4-3-3 World News


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: Новости и СМИ


ይህ የእርሶ፣ የአንተ፣ የአንቺ፣ የእናንተ፣ የኛ የሁላችንም ድምጽ ነው! ለሃሳብ አስተያየት ለመስጠት @atsbaha12 ይጠቀሙ

Связанные каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
Новости и СМИ
Статистика
Фильтр публикаций


ቴል አቪቭ-ሐማስ ከሚለቃቸዉ ታጋቾች አንዱ ኢትዮጵያዊ-እስራኤላዊ ነዉ

እስራኤልና ምዕራባዉያን መንግሥታት በአሸባሪነት የሚወነጅሉት የፍልስጤም ደፈጣ ተዋጊ ቡድን ሐማስ በቅርቡ ከሚለቃቸዉ ታጋቾች አንዱ ኢትዮጵያዊ-እስራኤላዊ ነዉ። እስራኤልና ሐማስ ባለፈዉ ጥር ባደረጉት ሥምምነት መሠረት በመጀመሪያዉ ዙር ከተለቀቁና ከሚለቀቁ ታጋቾች 6ቱ በመጪዉ ቅዳሜ ይለቀቃሉ ተብሎ ይጠበቃል። ከሥድስቱ ታጋቾች አንዱ ኢትዮጵያዊ-እስራኤላዊ አቬራ መንግሥቱ ነዉ።አቬራ መንሥቱ እንደ ሌሎቹ ታጋቾች ሐማስ መስከረም 29፣ 2016 ደቡባዊ እስራኤልን በወረረበት ወቅት የታገተ አይደለም።ጀሩሳሌም ፖስት የተባለዉ የእስራኤል ጋዜጣ ምንጮችን ጠቅሶ ባለፈዉ ጥር በኢንተርኔት እንደዘገበዉ የ38ት ዓመቱ ጎልማሳ እንደ ግሪጎሪያኑ አቆጣጠር መስከረም 7፣2014 በራሱ ፈቃድ ጋዛ ገብቶ እጁን ለሐማስ ሰጥቷል።በዘገባዉ መሠረት ያኔዉ የ28 ዓመት ወጣት የእስራኤል ወታደር እንደነበር ሐማስ አስታዉቋል።ይሁንና ሑዩማን ራይትስ ወች የተባለዉ የመብት ተሟጋች ድርጅትና ቤተሰቦቹ የሐማስን አባባል አልተቀበሉትም።ወጣቱ የአዕምሮ ሕመምተኛ ነዉ ይባላል።ጋዛ ከመግባቱ በፊት ከእናቱ ጋር ተጣልቶ እንደነበረም ጋዜጣዉ የመብት ተሟጋቹን ድርጅት ጠቅሶ ዘግቧል።(DW)

@Ethionews433 @Ethionews433


ናይሮቢ-ጎማ ከተማ ዉስጥ በተደረገ ዉጊያ ከ5000 በላይ ሰላማዊ ሰዉ ተገድሏል-መንግስት

የምሥራቃዊ ኮንጎ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ትልቅ ከተማ ጎማ ዉስጥ በተደረገ ዉጊያ በትንሹ 5000 ሰላማዊ ሰዎች መገደላቸዉን የሐገሪቱ መንግሥት አስታወቀ።የጎማ ከተማን ላለማስያዝና ለመያዝ የኮንጎ መንግስት ጦር፣የአፍሪቃ መንግስታት፣የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ወታደሮችና በሩዋንዳ የሚደገፈዉ የM23 አማፂያን ባለፉት ሳምንታት ከፍተኛ ዉጊያ ሲያደርጉ ነበር።የኪንሻ መንግሥት የሩዋንዳ ወታደሮች ከአማፂዉ ቡድን ጋር አብረዉ ተካፍለዉበታል ባለዉ ዉጊያ በትንሹ 5000 ሰዎች መገደላቸዉን ትናንት ማታ አስታዉቋል።የኮንጎ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ መንግሥት ቃል አቀባይ ፓትሪክ ሙያያ እንዳሉት እስከ ትናንት ድረስ 5000 ሰዎች መቀበራቸዉን መንግስታቸዉ ከተለያዩ ምንጮች አረጋግጧል።ይሁንና የሐገሪቱ የጤና ሚንስቴር የሆስፒታል ምንጮችን ጠቅሶ እንደዘገበዉ የሟቾቹ ቁጥር 8000 ሊደርስ ይችላል።የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በቅርቡ ባወጣዉ መግለጫ ግን የ2900 ሰዎች አስከሬን ማግኘቱን አስታዉቋል።አማፂዉ ቡድን ጎማን ከተቆጣጠረ በኋላ በመቶ ሺሕ የሚቆጠሩ ነዋሪዎች ተፈናቅለዋል፤ እስረኞች ተለቅቀዋል፣ የመንግስት፣ የድርጅቶችና የግል ንብረቶች ተመዝብረዋል።ጦርነቱ ዛሬም በተለይ ኖርድ ኪቩ በተባለዉ ግዛት መቀጠሉ ተዘግቧል።(DW)

@Ethionews433 @Ethionews433


እሳቱ በቁጥጥር ስር ውሏል ....!

@Ethionews433 @Ethionews433


ለቻይና ድርጅቶች መረጃ አሳልፎ በመስጠት የተጠረጠረው ዲፕሲክ

የደቡብ ኮርያው የግል መረጃ ጠባቂ ኮሚሽን የቻይናውን የሰው ሰራሽ አስተውሎት ድርጅት ዲፕሲክን የተጠቃሚዎችን የግል መረጃ አሳልፎ እየሰጠ ነው ሲል ወንጅሎታል።

መረጃውንም ለቻይናው ለቲክቶክ እናት ኩባንያ ባይትዳንስ አሳልፎ እንደሰጠ ገልጿል።

ዲፕሲክ ከባይትዳንስ ጋር ግንኙነት መፍጠሩን ደርሼበታለሁ ያለው የደቡብ ኮርያው የግል መረጃ ጠባቂ ኮሚሽን በትክክል ምን ዓይነት እና ምን ያህል መረጃዎች እንደተጋሩ ግን አልገለጸም።

ደቡብ ኮርያ ዲፕሲክን ያገደች ሲሆን ምክንያቷም ከግል መረጃ ደህንነት ጋር በተያያዘ መሆኑን አስታውቃለች።

አውስትራሊያ እና ታይዋንም ዲፕሲክን በመንግስት ተቋማት የኤሌክትሮኒክስ መገልገያዎች ላይ መጠቀም የከለከሉ ሀገራት ሆነዋል።

አንድ የአሜሪካ የሳይበር ደህንነት ድርጅትም ዲፕሲክ ከባይትዳንስ ጋር ቀጥተኛ የሲስተም ግንኙነት እንዳለው ማስረጃ ማግኘቱን አስታውቋል። በዚህም ዲፕሲክ ለባይትዳንስ ብቻ ሳይሆን ለሌሎች የቻይና ድርጅቶች ጭምር መረጃ አሳልፎ ሳይሰጥ እንደማይቀር ጠቁሟል።

ዲፕሲክ ይፋ በተደረገበት የጥር ወር ላይ በርካታ ተጠቃሚዎች ያገኘ እና በአጭር ጊዜ ውስጥ ገበያውን ያነቃነቀ የሰው ሰራሽ አስተውሎት ነው።

በደቡብ ኮርያ ከመታገዱ በፊት ከአንድ ሚሊየን ጊዜ በላይ ሰዎች ያወረዱት የሰው ሰራሽ አስተውሎት ነበር።


5ተኛ ተጨምሯል የአሳት አጥፊ መኪና




4ተኛ ተጨምሯል .....


3 የእሳት አደጋ ደርሷል .....

@Bisrat_Sport_433et @Bisrat_Sport_433et


ከአየር ጤና አከባቢ ጭሱ 📸

@Bisrat_Sport_433et @Bisrat_Sport_433et


ግራር ልዩ ቦታው ናትራን ፕላስቲክ ማከፋፈያ(ቤተሰብ አካዳሚ) አከባቢ የአሳት አደጋ ተነስቷል !📸

@Bisrat_Sport_433et @Bisrat_Sport_433et


Репост из: 4-3-3 ስፖርት በኢትዮጵያ™
💐💐💐💐የካቲት 12💐💐💐💐

ልክ በዛሬዋ ቀን ከ88 ዓመታት በፊት፥ የካቲት 12 የጣሊያን የቀድሞ ጀነራል ሩዶልፎ ግራዚያኒ ለይ በተደረገ የግድያ ሙከራ በቀል በማለት

በ3 ቀን ውስጥ 30,000 የሚሆኑ የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎችን በተለይም ምሁሮችን እያስለቀመ ያስፈጀው።

እንኳን ለ88ኛው የየካቲት 12 ሰማዕታት መታሰቢያ ቀን አደረሳችሁ!

@Bisrat_Sport_433et @Bisrat_Sport_433et


በአፍሪካ ህብረት ስብሰባ ወቅት በጅምላ የታሰሩ ወጣቶች እስከ 20 ሺህ ብር ከፍለው እየተለቀቁ መሆኑ ታወቀ

እሁድ እለት የተጠናቀቀው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ስብሰባ ከመጀመሩ በፊት ባሉት ቀናት አዲስ አበባ ውስጥ የታሰሩ ወጣቶች ገንዘብ ከፍለው እየተለቀቁ መሆኑ ታውቋል።

እነዚህ ልደታ አካባቢ በአፈሳ መልክ የታሰሩ ወጣቶች ጦር ሀይሎች አካባቢ ታስረው የቆዩ ሲሆን አሁን ላይ እስከ 20 ሺህ ብር እየከፈሉ፣ ሌሎቹ ደግሞ ለህዳሴ ግድብ የ2 ሺህ ብር ቦንድ እንዲገዙ እየተደረጉ መለቀቃቸውን መሠረት ሚድያ ከታሳሪዎቹ እና ቤተሰቦቻቸው ሰምቷል።

"በስብሰባው ምክንያት ተሰብስባቹ ተቀመጣችሁ ተብለው ቁጭ ብለው ከሚበሉበት በረንዳ የታፈሱት ባለፈው እሮብ ነበር" የሚለው አንድ የመረጃ ምንጫችን ከትናንት ጀምሮ የተወሰኑት እየተፈቱ መሆኑን ተናግሯል።

"ቦንድ ያልገዙት ተቀምጠው እኛ ወጣን" ያለን ደግሞ ለቦንድ 2 ሺህ ከፍሎ ነፃ የወጣ ግለሰብ ነው።

ከሰሞኑ እንደ ጉለሌ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ ያሉ ተቋማት ከእስር ተፈቺዎችን እና ተገልጋዮችን ለማገልገል ወይም ከእስር ለመልቀቅ የ 500 ብር የህዳሴ ግድብ ቦንድ በግዴታ እያስገዙ እንደሆነም ለማወቅ ችለናል።

መረጃን ከመሠረት!

@Ethionews433 @Ethionews433


ፑቲን 'አስፈላጊ ከሆነ' ከዜሌንስኪ ጋር ይመክራሉ ሲል ክሬምሊን አስታወቀ

ክሬምሊን ቭላድሚር ፑቲን የዩክሬኑን ፕሬዝዳንት ቮሎዲሚር ዘሌንስኪን "አስፈላጊ ከሆነ" ለማነጋገር መዘጋጀታቸውን አስታውቋል። የክሬምሊን ቤተመንግስት ቃል አቀባይ ዲሚትሪ ፔስኮቭ ለጋዜጠኞች እንደተናገሩት "ፑቲን ራሳቸው ካስፈለገ ከዜለንስኪ ጋር ለመደራደር ዝግጁ ነኝ ብለዋል። "ነገር ግን የስምምነቶች ህጋዊ መሰረት የዜለንስኪ ህጋዊነት ጥርጣሬ ውስጥ ሊጥል የሚችልበትን እውነታ ግምት ውስጥ በማስገባት ውይይት ያስፈልገዋል" ሲሉ አክለዋል።

በሌላ በኩል የዩክሬን ፕሬዝዳንት የአገራቸውን የግዛት አንድነት አስፈላጊነት አፅንዖት ሰጥተው በመናገር የዩክሬን የፀጥታ ዋስትና ጥያቄን በድጋሚ አንስተዋል። “እንደ አገር ሰላም እንፈልጋለን። ጦርነቱ እንዲያበቃ እንፈልጋለን። ሆኖም የዚህ ጦርነት ማብቂያ በተወሰኑ የጸጥታ ዋስትናዎች ላይ የተመሰረተ እንዲሆን እንፈልጋለን ሲሉ ዘለንስኪ መናገራቸውን የቱርክ መንግስት ሚዲያ ዘግቧል።

ፕሬዝዳንቱ ይህንን የተናገሩት ከቱርክ ፕሬዝዳንት ኤርዶጋን ጋር ከመገናኘታቸው በፊት በአንካራ አዲሱ የዩክሬን ኤምባሲ ህንፃ የመክፈቻ ስነ ስርዓት ላይ ነው። "እነዚህ የደህንነት ዋስትናዎች በዩናይትድ ስቴትስ፣ በአውሮፓ ህብረት፣ በቱርኪ እና በመላው አውሮፓ የደህንነት እንደሚሰጡ እንጠብቃለን በማለት አክለዋል። በምንም አይነት ሁኔታ ለጊዜው የተያዙ ግዛቶቻችንን እንደ ሩሲያ ግዛት አድርገን አንቀበልም፤ የዩክሬን አካል ናቸው ሲሉ ተደምጠዋል።

በስምኦን ደረጄ
@Ethionews433 @Ethionews433


ጀርመን ካለ አሜሪካ ፍቃድ ወታደሮቼን ወደ ዩክሬን አልክም አለች

አሜሪካ ያልተሳተፈችበትን በዩክሬን የሰላም አስከባሪ ተልዕኮ ላይ ወታደሮቿን እንዳማትልክ ጀርመን አስታዉቃለች፡፡

ያለ አሜሪካ ተሳትፎና ዕዉቅና የአዉሮፓ ወታደሮች ወደ ዩክሬን ቢላኩ ኃላፊነት እንደምትወሰድም የአገሪቱ ከፍተኛ ባለስልጣን መናገራቸዉን አሶሼትድ ፕረስ ዘግቧል፡፡

ከጀርመን በተጨማሪም ፖላንድ ጦሯን ወደ ዩክሬን እንዳምትልክ አስታዉቃለች፡፡

የእንግሊዙ ጠቅላይ ሚኒስትር ኬር ስታርመር ጦራቸዉን ወደ ዩክሬን እንደሚልኩ ማሳወቃቸዉ አይዘነጋም፡፡

@Ethionews433 @Ethionews433


በቶሮንቶ በደረሰ የአውሮፕላን አደጋ በሦስት ሰዎች ላይ ከባድ ጉዳት ደረሰ

*****
በቶሮንቶ ፒርሰን አለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ የተከሰተው የአውሮፕላን አደጋ ሦስት ሰዎችን ለከባድ ጉዳት ሲዳርግ ሌሎች 18 ሰዎች ደግሞ ቀላል ጉዳት ደርሶባቸዋል::

ከአሜሪካ ሚኒያፖሊስ ተነስቶ በቶሮንቶ ፒርሰን አውሮፕላን ማረፊያ ሲያርፍ በመገልበጡ ነው አደጋው የተከሰተው::

በአውሮፕላኑ ላይ የነበሩ 80 ተሳፋሪዎች በሙሉ ከአውሮፕላኑ መገልበጥ በኋላ ወዲያው እንደወጡ የአቪየሽን አስተዳደር ተናግሯል።

ኦንታርዮ የአየር አምቡላንስ ኦርጅ እንደገለጸው እስካሁን ባለው መረጃ በአደጋው ሟቾች እንደሌሉ ተናግረዋል።

ጉዳት የደረሰባቸውን ተሳፋሪዎች በአቅራቢያ ወደሚገኙ ሆስፒታሎች እንደሄዱ ተልጿል።

ባለቤትነቱ የዴልታ የሆነው አውሮፕላን በማረፍ ላይ ሳለ በነበረ ከባድ የአየር ፀባይ ምክንያት ሳይገለበጥ እንዳልቀረ ተገልጿል::

በሄለን

@Ethionews433 @Ethionews433


ከሚኒያፖሊስ የተነሳው አውሮፕላን ቶሮንቶ ላይ ሲያርፍ ተገለባብጦ ተከሰከሰ

ዛሬ ሰኞ ከሰአት በኋላ በቶሮንቶ ፒርሰን አውሮፕላን ማረፊያ የዴልታ አይሮፕላን ተከስክሶ ከዩናይትድ ስቴትስ የሚበሩ ተሳፋሪዎች ላይ ጉዳት አድርሷል።

@Ethionews433
@Ethionews433


የኤርትራው ፕረዚዳንት ኢሳያስ አፈወረቂ በሰሜኑ የኢትዮጵያ ክፍል አዲስ ግጭት ለመቀስቀስ እየሰራ ነው ሲል አልጀዚራ አስነብቧል

የኢሳያስ የ32 አመት የአገዛዝ ዘመን ኤርትራ ነፃነቷን ካወጀች በኋላ የህገመንግስት መዋቅር የላትም ብሏል። ሕገ መንግሥት የለም፣ ፓርላማ የለም፣ሲቪል ሰርቪስ የለም። ኤርትራ ውስጥ ህግ አስፈፃሚ፣ ህግ አውጭ እና ህጋዊ ተርጓሚ አንድ ብቻ ነው፣እሱም ፕሬዝዳንት ኢሳያስ ብቻ ነው ብሏል ዘገባው።

በኤርትራ ወታደራዊ አገልግሎትም በግዴታ እና የአገልግሎት ዘመኑ በጊዜ ያልተገደበ ነው።

ወጣት ኤርትራዊያን ከፕሬዚዳንቱ ጦር ለማምጣት እድሜ ልካቸውን በሽሽት ይኖራሉ።
በዚህም ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው የኤርትራ ወጣቶቾ በተለይ ወንዶች በህገ ወጥ መንገድ ወደ ጎረቤት ሀገራት እና አውሮፓ የሚሰደዱ እና ህይወታቸውን የሚያጠፉ ብዙ ናቸው።

ጦርነት የኤርትራ መንግስት ዋና የገቢ ምንጩ መሆኑን ዘገባው ያትታል። እዚህም እዚያም የሚቀሰቅስ ግጭት፣ አማፂያንን፣ወይም መንግስታትን በመደገፍ ጦርነትን ያባብሳል።

ዛሬ ኢሳያስ እንደገና ሊገመት በሚችል መልኩ አጥፊ በሆኑ እንቅስቃሴዎች ላይ ተጠምዷል።
በኢትዮጵያ ፌደራል መንግሥት እና በህወሓት መካከል የተፈጠረው ጦርነት በፕርቶሪያ ስምምነት ቢቋጭም ኢሳያስ አፈወርቂ በዚህ ስምምነት ደስተኛ አይደለም።

በዚህም በሰሜኑ የኢትዮጵያ ክፍል ድጋሚ ግጭት እንዲቀሰቀስ እየሰራ ነው፣አሁኑኑ እርምጃ መውሰድ  ይገባል" ሲል ዘገባው ያትታል።

@Ethionews433
@Ethionews433


ባጃጅ የሠራው የ14 ዓመት ታዳጊ

የ14 ዓመት ታዳጊና የ8ኛ ክፍል ተማሪ የሆነው አብዱልሃፊዝ ጸጋዬ የሚኖረው በጉራጌ ዞን ሙኽር አክሊል ወረዳ ነው።

የተለያዩ የፈጠራ ሥራዎች የሠራው አብዱልሃፊዝ እስካሁን ወደ አምስት የሚጠጉ የፈጠራ ሥራዎች መሥራቱንም ገልጿል። ከእነዚህም ውስጥ በኤሌክትሪክ እና በፀሐይ ብርሃን የሚሰራ ባለ ሦስት እግር ተሽከርካሪ ይገኝበታል።

ከቴክኖሎጂው ጋር የተዋወቀው የሰባት ዓመት ልጅ እያለ መሆኑን የሚገልጸው የፈጠራ ባለሙያው÷ የመብራት እና የመኪና ፈጠራ እጅግ እንደሚያስደስተው ተናግሯል።

ታዳጊው ወደ ፈጠራ ሥራ የተሳበው ነገሮች እንዴት እንደሚሰሩ መጠየቅ እና መመራመር ስለሚወድ መሆኑንም ይገልጻል።

የታዳጊው እህት አምሪያ ጸጋዬ የወንድሟን የፈጠራ ሥራዎችን በተመለከተ በሰጠችው አስተያየት የመጀመሪያ ሥራው የምግብ ማቅረቢያ ትሪን እንደመሪ በመጠቀም በእንጨት እና በሌሎች ቁሳቁስ መኪና መስራቱን ታስታውሳለች። ከዛ በኋላ ግን በተለያዩ የትምህርት ቤት ውድድሮች ላይ እየተሳተፈ ማሸነፍ መቻሉን ትናገራለች።

አብዱልሃፊዝ ወደ ፈጠራ ሥራዎች የገባው በአካባቢው ያሉ እናቶችን ችግር በመመልከት በተለይም እናቶች ወደ ጤና ተቋም ለመሄድ የሚገጥማቸውን ውጣ ውረድ በአቅሙ መፍትሄ ለመስጠት እንደሆነም ገልጿል።

ታዳጊው በፀሐይ ብርሃን የምትሄድ ባለሦስት እግር ወይም በተለምዶ ባጃጅ የምትባለውን ተሽከርካሪ፣ መለስተኛ አይሱዚ እና እሳት ማቀጣጠያ ከሠራቸው የፈጠራ ሥራዎች መካከል ተጠቃሽ ናቸው።

አብዱልሃፊዝ በፈጠራ ሥራዎቹ ምክንያት በወረዳ እና ዞን ደረጃ በተደረጉ የተለያዩ ውድድሮች ላይ በመሳተፍ ተሸላሚ መሆን ችሏል።

ወደ ፊት የሠራትን ባለ ሦስት እግር ተሽከርካሪውን ወደ ገበያ ለማውጣት እና ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ለማድረግ የሚያስፈልጉ ግብዓቶች ድጋፍ እንዲደረግለትም ጠይቋል።

@Ethionews433
@Ethionews433


የፕሪቶሪያውን ስምምነት በሚመለከት በአፍሪካ ሕብረት ሪፖርት ቀርቦ ውይይት ተካሄደ

በትግራይ ክልል የነበረውን ግጭት ያስቆመው የፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት ሂደትን በተመለከተና ከስምምነቱ "ሌሎች ምን እንማር?" በሚል ርዕስ ዛሬ የካቲት 9ቀን 2017ዓ.ም በአፍሪካ ህብረት ሪፓርት ቀርቦ ውይይት ተካሂዷል።

በዚህ ውይይት ላይም የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዚዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ እና የህወሓት ሊቀመንበር ደብረ ጽዮን ገብረሚካኤል(ዶ/ር) የተገኙ ሲሆን ከኢትዮጵያ መንግሥት በኩል ደግሞ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ጌድዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) ፣ የሰላም ሚኒስትሩ አቶ መሐመድ እድሪስ እና ሌሎች ተገኝተዋል።

የፕሪቶሪያውን ስምምነትና አፈፃፀም የተመለከተውን ሪፓርት ደግሞ ተሰናባቹ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ-መንበር ሙሳ ፉኪ ማህማት፣ የቀድሞ የናይጀሪያ ፕሬዚዳንትና የአፍሪካ ህብረት አደራዳሪ ቡድን ሰብሳቢ ኡሊሲንጎን ኦባሳንጆ እና ከፍተኛ ኮሚሽነሮች አቅርበዋል።ከአንድ ሰአት በላይ የዘለቀ ውይይት ከተካሄደ በኋላ አቶ ጌታቸው ከጋዜጠኞች ለቀረበላቸው ጥያቄዎች ምላሽ ሰጥተዋል።

የጊዜያዊ አስተዳደሩ ፕሬዚዳንት


በዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ አማፂው ቡድን ኤም 23 ሁለተኛውን ግዙፍ ከተማ ተቆጣጠረ

በሩዋንዳ የሚደገፉት ኤም 23 አማፂያን በኮንጎ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ሁለተኛዋ ትልቅ ከተማ ወደሆነችው ቡካቩ ገብተዋል። በአካባቢው ታጣቂው ቡድን ፈጣን የጦር እንቅስቃሴ እያደረገ መሆኑን የደቡብ ኪቩ ግዛት አስተዳዳሪ ዣን ዣክ ፑሩሲ ተናግረዋል ። ፑሩሲ እሁድ እለት ለሮይተርስ የዜና ወኪል እንደተናገሩት "የኤም 23 ታጣቂዎች በቡካቩ ውስጥ ይገኛሉ፣የኮንጎ ወታደሮች የከተማ ውጊያ እንዳይደረግ በማለት አካባቢውን ለቅቀው ወጥተዋል" ብለዋል።

የታጠቀው ቡድን በጥር ወር መገባደጃ ላይ የክልሉን ትልቁን ከተማ ጎማ ከተማን ከተቆጣጠረ በኋላ ወደ ሌሎች ከተሞች እየገሰገሰ ይገኛል። የቡካቩ በኤም 23 ቁጥጥር ስር መግባት በጣም አስፈላጊ የሆነውን የግዛት መስፋፋት የሚያሳይ ሲሆን ይህም አመፂ ቡድኑ ብረት ካነሳበት ከ2022 ወዲህ የቡድኑ ትልቅ ስኬት ሆኗል። የኮንጐ መንግስት አማፂያኑ ቡካቩ መግባታቸውን አረጋግጦ የሩዋንዳ ወታደሮችም አብረዋቸው ይገኛሉ ብሏል። መንግስት ግን ከተማዋ ሙሉ በሙሉ በኤም 23 ቁጥጥር ስር መሆኗን አልተናገረም።

ሩዋንዳ በኮንጎ ምድር ላይ ወረራ በማድረግ ለመዝረፍ እና ወንጀሎችን እንዲሁም ከባድ የሰብአዊ መብት ጥሰቶችን ለመፈጸም እቅዷን በግትርነት እየተከተለች ትገኛለች ሲል የሀገሪቱ መንግስት አስታውቋል። እሁድ እለት ቀደም ብሎ አንድ የአካባቢው ባለስልጣን ፣የደህንነት ምንጭ እና አምስት ምስክሮች አማፅያኑን በከተማይቱ ውስጥ ማየታቸውን ሪፖርት አድርገዋል። የታጠቀው ቡድን ቃል አቀባይ ለሮይተርስ የዜና ወኪል ከተማይቱን መያዛቸውን በማረጋገጥ “እዚያ ነን” ብለዋል ።

በስምኦን ደረጄ

@Ethionews433 @Ethionews433

Показано 20 последних публикаций.