👉በአዲስ አበባ 1.5 ሚሊዮን የቤት እጥረት መኖሩ ተነገረ
📌አልሚዎች በየአመቱ 200 እና ከዚያ በላይ ቤቶች እየገነቡ የከተማዋ የቤት ችግር መቅረፍ አይቻልም ተብሏል በመሆኑም ባለሀብቶች በቤት ልማት ላይ ትኩረት እንዲያደርጉ የከተማ አስተዳደሩ ጠይቋል።
✳️በቤት ልማት መሰማራት ለሚፈልጉ ባለሀብቶች ከተማ አስተዳደሩ ማበረታቻ እንደሚያደርግም አስታውቋል።
❇️የአዲስ አበባ ከተማ የኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ ግርማ ሰይፊ እንደተናገሩት በከተማው ያለው የቤት ፍላጎት እና አቅርቦቱ የተመጣጠነ አይደለም ብለዋል።
❇️ከተማዋ በልማት ምክንያት በርካታ ቤቶች በልማት እያፈረሰች ከመሆኑ ጋር በተያያዘም የቤት ፍላጎቱ እየጨመረ እንደሚገኝ ተናግረዋል።
❇️ከፍተኛ ፍላጎት የሚታይበት የቤት ችግር ለመቅረፍ ከተማ አስተዳደሩ የተለያዩ አማራጮች እያቀረበ ይገኛልም ብለዋል።
🚧የሪልዕስቴት አልሚዎች በአመት 200 እና ከዚያ በላይ ቤት እየሰሩ የከተማው የቤት ፍላጎት ማሟላት አይቻልም ሲሉም ተናግረዋል።
⏺ባለሀብቶች ከሪል ዕስቴት ከፍ ብለው በቤት ልማት ውስጥ ትኩረት አድርገው እንዲሰሩ ጠይቀዋል።
⏺ከዚህ በፊት በዘርፉ የነበሩ ማነቆዎች ከተማ አስተዳደሩ እየቀረፈ እንደሚገኝ የተናገሩት ኮሚሽነር ግርማ ባለሀብቶች ዕድሉን መጠቀም አለባቸው ብለዋል።
✳️ኮሚሽነሩ ይህንን ያሉት በቤት ልማት ዘርፍ ላይ የተሰማራው ዋልያ ሆምስ ባዘጋጀው መድረክ ነው።
🚧ዋልያ ሆምስ በአዲስ አበባ በተለያዩ ቦታዎች የገነባቸው ቤቶች በተመለከተ የማስተዋወቂያ ዝግጅት አድርጓል።
🔰ኩባኒያው ኡቡንቱ ዴሉክስ አፓርትመንት እና አጃንባ ቪላስ የተሰኙ ሁለት ፕሮጀክቶቹ ለዘርፉ ተዋናዮች እና ለመንግስት ሀላፊዎች አስተዋዉቋል።
🚧የዋልያ ሆምስ አፓርትመንቶች የሚገኙት በላንቻና በቅሎ ቤት አካባቢ መሆኑ ተነግሯል።
@etconp