አስኳላ-💚💛❤️


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: Психология


እዚህ Channel ላይ ያስተምራሉና ያዝናናሉ ብዬ የማስባቸውን ማንኛውም አይነት ፅሁፎች ከተለያዩ ቦታዎች እየለቀምኩ አቀርባለሁ። ስታነብ ታውቃለህ፣እራስህን ትመለከታለህ፣ክፉና ደጉን ትለያለክ። እዚህ የሚለቀቁ ፅሁፎች እኔ የተናገርኳቸው እና የፃፍኳቸው ብቻ አይደሉም። ከመፃፍ፣ከሶሻል ሚዲያ እና ከተለያዩ ሰዎች የሰበሰብኳቸው ጭምር ናቸው።

Comment▹ @Meklite21

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
Психология
Статистика
Фильтр публикаций


እብዱ ዮሐና
....................ምዕራፍ ስምንት(12)



.     የቤተ-ክርስቲያኑ ሥነ-ስርዓት እየተካሄደ ባለበት በዚህ ሰዓት ዮሐና በእነዚህ አሳዛኝና ስቃይን የሚፈጥሩ ሀሳቦች አእምሮው ተወጥሮ ነበር:: በዚህ ተቃራኒ ህይወት በሚስተዋልበት ቦታ ትንፋሽ አጥሮት ደረቱ በስቃይ እንዳይተረተር ስጋት እንደያዘው ሁሉ፣ እጆቹን አጣምሮ ደረቱን ተጫነው:: ዳግም እነዚያ የመጨረሻ ደሀ የሆኑትን፣ ልባቸው የደረቀውንና ምድር ውስጥ መጠለያ የሚፈልጉትን ምስኪኖች ተመለከታቸው፡፡

ዳግም በመወለድ አዲስ እውነተኛ ግዛት ማግኘት የሚፈልጉ እጅግ በጣም የተቸገሩ መንፈሳዊ ተጓዦችን መስለው ታዩት፡፡
በዚህ መልኩ የምርቃቱ ሥነ-ስርዓት ተጠናቅቆ የተሰበሰበው ህዝብ ወደየመጣበት ሊበተን ሲል፣ ዮሐና በተጨቆኑት ድሆች ስም ንግግር እንዲያደርግ ታላቅ ሀይል (መንፈስ) ሲገፋፋው ታወቀው፡፡

እናም ይህ የሚገፋው ታላቅ ኃይል ከሰማይና ከምድር ፊት እንደቆመ ሰባኪ ወደ ፊት አንደረደረው፡፡ ወደ መድረኩ ጥግ ወጥቶ ዓይኖቹን ወደ ሰማይ ወረወራቸውና እጆቹን ከፍ አድርጐ በማንሳት ወደ ሰማይ አመለከተ፡፡
ህዝቡ ሲሰበስብለት፣ ትኩረት እንዲሰጡ በሚያስገድድ ብርቱ ድምፅ ጮኸ ብሎ መናገር ጀመረ:- ........

«አቤቱ ከፍ ብሎ በሚታየው ደማቅ ብርሃን ተከበህ በዙፋንህ የተቀመጥከው የናዝሬቱ ሰው - ኢየሱስ ሆይ! እነሆ ካለህበት የሰማዩ ሰማያዊ ጉልላት ባሻገር ቁልቁል ወደዚህች ምድር ተመልከት፡፡ ፍጡሮችዋን ትናንትና እንደ ካባ ለብሰሃቸው ነበር፡፡ አቤቱ በህይወትህ ደም እንዲለመልሙ የዘራሃቸውን አበቦች የጢሻው አሜኬላዎች እንዴት ቀንጥለው እንደገደሏቸው ተመልከት! . . .

«አቤቱ መልካሙ እረኛ! በደረትህ ታቅፈው የነበረው ደካማ ጠቦት አሁን በተኩላዎች ተነጣጥሎ ተበልቷል፡፡ ንፁህ ደምህን ምድሪቱ መጣዋለች፡፡ ትኩስ ዕንባህ በሰዎች ልቦና ውስጥ ደርቋል፡፡ በእግሮችህ የቀደስከው ይህ መሬት የሀያላን እግሮች ደካሞችን የሚጨፈልቁበት፣ የጨቋኞች እጆች ደግሞ የደካሞችን ህይወት የሚያጠወልጉበት ጦር ሜዳ ሆኗል
ጥሪ ምንም.....

«አቤቱ! ችግረኞች ከጨለማው ውስጥ ሆነው አቤቱ ይላሉ፡፡ በስምህ ዙፋን ላይ ተቀምጠው ያንተን ቃል የሚሰብኩት ሰዎች ግን ጥሪያቸውን ነገሬ - አላሉትም:: እስካሁን የድሆች ዋይታና የለቅሶ አልተሰማቸውም፡፡ የመንፈስ አባት እንዲሆኑ የሳክካቸው ሰዎች በእጆችህ ያቀፍከውንና የባረክከውን የበግ ግልገል ዘነጣጥለው ለመዋጥ የሚራወጡ ተኩላዎች ሆኗል.....

«አቤቱ! ከአምላክ ልብ ዘንድ ይዘኸው የመጣኸው የህይወት ቃል በነዚያ መጻህፍት ገፆች ውስጥ ብቻ ተሸሽጐ የሚቀር ፍሬ-የለሽ ሆኗል፡፡ እናም በእሱ ቦታ አስፈሪ የፍርሃትና የስጋት ጩኸት ተተክቷል .....



..........ይቀጥላል............


👍👍👍👍👍👍👍👍
https://t.me/Asresee
https://t.me/Asresee
https://t.me/Asresee




ጉራማይሌ

አንተ ምትወዳትን ያቺን ሴት ለመሆን
እላይ ታች እላለሁ የሰማውህ ሠሞን
ዛሬ ቀይ ስትል
ቀለሜን ልቀይር ስሞክር ስጣጣር
ደግሞ ሲነጋልህ ፀይም ትለኛለህ
ከዚያ ደግሞ ጥቁር
መወሠን አቅቶህ ግራ ስትጋባ
እሺ እኔ ምን ልሁን የታባቴ ልግባ
ጉራማይሌ አንዲሆን ቀለሜ ተመኘው
ሁሉንም ፈልገህ ከኔ እንድታገኘው


REDU yekatit 07/2016


......✍️  @Reduu2325

👍👍👍👍👍👍👍👍
https://t.me/Asresee
https://t.me/Asresee
https://t.me/Asresee


።።።።። ዋ! ።።።።።

አይኔ ወደደሽ ስልሽ፣
አይኑን አጥፋው ብለሽ ገባሽ አሉ ስለት
ምኞትሽ ሰመረ
አይኖቼ ጠፉልሽ ይኸው አንደዘበት።

ግን መች ተውሻለው
በልቤ ብሩህ አይን ዛሬም አይሻለው።

ደግሞ አንደዚ ስልሽ አትወጅኝምና
ልቡንም አጥፋልኝ ብለሽ ትሳይና
ፀሎት ያልቅብሻል እሞትብሽና።

                  
.......የእናቴ ልጅ-(Tame)💚💛❤


💝
t.me/Asresee
💝
t.me/Asresee
💝
t.me/Asresee


እብዱ ዮሐና
....................ምዕራፍ ስምንት(11)



ታላላቅ ሰዎች - ለክብራቸው በሚመጥኑ ቃላት፣ በመፅሀፍ ቅዱስ ጥቅሶች፤ እንደዚሁም በዝማሬዎች እያወደሱ በደማቅ ሥነ-ስርዓት ተቀበሏቸው፡፡

አዲሱ ቤተ-ክርስቲያን ከተሰራበት ቦታ ሲደርሱም፣ በወርቅ የተሸለመ የቀሳውስት ካባ ተደረበላቸው፤ በጌጣጌጦች የተንቆጠቆጠ አክሊልም በራሳቸው ላይ ተደፋላቸው፡፡ ከዚያም ድንቅ የእጅ ሙያ ጥበብ የተገለፁበት በውድ የከበሩ ድንጋዮች ያጌጠ ቆልማማ ዘንግ ተሰጣቸውና ቀሳውስቱን ከኋላ አስከትለው በአንድ ላይ እያዜሙና እየዘመሩ ቤተ-ክርስቲያኑን ዞሩት፡፡ ከሁሉም አቅጣጫዎች መልካም መዐዛ ያለው ዕጣን ጢስና አየሩ ላይ የሚዋልል ጥርዥ፣ ብርዥ የሚል ነበልባል ያላቸው በርካታ ጧፎች የያዙ ዲያቆናት አጅበዋቸው ይታያሉ፡፡

በዚያ ሰዐት ዮሐና ከእረኞቹና ከአፈር ገፊዎቹ መሀል ቆሞ ሀዘን ባጠላባቸው ዓይኖቹ ይህንን ደማቅ ትዕይንት በአንክሮ ይመለከታል፡፡ በአንድ ወገን ከሀር የተሰሩ ካባዎችን፣ የወርቅ እጣን ማጤሻዎችን፣ በጌጣጌጦች የተሽቆጠቆጠ አክሊልንና በውድ የከበሩ ድንጋዮች ያጌጠ ዘንግን፤ በሌላ ወገን ደግሞ ለዚህ በዓል ደስታና የምርቃት ሥነ-ስርዓት እገዛ ለማድረግ ከትናንሽ መንደሮችና ሰፈሮች የመጡትን በከፋ ድህነት ተዘፍቀው የሚኖሩት ደሀና ምስኪን ሰዎችን ሲያይ - ጥልቅ የሀዘን ስሜት አድሮበት በምሬት በረጅሙ ተነፈሰ፡፡ በአንደኛው ወገን በከፋይና በሀር ልብሶች ውስጥ ያለው ምቾትና ስልጣን፤ በሌላኛው ወገን ደግሞ በተቀዳደደ ብጭቅጫቂ ቡትቶች ውስጥ ያለው ችጋርና መከራ ወለል ብለው ታዩት፡፡

እነዚያ በዓርማና ሜዳሊያ አሸብርቀው ራቅ ብለው የቆሙት ሀብታም «አስተዳዳሪዎች» ድምጻቸውን ከፍ አድርገው የሚፀልዩት ሰሀብትና ለስልጣናቸው ሲሆን፣ ደስ የሚሰኙትም በዚያ ከንቱ ክብራቸው ነው፡፡ እነዚህ ዝቅ ብለው ቆመው ደረታቸውን እየደቁ ጠልቆ ከሚገኘው የተሰበረ ልባቸው የሚወጣ እውነተኛ ፀሎት የሚፀልዩት ጐስቆላ፤ ትሁትና በድህነት የሚማቅቁ የመንደሯ ነዋሪዎች ግን ደስ የሚሰኙት በትንሳኤ ውስጥ ባለው ዘላለማዊ ህይወታቸው ነው፡፡

የአስተዳዳሪዎቹና የመሪዎቹ ስልጣን በአረንጓዴ ለምለም ቅጠሎች እንደተሞላው ረዥም ዛፍ ሲሆን፣ የህዝቡ ህይወት ግን መርከባ በማዕበል ተመትታ በሞት አፋፍ ላይ እንደደረስ ካፒቴን ነው፡፡ እናም መቅዘፊያዋ ተሰብሮባት፣ ሸራዋ - በንፋስ ተቀድዶባት፣ በተቆጣው የባህሩ ውሃና በአስፈሪው አውሎ ነፋስ ብቅ፣ ስጥም እንደምትል መርከብ በፍርሃት ሰጥ ለጥ ብለው የሚገዙ ታዛዥ ጭሰኞች ናቸው::

ለመሆኑ ከከፋ የጭቆና አገዛዝና ከጭፍን ታዛዥነት የትኛው ይሆን የሚቀድመው? የትኛው ነው የቱን የወለደው? የጭቆና አገዛዝ በታችኛው መሬት ላይ ካልሆነ በስተቀር የማያድግ ጠንካራ ዛፍ ይሆን? ወይስ ጭፍን ታዛዥነት ከእሾሆች በስተቀር ምንም የማይበቅልበት ምድረ-በዳ ሆኖ ይሆን?


..........ይቀጥላል..........


👍👍👍👍👍👍👍👍
https://t.me/Asresee
https://t.me/Asresee
https://t.me/Asresee


ሰዎች ችላ እንዳሉህ አንዴ ከተረዳህ ፤ ድጋሜ ወደነሱ ዝር አትበል፤አትረብሻቸው........

ይሄም የገባኝ....
ሰላም ስላት ሰላምህን ይንሳህ
.................. ባለችኝ ጊዜ ነበር።


@Asresee @Asresee @Asresee


ይህ ይበልጥ ህመም ነበረው፤ የተሳሳተን ሰው በትክክለኛው መንገድ ማፍቀር..!

@Asresee @Asresee @Asresee


እብዱ ዮሐና
....................ምዕራፍ አስር(10)


እናም የአባቶቻቸው ጥርሶች ከላይ እስከ ታች ይነቃነቃሉ!  አንቺ መልካም ስለሆንሽ አሁን ሂጂና ዕብዱን ልጅሽን የሰማዩ _ አምላክ እንዲፈውሰውና ልቦና እንዲሰጠው ፀልይለት፡፡»

*

ዮሐና በመጨረሻ ከእስር ቤቱ ወጥቶ ከብቶቹን እየነዳ በቀስታ እርምጃ ወደ ቤቱ እያመራ ነው፡፡ ከአጠገቡ ዕድሜ ያጐበጣቸው እናቱ ምርኩዛቸው ላይ አቀርቅረው አብረውት ያዘግማሉ፡፡ ከደሳሳ ጐጆዋቸው ሲደርሱ፣ ከብቶቹን ሳር እንዲግጡ ትቷቸው መስኮቱ አጠገብ ተቀመጠና በተመስጦ የምትጠልቀውን ፀሀይ መመልከት ያዘ፡፡

ከጥቂት ጊዜ በኋላ አባቱ ወደ እናቱ ጆሮ ቀረብ ብለው እነዚህን ቃላት ሹክ ሲሏቸው ሰማ፡- «ሳራ፣ ብዙ ጊዜ ነግሬሻለሁ:: ልጃችን አዕምሮው ተዛብቷል፡፡ ላለፉት ዓመታት ዮሐና ዕብድ መሆኑን ስነግርሽ አምነሽኝ አታውቂም ነበር፡፡ አሁን የተከበሩት አባት ሲነግሩሽ ግን አመንሽ፡፡ ዛሬ የፈፀማቸው ተግባራት የሚያረጋግጡት የእኔን እውነተኛነት ነውና ከዚህ በኋላ እንዳትቃወሚኝ፡፡››

ዮሐና ወደ ምዕራብ አቅጣጫ መመልከቱን ቀጠለ፡፡ በአድማስ ጥግ የምትጠልቀው ፀሀይ የምትፈነጥቀው ደብዛዛ ብርሃን፣ ጥቅጥቅ ያለውን ግዙፍ ዳመና ልዩ ህብር አላብሶታል፡፡ •


ሳምንቱ የፋሲካ በዓል የሚከበርበት ሳምንት ነው፡፡ የፆሙ ወራት አሁን በድግስ ተተክተዋል፡፡ የአዲሱ ቤተ - ክርስቲያን ግንባታ ተጠናቋል፡፡ ይህ አዲሱ ህንፃ በትናንሾቹ የተራው ህዝብ ደሳሳ ጐጆዎች መሃከል ጐላ ብሎ ቆሞ ሲታይ፣ የልዑል ቤተ - መንግስት ይመስላል፡፡

ህዝቡ የቤተ-መቅደሱን የምረቃ ክብረ-በዓል ለማክበርና በመሰዊያዎቹ ላይ ስለቱን ለማኖር ግር ብሎ ወጥተዋል፡፡ በርካታ ሰዎችም ከትንሿ ብሻሬ ከተማ ወጥተው በመንገድ ዳርና ዳር ተኮልኩለው የክቡርነታቸውን መምጣት እየተጠባበቁ ናቸው::

በመጨረሻ ጳጳሱ በወርቅ የተለበጠ ኮርቻ ባለው ድንቅ ፈረስ እቦታው እንደደረሱ፤ በወጣቶቹ የምስጋና ዝማሪዎች፣ በቀሳውስቱ ቅዳሴ፣ በዝማሬ ማጀቢያዎቹ ሳህኖች ድልቅታና በደውሎች ቅጭልጭልታ ታጅበው ወደ ከተማዋ ዘለቁ፡፡ ከወርቅ ባሸበረቀ ኮርቻና ክብር በተሰራ ልጓም ከተንቆጠቆጠው ፈረሳቸው ላይ ሲወርዱ፣ በርካታ የሀይማኖት አባቶችና

..........ይቀጥላል..........

👍👍👍👍👍👍👍👍
https://t.me/Asresee
https://t.me/Asresee
https://t.me/Asresee


ዕብዱ ዮሐና

ይቀጥል 👍
      አይቀጥል👎


Репост из: አስኳላ-💚💛❤️
.እውነት

   አንድ ቀን እውነትና ውሸት ይገናኛሉ። ውሸት ለእውነት ''ዛሬ አስደናቂ ቀን ነው'' ትላታለች። እውነት ወደ ሰማይ ቀና ብላ ትመለከትና እውነትም እጅግ ውብ መሆኑን ታስተውላለች። ከዚያም ቀኑን ሙሉ አብረው ያሳልፉና በመጨረሻም አንድ የውሀ ጉድጓድ ላይ ይደርሳሉ። ውሸት እውነትን በድጋሚ ''ውሀው በጣም ጥሩ ነው፣ አብረን እንታጠብ'' ትላታለች። እውነትም የጉድጓዱን ውሀ ባየች ጊዜ ጥሩ መሆኑን ተገነዘበች። በዚህም፣ እውነት የአብረን እንታጠብ ግብዣውን ተቀብላ ልብሳቸውን ከጉድጓዱ ዳር አስቀምጠው መታጠብ ይጀምራሉ።

  መታጠብያ ጉድጉዋድ ውስጥ እያሉ ውሸት ከውሀው በድንገት ትወጣለች ፣ የእውነትንም ልብስ ትለብስና ትሸሻለች። በሁኔታው በጣም የከፋት እውነት ከጉድጓዱ ትወጣና ውሸትን ለማግኘት እናም ልብሷን ለመቀበል በየቦታው ትሯሯጣለች። በየመንገዱ የምታገኛቸው ሰዎች እውነትን እርቃኗን በማየታቸው በንቀትና በንዴት ይመለከቷታል። ውሸትን ሮጣ መያዝ ያልቻለችው ምስኪኗ እውነት ወደ ጉድጓዱ ተመልሳ የውሀው ጉድጓድ ውስጥ በመደበቅ ለዓለም ስትል እርቃኗን ለዘላለም ተሸፍናለች። እነሆ ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ውሸት እንደ እውነት ለብሶ በአለም ዙሪያ በመዘዋወር የህብረተሰቡን ፍላጎት በማርካት ላይ ይገኛል።

  ዓለምም እውነትን የመፈለግ በጭራሽ ፍላጎት የለውምና የእውነት ለዘላለም ከጉድጓድ ውስጥ መቅረት አያስጨንቀውም። ዓለም፣ እውነት እርቃኗን ስትሆን የሚሸከምበት ሞራሉም ስለሌለው በመደበቋ ደስተኛ ነው።

👉👉Telegram channels 👇👇
https://t.me/Asresee 🌹🌹
https://t.me/Asresee 🌹🌹
https://t.me/Asresee 🌹🌹


እብዱ ዮሐና
....................ምዕራፍ ስምንት(9)



በጭራሽ አልደፈረሰም:: ለኢየሱስ ያለው ፍቅርም በፍጹም አልተለወጠም፡፡ ስቃይ ሀቀኛ ሰውን አይጐዳም፣ የጭቆና ቀንበርም ከእውነት ጐን የቆመን ሰው ጨፍጭፎ አያጠፋውም፡፡ በግፍ የሚያሰቃዩት እጆችም የልቡን ሰላም ሊወስዱበት አይችሉም:: ሶቅራጦስ ከዕፅዋት የተቀመመውን _ መርዝ በፈገግታና በኩራት አልነበረም እንዴ የተጐነጨው? ጳውሎስ ለእውነት ብሎ በልበ ሙሉነት በድንጋይ አልተወገረምን?

አዎን፣ አንታዘዝም ስንል የሚጐዳንና ስንክድ የሚገድለን ውስጣችን ነው፡፡ ህሊናችንን ስንቃወመው ነው የሚጐዳን፤ ስንከዳውም _ ነው የሚፈርድብን፡፡

*

የዮሐና ወላጆች ብቸኛው ልጃቸው ከብቶቹ ተወስደውበት እንደታሰረ ሰሙ:: አሮጊቷ እናቱ በከዘራቸው ድጋፍ ወደ ገዳሙ መጡና ቄስ-ገበዙ እግር ላይ ተደፉ:: አይኖቻቸው በእንባ እየታጠበና የቄስ-ገበዙን እጆች እየሳሙም፣ ለልጃቸው እንዲያዝኑለትና ባለማወቅ _ ለፈፀመው ተግባር ምህረት እንዲያደርጉለት ተማፀኗቸው፡፡

ቄስ-ገበዘ ከዓለማዊ ጉዳዮች በላይ እንደሆኑ ሁሉ ዓይኖቻቸውን ወደ ሰማይ ሰቀሉና፣ «እኛ የልጅሽን ንግግር ይቅር ብለን ጅልነቱን በቸልታ ልናልፈው እንችላለን፡፡ ነገር ግን ገዳሙ መክፈል የሚገባውን ሂሣብ የመጠየቅ ቅዱስ መብት አለው:: እኛ ጨዋ በመሆናችን የሰዎችን ህግ የመተላለፍ ተግባር ይቅር ብንልም፣ ሃያሉ ነቢይ ኤልያስ ግን ወደ ወይን ተክሎቹ ውስጥ አልፈው የሚገቡትንና በመሬቱ ላይ እንስሶቻቸውን ለግጦሽ የሚያሰማሩትን በፍጹም ይቅር አይላቸውም፣ አይምራቸውምም!» አሉዋቸወ፡

አሮጊቷ እንባቸው በተጨማደደው ጉንጫቸው ላይ ቁልቁል እየወረደ፣ ገና እንባ በተሞሉም ዓይኖቻቸው ቄስ - ገበዙን ቀና ብለው ከተመለከቷቸው በኋላ ከአንገታቸው ላይ ትንሽ የብር ሃብላቸውን አውልቀው በቄስ - ገበዙ እጅ ላይ አስቀመጡ፡፡ «አባቴ ከዚህ ሀብል በስተቀር ምንም ነገር የለኝም፡፡ ያለኝ ውድ ንብረት ይሄ ብቻ ነው:: የሰርጌ ዕለት እናቴ የሰጠችኝ ስጦታ ነው፡፡ ምናልባት ገዳሙ ብቸኛው ልጄ ለፈፀመው ጥፋት ይሄንን እንደ ንስሀ ይቀበለኝ ይሆን?»

ቄስ-ገበዘ- ሀብሉን ኪሳቸው ውስጥ የከተቱት ጊዜ እናቲቱ ምስጋናቸውን እያዥጐደጐዱ የቄሱን እጅ መላልሰው መሳም ጀመሩ፡፡

ቄስ-ገበዙ ትክ ብለው ተመለከቷቸውና፣ «ለዚህ ሀጢያተኛ ትውልድ ወዮለት! የመፅሀፉን ትዕዛዛት በመቃወማቸው መራራውን ፍሬ እንዲጐነጩ ሆነዋል::


..........ይቀጥላል..........


👍👍👍👍👍👍👍👍
https://t.me/Asresee
https://t.me/Asresee
https://t.me/Asresee


Репост из: አስኳላ-💚💛❤️
በማፍቀርህ የምትደሰተው ያንተን ያህል የሚያፈቅርህ ሰው ስታገኝ ብቻ ነው ካልሆነ እድሜ ልክህን በትዝታ ስትሰቃይ መኖር አልያም ከፍቅር መራቅን መምረጥ ይኖርብሀል።

👇👇👇👇👇👇
@Asresee
@Asresee
@Asresee


እብዱ ዮሐና
....................ምዕራፍ ስምንት(8)



በሸለቆዎቹ ድንጋዮች ላይ ስለሚቀር ፀሀይ ስትወጣ፣ የእውነት ንጋት ስትነጋ፣ ወንጀሉን ይፋ ታወጣዋለች፡፡»

የዮሐና ንግግር የመነኮሳቱን ትኩረት የሚስብ ተዓምራዊ ኃይል ነበረው:: እናም በልባቸው ውስጥ ቁጣን ቀሰቀሰ:: በውስጣቸው የታመቀው ክፋትም ነፋስ ዘራ:: በፍርግርግ ብረት ሳጥን ውስጥ እንደተዘጋበት የተራበ አንበሳ ጥርሳቸውን እያንገጫገጩ በንዴት ተንቀጠቀጡ፡፡ አሁን ወጣቱን ለመቦጫጨቅ ትዕግስት አጥተው በመስገብገብ የሚጠባበቁት አለቃቸው ምልክት እስኪሰጧቸው ድረስ ነው፡፡

ዮሐና ንግግሩን ገታ አድርጐ ፀጥ ሲል በመሀል የተፈጠረው አጭር ዝምታ፣ አንድን ቦታ በአውሎ ነፋስ ከተመታ በኋላ ፀጥ ረጭ እንደሚለው ዓይነት አስፈሪ ፀጥታ ነበር:፡ ከዚያም ቄስ - ገበዙ ጮክ ብለው ትዕዛዝ

አስተላለፉ፦


አ .ል .ወ .ድ .ሽ .ም .እ .ን.ጂ!!!!!

አልወድሽም እንጂ እኔ ከወደድኩሽ
ያዩሽም አይኖሩ ይቅርና የነኩሽ::
አልወድሽም እንጂ ከወደድኩሽማ
አደባባይ ቆሜ ከመሃል ከተማ
በጂጉ በሚልቅ ከወፎቹ ዜማ
አዜምልሽ ነበር ህዝብ ሁሉ እንዲሰማ::

ያው እንደነገርኩሽ....
አልወድሽም እንጂ እኔ ከወደድኩሽ
ፅሀይ ትቆማለች ጨርቃም አትወጣም
ነፋሱም ፅጥ ይላል ብርዱም አይበረታም::
ወንዞችም አይፈሱም ቆመው ይሰማሉ
የፍቅራቸው ነገር ዕፁብ ነው እያሉ::
ከፍቅራችን በላይ እጅግ የሚገርመው
እኛ ስንጎዳ ህዝቡን ነው የሚያመው::

አልወድሽም እንጂ.....
እኔ ከወደድኩሽ
ያው እንደነገርኩሽ
አመት አንድ ቀን ነው በፊትሽ በፊቴ
ምድርም አንድ እርምጃ ላንቺ ና ኔ ኮቴ::
እኔማ ስወድሽ...
ሰማይ ትጠባለች በፍቅራችን ደስታ
እኛ ከፈለግን ቀን ይሆናል ማታ::
እምልልሻለሁ "አልወድሽም እንጂ ከወደድኩሽ ብዬ"
ደስ አሰኝሻለሁ ሰጎንን ቀድሜ አንበሳን ታግዬ::

እኔ ከወደድኩሽ.....
እየተራመድን ነፋስ እንቀድማለን
እየተናገርን ዓለት እንሰብራለን
ከደመና መሃል ደመና እንፈጥራለን ::
አትጠራጠሪ
አልወድሽም እንጂ የወደድኩሽ ዕለት
ብረት እና ሳት ነን አንቺ ና ኔ ማለት::
እሳት ና ብረት ግጥም እና ዜማ
ንጉስ እና ንግስት እግር እና ጫማ
አንድ መሆን ታውቂያለሽ አንድ መልክ አንድ ቀለም
እኔ አንችን ስወድሽ የሚመስለን የለም::

ግን....
እኔ ከማልኩልሽ በሚበልጥ መሃላ
ከምድራዊው ፍቅር ባይደለ በሌላ
አለት በሆነ ልብ በማይጎድል ተስፋ
በማይናድ ፅናት ቅፅበት በማይጠፋ
በውበትሽ ሰክረው ቅኔ እየዘረፉ
በነበልባል ፍቅርሽ ነደው እየጠፉ
የሚወዱሽ አሉ
እኔ ከወደድኩሽ ታዲያ እነዚህ ሰዎች ምንድን ይሆናሉ።

══✿❀♡❀✿═
👍👍👍👍👍
https://t.me/Asresee
https://t.me/Asresee
https://t.me/Asresee


እብዱ ዮሐና....
.................ምዕራፍ ሰባት (7)


በእኔና በቅድመ አያቶቼ የሰማውን፤ ፀሀይ ለሁላችንም እኩል ሳር ያበቀለችበትን ትንሽ የግጦሽ መሬት ረገጥክ ብላችሁ ህግን እንደ ጣለ ወንጀለኛ በግድ ይዛችሁኛል:: በኢየሱስ ስም ስለምናችሁና መከራና ስቃይን ባሳለፈባቸው በነዚህ የተቀደሱ ቀናት ስማፀናችሁ፣ የማያውቀውን ነገር እንደሚዘላብድ ሰው አላግጣችሁብኛል፡፡ እንግዲያውስ ይህን መፅሀፍ ከእኔ ወስዳችሁ እዩትና ኢየሱስ ይቅር ያላለበትን ጊዜ ካለ አሳዩኝ:: ያንን የመለኮታዊ ኃይል አሳዛኝ መከራ ታሪክ አንብቡትና እየሱስ በተራራ ላይም ሆነ በቤተ-መቅደስ ውስጥ ሲያስተምር ስለምህረትና ደግነት ያልተናገረበትን ቦታ ካለ ንገሩኝ፡፡ ይቅር ያላለበትን ጊዜ መቼ ነው? በተራራ ላይ ሲሰብክ ነውን? ወይስ ምስኪኗን ሴተኛ አዳሪ በወነጀሉት ሰዎች ፊት በቤት-መቅደስ ሲያስተምር ነው? ወይስ በጐሎጐታ መስቀሉ ላይ ተሰቅሎ መላውን የሰው ልጅ ለማቀፍ እጆቹን በሰፊው በዘረጋበት ጊዜ ነው?..

«እናንተ ልባችሁ የደደረ! እስቲ ወደ እነዚህ አነስተኛ ከተሞችና መንደሮች ለአፍታ ቁልቁል ተመልከቱ:: በደሳሳ ጐጆአቸው ውስጥ ታመው በአልጋቸው ላይ በጣር የሚሰቃዩ ህመምተኞችን እስኪ ለአፍታ ተመልከቱ፡፡ በጭቆና ቀንበር በግፍ ተጠቅተው እስር ቤት የሚማቅቁትን ተስፋ የቆረጡ እነዚያ ያልታደሉ ንፁሀን ሰዎችን እስኪ ተመልከቷቸው:: በደጃፎቻችሁ ላይ ልቦናቸው ተዋርዶና ሰውነታቸው ዝሎ እጃቸውን ለምዕዋት የሚዘረጉ ነዳያንን እስኪ ልብ ብላችሁ እዩዋቸው፡፡ እንግዶች (መንገደኞች) ማረፊያ አጥተው በየጐዳናው ላይ ተኝተዋል፡፡ በመቃብር ስፍራዎቻቸው ውስጥ ጋለሞቶችና የሙት ልጆች ያነባሉ ...

«እናንተ ግን በመስኩ ላይ የሚበቅሉ ፍራፍሬዎችን እየተመገባችሁና በወይን ዘላዎቹ እየተደሰታችሁ በስንፍናና በስራ-ፈትነት፣ ግን ደግሞ በድሎትና በተድላ ትኖራላችሁ:: እንደዚያም ሆኖ ህመምተኞችንና እስረኞቹን አትጠይቁም፣ የራባቸውን አታጐርሱም፣ በርሃብ እየተጠበሱ እንደ ባርያ የሚለፉ ተከታዮቻችሁን ዞር ብላችሁ አታዩም፣ ለእንግዶች ማረፊያ አትሰጡም፡፡ ያዘነትንም አታፅናኑም፡፡ ለአካለ-ስንኩላን ሀዘናችሁን ገልጻችሁ አታውቁም፡፡ ከቀደሙ አባቶቻችን የዘረፋችሁትና በኃይል የያዛችሁት አልበቃ ብላችሁ፤ አሁንም እፉኝት ጭንቅላቱን እንደሚያቀና ሁሉ እጆቻችሁን ዘርግታችሁ ባሏ የሞተባት ሴት ላቧን አንጠፋጥፋ ያፈራችውን ጥሪት፣ ገበሬው ልጆቹን በህይወት ለማቆየት ሲል በሽምግልና ዘመኑ ያከማቸውን ሀብት በእምነቱ አስፈራርታችሁ ትዘርፋላችሁ::>

ዮሐና በረዥሙ ተንፍሶ ትንፋሹን ካሰባሰበ በኋላ፣ ራሱን በኩራት ወደ ላይ አቅንቶ ረገብ ባለ ድምፅ ቀጠለ-

«እናንተ ብዙ ናችሁ፤ እኔ ግን ብቻዬን ስለሆንኩኝ የፈለጋችሁትን ልታደርጉኝ ትችላላችሁ:: አንዲት የበግ ግልገል በሌሊት ጨለማ በተኵላዎች እጅ ትወድቅ ይሆናል፡፡ ነገር ግን የደሟ ፍንጣቂ እስክ ንጋት ድረስ.....


.........ይቀጥላል..........


👍👍👍👍👍👍👍👍
https://t.me/Asresee
https://t.me/Asresee
https://t.me/Asresee


አሁን ላይ የገባኝ ነገር እድሜያችን እየጨመረ በሄደ ቁጥር ማውራት እየቀነስን እንደምንሄድ ነው....በቀላሉ አንስቅም ማገዶ እንፈጃለን....ብንስቅ እንኳን እንብዛም አይደለም....ድሮ ብዙ የማያመን እኮ ምን አልባት በቀላሉ ስለምናወራ እና ስለምንስቅ ቢሆንስ....ማደግ ደስ የሚል ነገር ቢሆንም ነገሮችን ማስተዋል ስንጀምር ማደጋችንን እንጠላዋለን....

ብር እንደሌለን አስበን አንጨነቅም ምክንያቱም ልጆች ነበርና....የሌላ ሰው ሀላፊነት ነበርን....

ትልቅ ስትባል በንግግርህ መገመት ስለሚመጣ መርጦ ማውራት ትጀምራለህ....እድገት ደስ ይላል እኮ...ግን ትቆጠባለህ.... የተመረጡ ቃላቶችን ጣል ስታደርግ ቃልህ ውድ ይሆናል...ትከበራለህ....ከመከበርህ ጀርባ ግሳንግስ አለ....ሀብት...ስልጣን...እውቀት...ኩራት....ብዙ ብዙ...

እመኑኝ የትልቅነት ቀመር ከልጅነት ይከብዳል....በሰው አይን ከመሙላት ምን አልባት mathes ትምህርት ላይ ያለችዋን X ማግኘት ይቀላል...😊





በፍቅር እደሩልኝ ቤተሰቦቼ❤️
👍👍👍👍👍👍👍👍
https://t.me/Asresee
https://t.me/Asresee
https://t.me/Asresee


ሳንፈቅድ ለጀመርነው ሳናውቀው ለሚያበቃ! ድንገት በሆነ ቅፅበት ለሚበጠስ ህይወት ለሚሉት ሰንሰለት! ላንቀዳደም ከመገፋፋት! ላንደርስ ከመከፋፋት! ለማይሞላ ዓለም! ለማይሰምር ኑረት! ከመበላላት

#ፍቅር አይበልጥም ወይ?

በራሳችን ለይ እንኳ የመወሰን ቅንጣት አቅም ለሌለን ከንቱዎች! ከቅፅበት ወዲያ ምን ሊፈጠር እንደሚችል እንኳን ለማናውቅ ብኩኖች! ምንሮጥለትን ዓለም! ምንደክምለትን! ነገር ሁሉ ጥለን ለምናሸልብ ደካሞች!

#ፍቅር አይሻለንም ወይ?

በዝች ጤዛ ዓለም ለይ
ከመበላላት መስማማት
ከመለያየት መዛመድ
ከመጠላላት መዋደድ
ከጥላቻ
ከክፋት
#ፍቅር አይበጅም ወይ?
#ፍቅር አይበልጥም ወይ?
....... እእእ,????


በፍቅር እደሩልኝ ቤተሰቦቼ💚💛❤
👍👍👍👍👍👍👍👍
https://t.me/Asresee
https://t.me/Asresee
https://t.me/Asresee


እብዱ ዮሐና...

..........ምዕራፍ ስድስት (6)


ዮሐና ለጥቂት ጊዜ ፀጥ ብሎ ቆየ፡፡ ዓይኖቹ ብርሃን አንፀባረቁ፡፡ የፊቱ ገፅታም ፈካ:: ፍርሃትና አድርባይነት ከልቡ በነው የጠፉ ይመስል አቋሙም ከመማፀንና ከመለማመጥ ወደ ጥንካሬና ብርታት ተቀየረ፡፡ አንገቱን ቀና አድርጐ በድፍረት ቄስ ገበዙን እየተመለከተ ሲናገር፣ በድምፁ ውስጥ ዕውቀትና የወጣትነት ዘመን ቁርጠኝነት ይደመጥ ነበር-

«ደሀው የዕለት ጉርሱን የሚያገኝበትንና ህይወቱን የሚያቆይበትን የእርሻ መሬቱ፣ በወርቅና በብር የተሞላውን የገዳሙን ሳጥን የበለጠ ለማጨናነቅ ሲል መሸጥ ይገባዋልን? የተራቡት እንስሳት ባለማወቃቸው ያጠፉትን ጥፋት ቅዱስ ኤልያስ ይቅር ይላቸው ዘንድ ድሆች የበለጠ መደህየት፣ ምስኪኖችም በጠና ረሀብ ተሰቃይተው መሞት አለባቸውን?»

ቄስ-ገበዙ ጅንን እያሉ ራሳቸውን በአዎንታ ነቀነቁ፡፡ «እየሱስ ክርስቶስ በቅዱስ መጽሐፉ፣ ብሏል» አሉት ዓይኖቻቸውን ወደ ስማይ አቅንተው፡፡

ዮሐና ይህንን ሲሰማ በንዴት ጦፈ፡፡ ከንዴቱ ብዛት ልቡ በፍጥነት መምታት ጀመረች:: በመንፈስ ያደገ፣ ክብሩ የጨመረ፣ የረገጠው መሬት እንኳን ከፍ፣ ከፍ ያለ ያህል መስሎ ተሰማው፡፡ ጦረኛ ከጠላቱ ጋር ፊት ለፊት የተጋፈጠ ጊዜ ራሱን ለመከላከል ሲል ጐራዴውን እንደሚመዝ ሁሉ፣ እሱም ከልብሱ ስር ደብቆ ይዞት የነበረውን መጽሐፍ ቅዱሱን መዝርጦ አወጣና ድምጹን ከፍ አድርጐ በጩኸት፣ «እናንተ ግብዞች!» ሲል መናገር ጀመረ:: «እናንተ ግብዞች! በዚህ መጽሐፍ ውስጥ ያሉትን የክርስቶስ መልካም ትምህርቶች የምታጣምሟቸው እንዲህ እያረጋችሁ ነው፡፡ በዚህ መጽሐፍ ላይ እያላገጣችሁ ነው፡፡ የእናንተን እርኩስ ተግባርና ክፋት ለማስፋፋት ስትሉም ይህንን በህይወት ውስጥ ከሁሉ በላቀ የተቀደሰውን ትልቁን መጽሐፍ እየተጠቀማችሁበት ነው:: የእግዚአብሄር ልጅ ክርስቶስ ዳግም ተመልሶ መጥቶ ገዳሞቻችሁን ያወደመ፣ ፍርስራሹንም ወደ ሸለቆዎቹ የበተነ፣ እንዲሁም የተቀደሱ ሥፍራዎችንና መሰዊያዎችን በእሳት አጋይቶ አመድ ያደረጋቸው ጊዜ ወዮላችሁ! ከፍተኛ ቁጣ አርፎባችሁ የኢየሱስ የፈሰሰ ንፁህ ደምና የእናቱ የሀዘን ዕንባ እንደ ጐርፍ አጥለቅልቀው ቁልቁል ወደ እንጦሮጦስ የወረወሯችሁ ጊዜ ወዮ!___ በምትሳሉላቸው ጣኦቶቻችሁ ፊት በግንባራችሁ ተደፍታችሁ ለምትሰግዱ፣ በጥቁር ልብሶቻችሁ ስር የተግባራቶቻችሁን ጥቁርነት ለምትሸሽጉ እናንተ ወዮ!-- ከናፍሮቻችሁን ለፀሎት ብታንቀሳቅሱም፣ ነፍሳችሁ እግዚአብሄር አምላካችሁ ላይ ላመፀው፣ ልባችሁን በስጋዊ ፍላጐት ተሞልቶ እንደ አለት ለደደረው የክርስቶስ _ ጠላቶች ወዮላችሁ!---በአካል ከመሰዊያው ፊት በጨዋ ደንብ ለይምሰል ለምትንበረከኩ፣ መንፈሳችሁ ግን ከእግዚአብሄር ጋር ለሚፋለመው ለእናንተ ወዮ!........


..........ይቀጥላል............


👍👍👍👍👍👍👍👍
https://t.me/Asresee
https://t.me/Asresee
https://t.me/Asresee


.....እብዱ ዮሐና

   .     ምዕራፍ አምስት(5)


ከጉልበቴ ጥንካሬና ከእነዚህ እንስሳት በስተቀር ምንም ነገር የሌለኝ ደሀ ነኝ፡፡ እባካችሁ ከብቶቼን ልቀቁልኝ? በድጋሚ እዚህ ግድም እንደማልመጣ ቃል እገባለሁ» ሲል ተማፀናቸው፡፡ ይዣቸው

ቄስ-ገበዙ በአንድ እርምጃ ወደ እሱ ቀረቡና እጃቸውን ወደ ሰማይ ከፍ አድርገው፣ ‹‹እኛን እዚህ ቦታ ያስቀመጠን እግዚአብሄር ነው፡፡ ይህንንም የተቀደሰ መሬት እንድንጠብቅ መርጦናል፡፡ ይህ መሬት የታላቁ የቅዱስ ኤልያስ ሰፊ መሬት ነው፡፡ በመሆኑም በቻልነው መንገድ፣ ባለን አቅም ሁሉ ሌት ተቀን ልንጠብቀው ግድ ነው፡፡ ድንበሩን አልፎ ወደዚህ የተቀደሰ መሬት የተጠጋ ሁሉ በእሳቱ ይቃጠላል፡፡ የጥፋቱን ዋጋ ለገዳሙ ለመክፈል እምቢ ብትል ሳሩ በእንስሳቱ ሆድ ውስጥ እንዳለ ወደ መርዝነት ተቀይሮ ያጠፋቸዋል፡፡ የተጠየቅከውን እያንዳንዱን ፊልስ (ሽራፊ ሳንቲም) እስከ ምትከፍል ድረስ ከብቶቹን እዚህ በእኛ ግርግም ውስጥ ይቆያሉ፡፡ ምንም ማምለጫ መንገድ የለህም» አሉት፡፡

ቄሱ ሊሄዱ ሲል ዮሐና ካባቸውን ይዞ አስቆማቸውና በትህትና ይለምናቸው ገባ፡፡ «ጌታዬ፣ እየሱስ በተሰቃየባቸውና ማርያም በሀዘን ባለቀሰችበት በእነዚህ በተቀደሱ ቀናት እማፀንዎታለሁ፡፡ እባክዎትን ከብቶቹን ይልቀቁልኝና ልሂድ፡፡ በክርስቶስ ስም ልብዎ አይጨክንብኝ፡፡ እኔ ቤሳቤስቲ የሌለኝ ደሀ ነኝ፡፡ ገዳሙ ግን ሀብታምና በርካታ ንብረት (ወርቅና ብር) ያለው ነው፡፡ እባክዎ ይዘኑልኝ፡፡ የእኔን እጅ ለሚጠብቁት ለድህና በዕድሜ ለገፉ ወላጆቼ እዘኑላቸው፡፡ ጥፋት አጥፋቼ እናንተን ካስቀየምኩ እግዚአብሄር ይቅር ይለኛል፡፡»

ቄስ-ገበዙ በፌዝ ተመለከቱት፡፡ «ገዳሙ ግን ይቅርታ አያደርግልህም፡፡ አንዷን ሽራፊ ሳንቲም እንኳን አይምርህም፡፡ ያለብህን ዕዳ በሙሉ መክፈል አለብህ፡፡ ደንቆሮ! ሀብታምም ሆንክ ደሀ ጉዳዬ አይደለም፡፡ ደግሞስ አንተ ማን ነህና ነው በቅዱሳን ነገሮች የምትማፀነኝ? ምስጢራቸውን እና የተደበቁ ነገሮችን የምናውቀው እኛ ብቻ ነን፡፡ ከብቶቹን ነፃ የሚወጡት ላወደሙት እርሻ በአጠቃላይ ሶስት ዲናር ከከፈልክ ብቻ ነው፡፡»

‹‹አባቴ፣ ምንም የለኝም፡፡ ሰባራ ሳንቲም እንኳን የለኝም፡፡ እባክዎ አባቴ፣ ከፊትዎ ቆሞ ለሚማፀንዎ ለምስኪኑ እረኛ ይራሩለት:: ችግሬንም ይረዱልኝ ሲል ዮሐና በታፈነ ድምፅ ለመናቸው፡፡

ቄሱ ረጅም ፂማቸውን በጣቶቻቸው እያሻሹ፣ «እንግዲያውስ ሂድና ከፊሉን የእርሻ መሬትህን ሸጠህ ሶስት ዲናር ይዘህ ተመለስ አሉ፡፡ «ከዚህ ከተቀደሰው መሰዊያው ፊት በግድ የለሽነት ስትከራከር ቅዱስ ኤልያስን አስቆጥተህ በዘላለማዊ እሳት ትቃጠል ዘንድ ወደ ሲኦል ከምትወረወር የእርሻ መሬት ላይኖርህ መንግስተ ሰማያት ብትገባ ይሻላል።»

ሌሎቹ መነኮሳትም በመስማማት ጭንቅላታቸውን ነቀነቁ፡፡


       .........  ይቀጥላል ...


👍👍👍👍👍👍👍👍
https://t.me/Asresee
https://t.me/Asresee
https://t.me/Asresee


.....እብዱ ዮሐና
   ምዕራፍ  አራት(4)


ዮሐና የእግዚአብሄር ልጅ አካል ላይ በደረሰው ስቃይ አብሮት ሲሰቃይ፣ እንዲሁም በመንፈስ አብሮት በደስታ ሲሞላ | ሰዓታት አለፉ:: ከተቀመጠበት ቦታ ሲነሳ እኩለቀን ሆኖ ነበር፡፡ ፀሀይዋ አሁን አናት ትበሳለች፡፡

ዙርያውን ተመለከተ፡፡ ነገር ግን ከብቶቹን ማየት አልቻለም፡፡ በዚያ ለጥ ባለ የለምለም ሳር ሜዳ ላይ እንዴት ከዓይኑ ሊሰወሩ እንደቻሉ ግራ ተጋብቶ በየቦታው ፈለጋቸው:: ከመስኮቹ ባሻገር እንደ እጅ መዳፍ መስመሮች ከሚጥመዘመዘው ጐዳና አጠገብ ሲደርስ ከርቀት ጥቁር ልብስ የለበሰ አንድ ሰው በአትክልት ስፍራዎቹ መሀል ቆሞ አየ፡፡ በጥድፊያ ወደ ሰውየው አመራ።

ወደ ሰውየው ቀርቦ ሲመለከት፣ ከገዳሙ መነኮሳት አንዱ መሆናቸውን አወቀ፡፡ ዮሐና ጐንበስ ብሎ እጅ ከነሳ በኋላ፣ ከብቶቹን በዚያ የአትክልት ሥፍራ ውስጥ አይተው እንደሆነ ጠየቃቸው፡፡

መነኩሴው ንዴታቸውን ለመቆጣጠር እየሞከሩ ትክ ብለው አዩትና በኃይለ ቃል «አዎን አይቻቸዋለሁ፡፡ እዚያ ማዶ ናቸው፡፡ ና ተከተለኝ፡፡ የት እንደሚገኙ አሳይሃለሁ» አሉት፡፡

ዮሐና መነኩሴውን እስከ ገዳሙ ድረስ ተከተላቸው፡፡ በገዳሙ ውስጥ ከብቶቹን በአንድ ሰፊ ግርግም ውስጥ በጠፈር ታስረው በአንድ ሌላ መነኩሴ ሲጠበቁ አያቸው፡፡ መነኩሴው እንስሳቱ በተንቀሳቀሱ ቁጥር የሚመልሱበትና የሚዥሉጥበት ትልቅ ዱላ ይዘዋል፡፡ ዮሐና ከብቶቹን ለመውሰድ ወደዚያ ሲጠጋ መነኩሴው ካባውን ጨምድደው በመያዝ ፊታቸውን ወደ ገዳሙ ደጃፍ አዞሩና በጩኸት «ወንጀለኛው ልጅ ይኸውና! ይዤዋለሁ» አሉ፡፡

በጩኸታቸው የተነሳ ቄሶችና መነኩሳት ከተለያየ ማዕዘን እየሮጡ ብቅ፣ ብቅ አሉ። ከተቀሩት ባልደረቦቻቸው በለበሱት ምርጥ ልብስና በመራራ ባህሪያቸው የሚለዩት ቄስ-ገበዝ ከፊት ሆነው ይመሯቸዋል፡፡ የዘረፉትን ምርኮ ለመቀራመት እንደሚረባረቡ ወታደሮች ዮሐናን ከበቡት፡፡

በዚህ ጊዜ ዮሐና ቄስ-ገበዙን እየተመለከተ ረጋ ብሎ፣ «ወንጀለኛ ያላችሁኝ ለምንድ ነው? ለምንስ ያዛችሁኝ? እንደ ወንጀለኛ የምታይበት ምንም የፈፀምኩት ስህተት የለም» አላቸው፡፡

የቄሶቹ የበላይ እንደ መጋዝ በሚገዘግዝ ድምፅ፣ «ከብቶችህ የገዳሙ ንብረት በሆነ መስክ ላይ ሳር እንዲግጡ አድርገሃል» አሉት:: ከብቶቹ ተክሎቻችንን ተነጣጥሰው አበላሽተውታል፡፡ የወይን እርሻችንንም አውድመ ውታል፡፡ የያዝናቸውም በከብቶቹ ለደረሰው ጥፋት ኃላፊ በሆነው እረኛ ምትክ ነው፡፡›› ሲናገሩ ፊታቸው ላይ የሚታየው ንዴት ጨመረ።

«አባቴ ...» አለ ዮሐና፣ በሚያስተባብል ድምጽ። ግን እኮ ከብቶቹ

ምንም የማያውቁና መናገር የማይችሉ ፍጡራን ናቸው፡፡ እኔም ብሆን......


.............ይቀጥላል ...........


👍👍👍👍👍👍👍👍
https://t.me/Asresee
https://t.me/Asresee
https://t.me/Asresee

Показано 20 последних публикаций.