ሪፖርተር (Ethiopian Reporter)


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: Новости и СМИ


Ethiopian Reporter (ሪፖርተር) በሚዲያና ኮሙኒኬሽን ሴንተር በሳምንት ሁለቴ እየታተመ የሚወጣ ጋዜጣ ነው፡፡ ጋዜጣው ለነጻ ፕሬስ፣ ለነጻ ሐሳብናና ለነጻ መንፈስ መስፈን ይተጋል፡፡ Facebook: https://www.facebook.com/EThReporter Twitter: @EthioReporter LinkedIn: linkedin.com/in/ሪፖርተር-ሪፖርተር-123415146

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
Новости и СМИ
Статистика
Фильтр публикаций


#ማስታወቂያ

የካቲት 16 እየደረሰ ነው!
*
ግብይትዎን በፖስ ፈፅመው 10 ሺ ብር የሚሸለሙበት መርሀ ግብር የካቲት 16 ቀን 2017 ዓ.ም ይጠናቀቃል፡፡
ከ1,000 ብር ጀምሮ በፖስ ሲከፍሉ
እድል ከቀናዎ የ10 ሺ ብር ተሸላሚ ይሆናሉ፡፡

መልካም ዕድል!
***
የባንካችንን ትክክለኛ የማህበራዊ ትስስር ገፆች በመከተል ትክክለኛ እና ወቅታዊ መረጃ ያግኙ!
Facebook https://www.facebook.com/combanketh
Telegram https://t.me/combankethofficial

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
ሁሌም የሚተማመኑበት ባንክ!
#cbe #digitalbanking #pos #banking


#ማስታወቂያ

ከተለያየ የዓለም ክፍሎች የሚላክልዎትን ገንዘብ ከሕብረት ባንክ ይቀበሉ፡፡
ከባንካችን ጋር ከሚሰሩ ዓለም አቀፍ የገንዘብ አስተላላፊዎች ማለትም ዌስተርን ዪኒየን፣ መኒግራም፣ ትራንስፋስት፣ ሪያ ፣ዳሃብሺል እና ዩፔሲ እንዲሁም በባንኩ ስዊፍት ኮድ - UNTDETAA አማካኝነት ይቀበሉ፡

ሕብረት ባንክ
በሕብረት እንደግ!

📞 ለበለጠ መረጃ ወደ 995 ነፃ የጥሪ ማዕከል ይደውሉ፡፡
🤳 በቀላሉ አዳዲስ መረጃዎች እንዲደርስዎ የቴሌግራም ገፃችንን አሁኑኑ ይቀላቀሉ፡፡ https://t.me/HibretBanket
🌐 ሌሎች የማህበራዊ ገፆቻችንን እና ድህረ ገፃችንን linktr.ee/Hibret.Bank ይጎብኙ፡፡

#FastRemittances #MoneyTrasnfer #HibretBank #Swift


የፕሪቶሪያውን ስምምነት በሚመለከት በአፍሪካ ሕብረት  ሪፖርት ቀርቦ ውይይት ተካሄደ

በትግራይ ክልል የነበረውን ግጭት ያስቆመው የፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት ሂደትን በተመለከተና ከስምምነቱ "ሌሎች ምን እንማር?" በሚል ርዕስ ዛሬ የካቲት 9ቀን 2017ዓ.ም
በአፍሪካ ህብረት ሪፓርት ቀርቦ ውይይት ተካሂዷል።

በዚህ ውይይት ላይም የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዚዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ እና የህወሓት ሊቀመንበር ደብረ ጽዮን ገብረሚካኤል(ዶ/ር) የተገኙ ሲሆን ከኢትዮጵያ መንግሥት በኩል ደግሞ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ጌድዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) ፣ የሰላም ሚኒስትሩ አቶ መሐመድ እድሪስ እና ሌሎች ተገኝተዋል።

የፕሪቶሪያውን ስምምነትና አፈፃፀም የተመለከተውን ሪፓርት ደግሞ ተሰናባቹ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ-መንበር ሙሳ ፉኪ ማህማት፣ የቀድሞ የናይጀሪያ ፕሬዚዳንትና የአፍሪካ ህብረት አደራዳሪ ቡድን ሰብሳቢ ኡሊሲንጎን ኦባሳንጆ እና ከፍተኛ ኮሚሽነሮች አቅርበዋል።

ከአንድ ሰአት በላይ የዘለቀ ውይይት ከተካሄደ በኋላ አቶ ጌታቸው ከጋዜጠኞች ለቀረበላቸው ጥያቄዎች ምላሽ ሰጥተዋል።

የጊዜያዊ አስተዳደሩ ፕሬዚዳንት


#ማስታወቂያ


ዘወትር እሁድ የሚጠብቁት የሪፖርተር ጋዜጣ የተለያዩ መረጃዎችን ይዞ በገበያ ላይ ይገኛል
በድረገጻችን https://www.ethiopianreporter.com/ ላይም ያገኙታል።

----------||----------

የሪፖርተር ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን ይቀላቀሉ
ፌስቡክ↠ https://bit.ly/2Iv9bZB
ትዊተር↠ https://bit.ly/35qeNwV
ቴሌግራም↠ http://bit.ly/37OFEnC
ዩቲዩብ ↠ https://bit.ly/3p0jUQY

የ ስራ ማስታወቂያዎች ↠ EthiopianReporterJobs.com


ፖርላማው አስቸኳይ ስብሰባ ጠራ

በአራተኛ ዓመት የፓርላማ ዘመን የግማሽ ዓመት እረፍት ላይ የሚገኘው የህዝብ ተወካዮች ምክርቤት፣ ከተቋቋመ ሶስት አመታትን ያስቆጠረውን የአገራዊ ምክክር ኮሚሽንን ሪፓርት ለማዳመጥና በፓርላማ የፀደቀለትን የሶስት ዓመት የሥራ ጊዜ እንደገና ለማራዘም፣ በመጭው ማክሰኞ የካቲት 11 ቀን 2017 ዓ ም አስቸኳይ ስብሰባ ጠርቷል።

ኮሚሽኑ ያላጠናቀቃቸውን ስራዎች ለመጨረስ ተጫመሪ ጊዜ እንደሚያስፈልገው ከዚህ ቀደም ሲገልፅ ነበር። የኮሚሽኑ የሶስት አመት የስራ ዘመን በያዝነው የካቲት 2017 ዓም ይጠናቀቃል ።


የጅቡቲ ውጪ ጉዳይ ሚኒስትር ማሕሙድ አሊ ይሱፍ የአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር ሆነው ተመረጡ።

የ59 ዓመቱ ዲፕሎማት ለሚቀጥሉት አራት ዓመታት ኮሚሽኑን እንዲመሩ የተመረጡት ዛሬ በአዲስ አበባ መካሔድ በጀመረው የአፍሪካ ኅብረት ዓመታዊ የመሪዎች  ጉባኤ ላይ ነው።

አሊ ሞሐመድ ይሱፍ ላለፉት ሥምንት ዓመታት የኮሚሽኑ ሊቀ መንበር የነበሩት ሙሳ ፋኪ ማኅማትን ይተካሉ።

ይሱፍ የተመረጡት የኬንያው ጉምቱ ፖለቲከኛ ራይላ ኦዲንጋ እና የማዳጋስካር የቀድሞ የኤኮኖሚ እና የፋይናንስ ሚኒስትር ሪቻርድ ራንድሪያማንድራቶን አሸንፈው ነው።

የአፍሪካ ኅብረት 38ኛ ዓመታዊ የመሪዎች ጉባኤ በአዲስ አበባ ሲጀመር የአንጎላው ፕሬዝደንት ዮዋዎ ሎሬንሶ የዓመቱን የአፍሪካ ኅብረት ሊቀመንበርነት ከሞሪታኒያው ፕሬዝደንት ሞሐመድ ዑልድ ተረክበዋል።


መቶኛ ዓመቱን እያከበረ ያለው ጎንደር ዩንቨርስቲ  40ኛ ዙር የሕክምና ተማሪዎቹን አስመረቀ

ጎንደር ዩኒቨርሲቲው  ዛሬ የካቲት 8 ቀን 2017 ዓ.ም ፣ 254 ወንድ እና 112 ሴት   የሕክምና ተማሪዎቹን ያስመረቀው ለ40ኛ ጊዜ መሆኑንና ይኸም ዩኒቨርስቲው የተመሠረተበትን ምዕተዓመት እያከበረ ባለበት ጊዜ በመሆኑ ልዩ እንደሚያደርገው ተገልጿል።

ተቋሙ ህክምና ተማሪዎች 40ኛ ዙርና  21ኛ ዙር የፋርማሲ ተማሪዎችን ያስመረቀ ሲሆን፣  በሁለተኛ ዲግሪ፣ በሦስተኛ ዲግሪ፣ በስፔሻሊቲና ሰብ ስፔሻሊቲ የትምህርት ዘርፎችን ሲከታተሉ የቆዩ መሆናቸው ታውቋል።

በመርሃ ግብሩ  የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር  ዴዔታ ደረጄ ድጉማ (ዶ/ር ) ፣ የዩንቨርስቲው ፕሬዚዳንት አስራት አጸደወይን (ዶ/ር) ፣ የጎንደር ከተማ ከንቲባና  ሌሎች አካላት ተገኝተዋል።

በመድረኩ ንግግር ያደረጉት የዩንቨርስቲው ፕሬዝዳንት  አስራት አጸደወይን_ዶ/ር)፣   በቅድመ ምረቃና በድህረ ምረቃ ፕሮግራሞች ትምህርታቸውን ያጠናቀቁ ተማሪዎች፣ በኮሌጅ የትምህርት ጉባዔ ተመስክሮና በዩንቨርስቲው ሴኔት ጸድቆ ለምርቃት ቀን በቅተዋል ብለዋል፡፡

"ተመራቂ ተማሪዎች ኢትዮጵያ እናንተን በጥብቅ ትፈልጋችኋለችና ይህ ደስታ የእናት አገራችሁ ጭምር ነው" ያሉት ፕሬዝዳንቱ፣ የሰለጠኑበት ሙያ  ፈታኝና የተከበረ  ቢሆንም ውጤቱ ግን ፈዋሽ መሆኑን እንደሚገነዘቡ ጠቅሰዋል፡፡
በርካታ  "እንቅልፍ አልባ ለሊቶች፣ ስንፍናና ድካም የሻረ ትጋት በብዙ ተግዳሮቶች የተፈተነ ግን ያልተሸነፈ ጥንካሬያችሁ ለዛሬው ቀን አብቅቷችኋልና እንኳን ደስ አላችሁ" ሲሉ ለተመራቂ ተማሪዎች መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡

የጤና ሚኒስትር ዴዔታው  ዶ/ር ደረጄ ድጉማ በበኩላቸው፤ "ተመራቂዎች አድካሚውን የትምህርት ጉዞ በስኬት አጠናቃችሁ በጉጉት ስትጠብቁት ለነበረው የምርቃት ቀናችሁ እንኳን አደረሳችሁ" ያሉ ሲሆን፤ "ቀጣይ የአገራችን ጉዞ ዛሬ የምትመረቁት ተማሪዎች እጅ ላይ የሚወድቅ ነው" ብለዋል፡፡

ተመራቂ ተማሪዎች የተጣለባቸውን ኃላፊነት በብቃት ለመወጣት እራሳቸውን ማዘጋጀት እንደሚገባቸው ያሳሰቡት ዶ/ር ደረጄ፣ በቀጣይ ወደ ሥራ ሲገቡ በሙያቸው  አገራቸውንና ወገኖቻቸውን  ያለ ስስት እንዲያገለግሉ ጠይቀዋል፡፡
በተመረቁበት ሙያ ማህበረሰቡን ያለ ምንም አድሎ ሙያው የሚጠይቀውን ስነ ምግባር አክብረው  ሀላፊነታቸውን እንሚወጡ ቃል ገብተዋል።

ከ2010 ዓ/ም ጀምረው ሌሊትና ቀን ክረምትና በጋ ሳይሉ  ላለፉት 7 ዓመታት በአስቸጋሪና ፈታኝ ሁኔታ ማለፋቸውን ተመራቂ ተማሪዎች በተለይ ለሪፖርተር ተናግረዋል።
በኮሮና ቫይረስ ወቅት ለአንድ ዓመት  አቋርጠው  እንደነበር ያስታወሱት ተማሪዎቹ፣ በዚያም አንድ ዓመትን ጨምረው 7 ዓመት ቆይታ ማድረጋቸውን ተናግረዋል

በመርሃ ግብሩ ላይም በቅርቡ ሕይወቱ ያለፈውና በባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ በጠቅላላ ቀዶ ሕክምና ስፔሻሊስት እና የጉበት፣ የቆሽትና የሃሞት መስመር ሰብ ስፔሻሊስት ሃኪም የነበረውን ዶ/ር አንዱዓለም ዳኜን በማሰብ የህሊና ጸሎት ተደርጓል፡፡

ጎንደር ዩኒቨርስቲ 70ኛ ዓመትና አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል 100ኛ ዓመት የምሥረታ በዓል  በማክበር ላይ ሲሆን በስፖርታዊ ውድድር፣ አዳዲስ መሠረተ ልማቶችን በማስጀመር በነፃ ለማኅበረሰቡ አገልግሎት በመስጠት በዓሉን እንደሚያከብር መናገሩ ይታወሳ።

ዩኒቨርሲቲው  በ11 ኮሌጆች በ87 የቅድመ ምረቃ ፕሮግራሞች ዛሬ የተመረቁትን ጨምሮ  ከ300 በላይ በሁለተኛ ሦስተኛ ዲግሪና ስፔሻላይዜሽን ፕሮግራሞች ከ40 ሺሕ በላይ ያስተናግዳል። ።




የተባበሩት ዐረብ ኤምሬቶች መንግስት የ60 ሚሊዮን ዶላር ድጋፍ ሰጠ

በኢትዮጵያ ለዐይነ ስውራን ትምህርት መሠረተ ልማት የሚውል  የ60 ሚሊዮን ዶላር ድጋፍ  ከተባበሩት አረብ ኤምሬቶች መንግስት ዛሬ የካቲት 8 ቀን 2017 ዓም መሰጠቱ ታወቀ።
ድጋፉ የተሰጠው  የተባበሩት ዐረብ ኤምሬቶች ፕሬዚደንት ሼክ ሞሀመድ ቢን ዛይድ አል ናህያን በሰጡት መመሪያ ሲሆን የድጋፍ ስምምነቱን ቀዳማዊ እመቤት ዝናሽ ታያቸው ጋር መደረጉም ታውቋለል።

ድጋፉ ዩናይትድ አረብ ኤሜሬስት መንግሥት ዓለማቀፍ በጎ አድራጎት ተግባራትን ለማስተባበር በዘረጋው ማዕቀፍ፣ ኧርዝ ዛይድ ፊላንትሮፊስ (Erth Zayed Philanthropies) ሥር የሚተገበር ኾኖ፣ ከኢትዮጵያ መንግሥት ጋር በትብብር የሚፈጸም ሲሆን፣  ባለፈው ዓመት እ ኤ አ.ሜይ 2024 በአዲስ አበባ ተመርቆ በይፋ ሥራ የጀመረው ሼክ ፋቲማ ቢንት ሙባረክ የዓይነ ሥውራን ትምሕርት ቤትን ስኬታማ ጅማሮና ተሞክሮ በሀገር ዐቀፍ ደረጃ ለማሳደግ ያለመ መሆኑ ተገልጿል።

የድጋፍ ሰነዱን የካሊፋ ቢን ዛይድ አል ናህያን ፋውንዴሽን ዳይሬክተር ሚስተር ሞሐመድ ሐጂ አልኩሪ ፣  የውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር ምኒስትር ደኤታ  ሼክ ሻክቡት ቢን ናህያን አል ናህያንና የኧርዝ ዛይድ ፊላንትሮፊስ  የበላይ ጠባቂ፣ ጠቅላይ ሚኒስትር  ዓብይ አሕመድ አሊ(ዶ/ር) በተገኙበት ተፈርሟል።

1.2 ሚሊዮን ዜጎች የማየት ውሱንነትን በሚያስከትሉ የጤና እክሎች በተጠቁባት፤ ከነዚህም መካከል 332,000 ዓይነ ሥውራን ድጋፉ በተለይ የትምሕርትና የጤና አገልግሎት በበቂ ሁኔታ ባልተዳረሰባቸው ገጠራማ አካባቢዎች  ያለውን ሰብዓዊ ችግር ለመቅረፍ እንደሚያስችል ተገልጿል።

መሠረታዊ አገልግሎት በበቂ ሁኔታ  በማይገኝባቸው አካባቢዎች የሚኖሩ ዜጎችን የሚያጠቃው ነገር ግን በሕክምና ሊድን በሚችለው ትራኮማ በሽታ የተጠቂዎች ቁጥር ኢትዮጵያ ከዓለም ከቀዳሚዎቹ ተርታ ትገኛለች።
በትምሕርት ሚኒስቴር አስተባባሪነት የአዳዲስ የልዩ ፍላጎት ትምሕርት ቤቶች ግንባታ እንዲከናወን ዕቅድ የተያዘ ሲኾን፣ በዘመናዊ መርጃ መሣሪያዎች የሚደራጁ፣ሙያ-ተኮር ሥርዓተ-ትምሕርት የሚዘጋጅላቸው ኾነው፣ ዓይነ ሥውራን ተማሪዎችን በክኅሎትና በዕውቀት በማብቃት ለከፍተኛ ትምሕርትና የሥራ ዓለም የሚያዘጋጁ የልኅቀት ማዕከላት በመኾን ያገለግላሉ ተብሏል።

ሼክ ጣይብ ቢን ሞሐመድ ቢን ዛይድ አል ናህያን (Sheikh Theyab bin Mohamed bin Zayed Al Nahyan)እንደተናገሩት“አገራችን ድጋፍ ለሚያስፈልጋቸው ሁሉ እጇን ትዘረጋለች። በኢትዮጵያ ለሚገኙ ዓይነ-ሥውራን እና የዓይን ጤናቸው ለታወከ ተማሪዎች የምናደርገው ይህ ድጋፍ የዚህ ማሳያ ነው። ዓላማችን እነዚህ መሠረታዊ አገልግሎት የተጓደለባቸው ተማሪዎች በተሻለ ከባቢ ተምረው፣ የተሻለ ትምሕርት አግኝተው ሕልማቸውን ዕውን እንዲያደርጉ ማገዝ ነው። በአገራችንና በኢትዮጵያ መካከል ያለውን መልካም የትብብር መንፈስ ይህ ጅማሬ ፍሬያማ እንደሚያደርገው እምነታችን ከፍ ያለ ነው።” ብለዋል።

ሼክ ሻክቡት ቢን ናህያን አል ናህያን (Sheikh Shakhbout bin Nahyan Al Nahyan) በበኩላቸው “ዘላቂ ልማትና ስትራቴጂያዊ ትብብር ለዘላቂ ለውጥ መሠረት እንደኾኑ እንደ ሀገር ቀድመን ተረድተናል።ይህም ድጋፍ ማኅበረሰቦችን ከችግር ለማላቀቅ፣ ኢኮኖሚው ዕድሎችን እንዲፈጥር ለማስቻልና መሠረታዊ አገልግሎትን ለዜጎች ለማዳረስ ያለን ቁርጠኛ አቋም ማሳያ ይኾናል።ከኢትዮጵያ መንግሥት ጋር ያለን ትብብርም የአፍሪካ አገራት ትምሕርት ወጣቶችን ማብቂያና ዘላቂ ልማትን ማሳለጫ መኾኑን ተረድተው  በትምሕርት ልማት ላይ እንዲያተኩሩ ያለንን የትኩረት አቅጣጫ ይገልጽልናል" ብለዋል።

ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው በበኩላቸው “የተባበሩት አረብ ኤሜሬትስ መንግስት ጥራት ያለው ትምሕርትን ለሁሉም ዜጎቻችን ለማዳረስ የያዝነውን ግብ ለማገዝ የተደረገልን ድጋፍ በመንግሥታችንና በኢትዮጵያውያን ስም ምስጋና ማቅረብ እወዳለሁ። ይህ ድጋፍና አጋርነት ዓይነ-ሥውራን ተማሪዎች ተገቢና በቂ ዕድሎችን አግኝተው ስኬታማ እንዲኾኑ ከማገዙም በላይ ሁሉን-ዐቀፍ ማኅበረሰባዊ ዕድገት እንድናመጣ ትልቅ ግምት የምንሰጠው ድርሻ አለው” ብለዋል።

  የካሊፋ ቢን ዛይድ አል ናህያን ፋውንዴሽን ዳይሬክተር ጄኔራል ሞሀመድ ሀጅ አልኩሪ በበኩላቸው፣ “ትምሕርት መሠረታዊ የሰው ልጆች መብት ነው። ልጆችም ልዩ ፍላጎቶቻቸው ተሟልተውላቸው የመማር ዕድል ሊመቻችላቸው ይገባል። የትምሕርት መሠረተ ልማትና ሥርዓተ ትምሕርትን በማሻሻል አካታችና ሁሉን ጠቃሚ ልማት እንዲመጣ መሠረት በመጣል ላይ ነን። ይህም ድጋፍ ትምሕርት ለትውልዶች የዕድልና የዕድገት ምንጭ ለመኾኑ ማሳያ ከመኾኑ ባሻገር ዓለማቀፍ ትብብር ለዘላቂ ለውጥ ያለውን ትልቅ ሚና በድጋሚ የሚያረጋግጥ ነው” ብለዋል።




#ማስታወቂያ

Imala keessaniif karaa damee Baankii keenyaa kaffaltii raawwaachuu kan dandeessan ta'uu kabajaan isin beeksifna.
Juma'aa Gaarii Isiniif Hawwina!

የሐጅ ጉዞ ክፍያችሁን በቅርንጫፎቻችን ገቢ ማድረግ የምትችሉ መሆኑን በአክብሮት እንገልጻለን፡፡
መልካም ጁመዓ ይሁንልዎ !

#Siinqee_Bank    #Baankii_Siinqee    #ሲንቄ_ባንክ  #Siinqee_Digital #Siinqee_Ihsan
#EMPOWERED_TOGETHER


#ማስታወቂያ

ከተለያየ የዓለም ክፍሎች የሚላክልዎትን ገንዘብ ከሕብረት ባንክ ይቀበሉ፡፡
ከባንካችን ጋር ከሚሰሩ ዓለም አቀፍ የገንዘብ አስተላላፊዎች ማለትም ዌስተርን ዪኒየን፣ መኒግራም፣ ትራንስፋስት፣ ሪያ ፣ዳሃብሺል እና ዩፔሲ እንዲሁም በባንኩ ስዊፍት ኮድ - UNTDETAA አማካኝነት ይቀበሉ፡

ሕብረት ባንክ
በሕብረት እንደግ!

📞 ለበለጠ መረጃ ወደ 995 ነፃ የጥሪ ማዕከል ይደውሉ፡፡
🤳 በቀላሉ አዳዲስ መረጃዎች እንዲደርስዎ የቴሌግራም ገፃችንን አሁኑኑ ይቀላቀሉ፡፡ https://t.me/HibretBanket
🌐 ሌሎች የማህበራዊ ገፆቻችንን እና ድህረ ገፃችንን linktr.ee/Hibret.Bank ይጎብኙ፡፡

#FastRemittances #MoneyTrasnfer #HibretBank #Swift


#ማስታወቂያ

ቅድሚያ መስተንግዶ
ለሐጅ ተጓዦች!
****
ለ1446ኛው ዓ.ሒ የሐጅ ጉዞ ሲመዘገቡ፤
የክፍያ መለያ ኮዱን ይዘው በአቅራቢያዎ በሚገኝ የባንካችን ቅርንጫፍ ይገኙ፣
ቅድሚያ ተስተናግደው ክፍያዎን በፍጥነት መፈፀም ይችላሉ፡፡
በሁሉም የባንካችን ቅርንጫፎች አገልግሎቱን ያገኛሉ!
የሐጅ ጉዞዎ ሰምሮ
የልብ መሻትዎ እንዲሳካ እንመኛለን!
****
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
ሁሌም የሚተማመኑበት ባንክ!
#cbe #hajj #ethiopia


ህወሓት ህጋዊ የፖለቲካ ፓርቲ ፈቃዱ ታገደ

-የቦርድ ትእዛዝ አክብሮ ካልተገኘ ከሶስት ወር በኋላ እንደሚሰረዝ ተገልጿል

የምስረታ 50ኛ በዓሉን ለማክበር ቀናት የቀሩት ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) ፖለቲካዊ እንቅስቃሴ እንዳያደርግ ህጋዊ ፈቃዱ መታገዱን፤ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከሰአታት በፊት ይፋ ባደረገው መግለጫ አስታወቀ።

ቦርዱ የህወሓትን የፓርቲ ፈቃድ የሰረዘው በልዩ ሁኔታ ተመዝግቦና የኢትዩጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ህግ፣ መመሪያና ውሳኔዎችን አክብሮ መንቀሳቀስ ሲገባው በአዋጅ ቁጥር 1232/2016 አንቀጽ 3(11) ሀ እና አዋጁን ለማስፈጸም በወጣው መመሪያ አንቀጽ 16(6) ድንጋጌን ጥሷል በሚል ነው።

ነገር ግን ህወሓት ለዕግዱ ምክንያት የሆነውን ጥሰት በማረም አዋጁን፣ መመሪያውንና የቦርዱን ውሳኔዎችና ትዕዛዝ በማክበር ፓርቲው ሊያደርግ የሚገባውን ጠቅላላ ጉባኤ ለማድረግ የሚያስችለውን የጉባኤ ቅድመ ዝግጅት ስራዎች ለመስራት ለቦርዱ በጽሁፍ ሲያሳውቅና ቦርዱ ይህንኑ ሲያረጋግጥ በመመሪያው አንቀጽ 18(2) መሠረት እግዱን የሚያነሳለት መሆኑን አስታውቋል።


#ማስታወቂያ


የአየር መንገዱን አሠራር ጥሰዋል በተባሉ የአዲስ አበባ ሽያጭ ቢሮ ሠራተኞች ላይ ዕርምጃ መወሰዱ ተገለጸ

- የሕግ ክፍሉ ክስ መመሥረት የሚቻልባቸውን ሁኔታዎች እየተመለከተ ነው ተብሏል

ከኢትዮጵያ አየር መንገድ የማስታወቂያና የሕዝብ ግንኙነት የሥራ ክፍሎች ዕውቅና ውጪ፣ በቅጥር ግቢው ውስጥ የፎቶና የቪዲዮ ቀረፃዎች እንዲካሄዱ ፈቃድ ሰጥተዋል የተባሉ የአዲስ አበባ ሽያጭ ክፍል ሠራተኞች ላይ አስተዳደራዊ ዕርምጃዎች መወሰዱ ተገለጸ።

ይህ የተገለጸው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን ጣሰው፣ እንዲሁም የአየር መንገዱ የንግድ ዘርፍ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ለማ ያደቻ ወቅታዊ ጉዳዮችን አስመልክቶ ዛሬ የካቲት 5 ቀን 2017 ዓ.ም. በአየር መንገዱ ዋና መሥሪያ ቤት ጋዜጣዊ መግለጫ ሲሰጡ ነው።

ኢትዮጵያ እያስተናገደችው ስለምትገኘው የአፍሪካ ኅብረት ጉባዔን ጨምሮ በተለያዩ ወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ማብራሪያ የሰጡት ዋና ሥራ አስፈጻሚው አቶ መስፍን፣ በቅርቡ ለተዋናይትና ሞዴል ምሕረት ታደሰ (ፒፒሎ) የልደት በዓል አየር መንገዱ ፈቃድ ሰጥቶ ተቀርጿል በሚል ስለተሠራጩት የግለሰቧ ቪድዮዎችና ምሥሎች፣ እንዲሁም የአየር መንገዱ ከፍተኛ አመራሮች ስለጉዳዩ መረጃ አልነበራቸውም በሚል ስለተሰጠው ምላሽ ጉዳዩን በዝርዝር እንዲያብራሩ ከጋዜጠኞች ጥያቄዎች ቀርቦላቸዋል።

አቶ መስፍን፣ ‹‹ቪድዮው መቀረፁ ትክክል ነው። ለግለሰቧ ሕጋዊ ፈቃድ ተሰጥቶ የፀጥታ መምርያ ሒደቱን ተከትሎ ጥገና ወደሚደረግበት የአየር መንገዱ ቅጥር ግቢ ገብታ የተከናወነ ነው፤›› ብለው፣ ‹‹የፀጥታ ፕሮሲጀሩን አሟልታ ነው ቪድዮው የተቀረፀው። ለአዲስ አበባ ሽያጭ ቢሯችን ታኅሳስ 27 ጥያቄ ያቀረበችበት ቀን ሲሆን፣ ከሁለት ቀን በኋላ ፈቃድ ተሰጥቶ ቀረፃው ተካሂዷል፤›› ሲሉ ገልጸዋል።

ይሁንና አጠቃላይ ሒደቱ የአየር መንገዱን ተቋማዊ አሠራር በመጣስ መከናወኑን ተናግረው፣ ‹‹በአየር መንገዱ አሠራር መሠረት የማስታወቂያ ሥራዎች ሲሠሩ በሁለት መንገዶች ወይም የሥራ ክፍሎች በኩል ነው። አንደኛው በሕዝብ ግንኙነት ሥራ ክፍል ሲሆን፣ ሁለተኛው ፕሮሞሽንና ማስታወቂያ የሚባለው የሥራ ክፍል ደግሞ አየር መንገዱንና ሥራዎቹን በተመለከተ ለሕዝብ የሚተላለፉ ማስታወቂያዎችን የሚመለከተው ነው።  የአርቲስቷ ሥራ ግን ከእነዚህ ሁለት ክፍሎች ውጪ ነው የተሠራው። ጥያቄው ለአየር መንገዱ የአዲስ አበባ ሽያጭ ቢሮ ሲቀርብ ለእነዚህ ሁለት የሥራ ክፍሎች መተላለፍ ነበረበት፤›› ሲሉ አስረድተዋል።

የአየር መንገዱ ከፍተኛ አመራሮች ከአሠራር ጥሰት ባለፈ ስለጉዳዩ ከፍተኛ አመራሮቹ ዕውቅና አልነበራቸውም በሚል ያሠራጨውን መረጃ በተመለከተ ማብራሪያ የሰጡት ዋና ሥራ አስፈጻሚው፣ ‹‹የአዲስ አበባ ሽያጭ ቢሮ ለአዲስ አበባ የጥበቃ መምርያ በቀጥታ ነው ፈቃድ እንደተሰጣት የሚገልጽ ደብዳቤ የጻፈው፡፡ ከፍተኛ አመራሩ ስለጉዳዩ መረጃ ሊኖረው የሚችለው የማስታወቂያው ጥያቄ ቀደም ሲል በጠቀስኳቸው ሁለት የሥራ ክፍሎች በኩል ሲመጣ ብቻ ነው፣ ይህ አልሆነም። በኋላ  የተፈጠረውን ነገር ስንሰማም የአየር መንገዱ ከፍተኛ አመራሮች በቀጥታ ለኦዲት ክፍሉ መመርያ ሰጥተን፣ ስለጉዳዩ ሙሉ ሪፖርትና ምክረ ሐሳብ ካቀረበልን በኋላ ነው የተንቀሳቀስነው፡፡ የማስታወቂያ ሥራዎችን ለመሥራት ፈቅደን ቢሆንና በትክክለኛዎቹ የሥራ ክፍሎች በኩል አልፎ ቢሆን ኖሮ ውል ይኖረን ነበር፣ ግን ያለ ውል ነው ሥራው የተሠራው፤›› ብለዋል።

በአየር መንገዱ የአውሮፕላኖች ጥገና በሚካሄድበት ቅጥር ግቢ ቪዲዮውን የቀረፀችውና ምሥሉ ከተቀረፀ ከአንድ ወር በላይ ቆይታ ካሠራጨችው ግለሰብ ለአዲስ አበባ ሽያጭ ክፍል ፈቃድ ለመጠየቅ ገቢ የተደረገው ደብዳቤ፣ ‹‹የአየር መንገዱን ክብር በሚጠብቅ መልኩ አየር መንገዱን መሠረት በማድረግ አገሪቱን ለቱሪዝም ሥራዎች ለማስተዋወቅ›› የሚሉ ምክንያቶች የቀረቡ ሲሆን፣ ‹‹ማናቸውንም ምሥሎችና ቪዲዮዎችን ለአየር መንገዱ ገቢ እናደርጋለን፤›› በማለት የተጠቀሰ መሆኑን ሪፖርተር የተመለከተው ደብዳቤ ያሳያል፡፡

ይሁን እንጂ ማናቸውም ፎቶዎችም ይሁኑ ተንቀሳቃሽ ምሥሎች ለኢትዮጵያ አየር መንገድ የትኛውም የሥራ ክፍል ከግለሰቧ አስቀድመው እንዳልተሰጡ የሪፖርተር ምንጮች አረጋግጠዋል፡፡
ከዚህ አኳያ በሕግ ሊኖር የሚችል ተጠያቂነትን በተመለከተ ምላሽ የሰጡት  የአየር መንገዱ ዋና ሥራ አስፈጻሚ፣ ‹‹ከሕግ ክፍላችን ጋር ተነጋግረን በሕግ አግባብ የምትጠየቅበት ሆኖ ካገኘነው እንጠይቃለን፤›› ብለዋል።

‹‹ችግሩ የተፈጠረው በውስጣችን በተፈጠረ የአሠራር ክፍተት ነው። አስተዳደራዊ ዕርምጃዎችን ወስደናል፣ እየወሰድንም ነው። የአየር መንገዱ ከፍተኛ አመራር ጉዳዩን ትኩረት ሰጥቶ ነው የሚያየው። አንደኛ በዚህ ጉዳይ የተሳተፉት ላይ ጠበቅ ያለ ዕርምጃ እንወስዳለን። ሁለተኛ ጥፋቱ እንዳይደገም የሚያስችል አሠራር እየዘረጋን ነው፤›› ሲሉ ተናግረዋል፡፡




#ማስታወቂያ

Tajaajila baankii fi Maaykrofaynaansii walliin kennuudhaan Baankii isa jalqabaa

የባንክና ማይክሮፋይናንስ ጥምር አገልግሎት መስጠት የጀመረ ቀዳሚ ባንክ

#Siinqee_Bank    #Baankii_Siinqee    #ሲንቄ_ባንክ
#EMPOWERED_TOGETHER


#ማስታወቂያ

10,000 ብር ይሸለሙ!
***
እስከ የካቲት 16፣ 2017
ከ1,000 ብር ጀምሮ በፖስ ሲገበያዩ
10‚000 ብር በዕጣ ይሸለማሉ!

ቀላል ክፍያ ከሽልማት ጋራ!
***
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
ሁሌም የሚተማመኑበት ባንክ!
#cbe #digitalbanking #pos #banking

Показано 20 последних публикаций.