ESAT (ኢሳት🇪🇹)®


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: Новости и СМИ


ለማንኛውም አስተያየት እና ጥቆማ 👉 @Esat_tv_comment_bot
🇪🇹ኢሳት የኢትዮጵያ አይን እና ጆሮ🇪🇹

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
Новости и СМИ
Статистика
Фильтр публикаций


የፕሪቶሪያውን ስምምነት በሚመለከት በአፍሪካ ሕብረት ሪፖርት ቀርቦ ውይይት ተካሄደ‼️

በትግራይ ክልል የነበረውን ግጭት ያስቆመው የፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት ሂደትን በተመለከተና ከስምምነቱ "ሌሎች ምን እንማር?" በሚል ርዕስ ዛሬ የካቲት 9ቀን 2017ዓ.ም በአፍሪካ ህብረት ሪፓርት ቀርቦ ውይይት ተካሂዷል።

በዚህ ውይይት ላይም የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዚዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ እና የህወሓት ሊቀመንበር ደብረ ጽዮን ገብረሚካኤል(ዶ/ር) የተገኙ ሲሆን ከኢትዮጵያ መንግሥት በኩል ደግሞ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ጌድዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) ፣ የሰላም ሚኒስትሩ አቶ መሐመድ እድሪስ እና ሌሎች ተገኝተዋል።

የፕሪቶሪያውን ስምምነትና አፈፃፀም የተመለከተውን ሪፓርት ደግሞ ተሰናባቹ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ-መንበር ሙሳ ፉኪ ማህማት፣ የቀድሞ የናይጀሪያ ፕሬዚዳንትና የአፍሪካ ህብረት አደራዳሪ ቡድን ሰብሳቢ ኡሊሲንጎን ኦባሳንጆ እና ከፍተኛ ኮሚሽነሮች አቅርበዋል።ከአንድ ሰአት በላይ የዘለቀ ውይይት ከተካሄደ በኋላ አቶ ጌታቸው ከጋዜጠኞች ለቀረበላቸው ጥያቄዎች ምላሽ ሰጥተዋል።

የጊዜያዊ አስተዳደሩ ፕሬዚዳንት


የእርስዎን ቅንጡ ኑሮ የሚመጥን ዘመናዊ አፖርታማ እያፈላለጉ ነው??

በመሀል አዲስ አበባ ሳር ቤት አካባቢ
ላቅ ባለ ጥራት ተገንብቶ የተጠናቀቁ ቤቶች ባለቤት መሆን ይችላሉ።

ሆራ ሪል እስቴት እጅግ ዘመናዊ የሆኑ ባለ 4 መኝታ አፓርታማዎችን አቅርቦሎታል።

✅ በባለ 3 እና 4 መኝታ ክፍል አማራጭ

✅ በ 225 እና 305 ካሬ ስፋት

✅ ግንባታቸው 99 % የተገነቡ በ 2 ወር ውስጥ የምትረከቡት

✅ 50% የባንክ ብድር የተመቻቸላቸው


ለበለጠ መረጃ ይደውሉልን።

0920224609 | @Tsedalproperties


በመጨረሻው ዙር የእስረኞች ልውውጥ እስራኤል 369 ፍልስጤማውያንን ከእስር ለቀቀች‼️

በእስራኤል እና ሀማስ የተኩስ አቁም ስምምነት መሰረት በመጨረሻው ዙር የእስረኞች ልውውጥ ሃማስ 3 እስራኤላውያን ታጋቾችን ሲፈታ እስራኤል በምላሹ 369 እስረኞችን ለቅቃለች።

የእስራኤል ማረሚያ ቤት አገልግሎት 369 የፍልስጤም እስረኞች መፈታት ሙሉ ለሙሉ መጠናቀቁን የሚያረጋግጥ መግለጫ አውጥቷል።

በተመሳሳይ ዓለም አቀፉ የቀይ መስቀል ኮሚቴ በበኩሉ የእስረኞች ልውውጥ ማጠናቀቁን አስታውቋል።

በስድስተኛው ዙር የእስረኞች ልውውጥ እስራኤል 369 ፍልስጤማውያን እስረኞችን የፈታችው ሀማስ 3 ታጋቾችን መልቀቁን ተከትሎ መሆኑ ተነግሯል፡፡

@Esat_tv1
@Esat_tv1


የጅቡቲ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር መሃሙድ የሱፍ አዲሱ የአፍሪካ ህብረት ሊቀመንበር ሆነው ተመረጡ‼️

የ59 ዓመቱ ዲፕሎማት ለሚቀጥሉት አራት ዓመታት ኮሚሽኑን እንዲመሩ የተመረጡት ዛሬ በአዲስ አበባ መካሔድ በጀመረው የአፍሪካ ኅብረት ዓመታዊ የመሪዎች  ጉባኤ ላይ ነው።

የሱፍ የተመረጡት የኬንያውን የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር ራይላ ኦዲንጋ እንዲሁም የማዳጋስካሩን ሪቻርድ ራንድሪያማንድራቶን በማሸነፍ ነዉ።

55 አባል አገራት ያሉትን ህብረቱን እኤአ ከ 2017 ጀምሮ በሊቀመንበርነት ሲመሩ የነበሩትን ሙሳ ፋኪን በመተካት ያገለግላሉ።

@Esat_tv1
@Esat_tv1


ሰሜን ኮርያ የቶተንሀምን ጨዋታ አገደች‼️

የሰሜን ኮርያው መሪ ኪም ጆንግ ኡን በሀገሪቱ ውስጥ የሰሜን ለንደኑ ክለብ ቶተንሀም ጨዋታዎች እንዳይተላለፉ ማገዳቸው ተገልጿል።

ኪም ጆንግ ኡን ጠላት የሚሏቸው ጎረቤት ሀገራትን ተጨዋች የያዘ ክለብ ምንም አይነት ጨዋታ በሀገሪቱ ሚዲያ እንዳይሰራጭ ማዘዛቸውን ሚረር ዘግቧል።

የሰሜን ለንደኑ ክለብ ቶተንሀም በአምበልነት የሚመራው በደቡብ ኮርያዊው የፊት መስመር ተጨዋች ሰን ሁንግ ሚን መሆኑ ይታወቃል።

በርካታ ሚሊዮን ሰሜን ኮርያዊያን የእንግሊዝ ፕርሚየር ሊግን እንደሚከታተሉ ሲነገር የሀገሪቱ ብሔራዊ ቲቪ በቀን ውስጥ ለተወሰነ ሰዓት ጨዋታዎችን ያሳያል ተብሏል።

ይሁን እንጂ በቴሌቪዥን ጣቢያው የፕርሚየር ሊግ ጨዋታዎች የሚተላለፉት ከተደረጉ አራት ወራት በኋላ መሆኑ ተገልጿል።

@Esat_tv1
@Esat_tv1


በሬክተር ስኬል 6.0 የተለካ የመሬት መንቀጥቀጥ ከመተሐራ ከተማ አቅራቢያ ተከሰተ‼️

ከመተሐራ ከተማ ስድስት ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በሚገኝ አካባቢ ላይ በሬክተር ስኬል 6.0 የደረሰ የመሬት መንቀጥቀጥ መከሰቱን የአሜሪካ የጂኦሎጂካል ሰርቬይ መስሪያ ቤት አስታወቀ። ዛሬ አርብ ምሽት 5 ሰዓት ከ28 ደቂቃ ላይ የደረሰው ርዕደ መሬት፤ ባለፈው አንድ ወር ውስጥ ከተመዘገቡት ሁሉ በመጠን ከፍተኛው ነው።

የዛሬው የመሬት መንቀጥቀጥ ያስከተለው ንዝረት “በጣም ጠንካራ” ሆኖ የተሰማው በመተሐራ ከተማ ይሁን እንጂ መዲናይቱን አዲስ አበባን ጨምሮ በርካታ ከተሞችን ማዳረሱን የአሜሪካው የምርምር ተቋም ገልጿል። የርዕደ መሬቱ ንዝረት በአዋሽ ከተማ “መጠነኛ” እንደነበር ያመለከተው ተቋም፤ በአዳማ፣ ሞጆ፣ ቢሾፍቱ እና ደብረ ብርሃን ከተሞችም በተመሳሳይ መጠን መከሰቱን ጠቁሟል።

በመተሐራ እና አዋሽ ከተሞች አቅራቢያ ያሉ አካባቢዎች ባለፉት ወራት የመሬት መንቀጥቀጥ በተደጋጋሚ ሲከሰትባቸው የቆዩ ናቸው።

@Esat_tv1
@Esat_tv1


የደብረፅዮን እና የጌታቸው ቡድኖች ለመነጋገር ተስማምተዋል‼️

የህወሓት አመራሮች ችግሮቻቸውን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት የስነምግባር መመሪያ ተፈራረሙ
የህወሓት አመራሮች ሁሉን አቀፍ ችግሮቻቸውን በሰላምና በውይይት ለመፍታት ተስማምተዋል፤ ለዚህም ይረዳ ዘንድ የስነ ምግባር ደንብ አውጥተው ተፈራርመዋል ሲሉ የትግራይ የሀይማኖት አባቶች አስታወቁ።

የሀይማኖት አባቶቹ ዛሬ በመቀለ ከተማ በሰጡት መግለጫ፤ “ስምምነቱን ወደፊት ለማራመድ በሚል ሁለቱም ወገኖች የስነ ምግባር ደንብ አውጥተው ተፈራርመዋል” ማለታቸውን ትግራይ ቴሌቪዢን ዘግቧል፡፡

@Esat_tv1
@Esat_tv1


ሐማስ ታጋቾችን የሚለቀው በጋዛ የተኩስ አቁም ስምምነት መሠረት መሆኑን አስታወቀ‼️

እስራኤል ከተወሰኑ የጋዛ አካባቢዎች መውጣቷን ተከትሎ ፍልስጤማዊያን ወደ ቀያቸው መመለስ ጀምረዋል
ከ 2 ሰአት በፊት ሐማስ በጋዛ የተኩስ አቁም ስምምነት መሠረት ታጋቾችን መልቀቅ እንደሚቀጥል አስታወቀ።

ይህን የሐማስ ውሳኔ ተከትሎ የተኩስ አቁም ስምምነቱ ፈርሶ ድጋሚ ጦርነት ሊጀምር ይችላል የሚለው ስጋት ቀንሷል።

የፍልስጤሙ ታጣቂ ቡድን በግብፅ ከተካሄደ ውይይት በኋላ በሰጠው መግለጫ የግብፅ እና የኳታር አደራዳሪዎች "እንቅፋቶችን ያስወግዳሉ" ብሏል።

የግብፅ እና የኳታር አደራዳሪዎችም ተፈጥሮ የነበረው አለግባባት መፈታቱን አስታውቀዋል።
የእስራኤል መንግሥት ቃል አቀባይ በጉዳዩ ላይ አስተያየት ባይሰጡም ቡድኑ በሚቀጥለው ቅዳሜ ሶስት ታጋቾችን የማይለቅ ከሆነ ጦርነት ይጀመራል ብለዋል።

ሐማስ፤ እስራኤል ስምምነቱን ጥሳለች በሚል ታጋቾችን እንደማይለቅ ማስታወቁን ተከትሎ የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ባለፈው ማክሰኞ ጦርነት ይጀመራል የሚል ዛቻ አሰምተው ነበር።

ሐማስ፤ መጠለያዎችን ጨምሮ አስፈላጊ የሆኑ ሰብዓዊ እርዳታዎች እንዳይደርሱ አድርጋለች ሲል ነው እስራኤልን የከሰሰው። እስራኤል የሐማስን ወቀሳ ታስተባብላለች።

የአሜሪካው ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ እስራኤል ስምምነቱን እንድታቋርጥ ሐሳብ አቅርበው "ሁሉም ታጋቾች ቅዳሜ የማይፈቱ ከሆነ ገሀነም ይወርዳል" ማለታቸው ይታወሳል።

@Esat_tv1
@Esat_tv1


የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ አገልግሎቶችን በአንድ አጠቃሎ የያዘ የሞባይል መተግበሪያ ይፋ ሆነ‼️

በብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያ ፕሮግራም ፅህፈት ቤት የውስጥ አቅም ለምቶ ስራ ላይ የዋለው መተግበሪያው በአንድሮይድ እና አይኦኤስ (iOS) ኦፕሬቲንግ ሲስተሞች ለህዝብ ይፋ ሆኗል።

መተግበሪያው በተለያየ ምክንያት የፋይዳ ቁጥር የጠፋባቸው ወይም ያልደረሳቸው ወዲያውኑ መልሰው ማስላክ የሚችሉበት መሆኑን የብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያ ፕሮግራም ፅህፈት ቤት ኮሙኒኬሽን እና ህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቤኔዘር ፈለቀ በሰጡት መግለጫ አስታውቀዋል።

ከዚህ በተጨማሪ በመተግበሪያው የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያን በዲጂታል መልኩ ለማግኘት እንዲሁም አውርዶ ለመያዝ እንደሚቻልም ነው ኃላፊው የተናገሩት።

መተግበሪያው የተለያዩ ሂደቶችን አልፎ ከመረጃ መረብ ደህንነት አገልግሎት የብቃት ማረጋገጫ አግኝቶ ወደ ስራ መግባቱንም አስረድተዋል።

በምዝገባ ወቅት በባለሙያ ምክንያት የተሳሳተን የስነህዝብ መረጃም ጣቢያ ድረስ መምጣት ሳያስፈልግ በስልክ ማረም እንዲሁም የአድራሻ እና የኢሜል ለውጥ ሲኖር ካሉበት ሆኖ ማደስ የሚቻልበት ነው።

መተግበሪያው የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያን በካርድ መልክ አሳትሞ ለመያዝ፣ የካርድ ህትመት ለማዘዝ፣ አስተያየት እና ቅሬታ ለማቅረብ እንዲሁም የደንበኞች አገልግሎትን ለማግኘት የሚያስችል ለአጠቃቀም ቀላል እና ምቹ መሆኑንም አቶ አቤኔዘር ገልፀዋል።

ይህን መተግበሪያ ጨምሮ የተለያዩ የደንበኞች ፖርታሎች በብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያ ፕሮግራም ፅህፈት ቤት ባለሙያዎች መልማታቸውንም የፅህፈት ቤቱ የኮሙኒኬሽን እና ህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቤኔዘር ፈለቀ ተናግረዋል።

@Esat_tv1
@Esat_tv1


ሐማስ እስከ መጪው ቅዳሜ ታጋቾችን ካልለቀቀ ጦርነት እንደምትጀምር እስራኤል አስጠነቀቀች‼️

የታጋቾች መለቀቅ ጊዜው መራዘሙን ተከትሎ ቤንያሚን ኔታንያሁ በጦርነት በወደመችው ጋዛ ውስጥ እና በአካባቢው ጦራቸው እንዲሰማራ ማዘዛቸውን ተናግረዋል።

በመጀመሪያው ምዕራፍ የተኩስ አቁም ስምምነት መሰረት በመጪው ቅዳሜ ሶስት ታጋቾች ይለቀቃሉ የተባለ ቢሆንም ኔታንያሁ እየጠየቁ ያሉት ሶስቱን ብቻ ሳይሆን በአጠቃላይ ቀሪዎቹን 76ቱን መሆኑን አንድ ሚኒስትር ተናግረዋል።

ሐማስ ለሶስት ሳምንታት የሚፈጀውን የመጀመሪያውን የተኩስ አቁም ስምምነት ምዕራፍ "በማወሳሰብ፣ ወይም በማዘግየት እስራኤል ተጠያቂ ናት" የሚል ምላሽ ሰጥቷል

@Esat_tv1
@Esat_tv1


በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን የሱሉልታ ወረዳ ዋና አሥተዳዳሪ የሆኑት አበበ ወርቁ ራሱን የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት ብሎ በሚጠራው አማጺ ቡድን በደረሰባቸው ድንገተኛ ጥቃት መገደላቸውን ዋዜማ ከምንጮቿ ሰምታለች‼️

ታጣቂ ቡድኑ ጥቃቱን የፈጸመው ዛሬ የካቲት 5 ቀን 2017 ዓ.ም ከቀኑ 9 ሰዓት አካባቢ መሆኑን የገለጹት የዋዜማ ምንጮች፣ ከወረዳ አሥተዳዳሪው ጋር የነበረ የወረዳው የጸጥታ ዘርፍ ኃላፊ በቡድኑ ታፍኖ መወሰዱን አስረድተዋል።

ዋና አሥተዳዳሪው፣ የጸጥታ ዘርፍ ኃላፊው እና በርካታ የጸጥታ ኃይሎች ታጣቂ ቡድኑ በስፋት ይንቀሳቀስበታል ወደተባለው "ሞዬ ጋጆ" በተባለው ስፍራ ሲደርሱ አማጺ ቡድኑ ድንገተኛ የእሩምታ ተኩስ እንደከፈተባቸው ተጠቁሟል።
በዚህም ዋዜማ ለጊዜው ቁጥራቸውን ማጣራት ያልቻለችው የጸጥታ ኃይሎች ሲገደሉ፣ በርካቶች ደግሞ ቆስለው ጫንጮ ሆስፒታል መግባታቸውን ምንጮች ተናግረዋል።

ከጸጥታ ዘርፍ ኃላፊው በተጨማሪ በርካታ የጸጥታ ኃይሎች በቡድኑ ታፍነው መወሰዳቸውንም ዋዜማ ባደረገችው ማጣራት መረዳት ችላለች።

ከወራት በፊትም በተመሳሳይ በዚሁ ታጣቂ ቡድን ጥቃት የወረዳው ፖሊስ አዛዥ የሆኑት ኮማንደር ለገሰ ሥዩም መገደላቸውን ዋዜማ መዘገቧ ይታወሳል።

ሟቹ አበበ ከሁለት ዓመት በፊት የወረዳው ዋና አሥተዳዳሪ ሆነው ከመሾማቸው በፊት፣ የወረዳው የብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊ እንደነበሩ ዋዜማ የደረሳት መረጃ ያመለክታል።
©ዋዜማ

@Esat_tv1
@Esat_tv1


የአየር መንገዱን አሠራር ጥሰዋል በተባሉ የአዲስ አበባ ሽያጭ ቢሮ ሠራተኞች ላይ ዕርምጃ መወሰዱ ተገለጸ‼️

የሕግ ክፍሉ ክስ መመሥረት የሚቻልባቸውን ሁኔታዎች እየተመለከተ ነው ተብሏል፣

ከኢትዮጵያ አየር መንገድ የማስታወቂያና የሕዝብ ግንኙነት የሥራ ክፍሎች ዕውቅና ውጪ፣ በቅጥር ግቢው ውስጥ የፎቶና የቪዲዮ ቀረፃዎች እንዲካሄዱ ፈቃድ ሰጥተዋል የተባሉ የአዲስ አበባ ሽያጭ ክፍል ሠራተኞች ላይ አስተዳደራዊ ዕርምጃዎች መወሰዱ ተገለጸ።

ይህ የተገለጸው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን ጣሰው፣ እንዲሁም የአየር መንገዱ የንግድ ዘርፍ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ለማ ያደቻ ወቅታዊ ጉዳዮችን አስመልክቶ ዛሬ የካቲት 5 ቀን 2017 ዓ.ም. በአየር መንገዱ ዋና መሥሪያ ቤት ጋዜጣዊ መግለጫ ሲሰጡ ነው።

ኢትዮጵያ እያስተናገደችው ስለምትገኘው የአፍሪካ ኅብረት ጉባዔን ጨምሮ በተለያዩ ወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ማብራሪያ የሰጡት ዋና ሥራ አስፈጻሚው አቶ መስፍን፣ በቅርቡ ለተዋናይትና ሞዴል ምሕረት ታደሰ (ፒፒሎ) የልደት በዓል አየር መንገዱ ፈቃድ ሰጥቶ ተቀርጿል በሚል ስለተሠራጩት የግለሰቧ ቪድዮዎችና ምሥሎች፣ እንዲሁም የአየር መንገዱ ከፍተኛ አመራሮች ስለጉዳዩ መረጃ አልነበራቸውም በሚል ስለተሰጠው ምላሽ ጉዳዩን በዝርዝር እንዲያብራሩ ከጋዜጠኞች ጥያቄዎች ቀርቦላቸዋል።

አቶ መስፍን፣ ‹‹ቪድዮው መቀረፁ ትክክል ነው። ለግለሰቧ ሕጋዊ ፈቃድ ተሰጥቶ የፀጥታ መምርያ ሒደቱን ተከትሎ ጥገና ወደሚደረግበት የአየር መንገዱ ቅጥር ግቢ ገብታ የተከናወነ ነው፤›› ብለው፣ ‹‹የፀጥታ ፕሮሲጀሩን አሟልታ ነው ቪድዮው የተቀረፀው። ለአዲስ አበባ ሽያጭ ቢሯችን ታኅሳስ 27 ጥያቄ ያቀረበችበት ቀን ሲሆን፣ ከሁለት ቀን በኋላ ፈቃድ ተሰጥቶ ቀረፃው ተካሂዷል፤›› ሲሉ ገልጸዋል።

ይሁንና አጠቃላይ ሒደቱ የአየር መንገዱን ተቋማዊ አሠራር በመጣስ መከናወኑን ተናግረው፣ ‹‹በአየር መንገዱ አሠራር መሠረት የማስታወቂያ ሥራዎች ሲሠሩ በሁለት መንገዶች ወይም የሥራ ክፍሎች በኩል ነው። አንደኛው በሕዝብ ግንኙነት ሥራ ክፍል ሲሆን፣ ሁለተኛው ፕሮሞሽንና ማስታወቂያ የሚባለው የሥራ ክፍል ደግሞ አየር መንገዱንና ሥራዎቹን በተመለከተ ለሕዝብ የሚተላለፉ ማስታወቂያዎችን የሚመለከተው ነው። የአርቲስቷ ሥራ ግን ከእነዚህ ሁለት ክፍሎች ውጪ ነው የተሠራው። ጥያቄው ለአየር መንገዱ የአዲስ አበባ ሽያጭ ቢሮ ሲቀርብ ለእነዚህ ሁለት የሥራ ክፍሎች መተላለፍ ነበረበት፤›› ሲሉ አስረድተዋል።

የአየር መንገዱ ከፍተኛ አመራሮች ከአሠራር ጥሰት ባለፈ ስለጉዳዩ ከፍተኛ አመራሮቹ ዕውቅና አልነበራቸውም በሚል ያሠራጨውን መረጃ በተመለከተ ማብራሪያ የሰጡት ዋና ሥራ አስፈጻሚው፣ ‹‹የአዲስ አበባ ሽያጭ ቢሮ ለአዲስ አበባ የጥበቃ መምርያ በቀጥታ ነው ፈቃድ እንደተሰጣት የሚገልጽ ደብዳቤ የጻፈው፡፡ ከፍተኛ አመራሩ ስለጉዳዩ መረጃ ሊኖረው የሚችለው የማስታወቂያው ጥያቄ ቀደም ሲል በጠቀስኳቸው ሁለት የሥራ ክፍሎች በኩል ሲመጣ ብቻ ነው፣ ይህ አልሆነም። በኋላ የተፈጠረውን ነገር ስንሰማም የአየር መንገዱ ከፍተኛ አመራሮች በቀጥታ ለኦዲት ክፍሉ መመርያ ሰጥተን፣ ስለጉዳዩ ሙሉ ሪፖርትና ምክረ ሐሳብ ካቀረበልን በኋላ ነው የተንቀሳቀስነው፡፡ የማስታወቂያ ሥራዎችን ለመሥራት ፈቅደን ቢሆንና በትክክለኛዎቹ የሥራ ክፍሎች በኩል አልፎ ቢሆን ኖሮ ውል ይኖረን ነበር፣ ግን ያለ ውል ነው ሥራው የተሠራው፤›› ብለዋል።

በአየር መንገዱ የአውሮፕላኖች ጥገና በሚካሄድበት ቅጥር ግቢ ቪዲዮውን የቀረፀችውና ምሥሉ ከተቀረፀ ከአንድ ወር በላይ ቆይታ ካሠራጨችው ግለሰብ ለአዲስ አበባ ሽያጭ ክፍል ፈቃድ ለመጠየቅ ገቢ የተደረገው ደብዳቤ፣ ‹‹የአየር መንገዱን ክብር በሚጠብቅ መልኩ አየር መንገዱን መሠረት በማድረግ አገሪቱን ለቱሪዝም ሥራዎች ለማስተዋወቅ›› የሚሉ ምክንያቶች የቀረቡ ሲሆን፣ ‹‹ማናቸውንም ምሥሎችና ቪዲዮዎችን ለአየር መንገዱ ገቢ እናደርጋለን፤›› በማለት የተጠቀሰ መሆኑን ሪፖርተር የተመለከተው ደብዳቤ ያሳያል፡፡

ይሁን እንጂ ማናቸውም ፎቶዎችም ይሁኑ ተንቀሳቃሽ ምሥሎች ለኢትዮጵያ አየር መንገድ የትኛውም የሥራ ክፍል ከግለሰቧ አስቀድመው እንዳልተሰጡ የሪፖርተር ምንጮች አረጋግጠዋል፡፡
ከዚህ አኳያ በሕግ ሊኖር የሚችል ተጠያቂነትን በተመለከተ ምላሽ የሰጡት የአየር መንገዱ ዋና ሥራ አስፈጻሚ፣ ‹‹ከሕግ ክፍላችን ጋር ተነጋግረን በሕግ አግባብ የምትጠየቅበት ሆኖ ካገኘነው እንጠይቃለን፤›› ብለዋል።

‹‹ችግሩ የተፈጠረው በውስጣችን በተፈጠረ የአሠራር ክፍተት ነው። አስተዳደራዊ ዕርምጃዎችን ወስደናል፣ እየወሰድንም ነው። የአየር መንገዱ ከፍተኛ አመራር ጉዳዩን ትኩረት ሰጥቶ ነው የሚያየው። አንደኛ በዚህ ጉዳይ የተሳተፉት ላይ ጠበቅ ያለ ዕርምጃ እንወስዳለን። ሁለተኛ ጥፋቱ እንዳይደገም የሚያስችል አሠራር እየዘረጋን ነው፤›› ሲሉ ተናግረዋል፡፡

@Esat_tv1
@Esat_tv1




ለመቄዶንያ የአረጋውያንና የአእምሮ ህሙማን መርጃ እየተደረገ ባለው ገቢ ማሰባሰብያ በ4 ቀናት 200 ሚሊዮን ብር ደረሰ‼️

ለመቄዶንያ የአረጋውያንና የአእምሮ ህሙማን መርጃ  የገቢ ማሰባሰቢያ እየተካሄደ በሚገኘው መርሀ ግብር ላይ በ4 ቀናት ብቻ 200,000,000 (ሁለት መቶ ሚሊዮን) ብር መሰብሰብ ተችሏል።

በዚህ የበጎ ዓላማ፣ በጎፈንድ ሚ  341 ሺ 538 ዶላር እንዲሁም በካሻኘ እና ዜል ደግሞ 528 ሺ ዶላር ገቢ ሆኗል። ይኸን ድጋፍ በመላው ዓለም የሚገኙ በርካታ ኢትዮጵያውያን እየተረባረቡ ይገኛሉ።

መርሀ ግብሩን ሰይፉ ኦን ኢቢኤስ በማህበራዊ ሚዲያ በቀጥታ ስርጭት ለተመካቾች እየደረሰ ሲሆን፣ ከተለያዩ የሀይማኖት ተቋማት የመጡ መምህራን፣ የኪነ ጥበብ ሰዎች እና የሚዲያ ባለሞያዎች መድረኩን በማድመቅ ለጋሾችን በማበረታታት ላይ ናቸው።

አሁንም በዚህ የገቢ ማሰባሰቢያ "ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን በቂ ነው" የምትሉ ወገኖች ድጋፋችሁን እንድትቀጥሉ አዘጋጆቹ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።

@Esat_tv1
@Esat_tv1


የአፍሪካ ህብረት ጉባኤ ተጀምሮ እስከሚጠናቀቅ የሞተር ሳይክል እንቅስቃሴ ተከልክሏል‼️

🗣 የአዲስ አበባ ከተማ ትራንስፖርት ቢሮ

በአዲስ አበባ ከተማ የሚካሄደው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ ተጀምሮ እስከሚጠናቀቅ ድረስ የሞተር ሳይክል እንቅስቃሴ መከልከሉን የአዲስ አበባ ከተማ የትራንስፖርት ቢሮ አስታውቋል።

በዚህም ከዛሬ የካቲት 04 2017 ዓ.ም ከዚህ ሰዓት ጀምሮ እስከ የካቲት 09 2017 ዓ.ም ድረስ በመዲናዋ በየትኛውም አካባቢ ሞተር ሳይክል ማሽከርከር የማይቻል መሆኑን ቢሮው በማህበራዊ ትስስር ገፁ ገልጿል።

@Esat_tv1
@Esat_tv1


በወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ ከመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት የተሰጠ መግለጫ‼️

@Esat_tv1
@Esat_tv1


ሳዑዲ ኔታንያሁ ፍልስጤማውያንን በማፈናቀል ዙሪያ የሰጡትን አስተያየት ውድቅ አደረገች‼️

ኔታያሁ “በሳዑዲ ግዛቷ ላይ የፍልስጤም መንግስት መመስረት ትችላች” ሲሉ መናራቸው ይታወሳል። ሳዑዲ "ይህ የወራሪና አክራሪ አስተሳሰብ የፍልስጤም ግዛት ለፍሊስጤማውያን ምን ማለት እንደሆነ አይረዳም" ብላለች።

@Esat_tv1
@Esat_tv1


ዶናልድ ትራምፕ የአፍሪካ መሪዎች ሰው መሆናቸውን እጠራጠራለሁ አሉ‼️

ከ50 ዓመታት የአህጉሪቷ የነጻነት ጉዞ በኋላ፣ ለህዝባችው አስፈላጊውን መሠረተ ልማት ካላሟላችው ሰው ነን ብላችው ታስባላችው?


በወርቅ፣ በአልማዝ፣ በነዳጅ፣ በዩራኒየም፣ በብረት፣ በማዕድን፣ በብር፣ በማግኒዥየም፣ በነሐስ፣ በጋዝ የተፈጥሮ ሃብቶቻችው ላይ ተቀምጣችው፣ ህዝባችው በረሃብ፣ በትምህርት አለመዳረስ፣ በጤና አገልግሎት እጦት፣ ቢሞት፣ ሰው ነን ብላችው ታምናላችው?

በስልጣን ላይ ቆይታችው፣የራሳችሁን  ዜጎች ለመግደል ከውጭ የጦር መሣሪያዎችን ስታስገቡ፣ ሰው ነን ብላችው ታስባላችው?

የገዛ ዜጎቻችሁን እንደውሻ ስታንገላቱና ስትገድሉ፣ ማን ዜጎቻችሁን እንዲያከብር  ትጠብቃላችው?

በራሳችው  አገር ላይ ቀማኛና ሌባ በመሆናችው ፣ የሃገራችሁን  ሀብቶች ሁሉ በመስረቅ፣ አብዛኞቹ ዜጋዎቻችው በስደትና በድህነት ውስጥ እንዲያልፉ ስታረጉ፣ የሰው ልጆ ነን ብላችው ታስባላችው?

ትራምፕ ይሄን የተናገሩት ሰሞኑን በዋሽንግተን ዋይት ሀውስ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ነው።

@Esat_tv1
@Esat_tv1

Показано 18 последних публикаций.