ግን አብሯቹ ያሉት ጓደኞቻቹ ወይም ወንድም/እህታቹ ስለ አንዳንድ ዩኒቨርስቲ መረጃ ሊኖራቸው ይችላል፡፡

6. የምትመርጧቸው ዩኒቨርስቲ ከከተማቹ ውጪ ከሆነ ፤ ስለከተማው ደህንነት እና ጸጥታ መረጃ አሰባስቡ፡፡

7. ዩኒቨርስቲው ያለበት ከተማ አየር ጸባይ ከግምት ውስጥ አስገቡ። አንዳንድ ተማሪዎች በጣም ሞቃታማ ቦታ ለዓመታት መኖር ሊያስቸግራቸው ይችላል።

ለተጨማሪ መረጃ👇👇👇👇

❤️ @temhert_bebete
❤️ @temhert_bebete


የኢፌድሪ ትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ፕሮፌሰር ብርሐኑ ነጋ ትናንት የፈተናውን መጠናቀቅ አስመልክተው ለብዙሐን መገናኛ በሰጡት መግለጫ ለፈተና ከተመዘገቡ ተማሪዎች መካከል ከ9ሺህ በላይ የአማራ ክልል ተማሪዎች ፈተናውን አልወሰዱም ብለዋል፡፡


የዘንድረውን የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ለመውሰድ ከተመዘገቡ የአማራ ክልል ተማሪዎች መካከል ከ9ሺህ በላይ የሚሆኑት ፈተናውንእንዳልወሰዱ ትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ። በሰሜን ሸዋ ዞን ካራቆሬ ከተማ የህዳሴ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪ ለፈተናው ቢመዘገብም ፈተናውን እንዳልወሰደ ተናግሯል፡፡
በዚህ ዓመት በአማራ ክልል 200 ሺህየ12ኛ ክፍል ተማሪዎችን ለማስፈተን እቅድ የተያዘ ቢሆንም በክልሉ ከተፈጠረው የፀጥታ ችግር ጋር በተያያዘ 96ሺህ ያክሉ ለፈተና መመዝገባቸውን ቀደም ሲል የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ ማሳወቁ ይታወሳል፡፡ ፈተናውን ካልወሰዱ ተማሪዎች መካከል በሰሜን ሸዋ ዞን የካራ ቆሬ ከተማ ነዋሪና የህዳሴ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪ ኑሩ ደሊል ለመፈተን ምዝገባ አካሂዶ የነበረ ቢሆንም በአካባቢው በነበረው ጦርነት ምክንያት የዓመቱን ትምህርት ማጠናቀቅ ባለመቻሉ ፈተናውን በሌላ ጊዜ ለመውሰድ መገደዱን ተናግሯል፡፡

አንድ የአጣየ ከተማ ነዋሪ በበኩላቸው ተማሪዎች በአለው የፀጥታ ችግር ምክንያት በአጣየ ከተማ የሚገኙ የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ፈተናውን አልወሰዱም ብለዋል፣ ተማሪዎቹ በትምህርት ገበታ ላይ የቆዩ ቢሆንም አልፎ አልፎ በሚከሰት የፀጥታ ችግር ምክንት የዓመቱን ትምህርት መሸፈን እንዳልቻሉ አስረድተዋል፡፡

ሌላ የከተማዋ ነዋሪም ተማሪዎቹ አብዛኛውን የትምህርት ክፍል ያልሸፈኑ በመሆናቸው ፈተናውን በመስከረም 2017 ዓ ም እንዲወሰዱ እንደሚደረግ መስማታቸውን አስረድተዋል፡፡
የኢፌድሪ ትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ፕሮፌሰር ብርሐኑ ነጋ ትናንት የፈተናውን መጠናቀቅ አስመልክተው ለብዙሐን መገናኛ በሰጡት መግለጫ ለፈተና ከተመዘገቡ ተማሪዎች መካከል ከ9ሺህ በላይ የአማራ ክልል ተማሪዎች ፈተናውን አልወሰዱም ብለዋል፡፡
“በአገር አቀፍ ደረጃ ለፈተናው የተቀመጡት 684 ሺህ 372 ተማሪዎች ናቸው፣ ከቀሩት፣ ወደ ፈታናው ካልመጡት 17ሺህ 377 ተማሪዎች መካከል 9ሺህ 152 በአማራ ክልል ከፀትታ ጋር ሳፈተኑ የቀሩ ናቸው፡፡” ብለዋል፡፡
ከፀጥታ አኳያ ሐምሌ 3/2016 ዓ ም በክልሉ ማዕከላዊ ጎንደር ዞን ተማሪዎችንና ሌለሎች ሰዎችን ይዞ ወደ ፈተና ጣቢያ በሚሄድ  ተሸከርካሪ ላይ ታጣቂዎች በወሰዱት ጥቃት አንድ ተማሪ መሞቱንና ሌሎች ሁለት መቁሰላቸውን አመልክተዋል፣ ተማሪ ያልሆኑ ሌሎች ሁለት ሰዎች በዚሁ ጥቃት ህይወታቸው ሲያልፍ ሌሎች ስድስት ተሳፋሪዎች ደግሞ መቁሰላቸውን ሚኒስትሩ በመግለጫቸው ተናግረዋል፡፡

ፕሮፌሰር ብርሀኑ በዋቻሞ ዩኒቨርሲቲ ደግሞ አንድ የግል ተፈታኝ ተማሪ በደረሰበት የልብ ህመም ወደ ሆስፒታል ቢላክም ህይወቱ ማለፉን አመልክተዋል፡፡
የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ ቀደም ሲል በሰጠው መግለጫ፣ በተፈጠረው የፀጥታ ችግር ምክንያት በክልሉ በዋናነት በጎጃም ቀጠና የሚገኙ ትምህርት ቤቶች ወደ ስራ አልተመለሱም፣ በዚህም 3 ሚሊዮን የሚጠጉ ተማሪዎች ከትምህርት ውጪ እንደሆኑ ተመልክቷል፡፡

  #DW

SHARE❤️
https://t.me/+QcLpbg9EiMllODhk
https://t.me/+QcLpbg9EiMllODhk


ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ

ትምህርት ሚኒስቴር በተጨማሪም ለዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች በቀን ተተምኖ የሚመደበው ሂሳብ ማሻሻያ ተግባራዊ ለማድረግ የሚያስችል ስራዎች እያጠናቀቅሁኝ ነው አለ!

ትምህርት ሚኒስቴር ለዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች በቀን ተተምኖ የሚመደበው ሂሳብ ማሻሻያ ከ2017 ጀምሮ ተግባራዊ ለማድረግ የሚያስችል ስራዎች እያጠናቀቅሁኝ ነው አለ፡፡በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚማር አንድ ተማሪ በቀን ለምግብ የሚታሰብለት ዋጋ 22 ብር ነው፡፡በዚህ ዋጋ ቁርስ፣ ምሳውና እራቱን መመገብ ይቻል ተብሎ ተተምኖለታል፡፡አሁን ያለው ነባራዊ ሁኔታ ግን ይህ 22 ብር አንዳንድ አካባቢዎች የአንድ ሲኒ ሻይን ሂሳብን እንኳን መሸፈን አይችልም፡፡

በዚህም ምክንያት በተለያዩ ጊዜያት በህዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት ጨምሮ ዋጋ ማስተካከያ ሊደረግ ይገባል፡፡ጊዜውን ያማከለ ትመና አይደለም የሚል ተቃውሞ ሲነሳ ይደመጣል፡፡የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ አሁን ያለው የኑሮ ሁኔታ እና ለዩኒቨርስቲ ተማሪዎች የሚመደበው የቀን ዋጋ ተመን አይመጣጠንም ይላሉ፡፡ይህንን ችግር ለመቅረፍ ጥናት እየተደረገ ነው ያሉ ሲሆን እስከ ነሃሴ ድረስ ስራዎች ተጠናቀው በአዲሱ የትምህርት ዘመን አዲስ የቀን ዋጋ ተመን ይፋ ይደረጋል ብለዋል፡፡

ከዚህ ባለፈም የዩኒቨርስቲ መምህራን ኑሮ ከብዷቸው ደሞዝ አንሷቸው በተጓዳኝ የጉልበት ስራ እየሰሩ መሆኑን በተለያዩ ጊዜያት ሲናገሩ እንደነበር ይታወሳል፡፡ፕሮፌሰር ብርሃኑ ለዩኒቨርሲቲ መምህራን የሚከፈለው ደመወዝ አነስተኛ ነው ይህንን ችግር ለመፍታት ከገንዘብ ሚኒስቴር እና ከሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ጋር እየተነጋገርን ነው፡፡

SHARE❤️
https://t.me/+QcLpbg9EiMllODhk
https://t.me/+QcLpbg9EiMllODhk


Forward from: ENGLISH ACADEMY™
የ2016 ዓ.ም የ6ኛ ክፍል መልቀቂያ ከተማ አቀፍ ፈተና ውጤት ይፋ ሆነ።

ተማሪዎች ከዚህ በታች ያለውን ማስፈንጠሪያ በመጫን መለያ ቁጥርና ስም በማስገባት ውጤታችሁን መመልከት ትችላላችሁ፡፡

https://aa6.ministry.et/#/result

Or

@emacs_ministry_result_qmt_bot


✔️ ተጨማሪ ትምህርታዊ መረጃ ለማግኘት ቻናላችን ይቀላቀሉ

🔵 https://t.me/temhrt_minster
🔵 https://t.me/temhrt_minster


ትምህርት ሚኒስቴር ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሪሚዲያል ተማሪዎች የፕሮግራም ድልድል የሚሰሩበትን መስፈርት አሳውቋል።

በሚኒስቴሩ የአካዳሚክ ጉዳዮች ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኤባ ሚጀና (ዶ/ር) በቀን ሐምሌ 10/2016 ዓ.ም ተፈርሞ ለሁሉም የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች እና ለሁሉም የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የተላከው ደብዳቤ ከላይ ተያይዟል።


በደብዳቤው የሪሚዲያል ተማሪዎቹን ወደ ፕሮግራም ለመመደብ በሚደረግ ድልድላ ተመሳሳይ መሰፈርት መጠቀም እንደሚያስፈልግ ተገልጿል።

ሁሉም ተማሪዎች በዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና 20%፣ በአንደኛ ሴሚስተር አማካይ ውጤት 50% እና ወደ መስክ መግቢያ ፈተና 30% ብቻ የሚደለደሉ መሆኑን ደብዳቤው ያስረዳል።

SHARE❤️
https://t.me/+QcLpbg9EiMllODhk
https://t.me/+QcLpbg9EiMllODhk


2018 እና 2019 የተከፈቱ ሁለት ግሩፖች አሉን መግዛት የሚፈልግ @Tmhert_bebete_info_bot ላይ ቶሎ አናግሩን👆👆


#NATIONAL_EXAM

ለሁለተኛ ዙር የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ መልቀቂያ ፈተና ተፈታኞች ዛሬ ዩኒቨርሲቲዎች አጠቃላይ ገለፃ ይሰጣሉ፡፡

የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች የ12ኛ ክፍል ፈተና ከነገ ሐምሌ 9/ 2016 ዓ.ም ጀምሮ ለሦስት ተከታታይ ቀናት በወረቀት እና በኦንላይን እንደሚሰጥ ይታወቃል።

ተፈታኞች ወደየተመደቡበት ዩኒቨርሲቲ የገቡ ሲሆን፤ በዛሬው ዕለት በፈተናው ዲሲፕሊን ዙሪያ አጠቃላይ ገለፃ እየተደረገላቸው ነው፡፡

ምስል፦ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ

SHARE❤️
https://t.me/+QcLpbg9EiMllODhk
https://t.me/+QcLpbg9EiMllODhk


የ6ኛ ክፍል ውጤት በቀጣይ ሳምንት ይለቀቃል !

የአዲስ አበባ ከተማ ትምህርት የቢሮ ኃላፊ ዶ/ር ዘላለም ሙላቱ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የሠጡት ቃል ፦

“ የ8ኛ ክፍል ውጤት ዛሬ ተለቋል። የማለፊያ ውጤት ወስነን ቆርጠን ይፋ አድርገናል።

ወንድም ሴትም 50ና ከዚያ በላይ ያመጡ ናቸው ወደ ሚቀጥለው ክፍል የሚያልፉት። የአካል ጉዳተኞች ማለፊያ ነጥብ 45 እና ከዚያ በላይ ነው።

78 በመቶ የሚሆኑት ተፈታኞቻችን አልፈዋል።

የ6ኛ ክፍል ውጤት በቀጣይ ሳምንት ይለቀቃል። ”


የ8ኛ ክፍል ፈተና ውጤት መመልከቻ : https://aa.ministry.et/account#/student-result
(መለያ ቁጥርና ስም ያስገቡ)

SHARE❤️
https://t.me/+QcLpbg9EiMllODhk
https://t.me/+QcLpbg9EiMllODhk


Forward from: ትምህርት በቤቴ®
የ2016 ዓ.ም የ8ኛ ክፍል መልቀቂያ ከተማ አቀፍ ፈተና ውጤት ይፋ ሆነ።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የአጠቃላይ ካውንስል አባላት በማለፊያ ውጤቱ ዙሪያ ውይይት በማድረግ የማለፊያ ነጥቡን ይፋ አድርገዋል።

በዚሁ መሰረት የ2016 ዓ.ም የ8ኛ ክፍል መልቀቂያ ከተማ አቀፍ ፈተና የማለፊያ ነጥብ 50 ሲሆን ለአካል ጉዳተኛ ተማሪዎች ደግሞ 45 እንዲሆን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የአጠቃላይ ካውንስል አባላት በሙሉ ድምጽ አጽድቀዋል።

የ2016 ዓ.ም የ8ኛ ክፍል መልቀቂያ ከተማ አቀፍ ፈተና በአጭር ጊዜ ታርሞ ይፋ መደረጉ ተማሪዎች ለቀጣዩ የትምህርት አመት ከወዲሁ በቂ ዝግጅት እንዲያደርጉ የሚያስችል ተግባር መሆኑን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ዘላለም ሙላቱ ገልጸው በቀጣይ ጥቂት ቀናት የ6ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ውጤት በተመሳሳይ ይፋ የሚደረግ መሆኑን አስገንዝበዋል።

በ2016 ዓ.ም የ8ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ከወሰዱ 85,219 በመንግስትና በግል ትምህርት ቤቶች በቀን እና በማታ ትምህርታቸውን ከተከታተሉ ተማሪዎች መካከል 67,903 የሚሆኑት ማለትም 78.9% ያህሉ 50% እና በላይ ማምጣታቸውን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የፈተና ዝግጅትና አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ዲናኦል ጫላ አስታውቀዋል።

ተማሪዎች ከዚህ በታች ያለውን ማስፈንጠሪያ በመጫን መለያ ቁጥርና ስም በማስገባት ውጤታችሁን መመልከት ትችላላችሁ፡፡

👇👇👇👇👇👇
https://aa.ministry.et/account#/student-result

ለተጨማሪ መረጃ👇👇👇👇

❤️ @temhert_bebete
❤️ @temhert_bebete


Forward from: ትምህርት በቤቴ®
2016 APTITUDE ENTRANCE QUESTIONS.pdf
3.5Mb
📄2016 HAMLE Entrance Exam SAT ( aptitude )

📚Subject :- SAT | Social Science የተፈተኑት ነው

ለተጨማሪ መረጃ👇👇👇👇

❤️ @temhert_bebete
❤️ @temhert_bebete


Forward from: ትምህርት በቤቴ®
Social Maths EXam 2016 @ethiouniversity1.pdf
875.1Kb
Social English 2016 Exam @ethiouniversity1.pdf
1.6Mb
የ 2016 የ 12ኛ ክፍል ፈተና 👏

☑️Subject :- Maths

🪞ዛሬ የሶሻል ተማሪዎች የተፈተኑት ፈተና ነው። ለናቹራል ተማሪዎች ስለሚጠቅማችሁ Practice አድርጉ✌️

ለተጨማሪ መረጃ👇👇👇👇

❤️ @temhert_bebete
❤️ @temhert_bebete


👏👏👏👏

የወሰዳቸውን 52 ኮርሶች በሙሉ A+ ያመጣው ተመራቂ

ተማሪ መርቲኑ ቶሌራ በ2016 ዓ.ም ከአምቦ ዩኒቨርሲቲ በአካውንቲንግና ፋይናንስ ትምህርት መስክ በመጀመሪያ ዲግሪ ተመርቋል፡፡

ባለብሩህ አዕምሮው ተማሪ መርቲኑ 4.00 አጠቃላይ ውጤት (CGPA) በማምጣት የወርቅ ሜዳሊያ እና የዋንጫ ተሸላሚ ሆኗል፡፡

ተማሪ መርቲኑ በዩኒቨሲቲ ቆይታው የወሰዳቸውን 52 ኮርሶች በሙሉ A+ በማምጣት ድንቅ ውጤት አስመስግቧል።

SHARE❤️
https://t.me/+QcLpbg9EiMllODhk
https://t.me/+QcLpbg9EiMllODhk


የ2016 ዓ/ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ መልቀቂያ ፈተና መርሃግብር

መልካም እድል

SHARE❤️
https://t.me/+QcLpbg9EiMllODhk
https://t.me/+QcLpbg9EiMllODhk


ቴሌግራም Officially ወደ ገንዘብ መስሪያ አፕነት እየተለወጠ ነው በትላንትናው እለት ሰው በመጋበዝ ብቻ በርካታ ገንዘብ የመሰብሰብ እድልን ፈጥሯል ብዙዎችን ገና አልነቁበትም እመኑኝ ከየትኛውም ኤርድሮፕ በላይ በዚ ገንዘብ ታገኛላችሁ።

ያገኛችሁን ታወጣላችሁ list ሚደረግ ነገር የለም ክፍያው በ TON ነው

https://t.me/major/start?startapp=433177540
በዚህ ሊንክ ማየት ይቻላል


የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ ሀገር አቀፍ የ12ኛ ክፍል ፈተና በኦንላይንም በወረቀትም እንደሚሰጥ የሚገልጸውን የትምህርት ሚኒስቴር መረጃ አጋርቷል።

' የኦንላይን ፈተናው ቀርቷል ፣ አልቀረም ' ብሎ ውሳኔ የሚሰጠው ማዕከላዊው ትምህርት ሚኒስቴር ብቻ ነው።

ትምህርት ሚኒስቴር አስረግጦ በተደጋጋሚ የኦንላይን ፈተና እንደሚሰጥ አሳውቋል።

ተማሪዎች ተረጋግታችሁ ለፈተናው ተዘጋጁ።

ተማሪዎችን ውዝግብ ውስጥ የከተተው ምንድነው ?

ባለፉት ቀናት በተለይ አዲስ አበባ በተሰጠው የሙከራ ፈተና ወቅት በተለያዩ ትምህርት ቤቶች ሲስቱም አስቸጋሪ ነበር።

ወላጆችም ሲስተሙ ካስቸገረ " ልጆቻቸው ዩኒቨርሲቲ ገብተው ይፈተናሉ " ተብሎ ከት/ቤት እንደተነገራቸው ለቲክቫህ ተናግረዋል።

በኃላ ግን አንዳንድ ትምህርት ቤቶች ሲስተሙ ተስተካክሎ ዛሬ በተሳካ ሁኔታ የሙከራ ፈተና መፈተናቸውን ተናግረዋል።

ዛሬ ሁሉም ሳይሆኑ አንዳንድ  ትምህርት ቤቶች ለተማሪዎች " ፈተናው በኦንላይን አይሰጥም " በማለት ኮምፒዩተር እንደመለሱላቸው ተማሪዎች ተናግረዋል።

ይህ ግን በፍጹም በትምህርት ሚኒስቴር በኩል በወረደ ትዕዛዝ አልነበረም።

ለሁሉም ግን ውሳኔ የሚሰጠው ትምህርት ሚኒስቴር ብቻ ነው።

ተማሪዎች ይህን ሀገራዊ የተማሪዎች ጉዳይ መረጃ መከታተል ያለባችሁ ከትምህርት ሚኒስቴር ብቻ መሆን አለበት።

ፈተናው መቅረቱን፣ በሌላ መንገድ እንደሚሰጥ ወይም በኦንላይን እንደሚሰጥ የሚያሳውቀው ትምህርት ሚኒስቴር ብቻና ብቻ ነው።

ሚኒስቴሩ " የኦንላይ ፈተና ቀርቷል " የሚለው ሀሰት እንደሆነ በማስገንዘብ ተፈታኞች ለኦንላይን ፈተናው እንዲዘጋጁ አሳስቧል።

ተማሪዎች ተረጋግታችሁ የትምህርት ሚኒስቴርን መመሪያ እና ውሳኔዎች ተከተሉ። እዚያም እዚህም በሚወራ ወሬ አትረበሹ !

SHARE❤️
https://t.me/+QcLpbg9EiMllODhk
https://t.me/+QcLpbg9EiMllODhk


የ12ኛ ክፍል ተፈታኞች ግዴታ እና የተከለከሉ ነገሮች

1. ማንኛውም ተፈታኝ አጤሬራ፣ ስልክ፣ ሃርድ/ፍላሽ ድስክ፣ ስማርት ሰዓት፣ የጌጥ መነጽር፣ ጌጠኛ ቀለበት፣ ማጂክ ጃኬት፣ ቁልፍ ወይም ምንም ዓይነት ድምጽና ምስል
የሚቀዱ/የሚቀርጹ ኤሌክትሮኒክስ መሣሪያዎችን ይዞ ወደ መፈተኛ ክፍል ውስጥ መግባት የተከለከለ ነው፡፡ 

2. ፈተና በሚሰጥባቸው ኮምፕዩተሮች ላይ በሚመለከተው አካል ደህንነቱ ያልተረጋገጠ የትኛውንም ዓይነት መተግበሪያ መጫን ወይም ማህበራዊ ሚዲያዎችን መጠቀም  የተከለከለ ነው፡፡ ሆኖ ሲገኝም የፈተና ውጤት ከመሰረዝ በተጨማሪ አግባብነት ባለው ህግ ተጠያቂ  ያደርጋል፡፡

3. ፈተና እየተሰጠ ባለበት ወቅት በማንኛውም አማራጭ የመፈተኛ ኮምፕዩተሮችን በመጠቀም የኤሌክትሮኒክ መልዕክት ለማንኛውም ሶስተኛ ወገን መላክም ሆነ መቀበል በጥብቅ የተከለከለ ነው፡፡ ሆኖም ሲገኝ ያለ ምንም ቅድመ ሁኔታ ፈተናው የሚሰረዝ ይሆናል፡፡ አግባብነት ባለው ህግ ተጠያቂ ይሆናል፡፡

4. ማንኛውም ተፈታኝ ከመፈተኛ ክፍል ውጭ ሆኖና ለፈተና ሥራ ተለይቶ እውቅና ከተሰጠው ኮምፕዩተር ውጭ ለመፈተን መሞከር ወይም መፈተን በጥብቅ የተከለከለ ሲሆን ሆኖ ከተገኘ የፈተና ውጤቱ ሙሉ በሙሉ ይሰረዛል፤ አግባብነት ባለው ህግ ተጠያቂ ይሆናል፡፡  

5. ለፈተና ሥራ የሚያገለግሉ የይለፍ ቀሎችን (Password) በማንኛውም ሁኔታ ለሶስተኛ ወገን አሳልፎ መስጠት ወይም ጥንቃቄ በጎደለው ሁኔታ መያዝ ወይም በቀላሉ ተገማች ማድረግ የተከለከለ ነው፡፡ ይህ እንደተጠበቀ ሆኖ ዓይነ ስውራን ተፈታኞች ለአንባቢዎቻቸው ወይም የአካል ጉዳት ያለባቸው ተፈታኞች ለረዳቶቻቸው ሊሰጡ ይችላሉ፡፡ 

6. ማንኛውም ተፈታኝ ወደ መፈተኛ አዳራሽ መግቢያ ካርድ እና ማንነቱን በግልጽ ለመለየት የሚያስችል የትምህርት ቤት ወይም የቀበሌ መታወቂያ ወይም የወሳኝ ኩነት ምስክር ወረቀት ይዞ የመገኘትና ሲጠየቅም የማሳየት ግዴታ አለበት፡፡ ወደ መፈተኛ አዳራሽ መግቢያ ካርድ ሳይዙ መፈተን የተከለከለ ነው፡፡

7. ተፈታኞች በሐኪም ከታዘዘ መድኃኒት ውጭ ወደ መፈተኛ ክፍል ምንም ዓይነት መድኃኒትና መድኃኒት መውሰጃዎችን ይዞ መግባት በጥብቅ የተከለከለ ነው፡፡

8. ተፈታኞች ወደመፈተኛ አዳራሽ ምግብና ውሃ ይዘው መግባት የጠከለከለ ነው፡፡ ነገር ግን አስቀምጠው ለፈታኝ መምህር እያሳወቁ ሲፈቀድላቸው መጠቀም ይችላሉ፡፡  
ውስጥ መግባት የተከለከለ ነው፡፡ በጤና ምክንያት የግዴታ መጠቀም ያለባቸው ሲሆኑ ከመፍተኛ ከፍል ውጪ (በር አካባቢ) አስቀምጠው ለፈታኝ መምህር እያሳወቁ ሲፈቀድላቸው መጠቀም ይችላሉ፡፡

9. ተፈታኞች የተሟላ አካላዊ ፍተሻ ተደርጎና ማንነታቸው በግልጽ ተለይቶ ወደ መፈተኛ አዳራሽ የሚገቡ ይሆናል፡፡ ለዚህም የመተባበር ግዴታ አለባቸው፡፡  

10. አካላዊ ፍተሻ ሳይደረጉ ፈተና ወዳለበት ሰርቨር እና ኮምፕዩተሮች አካባቢ ወይም ክፍሎች ውስጥ መግባት የተከለከለ ነው፡፡

11. በግልጽ ያልተፈቀደለትን ማንኛውንም ሰው ወደ መፈተኛ ክፍሎች ይዞ መግባት እና ፈተና የሚሰራባቸውን ኮምፕዩተሮች እንዲነካካ ወይም እንዲጠቀምባቸው መፍቀድ በጥብቅ የተከለከለ ነው፡፡

SHARE❤️
https://t.me/+QcLpbg9EiMllODhk
https://t.me/+QcLpbg9EiMllODhk


የ2016 ዓ.ም የ 12ተኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በወረቀት እና በኦንላይን ይሰጣል ተብሎ የነበረ ቢሆንም ከሰሙኑ በሙከራ ጊዜ ባገጠሙ መሰናክሎች ምክንያት በበየን መረብ ወይም ኦላይን ሊሰጠ የነበረው ፈተና መቅረቱን እና ተማሪዎች ወደ ዩንቨርስቲ በመግባት ፈተናቸውን እንደሚወስዱ ተገልጿል።

የማህበራዊ ሳይንስ ተፈተኞች ከ እሁድ ሰኔ 30 ጀምሮ እሰከ ሀምሌ 1 ድረስ ወደ ዩንቨርስቲ የሚገቡ ሲሆን ፈተናው ሀምሌ 3 ይጀምሯል።

SHARE❤️
https://t.me/+QcLpbg9EiMllODhk
https://t.me/+QcLpbg9EiMllODhk


#ATTENTION🚨

“ የ2 አውቶብስ ተማሪዎች በታጣቂዎች ታግተዋል ” - ከእገታ ያመለጠ ተማሪ

“ ‘ ከአሁን ወዲህ ስልኬ አይሰራም ፤ ታግተናል ’ አለችኝና ከዛ ስልኳ አይሰራም ” - የአንዷ ታጋች ተማሪ እህት

“ አጋቾቹ ለአንድ ተማሪ 400 ሺህ ብር እየጠየቁ ነው ” - የወንጌላውያን ክርስቲያን ተማሪዎች ህብረት

ሰኞ እለት ተሳፍረው ወደ ቤተሰብ እየተጓዙ የነበሩ የደባርቅ ዩኒቨርሲቲ ከ2ኛ እስከ 4ኛ ዓመት ያሉ ተማሪዎች በታጣቂዎች መታገታቸውን የዓይን እማኝ፣ የታጋች ቤተሰብና ዩኒቨርሲቲው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገለጹ።

አንድ ከእገታው አመለጥኩ ያለ ተማሪ ፥ ሶስት (3) አውቶብሶች የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች እየተጓዙባቸው የነበሩ ረቡዕ ሰኔ 26 ቀን 2016 ዓ/ም ከረፋዱ 4 ሰዓት ገደማ ገብረ ጉራቻ የሚባል ቦታ ሲደርሱ መታገታቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግሯል።

ከ3 አውቶብሶች 2ቱን ታጣቂዎች እንዳስቆሟቸው፣ ተሳፋሪዎቹን ካስወረዷቸው በኋላ አግተው ወደ ጫካ እንዳስገቧቸው፣ እርሱ ገለባ ውስጥ ተደብቆ እንዳመለጠ ገልጾ፣ “ የሁለቱ አውቶብስ ተማሪዎች በታጣቂዎች ታግተዋል ” ብሏል።

ከታጋቾቹ መካከል የሚያውቃቸው የIT ፣ የአኒሚል ሳይንስ ዲፓርትመንት ተማሪዎች እንዳሉ ገልጾ፣ ያገቷቸው “የሸኔ ታጣቂዎች” መሆናቸውን አስረድቷል።

አንዷ የታጋች እህት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጠችው ቃል፣ “ ረቡዕ 3 ሰዓት ከ28 ደቂቃ ደወለችልኝ (እየሮጡ ነበር፣ የተኩስ ድምጽም ነበር) ‘በቃ ከአሁን ወዲህ ስልኬ አይሰራም። ላታገኝኝ ትችያለሽ በታጣቂዎች ታግተናል’ አለችኝ። መለሽ ስደውል ስልኳ አይሰራም ” ብላለች።

ቤተሰቡ ሁሉ በጣም ከፍተኛ ጭንቀት ላይ በመሆኑ የሚመለከታቸው አካላት ሁሉ ታጋቾቹን በህይወት እንዲያተርፏቸው ተማጽናለች።

በደባርቅ ዩኒቨርሲቲ ፤ የወንጌላውያን ክርስቲያን ተማሪዎች ህብረት በበኩሉ፣ እገታው እውነት መሆኑን እንዳረጋገጠ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግሯል።

ኀብረቱ በሰጠው ቃል “ አጋቾቹ ለአንድ ተማሪ 400 ሺህ ብር እየጠየቁ ነው። ‘ ገንዘቡን ካላመጣችሁ እንገድላችኋለን ’ እያሏቸው ይገኛል ” ሲል የሰማውን አስረድቷል።

የሞቱ ፣ የተጎዱ ስለመኖራቸው የደረሰው መረጃ እንደሌለ የገለጸው ማህበሩ ፣ የሚመለከታቸውን  አካላት ሁሉ ለማነጋገር ጥረት እያደረገ መሆኑን ገልጿል።

በጉዳዩ ላይ የደባርቅ ዩኒቨርሲቲ የሰጠውን ምላሽ በቀጣይ ይቀርባል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

SHARE❤️
https://t.me/+QcLpbg9EiMllODhk
https://t.me/+QcLpbg9EiMllODhk

20 last posts shown.