ሰበር ዜና!! በቋሪት ወረዳ ሶስቱ ነበልባል ብርጌዶች ማለትም ..‼️‼️1ኛ. በሻለቃ የኔዓለም ዘለቀ በቀጥታ የተመራው በገረመው እንዳወቅ ብርጌድ
2ኛ.በሻለቃ ዝናቡ ልንገረው በቀጥታ የተመራው በደጋዳሞት ብርጌድ
3ኛ. በኢንጂነር ማንችሎት በቀጥታ የተመራው በጣና ብርጌድ …… በጋራ በመሆን በተሰራ ኦፕሬሽን እጅግ አስደናቂ ድሎች ተመዝግበዋል።
በዚህም በቋሪት ወረዳ መሽጎ ከነበረው 59ኛ ክፍለጦር አመራሮች ውስጥ ሶስቱ መደምሰሳቸው ታወቀ።
1ኛ. ኮለኔል ሙሀመድ
2ኛ. ሻንበል ደረጀ
3ኛ. ገና የስም መረጃው እጃችን ያልደረሰ አንድ ሻምበል ይገኝበታል።
በዚህ ውጊያ 175 አባላት ያሉት 2ተኛ ሻለቃ ጦር የተሳተፈ ሲሆን ነገር ግን በነበልባል ፋኖዎቻችን ተደምስሶ የአመራሮቹን አስከሬን በሄሊኮፕተር ይዞ መሄዱ ታውቋል። በዚህ ውጊያ ሌሎች በርካታ መቶ አለቆች እና የጋንታ መሪዎች መደምሰሳቸውም ተነግሯል።
የወታደሮቹን በድን ለመሰብሰብ የመጣችው 5ኛ ሻለቃም ከባድ ምት ሲያርፍባት ለመመለስ መገደዷ ታውቋል። ከወገን በኩል ቀላል የመቁሰሰል አደጋ ያጋጠመ ሲሆን የተሰዋ ግን እንደሌለ ምንጮች ገልጸዋል።
@B