♦️✨️ሽማግሌው✨️♦️
🎗አስተማሪ አጭር ታሪክ🎗
🥇በግሩም ተበጀ የተፃፈ
🥈በ《山ㄒ丂》♤ Ҝ丨几ᎶƊㄖ爪 😵 Telegram Channel የቀረበ
__
ገና በጠዋቱ...2፡30 ላይ....ክሊኒካችን በህመምተኛ በተጨናነቀበት ወቅት ነበር
አንድ አረጋዊ ወደ ክሊኒካችን የገቡት። በግራ ክንዳቸው ላይ የቁስል እሽግ
ይታያል። በግምት 70 ዓመት የሚሆናቸው አዛውንት ናቸው። በቀስታ አግዳሚው
ወንበር ላይ ተቀምጠው ሰዓታቸውን ማየት ጀመሩ።
የቸኮሉ ይመስላሉ፡፡
“ምን ልርዳዎት” አልኳቸው፡፡
የቁስሉ እሽግ እንዲቀየርላቸው ነው የመጡት። ከ30 ደቂቃ በኋላ ግን ቀጠሮ
ስላላቸው ቸኩለዋል፡፡
ህክምና ሊያገኙ የሚችሉት ገና ከ1 ሰዓት በኋላ እንደሆነ ይገባኛል፡፡ ምን ማድረግ
እችላለሁ! ግን እስቲ ቢያንስ ቁስሉን ፈትቼ ልየው ብዬ እሽጉን ስፈታው ቁስሉ
ደርቋል፡፡
በጣም ጥሩ!
ከአንዱ ዶክተርጋ ተነጋገርኩ። አስፈላጊውን መድሃኒቶችና የህክምና ቁሳቁሶች
ወስጄ ህክምናውን አከናወንኩላቸው፡፡ አረጋዊው ወደ ቀጠሯቸው በጣም
በመቸኮላቸው ምክንያት ትዕግስት አጥተዋል። አሁንም አሁንም የሚያዩት የእጅ
ሰዓታቸው ቁስሉ ያለበት ግራ ክንዳቸው ላይ ነው ያለው፡፡ ስለዚህ እንዴት
ሰዓታቸውን ይዩ...፡፡ ቁስሉን እየፈታሁላቸው እሳቸው አስግገው ሰዓታቸውን
ለማየት ይጣጣራሉ፡፡
“ለመሆኑ ይሄን ያህል የቸኮሉበት ቀጠሮዎት የት ነው...” አልኳቸው እንደ
ጨዋታ ያህል።
“3፡00 ሰዓት ላይ ከባለቤቴ ጋር ቁርስ ለመብላት ቀጠሮ አለኝ” አሉኝ።
“አሀ...”
ቁስላቸውን መልሼ እያሸግኩላቸው አረጋዊው ታሪካቸውን አጫወቱኝ፡፡
እንዳሉኝም እንዲህ የቸኮሉት ከሚስታቸው ጋር 3፡00 ሰዓት ላይ ቁርስ የመብላት
ቀጠሮ ስላላቸው ነው፡፡ ሚስታቸው ግን ቤት አይደለም ያሉት፡፡ ህመምተኛ
ናቸው፡፡ ሆስፒታል ነው ያሉት፡፡
“ባለቤትዎ ሀይለኛ ሴት ናቸው ማለት ነው...ለዚህ ነው ላለማርፈድ ይሄን ያህል
የቸኮሉት” አልኳቸው።
“አይ...እሷ እንኳ ምንም አትለኝም” አሉኝ አረጋዊው፤ “እኔው ነኝ ...፡፡”
“እንዴት...” አልኳቸው እንዲጫወቱ ፈልጌ።
“አዬ ልጄ፣ ባለቤቴማ ላለፉት አምስት ዓመታት አልዛሜር በተባለ የመርሳት
በሽታ ተይዛ ባለቤቷ እንደሆንኩ እንኳ አታውቅም” አሉኝ ትክዝ ብለው፡፡
ገረመኝ። አረጋዊው ላለፉት አምስት አመታት አንድም ቀን ሳያስተጓጉሉ
ሆስፒታል እየሄዱ ከባለቤታቸው ጋር ቁርስ ቆርሰዋል፡፡ ባለቤታቸው ግን
እያንዳንዱን ቀን ከተለያየ ሰው ጋር ቁርስ እንደበሉ ነው የሚያውቁት፡፡
ግማሽ ምዕተ ዓመት በዘለቀው ትዳራቸው...የትዳር አጋራቸው የሆኑትን
ባለቤታቸውን ፈጽሞ ረስተዋል። ምስኪኑ አረጋዊ ግን ሁልቀን ሳያረፍዱ
ሆስፒታል እየተገኙ ጨርሶ ከማያስታውሷቸው ባለቤታቸው ጋር ፍቅርን
ይቆርሳሉ፡፡
🔸️ THE END 🔹️
◇
https://t.me/+eroSuqSQh49kYzJk♤
@TheDarkJah♧
@Nahpac28