በኢትዮጵያ 39 በመቶ የሚሆኑት ከአምስት አመት በታች ያሉ ህጻናት የመቀንጨር ቸግር ገጥሟቸዋል ተባለ
ጤና ሚኒሲቴርና ዩኒሴፍ ባደረጉት ጥናት መሰረት ትግራይን ሳይጨምር በኢትዮጵያ 39 በመቶ ከአምስት አመት በታች ያሉ ህጻናት የመቀንጨር ችግር እንዳጋጠማቸው ታዉቋል፡፡
በጤና ሚኒሲቴር የስርዓተ ምግብ ማስተባበሪያ ክፍል ፤የስርዓተ ምግብ መከታተል የዴስክ ሃላፊ ቅድስት ወልደሰንበት፤ይህ ቁጥር የትግራይ ክፍል ጥናቱ ሲታይ ከዚህ ሊያልፍ እንደሚችል ስጋታቸዉን ገልፀዉልናል፡፡
ባለፉት በርካታ ዓመታት የመቀንጨር ምጣኔ የቀነሰ መስሎ ቢታይም፣ በቅርቡ በተደረገው ጥናት ከፍተኛ መሆኑ ጠቁመዋል፡፡
ይህም 39 በመቶ ዕድሜያቸው ከአምስት ዓመት በታች የሆኑ ሕፃናት የመቀንጨር፣ 11 በመቶ ያህሉ ደግሞ የመቀንጨር ምጣኔ እንደታየባቸው ተናግረዋል፡፡
ለዚህም ለልጆች የተመጣጠነ ምግብ እጥረት በርካታ ምክንያቶች አሉ ያሉት ሃላፊዋ፤ የተመጣጠነ ምግብ እጥረት፣ ድህነት፣ በቂ የጤና እንክብካቤ እጥረት፣ የጡት አለማጥባት፣ የንጽህና እጦትና የኑሮ ሁኔታ ዋና ዋናዎቹ ብለዋል።
ከዚህ በተጨማሪ በሃገሪቱ ዉስጥ ያለዉም የሰላምና ፀጥታ ችግር አንዱ ምክንያት ነዉ ብለዉናል፡፡
ከአምስት ዓመት በታች በሆኑ ሕፃናት ላይ ከሚደርሰው ሞት ግማሽ ያህሉ በተመጣጠነ ምግብ እጥረት ሳቢያ የሚከሰት ነዉ፡፡
ከሞት የተረፉትም፣ የአዕምሮ ዘገምተኛ የመሆን ዕድላቸው የሰፋ ከመሆኑም ባሻገር፣ የመማር፣ የማሰብ፣ የመረዳትና የማስታወስ ችሎታቸውም ዝቅተኛ ነው ተብሏል፡፡
በአዋቂነት ዘመን በሚሰማሩበት ዘርፍ ሁሉ ውጤታማና አምራች ዜጋ እንደማይሆኑም ገልጸዋል፡፡
የኢትዮጵያ የምግብ ሥርዓት ትራንስፎርሜሽን አያያዝን በተመለከተ ዲዛይን ተደርጎ ከሚመለከታቸዉ ባለድርሻ አካላት ጋር እየተሰራ ነዉም ብለዉናል፡፡
ከዚህ ዉጭ ሁሉ ማህበረሰብ እዚህ ላይ ርብርብ ሊያደርግ እንደሚገባ ተገልጿል፡፡
[ልዑል ወልዴ]
@Ethionews433 @Ethionews433