Фильтр публикаций


መጋቢት 02/2017
የጤና ሚኒስቴር ለቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ማስተማሪያ ሆስፒታል ከ 5 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት የህክምና ቁሳቁስ በእርዳታ መልክ ሰጠ፡፡
*******
የማስተማሪያ ሆስፒታሉን የጤና አገልግሎት ሥራን ለመደገፍና ደረጃዉን ለማሻሻል ከጤና ሚኒስቴር ጋር በቅርበት ሲሰራ የቆየ መሆኑን በርክክቡ ወቅት የተገኙት የቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ በም/ፕሬዝዳንት ማዕረግ የጤና ኢንስቲትዩት ቺፍ ኤክስኪዩቲቭ ዳይሬክተር ዶ/ር ሳፋይ ኤለማ ገልጾዋል፡፡

አያይዘዉም ዶ/ር ሳፋይ በድጋፍ መልኩ የተሰጡ ቁሳቁሶች በአሁኑ ሰዓት ለሆስፒታሉ በጣም አስፈላጊና እጥረት የሚታይባቸዉ ቁሳቁሶች መሆናቸዉን በመጥቀስ ለተደረገዉ ድጋፍም ምስጋናቸዉን አቅርቧል፡፡

የህክምና ቁሳቁሶቹ ድጋፍ የተደረጉት በጤና ሚኒስቴር አማካኝነት በኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ ድርጅት በኩል ሲሆን የቀረቡ ቁሳቁሶችም Warmer-radiant infant, Refrigerator- Blood Bank, phototherapy ,Couch Examination Adult ,Couch Delivery ,Bed-patient adult ,Unesthesia Machine እና የመሳሰሉት ቁሳቁሶች መሆናቸዉን ከመረካከቢያ ሰነዱ ላይ ያገኘነዉ መረጃ ያመላክታል፡፡


አሬሮ የካቲት 30/2017 ዓ.ም (ቡሌ ሆራ ዩኒቨርስቲ)
ከቡሌ ሆራ ዩኒሸርሲቲ የተወጣጡ የልኳን ቡድን በ72ተኛው የቦረና ባሊ ስልጣን ሽግግር ላይ ተገኙ።
********
በገዳ እና ባህል ጥናት ኢንስቲትዩት የሚመራዉ የልኳን ቡድን ከስረዓቱ አንድ ቀን በፊት በአሬሮ ወረዳ አረዳ ጅላ በዳሳ በመገኘት በ72ተኛዉ የቦረና ባሊ ርክክብ ላይ ታድመዋል።

የስልጣን ርክክቡ ከፋላሳ ጎጌሳ አባ ገዳ ኩራ ጃርሶ ኩራ ወደ መርዲዳ ጎጌሳ አባ ገዳ ጉዮ ቦሩ ጉዮ ሰላማዊ በሆነ መንገድ የስልጣን ርክክቡ ተከናዉነዋል። በስርዓቱ ላይ ከሀገር ውስጥ እና ከዉጭ ሀገር ትላልቅ የመንግስት ባለስልጣናት ፣የኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት ፕረዘዳንት አቶ ሽመልስ አብዲሳ ፣ ታዋቂ ሙዚቀኞች ፣ አባ ገዳዎች እና ሌሎች ታዳሚዎች የተሳተፋ ሲሆን ፣ ስረዓቱ በደማቅ ሁኔታ ተከናዉነዋል።

በስረዓቱ ላይም የገዳ የእርከን ደረጃ የሚያሳዩ ደበሌዎች፣ ትንሹ ጋሜ፣ ትልቁ ጋሜ፣ ኩሳ፣ ራባ ፣ዶሪ ፣ገዳ ፣ዩባ1ኛ እስከ ዩባ 3ተኛ እንዲሁም ገደሞጂ ጭምር ተገኘተዋል።በተጨማሪም የተለያዩ የባህላዊ መገልገያ መሳሪያዎች፣ የባህላዊ አለባበስ እና ባህላዊ ገልማዎች በመዘጋጀት ለእይታ ለታዳሚዎች ቀርበዋል።

የቡሌ ሆራ ዩኒሸርሲቲ







Показано 5 последних публикаций.