EOTC ቤተ መጻሕፍት


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: не указана


ይህ Channel የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ያን የሆኑ ቅዱሳት መጻሕፍት፤ ስብከትች እንዲሁም የተለያዩ ለአብነት ትምህርት የሚሆኑ በድምፅ ፤ይሁን በጹሁፍ እንዲሁም በ Video ሚለቀቅበት Channl new
ተጨማሪ ወይም ሚፈልጉትን መፃህፍት
ብለው ይጠይቁን
ማስታወቂያም እንሰራለን በውስጥ መስመር ይጠይቁን
የሰማነዉን እንናገራለን!
ያየነዉን እንመሰክራለን!

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
не указана
Статистика
Фильтр публикаций


Репост из: ተ҈ ዋ҈ ህ҈ ዶ҈
🔔✝ ከመምህራን የማንን ትምህርት ማግኘት ይፈልጋሉ?👇

┏━━━━━━━━━━━━━━┓
🔔 መምህር ምሕረተአብ አሰፋ
┗━━━━━━━━━━━━━━┛
┏━━━━━━━━━━━━━━┓
🔔 መምህር ዘበነ ለማ
┗━━━━━━━━━━━━━━┛
┏━━━━━━━━━━━━━━┓
🔔 መምህር ሄኖክ ኃይሌ
┗━━━━━━━━━━━━━━┛
┏━━━━━━━━━━━━━━┓
🔔 መምህር ዮርዳኖስ አበበ
┗━━━━━━━━━━━━━━┛
┏━━━━━━━━━━━━━━┓
🔔 አባ ገብረ ኪዳን
┗━━━━━━━━━━━━━━┛
┏━━━━━━━━━━━━━━┓
🔔 መምህር ያረጋል አበጋዝ
┗━━━━━━━━━━━━━━┛
┏━━━━━━━━━━━━━━┓
🔔መጋቢ ሐዲስ እሸቱ አለማየሁ
┗━━━━━━━━━━━━━━┛
┏━━━━━━━━━━━━━━┓
🔔 መምህር እዮብ ይመኑ
┗━━━━━━━━━━━━━━┛
┏━━━━━━━━━━━━━━┓
🔔መምህር ገብረ እግዚአብሔር
┗━━━━━━━━━━━━━━┛
┏━━━━━━━━━━━━━━┓
🔔መምህር አባ ገብረ ኪዳን
┗━━━━━━━━━━━━━━┛

🔗የሁሉንም መምህራን ትምህርት ለማግኘት🔔
🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧


እግዚአብሔር ለምን ዝም ይላል?
             
Size:-82.9MB
Length:-1:38:35

    በርእሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማ

@kendilebirihan
@kendilebirihan
@kendilebirihan


እንደ ሁኔታው ለብቻው ልመለስበት እችላለሁ) በጣም የተለያዩ ሀሳቦች ናቸው። እንዲህ ያለው ችግር ቀደም ብሎም የነበረ ችግር ነው። ስለዚህ አሁንም ለመርታት በሚፈልግ ልቡና ውስጥ ሆኖ ጥቅሶችን ከዐውዳቸው ነጥሎ አውጥቶ መጠቀም ችግርን ያባብስ እንደሆን እንጂ መፍትሔ ሊሆን አይችልምና ከዚህም መጠበቅ ተገቢ ነው።

4) ከመጠራጠር አለመጀመር

መና/ፍቃን ሀሳብ እና ጥያቄ ሲያነሱ የእነርሱን አመክንዮ እና ፍረጃ ሰምቶ ነባር ትምህርቶችን ወይም ምንጮቻችን ከመጠራጠር መጀመር በጣም አደገኛ ነገር ነው። ለምሳሌ ሳጥናኤል እኔ ፈጠርኳችሁ ባለ ጊዜ በጥርጥር የጀመሩት እውነት በተገለጠ ጊዜ ከእርሱ ጋር አብረው ወድቀው የሚያስቱ መናፍስት ሆኑ እንጂ ሲመለሱ አላየናቸውም። እውነቱን ባያውቁም በያለንበት እንቁም ባለው በቅዱስ ገብር ኤል ቃል ጥርጥሩን ሳያስገቡ የጸኑት ግ ን በኋላ እግዚአብሔር እውነቱን ገልጾላቸዋል። ይህ የመጀመሪያው የፍጥረት ፈተና የሚያስረዳን ከመጠራጠር መጀመር ምን ያህል አደገኛ መሆኑን ብቻ ሳይሆን መንገዱ ዲያብሎሳዊ መሆኑን ነው። በሳይንስ ከመጠራጠር መጀመር ወደ ዕውቀት ይወስዳል ከሚባለው በተቃራኒ በሃይማኖት በመጠራጠር አለመጀመር መሠረታዊ ጉዳይ ሆኖ እናገኘዋለን ማለት ነው።

በዚሁ መንገድ ካየን አንዳንድ የግእዝ ምንጮቻችን ከሌላ ሀገር ምንጮች ስናነጻጽር በቀጥታ ላይገጥሙልን ይችላሉ። ለምሳሌ ያህል ገድለ ጊዮርጊስን ስንመለከት ሰማዕቱን ያሰቃየውን ንጉሥ ዱድያኖስ ይለዋል። በሌላው ሀገር ግን ያሉት ምንጮች በሙሉ ደግሞ ንጉሡን ዲዮቅልጥያኖስ ይሉታል። ይህ በመሆኑ የእኛ ምንጭ ስሐተት ነው ልንል አንችልም። እኔ እንኳ በአቅሜ በአደረግሁት ፍለጋ አንድ ጥናት ላይ የጥንት ምንጮች ዱድያኖስ ይሉ እንደነበር አግኝቻለሁ። ስለዚህ ይህ ስም ምንጫችን ስሐተት መሆኑን ሳይሆን ምንጫችንን ወይም አቀባይ ቋንቋችንን እንድንመረምር እና የእኛ ቅጂ ከቀዳማውያን ምንጮች መሆኑን ይጠቁማል እንጂ ልዩ መሆኑ ስሕተት መሆኑን ሊያሳይ አይችልም ማለት ነው።

በገድለ ተክለ ሃይማኖት ላይ ያለው የሞቱበትን በሽታ እንደመስቀሌ እቆጥርልሃለሁ የሚለውን ሀሳብ ስሑታኑ ባነሡበት መንገድ ተመልክቶ ከመጠራጠር ከመጀመር ወደ ገድሉ ጠልቆ ገብቶ ምክንያቱን ከማጥናት መጀመር ከብዙ በሽታ ይፈውሳል። በዚሁ ጉዳይ ላይ ገድሉን ስንመለከት አቡነ ተክለ ሃይማኖት ትልቁ ፍላጎታቸው የደም ሰማዕትነትን ማግኘት ነበር። ዘመኑ ደግሞ ያንን አልፈቀደላቸውም። ስለዚህ ጌታ በበሽታ የገጠማቸውን ተጋድሎ እንደ ሰማዕትነት ወይም መስቀል እንደሚቆጥርላቸው ቃልኪዳን ገባላቸው ይላል እንጂ መና/ፍቃኑ የሚሉትን ወይም ሊሉ የሚፈልጉትን ገድሉ በፍጹም አይልም።

በገድለ ቅዱሳንና በገድለ ቅዱሳን መጽሐፍ መካከል ልዩነት እንኳ ቢኖር ወደ ቀዳማይ ምንጭ በሚደረግ ጥናት ይስተካከላል እንጂ ገድለ ቅዱሳንን ወደ መጠራጠር ሊወስድ አይችልም። በርግጥ የሰው አእምሮ ውሱን ስለሆነ ለእንዲህ ያለ ፈተና ተደጋግሞ ሊወድቅ ይችላል። እንዲህ ያሉትን ነገሮች ደግሞ መጽሐፍ ቅዱስም ያስረዳል። ለምሳሌ ያህል በሰማርያ እጅ ከባድ ረሀብ ተነሥቶ ሁለት ሴቶች ልጆቻቸውን ቀቅለው ለመብላት ከተስማሙና የአንዲቱን ከበሉ በኋላ ሁለተኛ ልጇን ስትደብቅ በተፈጠረው ክርክር ንጉሡ ስሞቶ በኤልሣዕ ላይ ተቆጥቶ ነበር። በኋላ ላይ ግን “የእግዚአብሔርን ቃል ስሙ፤ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ ነገ በዚህ ጊዜ በሰማርያ በር አንድ መስፈሪያ መልካም ዱቄት በአንድ ሰቅል፥ ሁለትም መስፈሪያ ገብስ በአንድ ሰቅል ይሸመታል አለ። ንጉሡም በእጁ ተደግፎ የነበረ አለቃ ለእግዚአብሔር ሰው መልሶ፦ እነሆ፥ እግዚአብሔር በሰማይ መስኮቶች ቢያደርግ ይህ ነገር ይሆናልን? አለው። እርሱም፦ እነሆ፥ በዓይኖችህ ታየዋለህ፥ ከዚያም አትቀምስም አለ” /2ኛ ነገ 7/ ተብሎ እንደተጻፈ ንጉሡ በመጠራጠሩ ምክንያት በሕይወቱ እንዲቀጣ ሆኗል። ስለዚህ ከመጠራጠር መጀመር ውጤቱ አደገኛ መሆኑን መረዳት እና በእምነት ጸንቶ የማያውቁትን ለማውቅ መጣር ተገቢነት ይኖረዋል ማለት ነው። ለዛሬው በእነዚሁ ልፈጸም። ወስብሐት ለእግዚአብሔር፤ አሜን

©ዲያቆን ብርሀኑ አድማስ
@EotcLibilery
@EotcLibilery
@EotcLibilery


ስለ ሃይማኖታዊ ውይይት አንዳንድ ነገሮች

ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ በማኅበራዊ ሚዲያው ሃይማኖታዊ ክርክሮች በረከት እያሉ መጥተዋል። እነርሱን ተከትሎ ደግሞ በአንድ ቤት ውስጥ ባሉትም መካከል ውይይቶች አለፍ ሲልም መነቃቀፎች አንዳንድ ጊዜም ደግሞ በእወቀትም ይሁን ያለዕውቀት መጠላለፍ የሚመስሉ ሁኔታዎች እንዳሉ ይታያል። በእንዲህ ያለው ጊዜ ማድረግ የሚገባን ምንድን ነው የሚሉ ድምፆችም ይሰማሉ። የምናደርገው ነገር በዚህ ጊዜ በዚያ ጊዜ የሚባልበት መሆኑ ባይቀርም በእኔ እምነት በአግባቡ ከተጠቀምንበት እና ከተማርንበት ከሁሉም ልንጠቀም እና መንገዳችንን ትክክል የሆነልን እርሱኑ ልናጸና ፈንገጥ ያልነው ወይም የመንገድ ጠርዝ በመርገጥ የተንሸራተትን ካለንም ልንመለስ እና በመሐል መንገድ እንድንጓዝ ሊጠቅመን ይችላል። እጅግ በትንሹ ከሰማኋቸው ተነሥቼ አጠቃላይ መርሕ ተኮር ሁኔታዎች በዚህ ጽሑፍ ልጠቁምና እንዳስፈላጊነቱ ደግሞ በመከራከሪያ ነጥቦቹም ላይ ላክል እችላለሁ። ከዚህ በፊት “አድማሱ ጀንበሬ ሕይወቱ እና ትምህርቱ” የሚለው መጽሐፍ ሲታተም በመቅድምነት የወጣ አጭር ጽሑፍ ላይ ከንባቦቼ ከቀራረምኩት የተወሰኑ ሀሳቦችን ማጋራቴ ይታወቃል። እነዚያን ያላየ ቢያያቸው አንድ ነገር እንኳ የሚጠቅም ሊያገኝ ይችላል ብዬ አምናለሁ። እነዚያን ያነሣሁበት ምክንያት ግን እነዚህን ጉዳዮች የእነዚያ ቀጣይ አድርጋችሁ እንድትወስዷቸው ለማሳሰብ ያህል ነው።

በውይይትም ሆነ በክርክር ውስጥ ያለን አገልጋዮች ልንጠነቀቅባቸው የሚገቡን ጉዳዮች መካከል

1) በራስ ማስተዋል አለመደገፍ

በመጽሐፍ ቅዱስ ቅዱስ ከተጻፉት ታሪኮች፣ ምክሮች እና ትርጓሜዎች መካከል አንደኛው በራሳቸን መረዳት፣ ማስተዋል (reasoning) ላይ እንዳንደገፍ እና በዚህ ምክንያት ወደ ፈተና እናዳንገባ መጠበቅን የሚመለከት ነው። ለምሳሌ ያህል ያዕቆብ ከዔሳው ብኩርናውን የወሰደበትን ሒደት ስንመለከተው በምንም ዓይነት ተፈጥሮአዊ አመክንዮ ይሠራል ይሆናል ለማለት የሚቻል አይደለም። የአብርሃምና ሣራ እንዲሁም የዘካርያስ እና የኤልሳቤጥ በዕርጅና ልጅ መውለድ የሚያስተምረንም ይህንኑ ነው። ዋናው ጉዳይ ግን እግዚአብሔር እርሱ ባወቀ ኤሳው ቀድሞ እንዳይወለድ እና ያዕቆብ ቀድሞ እንዲወለድ ማድረግ እየቻለ ከተወለደ በኋላ በኩርናውን እንዲወስድ ለምን አደረገ? ለእነ አብርሃም እና ለእነ ዘካርያስ ልጆችን ቀድሞ ለምን አልሰጣቸውም ብለን ብንጠይቅ ዋናው መልስ እግዚአብሔር ሊያስተምረን የፈለገው ከተፈጥሮ ሕግ እና ከየትኛውም አመክንዮ ወይም የሰው የሕሊና መረዳት የሚያልፉ ነገሮችን የሚያደርግ መሆኑን ለማሳየት ነው። በመጽሐፍም “በፍጹም ልብህ በእግዚአብሔር ታመን፥ በራስህም ማስተዋል አትደገፍ፤” /ምሳ 3 ፡ 5/ ተብሎ የተጻፈው ለዚህ ነው።

በርግጥ ሃይማኖት የሚባለውም ይህ ነው። ከመረዳታችን እና ከሎጂካችን ባሻገር እግዚአብሔር የሠራውንና የሚሠራውን ማመን። ጌታችን ከእመቤታችን ከንጽሕት ቅድስት ድንግል ማርያም የተጸነሰበት፣ የተወለደበት፣ የሞተበት፣ ድኅነታችን የፈጸመበት፣ የእመቤትችን በሁለንተና ንጽሕት መሆን እና የመሳሰሉትን ነገሮች መረዳት የሚቻለው ያዕቆብ ከዔሳው ብኩርናውን በወሰደበት መንገድ ብቻ ነው። ይህም ማለት ከሎጂክና ከአመክንዮ ተላልቅቆ እግዚአብሔር አምላክነቱን በየዘመኑ ትውልድ እግዚአብሔርነቱን የገለጸባቸውንና በአእምሮ ከመታሰብ፣ በሎጂክ ከመረዳት በላይ የሆኑትን በመቀበል ነው። ያዕቆብ ብኩርናን የወሰደበት መንገድ በእምነት የምንቀበለው ብቻ ነውና። እነዚህ ነገሮች የተፈጸሙት፣ እና በቅዱሳት መጻሕፍት የተመዘገቡበት ዋና ዓላማም የአካላዊ ቃል ሰው መሆን ጋር ተያይዞ ለሚነሱ ጥያቄዎች በሙሉ አስቀድመው የተዘጋጁ መልሶች እንዲሆኑ ነው።

በራስ ማስተዋል ወይም በራስ የመረዳት ችሎታ ላይ መደገፍ ቢያንስ ሁለት ታላላቅ ፈተናዎችን ወደ እኛ ያመጣል። የመጀመሪያው ከእምነት መጉደል ነው። ይህ ደግሞ እንኳን በእኔ ቢጤዎች ይቅርና ጻድቁ ዘካርያስንም ፈትኖታል። ዘካርያስ ቅዱስ ገብርኤልን የተከራከረው ዕውቀት ወይም የተፈጥሮ ሕግ ገድቦት ነውና። ሰው ካረጀ ካፈጀ በኋላ አይወልድም የሚለው ዕውቀቱ ወይም የተፈጥሮ ሕጉ ስሕተት ሆኖ አልነበረም። የእግዚአብሔር የማዳን ሥራ ግን ከእነዚህ የሚያልፍ ነበረ። ስለዚህ በመረዳት ወይንም በማስተዋላችን ላይ መደገፍ መጀመሪያ የሚያመጣው ፈተና እንኳን ሰዎች መላእክትም ቢናገሩን እንድንከራከር ሊያደርገን ይችላል ማለት ነው። ሌላው ቀርቶ ትናንት ያከበርነው የልደተ ስምዖን ታሪክ የሚያስታውሰንም ይህንኑ ገጠመኝ ነው። ሴት እንጂ ድንግል አትወልድም የሚል ሀሳብ ይዞ ድንግል ትጸንሳለች የሚለውን የነቢዩን የኢሳይያስን ቃል ሴት ወደሚል ለመቀየር ሞክሮ ከእግዚአብሔር ይህን ሳያይ እንዳይሞት የተረዳው የእግዚአብሔር አሠራር ከሰው ማስተዋል እና መረዳት ባሻገር ስለሆነ ነው። በዚህች መንገድ መጓዝ የጀመረ ሰው አይሁድ ከመስቀል ውረድና እንመንብህ እንዳሉት በራስ መረዳት ቅድመ ሁኔታ አስቀመጦ እግዚአብሔርን መፈተኑ የማይቀር ነው።

ሁለተኛው እና ከባዱ ፈተና ደግሞ ሌሎች ይህን መረዳት እንደማይችሉ በማሰብ የዲያብሎስ ረቂቅ ወጥመድ በሆነው የትዕቢት ወጥመድ ውስጥ መውደቅን ሊያስከትል ይችላል። ይህ ደግሞ ብዙ ጥፋቶችን አከታትሎ ያመጣብናል። ሰሎሞን “በልቡ የታበየ ሁሉ በእግዚአብሔር ዘንድ ርኩስ ነው፥ እጅ በእጅም ሳይቀጣ አይቀርም” /ምሳ 16 ፡ 5/ ሲል እንደገለጸው ቅጣቱም ቀጥታ ከእግዚአብሔር ይሆናል። ለሰውየው ግን እያወቀ ወይንም እውቀቱ ትክክል ስለሆነ እንጂ እየታበየ እና እየተጎዳ እንደሆነ አይሰማውም። ለዚህም ነው “ለሰው ቅን የምትመስል መንገድ አለች፤ ፍጻሜዋ ግን የሞት መንገድ ነው” /ምሳ 16 ፡ 25/ ተብሎ የተጻፈው ። ስለዚህ ከሁለቱም ለመጠበቅ በራስ መረዳት ላይ አለመደገፍ ትልቁ መፍትሔ ነው። የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች እና ምክሮች ያረጋገጡልንም ይህንኑ ነው።

2) ከትዕቢት / ካለመሸነፍ መንፈስ መራቅ

የትዕቢት ነገር ከላይም የተጠቆመ ቢሆንም በዓለም ለተፈጠሩት ችግሮች ሁሉ መሠረቱ ትዕቢት ነው። በተለይ በሰው ፊት ተሸናፊ መባልን፣ አያውቅም መባልን መፍራት፣ ተሳስቷል መባልን መሸሽ ወደ ማስረዳት እና ራስን ነጻ ለማውጣት ሲባል ወደ ተለጠጠ ክርክር ይስባል፣ ከዚያም ወደ ባሰው ችግር ወይም ፈተና ሊያደርስ ይችላል። ስለዚህ ጥያቄዎች ሲፈጠሩ ቆም ብሎ ማድመጥ ፣ መጸለይ እና ቅዱሳት መጻሕፍትን እያጠኑ ሊቃውንትን ደጋግሞ መጠየቅ ብዙ ችግሮችን ያስወግዳል። ይልቁንም ልሳሳት እችላለሁ በሚል ትሑት ሰብእና ውስጥ ሆኖ እግዚአብሔርን የሚለምን ሰው እግዚአብሔር በፍጥነት ከዚህ ችግር እንደሚያወጣው የታመነ ነው።

3) የምንጮችን ዐውድ በአግባቡ ለመራዳት መጣር

ብዙ ጊዜ ወደ ክርክር ተይዘው የሚወጡት ምንጮች ወይም ማስረጃዎች በራሳቸው ምንም ችግር የለባቸውም። ሆኖም ከተነገሩበት ወይም ከተጻፉበት ዐውድ አውጥተን ከተመለከትናቸው ችግር ውስጥ ልንወድቅ እንችላለን። ለምሳሌ ያህል ጥንተ አብሶን በተመለከተ የሚነሣው ክርክር ለዚህ ጥሩ ምሳሌ ሊሆን ይችላል። የጥንት ሊቃውንት ጌታ ሥጋውን ከሰማይ ይዞ ወርዷል፣ በእመቤታችን አደረባት እንጂ ሥጋን ከእርሷ አልነሣም ለሚሉ የዚያ ዘመን መና/ፍቃን የተሰጡ መልሶች ያንኑ የበደለውን ሰው የአዳምን ሥጋ ነው የተዋሐደ ሲሉ ያንን የሳተውን፣ የወደቀውን፣ የጎሰቆለውን የእዳም ሥጋ እንደተዋሐደ ተከራክረው አስረድተዋል። ሆኖም እነዚህ አገላለጾች እመቤታችንን ጥንተ አብሶ አለባት ሊያስብሉ አይችሉም። (ይህን ጉዳይ


፩ኛ፦ ጠንቅቀን በማናውቀው ጉዳይ ላይ መናጆ/አንጃ ሆነን አስተያየት አለመስጠት መልካም ነው።

፪ኛ፦ የዕውቀታችንን ምንጭ መመርመር መልካም ነው። ከልምድ ነው? ከመጽሐፍ ነው? ከመምህር ነው? ከመሰለኝ ነው? ከምንድን ነው?

፫ኛ፦ የሰውን አለማወቅ እንደ Advantage ተጠቅሞ ማታለል አይገባም። ለምሳሌ ማንኛውም ክርስቲያን ንስሓ ገብቶ ሥጋውን ደሙን መቀበል ይገባዋል። ወደ ገጠር ስንሄድ ግን ወጣት አይቆርብም እያሉ አንዳንድ ሰዎች ሲከለክሉ ይስተዋላል። ይህ ስሕተት ነው። አንዱ መምህር ሄዶ ንስሓ እየገባችሁ ሥጋውን ደሙን ተቀበሉ ቢል ሰው ከልምዱ ተነሥቶ ሊጠላው ይችላል። የተናገረው ግን እውነት ነው። ሌላ እወደድ ባይ መምህር አዎ ወጣት መቁረብ የለበትም ብሎ ሕዝቡ የሚያቀርባቸውን አመክንዮዎች ቢያቀርብ ሕዝቡ ደስ ሊለው ይችላል። ሕዝቡም የዚህ ደጋፊ ሊሆን ይችላል። መማር እንደዚህ ነው ሊልህ ይችላል። እውነታው ግን የላይኛው ነው። በዚህ ጊዜ ከሕዝቡ የሐሰት ፈጠራ ይልቅ እግዚአብሔራዊውን እውነት ተናግሮ ከመሸበት ማደር ይገባል።

፬ኛ፦ ፈሪሳዊነትን እናስወግድ። ፈሪሳውያን በእግዚአብሔር ቃል ላይ የራሳቸውን ወግ እየጨመሩ ያስተምሩ ነበር። ለወጋቸው መጽሐፋዊ ወይም ቅዱስ ትውፊታዊ የሆነ ማስረጃ የላቸውም። ግን ሕዝቡ ወጋቸውን እንደ ጽጽቅ እንዲያይላቸው ይጥሩ ነበር።

፭ኛ፦ ክፉ ነገሮችም፣ መልካም ነገሮችም በትውፊት ከትውልድ ወደ ትውልድ ሊተላለፉ ይችላሉ። እኛ ቅዱስ ትውፊትን መቀበል አለብን። ቅዱስ ትውፊት በመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት ላይ የተመሠረተ ነው። ከመጽሐፍ ቅዱስ አስተምህሮ የሚቃረን ከሆነ ትውፊት ቢሆንም እንኳ ቅዱስ ትውፊት ስላልሆነ አንቀበለውም።

፮ኛ፦ እግዚአብሔር ልብን የሚመረምር ስለሆነ ከእያንዳንዱ ሐሳባችን፣ ንግግራችን፣ ተግባራችን ጀርባ ያለውን ጉዳይ መመርመር ይገባናል። ከፍቅር ተነሥተን ነው? ከጥላቻ ተነሥተን ነው? ለሃይማኖታችን ከማሰብ ነው? ከአንጃነት ነው? ከምቀኝነት ነው? ከቅንዐት ነው? እግዚአብሔርን ከመውደድ ነው? በጠቅላላው ልባችንን እንፈትሽ። በእያንዳንዱ ንግግራችን፣ በእያንዳንዱ ሐሳባችን፣ በእያንዳንዱ ተግባራችን በእግዚአብሔር ፊት እንመዘንበታለንና።

፯ኛ፦ አንዳንዱ ሊሳደብ፣ ክፉ ስም ሊሰጥ ይችላል። አንዳንዱ ደግሞ ሊዋሽ ይችላል። በዚህ ጊዜ ስድቡን ቸል ብሎ ጉዳዩ ላይ ማተኮር መልካም ነው። ታግሠው ሲቀበሉት የበረከት ምንጭ ነውና። (አንዳንዱ የማስረዳት አቅም ሲያጥረው ስድብን እንደ አማራጭ ሊጠቀም ይችላል። ስለዚህ የሰውየውን ድክመቱን መረዳትና ንቆ መተው መልካም ነው)።

፰ኛ፦ ንግግሮችን፣ ጽሑፎችን ከነዐውዳቸው ለመረዳት መጣር ይገባል።

፱ኛ. ሟች መሆናችንን ለአፍታም ቢሆን መዘንጋት የለብንም። መቼ እንደምንሞት ስለማናውቅ ከመሞታችን በፊት መሥራት አለብን ብለን ያሰብነውን ጉዳይ ለመፈጸም መትጋት ይገባናል።

፲ኛ፦ አጥፍተን ከነበረ ይቅርታ ማለትን እንልመድ። ትሑት ልቡናን ገንዘብ እናድርግ። ፈሪሀ እግዚአብሔርን እናስቀድም።

© በትረ ማርያም አበባው
@EotcLibilery
@EotcLibilery
@EotcLibilery


ጊዜ ለምን? || ጾመ ነነዌ
             
Size:-82.9MB
Length:-1:29:33

    በርእሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማ
@mezigebehayimanot
@mezigebehayimanot
@mezigebehayimanot














"ይእዜ ትስዕሮ ለገብርከ በሰላም እግዚኦ በከመ አዘዝከ ፡-አቤቱ ባሪያህን እንደ ቃልህ በሰላም አሰናብተው" ስምዖን አረጋዊ

#የካቲት_8  ፤ የጌታችን  ከከበርች ልደት በኋላ  ወደ ቤተመቅደስ የገባበት ዕለት ኾነ ፡፡ በዓሉ ከጌታችን ንዑስ በዓሎች መኻከል አንዱ ነው ፡፡
++++
የካቲት 8 ፤ ልደተ ስምዖን አረጋዊው  ፣ ካህን ፣ ጻድቅ ፣ ነቢይ ፡፡

+ በዓሉ የመድኀኔዓለም ቢሆንም ስምዖን አረጋዊ አማናዊ ድኅነት አግኝቶበታልና ፣  በእርጅና ምክንያት ከአልጋ ላይ ተጣብቆ ሲኖር ታድሶበታልና እንደ 30 ዓመት ጎልማሳም ዘሏልና  በዓሉ ይከብራል ። ስምዖን ብቻ ሳይሆን የሰው ልጅ ሁሉ የድኅነት ባለቤት ኾኖበታልና በዓሉ ይከብራል ።

++++

ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከድንግል ማርያም በተወለደ በ40 ቀኑ የኦሪትን ሕግ ለመፈጸም ወደ ቤተ መቅደስ ገባ ። ይህም ሕግን ሊፈጽም እንጂ ሊያፈርስ አለመምጣቱን በቃልም ፣ በግብርም የገለጠበት በዓል መኾኑን ያስረዳናል። ሥርዓቱን ለመፈጸም እናቱ ቅድስት ድንግል ማርያምና አረጋዊው ቅዱስ ዮሴፍ ጌታቸውን ይዘው፣ የርግብ ግልገሎችና ዋኖስ ጨምረው ወደ ቤተ መቅደስ ሔዱ ።

++++

የስምዖን አረጋዊ ነገርም እንዲኽ ነው ..
ዓለም በተፈጠረ በ5,200 ዓመታት በጥሊሞስ የተባለ ንጉሥ በግሪክ ነግሦ ነበር። ዓለሙን እንደ ሰም አቅልጦ፣ እንደ ገል ቀጥቅጦ የገዛው መሆኑን ገልጦ፣ የቀረው ነገር አለመኖሩን ሲናገር ባለሟሎቹ በእሥራኤል ጥበብ የመላባቸው 46 መጻሕፍት ስላሉ እነርሱን አላስተረጎምክም አሉት። እስራኤልን አስገብሮ ስለነበር 46ቱን የብሉይ ኪዳን መጻሕፍት ከ72 የአይሁድ ሊቃውንት ጋር አስመጣ። አይሁድ ተንኮለኛ መኾናቸውን ስለሚያውቅ 36 ድንኳን እንዲዘጋጅ አድርጎ ኹለት ኹለቱን መድቦ፣ የየድንኳኑን ሊቃውንት የሚቆጣጠሯቸው አንዳንድ ጠባቂዎች ጨምሮ  እንዲተረጕሙ አዘዛቸው።

በዚህ ምክንያት በ284 ዓመት ከክርስቶስ ልደት በፊት 46ቱ የብሉይ ኪዳን መጻሕፍት ከዕብራይስጥ ወደ ልሳነ ጽርዕ (ግሪክ) በ70ው ሊቃናት ተተረጐሙ። ከ70 ሊቃናት በመኻከል አንዱ የነበረው #ስምዖን ምሁረ ኦሪት ነበር። ይተረጕም ዘንድ መጽሐፈ ኢሳይያስ ደረሰው። ታዲያ ይህ ሊቅ የትንቢቱን መጽሐፍ እየተረጎመ ሳለ ምዕራፍ ፯ ላይ ሲደርስ የሕይወቱን አቅጣጫ ወደ ዘላለማዊ በረከት የሚያሳድግ ልዩ ገጸ ንባብ ገጠመው ።  እርሱም
“ ስለዚኽ ጌታ ራሱ ምልክት ይሰጣችኋል፤ እነኾ ፥ ድንግል ትፀንሳለች፥ ወንድ ልጅም ትወልዳለች፥ ስሙንም አማኑኤል ብላ ትጠራዋለች።” ኢሳ 7፥14 የሚል ነበር።
ስምዖንም "እንዴት ድንግል ትፀንሳለች?" ብሎ "ድንግል" የሚለውን "ሴት" ብሎ ቀይሮ " ሴት ትፀንሳለች " ብሎ ለማረም ይሞክርና አመሻሽ ላይ ስለነበር እንቅልፍ ሸለብ አድርጎት ሲነቃ የቀየረው ተቀይሮበት " ድንግል ትጸንሳለች" የሚል ሁኖ ያገኘዋል።  ተሳስቼ ነው ብሎ አሁንም ሊያበላሽ ሲሞክር መልአኩ ሦስት ጊዜ አርሞበት  በሦስተኛው መልአኩ ራሱ ተገልጦለት "ይህችን ድንግል ሳታይና ልጇንም ታቅፈህ ሳትባረክ አትሞትም"
( የተጠራጠርከውን ሳታይ አትሞትም ብሎ ብሎ ነግሮት )  ተሰወረ። አረጋዊ ስምዖንም ከዚያች ዕለት ጀምሮ መድኅን ክርስቶስ እስከሚወለድ ለ284 ዓመታት ከአልጋ ጋር ተጣብቆ ኖረ።
አምላካችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከድንግል ማርያም በተወለደ በ40 ቀኑ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምና አረጋዊው ቅዱስ ዮሴፍ ወደ ቤተ መቅደስ ይዘውት ወጡ ። በዕለቱም መልአከ እግዚአብሔር አረጋዊ ስምዖንን ቀስቅሶ ተስፋ የሚያደርገው አዳኝ ክርስቶስ መምጣቱን ነገረው። በዚህ ጊዜ አረጋዊ ስምዖን አካሉ ታድሶ፣ እንደ 30 ዓመት ወጣት እምር ብሎ ከአልጋው ተነሣ። በፍጥነትም ወደ መቅደስ ገባ። መድኀኔዓለምን ከድንግል ማርያም ተቀብሎ በመታቀፍ "ይእዜ ትስዕሮ ለገብርከ በሰላም እግዚኦ በከመ አዘዝከ፡-አቤቱ ባሪያህን እንደ ቃልህ በሰላም አሰናብተው"

(" ጌታ ሆይ፥ አን እንደ ቃልህ ባሪያህን በሰላም ታሰናብተዋለህ ፤ ዓይኖቼ በሰዎች ሁሉ ፊት ያዘጋጀኸውን ማዳንህን አይተዋልና፤
ይኽም ለአሕዛብ ሁሉን የሚገልጥ ብርሃን ለሕዝብህም ፳ኤል ክብር ነው።" (ሉቃ 2÷29-32)  )
በማለት ጸለየ። 

አምላኩም ጸሎቱን ሰምቶት በዛሬው ዕለት ዐረፈ። ከበዓሉ በረከት ይክፈለን። አሜን!!

የሊቁ ስምዖን  አረጋዊ በረከት እና ምልጃ አይለየን !
በዓለ ስምዖን በዐይቢይነት  ሜላት ደብረ ገነተ ኢየሱስ  ይከብራል  ፡፡
ጐንደር   -- › አንዳቤቴ ወረደ   -- › ገነተ ኢየሱስ  
በ13ኛ መቶ ክፍለ  ዘመን በአጼ ሰይፈ አርዕድ ዘመነ መንግስት
ልዕልት ሜላተ ወርቅ ያሰተከለችው ደብር ነው ፡፡
+++
በዓሉ በኢየሱስ ስም የተሰየሙ አድባራትና ገዳማት ላይ ይከበራል !

@EotcLibilery
@EotcLibilery
@EotcLibilery


የጸናውን አስቡ
             
Size:-63.4MB
Length:-1:08:26

    በርእሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማ
@Nigatu5
@Nigatu5
@Nigatu5


ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ጾመ ነነዌን አስመልክተው አባታዊ መልእክት አስተላልፈዋል !

ጥር 29 ቀን 2017 ዓ.ም(ተ.ሚ.ማ/አዲስ አበባ)

ሰኞ የካቲት 3 ቀን 2017 ዓ.ም የሚጀመረውን የፈጾመ ነነዌን አስመልክቶ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት  የሰላምና የጸሎት አዋጅ መግለጫ ሰጥተዋል።

ሙሉ መልእክቱ እንደሚከተለው ቀርቧል

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!

ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ የተላለፈ የምህላ ሱባኤ፡-

‹‹ቀድሱ ጾመ ወስብኩ ምህላ አስተጋብኡ ሕዝበ ሊቃውንተ ሕዝብ፤ ጾምን ቀድሱ፣ጉባኤውንም አውጁ፤ሽማግሌዎችንና በምድር የሚኖሩትን ሁሉ ወደ ኣምላካችሁ ወደ እግዚአብሔር ቤት ሰብስቡ፤ ወደ እግዚአብሔርም ጩኹ (ኢዩ ፩÷፲፬)።

ሁላችንም እንደምናውቀው ያለንበት ዓለም የመከራ ዓለም ነው፣ መከራው በኛ ስሕተትና ክፋት የመጣና እየሆነ ያለ መሆኑም ይታወቃል፤ እኛ የምንፈጽመው ጥቃቅንና ትላልቅ ግብረ ኃጢአት እግዚአብሔርን እንደሚያስቈጣ በቅዱስ መጽሐፍ ተረጋግጦ ያደረ ነው፤ ለዚህም ከነነዌ ነዋሪ ሕዝብ የበለጠ ማስረጃ የለንም፤ የነነዌ ከተማ ነዋሪዎች በፈጸሙት ግብረ ኃጢአት እግዚአብሔርን አስቈጥተዋል፤ ድርጊታቸው እግዚአብሔርን የሚያስቆጣ ቢሆንም እሱ ምሕረቱን ማስቀደም ስለፈለገ በዮናስ በኩል አስጠንቅቆአቸዋል፤ የነነዌ ነዋሪዎችም በዮናስ በኩል የደረሳቸውን የንስሓ ጥሪ ወዲያውኑ ተቀብለው በምህላ፣ በጾም፣ በጸሎት ንስሓ ስለገቡ እግዚአብሔር ፍጹም ይቅርታ አድርጎላቸዋል፤

•  የተወደዳችሁ ኢትዮጵያውያንና ኢትዮጵያውያን ልጆቻችንና ወገኖቻችን !

እኛ ሰዎች ዛሬም በየሰዓቱ ብቻ ሳይሆን በየደቂቃው እግዚአብሔርን የሚያስቆጣ አበሳ እንደምንፈጽም ማወቅ ኣለብን፣ አበሳውና ኃጢኣቱ ሲበዛ እግዚአብሔር እውነተኛ ዳኛ ነውና ወደ ዳኝነት ተግባሩ ይገባል፤ይህ ደግሞ በሰብአ ትካት በሰዶምና በጎሞራ ያስተላለፈውን ዳኝነት ያስታውሰናል፤ አሁን ያለንበት ዘመን ዓመተ ምሕረት በመሆኑ እግዚአብሔር ለጊዜው ቢታገሠንም በኃጢኣታችን የምንጠየቅበት ጊዜ አዘጋጅቶአል፤ ዛሬም ቢሆን የማናስተውለው ሆነን ካልሆነ በስተቀር እግዚአብሔር ተግሣጹን ማስተላለፍ አላቆምም፤ በምድራችን ላይ በምናደርሰው የተዛባ ተግባር በጐርፍ፣ በድርቅ፣ በመሬት መንቀጥቀጥና በአየር መዛባት እየገሠጸን እንደሆነ ማስተዋል አለብን።

እግዚአብሔር ከጥንቱ ከጠዋቱ ጀምሮ ምድርን እንድንከባከባት፤ እንድናበጃት፣ እንድናጠብቃትና እንድናለማት አዞናል፤ ሆኖም ይህን ትእዛዙን ገሸሽ አድርገን በኬሜካልና በመርዛም ጋዝ ምድርን በመበከል፣ደንዋን በመመጠርና ራቁቷን በማስቀረት በምናደርገው ድርጊት አበሳ እየፈጸምን እንደሆነ ያወቅነው አይመስልም፤ በዚህም ምክንያት በጐርፍ፣ በድርቅ ለሰው ልጆች በማይመች የኣየር ፀባይ ወዘተ . . . ስጋት ውስጥ እየወደቅን ነው።

በሌላም በኩል በምናወሳስበው የአስተዳደር ርእዮትና መሳሳብ የእግዚአብሔር ገንዘብ የሆነውን ሕዝብ እርስ በርሱ እንዲጋጭና ያላስፈላጊ አደጋ ላይ እንድወድቅ እያደረግን ነው፤ በዚህም ጠንቅ ሰላም እየደፈረሰ፣ ፍቅርና አንድነት እየላላ የሃይማኖት ክብርና ልዕልና እየተነካ ራሳችንንም እየጐዳን ነው፤በዚህ ሁሉ ተግባራችን  እግዚአብሔርን እያሳዘንን ነው፤ ይህ ሊገባንና ሊቈረቁረን ይገባል፤

የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን ምእመናንና ምእመናት

ለችግሮች ሁሉ መፍትሔ አላቸው፤ መፍትሔውም የሚገኘው ከእግዚአብሔርና ከእኛ ነው፤ ከእኛ በንስሓ ተመልሰን ከልብ እግዚአብሔርን ይቅርታ መጠየቅና ከክፉ ተግባራችን በእውነት መጸጸት ይጠበቃል፤ እግዚአብሔር ደግሞ ይህንን ዓይነቱ ንስሓ ከኛ መኖሩ ሲመለከት ምሕረትና ይቅርታን ይለግሰናል፤በዚህም መፍትሔና ፈውስ ይገኛል፤ ከዚህ አንጻር በአሁኑ ጊዜ ለሀገራችንና ለዓለማችን ስጋት የሆኑ የጦርነት ክሥተቶች፣ የመሬት መንቀጥቀጥ፣ የአየር መዛባት፣የድርቅ መከሠት፣የጎርፍ መጥለቅለቅ የሰላም መደፍረስ፣ የሰላማውያን ወገኖች መጎዳት፣ የፍቅርና የአንድነት መላላት ወዘተ. . . . ከምድራችን ተወግደው ፍጹም ምሕረትና ሰላም እናገኝ ዘንድ በኃጢኣታችን ተጸጽተን በምህላ ንስሓ መግባት አለብን፤ ከዚህ አኳያ ከጥንት ጀምሮ በቤተክርስቲያናችን ቀኖናዊ ሥርዓት መሠረት በየዓመቱ የሚጾመው ጾመ ነነዌ ለዚህ አመቺ ጊዜ ስለሆነ ከየካቲት ፫ ቀን ፳፻፲፯ ዓመተ ምሕረት ጀምሮ  ለሦስት ቀናት ከልኂቅ እስከ ደቂቅ ሁላችንም ጠዋትና ማታ በየቤተክርስቲያኑ ዐውደ ምሕረት እየተገኘን በንስሓ በዕንባ በጸሎት በምህላ የእግዚአብሔርን ምሕረትና ይቅርታ እንድንጠይቅ፤ እንደዚሁም በሀገራችንና በውጭ ያላችሁ ሊቃውንተ ሕዝብ ቀኖናውን ጠብቃችሁ ይህንን በማስፈጸም ምህላውን በቀኖናው መሠረት እንድታከናውኑ በእግዚአብሔር ስም አባታዊ መልእክታችንን እናስተላልፋለን።

እግዚአብሔር አምላካችን ምሕረቱን ይቅርታውንና ሰላሙን ለሀገራችንና ለዓለማችን ይስጠን፤ ምህላችንንም ይቀበልልን።

   “እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ይባርክ”

ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን!!

አባ ማትያስ ቀዳማዊ
ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት

ጥር 29 ቀን 2017 ዓ.ም
አዲስ አበባ ኢትዮጵያ


ትዳር ክቡር ነው አትፋቱ
             
Size:-64.2MB
Length:-1:09:17

    በርእሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማ
@mezigebehayimanot
@mezigebehayimanot
@Mezigebehayimanot


ተአምረ ማርያም
             
Size:-120.6MB
Length:-2:10:16

    በርእሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማ
@mezigebehayimanot
@mezigebehayimanot
@mezigebehayimanot


የማርያም አዳራሽ - መርጡለ ማርያም !

ባሕር ዳር: ጥር 21/2017 ዓ.ም (አሚኮ) በጎጃም ከሚገኙት አያሌ ቅዱሳት ገደማት መካከል አንዷ የታላቋ እና የጥንታዊቷ ርዕሰ ርዑሳን መርጡለ-ማርያም ገዳም ናት።

ርዕሰ ርዑሳን መርጡለ ማርያም ገዳም የምትገኘው በጎጃም በእነብሴ ሳር ምድር ወረዳ ዋና ከተማ መርጡለ-ማርያም ነው።

መርጡለ-ማርያም ትርጉሙ የማርያም አዳራሽ ማለት ነው። ርዕሰ ርዑሳን መርጡለ ማርያም ገዳም አሁን የያዘችውን የስም መጠሪያ ከመያዟ በፊት በተለያዩ ዘመናት አራት ጊዜ የስም መለዋወጦች አጋጥሟታል።

መጀመሪያ ሀገረ ሰላም ቀጥሎ ሀገረ እግዚአብሔር ተብላለች። ከዚያም ጽርሐ አርያም ተብላ ተጠርታለች በመጨረሻም አሁን የምትጠራበትን መርጡለ ማርያም የሚለውን ስያሜ አግኝታለች።

ይች ታላቅ እና ጥንታዊት ገዳም የተመሠረተችው ከእስራኤሉ ንጉሥ ሰሎሞን እና ከኢትዮጵያዊት ንግሥት ሳባ (ማክዳ) የተወለደው ቀዳማዊ ምኒሊክ ይዟቸው በመጣ ፫፻፲፰ (318) የኦሪት ካህናት በ4500 ዓመተ ዓለም ነው።

ወደ ዚች ቦታ የመጡት የኦሪት ካህናት መሥዋዕተ ኦሪትን በመሰዋት የኦሪትን አምልዕኮት ሲፈጽሙ ኖረዋል። መርጡለ ማርያም በኢትዮጵያ መስዋዕተ ኦሪት ሲሰዋባቸው ከነበሩት አራቱ ጥንታዊ አብያተ ክርስቲያናት ማለትም አክሱም ጽዮን፣ ተድባበ ማርያም እና ጣና ቂርቆስ መካከል አንዷ ነበረች፡፡

ገድለ አብርሃ ወ አጽብሃ እና ገድለ አባ ሰላማ ከሳቴብርሃን እንደሚያስረዱት ሕሩያን ነገሥታት አብርሃ ወ አጽብሃ ከጳጳሱ አባ ሰላማ ከሳቴ ብርሃን ጋር በመኾን በ፫፻፴፫ (333) ዓ.ም ዓባይን ተሻግረው ጎጃም ምድር መርጡለ ማርያም ደረሱ።

በዚህ ቦታ ሕዝበ ክርስቲያኑን ወንጌል አስተምረው መክረው ከኦሪት ወደ ሐዲስ ከአምልኮተ ጣኦት ወደ አምልኮተ እግዚአብሔር መልሰው ካጠመቁ በኋላ ሕዝበ ክርስቲያኑ አምልኮቱን የሚፈጽምበት ቤተ ክርስቲያንን ለመሥራት አሰቡ።

ቦታው ላይ የሚያምር ቤተ ምኩራብ ስለ ነበር ይህንን ለታሪክ ትተን ሌላ ቦታ ላይ እንሥራ በማለት በስተምሥራቅ አሻጋሪ ካለው ተራራ አሁን ግንብ ወሬ እየተባለ ከሚጠራው ኮረብታ ላይ ቁፋሮ ጀመሩ።

ነገር ግን መሬቱ የእሳት ትንታግ እየተፋ አልቆፈር አለ። በመኾኑም በዚህ ቦታ ቤተ ክርስቲያን እንሠራ ዘንድ እግዚአብሔር አልፈቀደም። ፈቃደ እግዚአብሔርን እናውቅ ዘንድ ለ፫ (3) ተከታታይ ቀናት ሱባኤ እንግባ በማለት በ፭ (5) በአካባቢው ባሉ የተለያዩ ኮረብታዎች ሱባኤ ገቡ።

ሱባኤ የገቡባቸው ከረብታዎችም፡-
👉የኦሪቱ ሊቀ ካህን አብኒ ኮረብታ
የሐዲሱ ሹም ሐዲስጌ ኮረብታ
👉የጳጳሱ አቡነ ሰላማ ሰላምጌ ኮረብታ
👉በንጉሥ አብርሃ አብርሂ ኮረብታ
👉በንጉሥ አጽብሃ ዜነዎ ኮረብታ ላይ እንደነበሩ ይነገራል

ንጉሥ አጽብሃም ከሁሉም አስቀድሞ ወደ አባ ሰላማ ከሳቴ ብርሃን በመሄድ ያየውን ራዕይ ተናገረ። ሌሎችም መጥተው ያዩትን ሁሉ ተናገሩ አባ ሰላማም ይህንን ራዕይ ያዩ መኾናቸውን ነገሯቸው። ሁሉም በአንዲት ሌሊት አንድ ዓይነት ራዕይ አዩ።

ያዩት ራዕይም « ዐሥራ ሁለት በሮች ያላት አንድ አምደ ብርሃን የቤተ መቅደሱ መሠረት ከተጀመረበት ኮረብታ ተነስታ እያበራች የጥንቱ ቤተ ምኲራብ ከሚገኝበት ጽርሐ አርያም አምባላይ ስታርፍ » ነበር፡፡

ጧት ወደ ቦታው ሲሄዱ የጥንቱ አስደናቂው ቤተ ምኩራብ መሬት ውስጥ ተቀብሮ ለጥያለ አረንጓዴ ሜዳ ኾኖ አገኙት፡፡

ነገሥታቱ አብርሃ ወ አጽብሃ በቦታው ቤተ መቅደስን ይሠሩ ዘንድ ወደዱ። በወርቅ እና በእንቁ አምዶችን እና አረፍቶችን ልዩ አድርገው በማስጌጥ የማርያምን ቤተመቅደስ ሠሩ።

ሥርዓትንም በመደንገግ ካህናትን ዲያቆናትን እንዲሁም ሁሉንም ሊያሥተዳድር የሚችል ሊቀ ካህናት ርዕሰ ርዑሳን ብለው ሾሙ። መቅደሷንም መርጡለ ማርያም ብለው ሰየሟት።

ንጉሥ አብርሃ ወ አጽብሃም እግዚአብሔር በመራቸው መሠረት በጳጳሱ በአባ ሰላማ አስባርከው በጽርሐ አርያም አምባላይ አስደናቂውን ባለ ፲፪ (12) ቤተመቅደስ ባለ ፩ (1) ፎቅ ቤተ መቅደስ ሠርተው በወርቅ በእንቁ በከበሩ ማዕድናት አስጊጠው ጥር ፳፩ (21) ቀን የእመቤታችንን ጽላት በደማቅ ሥነ ሥርዓት አስገብተዋል።

ይህ ቤተ ክርስቲያን እጅግ የተለየ በልዩ ልዩ ቅርፅ ያጌጠ በወርቅ እና በእንቁ የተለበጠ አስደናቂ የጥበብ አሻራ ያረፈበት ነበር። ይህ ቤተ መቅደስ በዮዲት ጉዲት ዘመን በ፰፻፵፪ (842) ዓ.ም ተቃጥሏል።

በ፰፻፹፪ (882) ዓ.ም የነገሠው አንበሳ ውድም በዮዲት የተቃጠለውን ቤተ ክርስቲያን እንደገና አሠርቶታል። ይህንን ቤተ ክርስቲያን ዐፄ በእደ ማርያም በ፲፬፻፷ (1460) ዓ.ም አሳድሶታል። ባለቤቱ ንግሥት እሌኒ ደግሞ የአንባውን ዙሪያ አሠርታለች። አሁንም የገዳሟ ዙሪያ የእሌኒ ውድሞ ይባላል።

ገድለ አብርሃ ወ አጽብሃ፣ ገድለ አባ ሰላማ ከሳቴብርሃን እና በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የተሠራ ዘጋቢ ፕሮግራም እንደሚያስረዳው መርጡለ ማርያም በዋጋ የማይተመን ከፍተኛ የቅርስ ክምችት ያላት ገዳም ናት፡፡

እነዚህ ውድ ቅርሶች በመርጡለ ማርያም ሙዚየም ውስጥ የሚገኙ የአብርሃ ወአጽብሃ የወርቅ መስቀል፣ በ445 ዓ.ም የተጻፈ ግዕዙን በግዕዝ የሚተረጉም አርባዕቱ ወንጌል፣ የአጼ በእደ ማርያም ራስ ቁር እና የወርቅ ለምድ፣ የንግሥት እሌኒ የክብር ካባ እና የብር ዋንጫ፣ የብር እና የወርቅ መስቀሎች፣ የወርቅ አክሊሎች፣ የወርቅ ከበሮ፣ የአጼ ገላውዲዮስ ዳዊት እና ካባ፣ የብራና መጻሕፍት እና የመሳሰሉትን ለአብነት መጥቀስ ይቻላል፡፡

ጥር 21 የሚከበረው በዓለ አስተርእዮ ማርያም የመርጡለ ማርያም ልዩ የክብረ በዓል ቀን ነው፡፡ አስተርእዮ ማርያም በመርጡለ ማርያም በልዩ ልዩ ሃይማኖታዊ ክዋኔዎች የሚከበር ደማቅ በዓል ነው፡፡

@mezigebehayimanot
@mezigebehayimanot
@mezigebehayimanot


የደቡቧ ኮከብ ብርብር ማርያም= የኦሪትና የሀዲስ ኪዳን ማህተም
~~~~~~~

የደቡቧ የአጥቢያ ኮከብ በመባል የምትታወቀው ብርብር ደብረ ማርያም ገዳም የምትገኘው በጋሞ ዞን በምዕራብ ዓባያ ወረዳ ቦላ ሔራ ቀበሌ ልዩ ስሙ ደጋ ብርብር እየተባለ በሚጠራው ከፍተኛ ቦታ ላይ ነው፡፡

ደብረ ማርያም ብርብር ገዳም ቀደም ሲል በኦሪት ቤተ መቅደስ የተተከለችው ከጌታችንና መድሃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ቅድመ ልደት 400 ዓመት አካባቢ ነበር።

በሀገራችን ኢትዮጵያ መሥዋዕተ ኦሪት ከሚሰዋባቸው ትምህርተ ብሉይ ከሚሰጥባቸው አክሱም ጽዮን፣ ተድባብ ማርያም፣ መርጡለ ማርያምና ጣና ቂርቆስ አብያተ መቃድስ ጋር በኦሪቱ ሥርዓትና በምኩራብ በአይሁድ ደንብ ትተዳደር ነበር።

በዘመነ ሐዲስ በአምስተኛው መቶ ክፍለ ዘመን አጋማሽ ላይ ደግሞ የቤተ መቅደስዋን የጥንት ታሪክና ዝና የሚያውቁት አጼ ገብረ መስቀል ብርብር በተባለችው ቤተ መቅደስ ሥርዓት ሐዲስ ዘመንን የሚመለከት ታቦት ገብቶ ሊወደስባትና ሊቀደስባት እንደሚገባ አስበው በታቦተ ማርያም ስም ቅዱስ ያሬድ እና ጻድቁ አቡነ አረጋዊን ታቦተ ማርያምን አስይዘው በአያሌ ሠራዊት ታጅበው ከአክሱም ጽዮን በብዙ ጉዞና ድካም ወደ ቦታው ደረሱ።

ግንቦት 21 ቀን ጻድቁ አቡነ አረጋዊ ቤተ መቅደሱን በሜሮን አክብረው ታቦተ ማርያምን አስገብተው ቅዳሴ ቤቷን አከበሩ።

በዚህ መሠረት አገልግሎቷን ከኦሪት እስከ ሐዲስ ኪዳን ስትቀጥል የደቡብ ኢትዮጵያ የሃይማኖት ማዕከል
በመባል የምትገለጸው ጥንታዊቷ ደብረ ማርያም ብርብር ገዳም በየዘመኑ የቤተክርስቲያናችን ላይ የሚነሱ አጽራረ አብያተ _ ክርስቲያናት ታሪኳን ለማጥፋት ቢጥሩም በተለያዩ ጊዜያት የተለያዩ ድንቅ ተዓምራትን በማድረግ ለዚህ ትውልድ ደርሳለች።

አናኒያንና አዛሪያን የሚባሉ ሊቃነ ካህናት ታቦተ ጽላቱን ከኢየሩሳሌም ቀይ ባህርን አሻግረው ከአክሱም ታቦተ ፅዮን ጋር እንዳመጧት ይነገራል፡፡
ብርብር ማርያም በምትባለው የታሪክ የእውነት የመመረጥ እና የበረከት ዶሴ ውስጥ በምኩራብ ስርዓት በዘመነ ኦሪት ከነበሩት ከሊቃ ካህኑ ሳዶቅ ልጅ ካህኑ አዛርያስ እስከ ጉባኤ ኒቂያ አዘጋጅ ከሆነው የንግስት እሌኒ ልጅ ንጉስ ቆስጢንጢኖስ ድረስ በድምቀት ጎልተው ይነበባሉ።

በኢትዮጽያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ታሪክ የመጀመርያው ሊቀጻጳስ ከሆኑት ከአቡነ ከሳቴ ብርሃን (ፍሬምናጦስ ) እስከ ከሳቱ ቅዱሳን አካል ከሆኑት አቡነ አረጋዊ ድረስ በእዚህች ገዳም በረከት አፈስው ሱባኤ ይዘው ፀሎትና ቡራኪያቸውን አስቀምጠው ለትውልድ አልፈዋል።

የዜማው ሊቅ ስውሩ አባታችን ቅዱስ ያሬድ በመላእክት ጣዑመ ዜማ በሰማያውያን ለዛ በእዚህች ገዳም የምስጋና መሰዋት ዘርግቶ አልፎባታል።
በእዚህች ገዳምን ፃዲቁ አባታችን አቡነተክለሐይማኖት መንበረ አድርገዋት የወንጌል ዘርን በደቡብ ኢትዮጽያ ውስጥ ዘርተዋል።

ከኢዛና ሳይዛና እስከ አፄ ልብነድንግል፤ከአፄ ገብረመስቀል እስከ አፄ ዘርያዕቆብ ፤ ከአፄ ምኒልክ እስከ ጃንሆዬ ድረስ እጅ መንሻ እና መባ ለደቡቧ ኮከብ ለሆነችው ለብርብር ማርያም ሰጥተዋታል በረከት አፍሰውባታል።
በሀገር ላይ መከራ እና ወረራ ተከስቶ ጠላቶች በተነሱበት ጊዜ ከታቦተ ጽዮን እስከ ግማደ መስቀል በእዚህች ገዳም ሰንብተው ህዝቡን ባርከው ምድሯን ቀድሰው አልፈዋል።

እንግዲህ የእዚህች ገዳም ስም የደቡቧ ኮከብ ርዕሰ አድባራት ወገዳማት ሰማያዊት ጽዮን ብርብር ማርያም ትባላለች።

በህገ ኦሪት ከክርስቶስ ልደት 800 ዓመት በፊት በደብተረ ደንኳን በሊቀ ካህኑ ሳዶቅ ልጅ ካህኑ አዛርያስ ህገ እግዚአብሔር ተዘርግቶባታል።
በ1440 ዓ.ም አፄ ዘርዓ-ያዕቆብ ከትግራይ፣በ530 ዓ.ም አፄ ልብነ-ድንግል እንዲሁም በ1961 ዓ.ም ግርማዊ ቀዳማዊ አፄ ኃይለሥላሴ ወደ ቤተ-ክርስቲያኗ በመምጣት መሳለማቸውና ድጋፍ እንዲሆን የሰጧቸው የተለያዩ ንዋዬ ቅድሳትን በገዳሟ ይገኛሉ።

የብርብር _ ማርያም ገዳም ከጋሞ ዞን ርዕሰ ከተማ አርባምንጭ 67 ኪ.ሜ ርቀት እንዲሁም ከምዕራብ አባያ ወረዳ ከተማ ብርብር 82 ኪ.ሜ ርቀት ላይ ትገኛለች፡፡
ከተለያዩ የሀገሪቱ አከባቢዎች የሚጡ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ እምነት ተከታይ ምዕመናን አዘውትረው ፀሎት የሚያደርሱበት ስፍራ ነው፡፡

ጥንታዊና ታሪካዊ የሆኑ በርካታ ንዋየ ቅድሳትና መንፈሳዊ ቅርሶች ያቀፈች ገዳም ናት።
በዚህች ገዳም በርካታ ሀገርንና ህዝብን ሊጠቅሙ የሚችሉ የባህልና የቅርስ ማስረጃዎች ይገኛሉ።
ይህንንም ከግምት በማስገባት የኢፌድሪ ቅርስ ጥናትና ጥበቃ ባለስልጣን በሀገር ቅርስነት መዝግቦ በተለያዩ ጊዜያቶች እየተንከባከባትም ይገኛል።

የገዳሟ የቅርስ ይዘትን ስንመለከት ፦ በርካታ የብራና መፃህፍት፣ ከነገሥታት የተበረከቱ ጥንታዊ መፅሐፍት ፣ የቅዳሴ መስቀሎችና ሌሎች ቅርሶች ይገኛሉ።
የዚህችን ገዳም ታሪካዊነት ከሚያሳዩ የቁም ማስረጃዎች ዋና ዋናዎቹ ገዳሟ በአካባቢው የጋሞ ቤት አሰራር መሠረት የተሰራ ሲሆን የህንጻው ባህላዊ የቤት አሰራርም ጥበብ አሁን ላይ ይዘቱን እንደጠበቀ ይገኛል፡፡

የብርብር ማርያም ገዳም በአሁኑ ወቅት በጥሩ ሁኔታ ላይ ብትሆንም ቅርሶቹ የሚገኙበት ሁኔታ ካላት ውድ ዘመን ተሻጋሪ ሀብት አንጻር ለአደጋ የተጋለጠ በመሆኑ ከትውልድ ወደ ትውልድ እንዲተላለፍ ዘመናዊ ቤተ-መዘክር ሊገነባለት ይገባል።
አክሱም ጽዮንን ተሳልመው ይሆናል፤ጣና ቂርቆስን ረግጠው ሊሆን ይችላል፤ከተድባባ እና መርጦለማርያምንም በረከት ቢያፍሱም መልካም ነው።

ነገር ግን ብርብር ማርያም የምትባል አንድ ደቡቧዊር የህገ ኦሪትና ህገ ወንጌል ግምጃ ቤት በጋሞዎች መንደር አለች።

እሷ ትቀራችዋለች። ይሳለሟት፤ይርገጧት። በረከትና ቃልኪዷኗ ነፍስን አንጽቶ ስጋን የሚያከብር ነው።
@EotcLibilery
@EotcLibilery
@EotcLibilery


የሰማዕታት ውበት
             
Size:-59.9MB
Length:- 1:04:40

    በርእሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማ
@mezigebehayimanot
@mezigebehayimanot
@mezigebehayimanot

Показано 20 последних публикаций.