ሪፖርተር (Ethiopian Reporter)


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: Новости и СМИ


Ethiopian Reporter (ሪፖርተር) በሚዲያና ኮሙኒኬሽን ሴንተር በሳምንት ሁለቴ እየታተመ የሚወጣ ጋዜጣ ነው፡፡ ጋዜጣው ለነጻ ፕሬስ፣ ለነጻ ሐሳብናና ለነጻ መንፈስ መስፈን ይተጋል፡፡ Facebook: https://www.facebook.com/EThReporter Twitter: @EthioReporter LinkedIn: linkedin.com/in/ሪፖርተር-ሪፖርተር-123415146

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
Новости и СМИ
Статистика
Фильтр публикаций


 የአትክልትና ፍራፍሬ ምርት ከ60 በመቶ በላይ ብክነት እንደሚያጋጥመው ተጠቆመ

ከተለያዩ አካባቢዎች ተመርቶ ወደ ገበያ የሚቀርበው የአትክልትና ፍራፍሬ ምርት በሚጓጓዝበት ወቅት ከ60 በመቶ በላይ የሚሆነው ብክነት እንደሚያጋጥመው፣ የኢትዮጵያ ኅብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት አስታወቀ፡፡
የተለያዩ የግብርና ምርቶች ከአዲስ አበባ ዙሪያም ሆነ ራቅ ካሉ አካባቢዎች በትራንስፖርት በሚጓጓዙበት ወቅት በተለይ በአትክልትና ፍራፍሬ ምርቶች ላይ ከፍተኛ የሆነ ብክነት እንደሚያጋጥም የተናገሩት፣ በኅብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የምግብ ጤና ተመራማሪና የዲቪዥን ኃላፊ እንዳለ አማረ (ዶ/ር) ናቸው፡፡
ተመራማሪው ይህንን ያሉት በአዲስ አበባ ውስጥ ያለውን የተመጣጠነ ምግብ እጥረት ለመቅረፍና ጤናማ የአመጋገብ ሥርዓት ለማበጀት ያለመ ኢኮ ፉድ ሲስተም የተባለ ፕሮጀክት፣ ማክሰኞ መጋቢት 9 ቀን 2017 ዓ.ም. ይፋ ሲደረግ ነው፡፡
ፕሮጀክቱ በኢትዮጵያ ኅብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት አጋርነትና በጋልዌይ ዩኒቨርሲቲ መሪነት በአዲስ አበባ በተመጣጣኝ ዋጋ ሊገኙ የሚችሉ የ...

ተጨማሪ ያንብቡ: https://www.ethiopianreporter.com/139400/


ተንቀሳቅሶ የመሥራት መብት ጉዳይ በአዲሱ የጎዳና ንግድ ደንብ መነጽር

በየቦታው ገመድ ወጥረው ‹‹ወዲህ በሉ›› እያሉ ገንዘብ የሚቀበሏቸው ሰዎች መብዛታቸውን የሚናገረው ስሙ እንዳይጠቀስ የፈለገ አንድ ሾፌር፣ በየቀኑ 4,000 እና 5,000 ብር መድቦ መንቀሳቀስ የእሱና የሌሎች ሹፌሮች ግዴታ እንደሆነ ይናገራል፡፡ ለእነዚህ ሰዎች ‹‹ወዲህ በሉ›› የሚል ቅጽል ስም ሾፌሮቹ እንዳወጡላቸው የሚገልጸውና በተለይ ከአዲስ አበባ ወደ ድሬዳዋ፣ ከሐረርና ከጅግጅጋ የመሳሰሉ አካባቢዎች ወደ ምሥራቅ የአገሪቱ ከተሞች በመለስተኛ ዕቃ ጫኝ ተሸከርካሪ ሸቀጥ በማመላለስ ሥራ ለ12 ዓመታት ተሠማርቶ የቆየው አሽከርካሪው፣ በዚህ መስመር ባሉ ኬላዎች በየቀኑ የሚገጥመውን በሰፊው ለሪፖርተር ተናግሯል፡፡  
‹‹አንድ ወቅት በየመንገዱ ያሉ ኬላዎችን እንዳለ አንስተዋቸው ጭሮ (አሰበ ተፈሪ) አካባቢ የሚገኘው የአርበረከቴ፣ እንዲሁም የአዋሽ ጉምሩክ ኬላዎች ብቻ ቀርተው ነበር፡፡ የዚያ ግፍ ነው መሰለኝ አሁን ከአዲስ አበባ ተነስተህ ድሬዳዋ እስክትደርስ 37 ገመ...

ተጨማሪ ያንብቡ: https://www.proworksmedia.com/139477/


ለጋዜጠኞች ጥበቃና ከለላ ይሰጣል የተባለ አገር አቀፍ የዕውቅና ማረጋገጫ መታወቂያ ሊዘጋጅ መሆኑ ታወቀ

ጋዜጠኞች በሥራቸው ወቅት ለሚደርስባቸው ተፅዕኖ፣ እንግልትና አፈና ጥበቃና ከለላ ይሰጣል የተባለ የሙያ የዕውቅና ማረጋገጫና ወጥ የሆነ አገር አቀፍ መታወቂያ ሊዘጋጅ መሆኑ ታወቀ፡፡
የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ምክር ቤት በኢትዮጵያ ጋዜጠኞች ምዝገባ፣ የሙያ ማረጋገጫና በብሔራዊ ሚዲያ ሽልማት ዕውቅና አሰጣጥ ዙሪያ መጋቢት 9 ቀን 2017 ዓ.ም. በአዝማን ሆቴል ዓውደ ጥናት አካሂዷል፡፡
በባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ የጋዜጠኝነትና ኮሙዩኒኬሽን መምህር አየለ አዲስ (ዶ/ር) እንደተናገሩት፣ በኢትዮጵያ ያለው የሚዲያ ነባራዊ ሁኔታ በርካታ ተግዳሮቶች የተደቀኑበት ነው፡፡ ከእነዚህም መካከል የጋዜጠኛው መረጃ የማግኘት መብት የተገደበበትና የጋዜጠኛው ደኅንነት አደጋ ውስጥ የሚወድቅበት ሁኔታ ያለ መሆኑ በቀዳሚነት ሊጠቀስ ይችላል፡፡
‹‹የዘፈቀደ እስር፣ እንግልት፣ ስደትና ከሚሠሩበት የሚዲያ ተቋም ጋር ተያይዞ የሚከሰት መገለል በጋዜጠኞች ላይ የሚደርሱ ችግሮች ናቸው፤›› ያሉት ...

ተጨማሪ ያንብቡ: https://www.ethiopianreporter.com/139405/


ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለዶ/ር ደሳለኝ ጫኔ የሰጡት ምላሽ
▶️ ሙሉ ቪዲዮውን ለማየት ይህን ሊንክ ይጫኑ: https://youtu.be/8fRfk8I5Fyw


የመንግሥትና የግል ሠራተኞች ከደመወዛቸው ለአደጋ ሥጋት ክፍያ እንዲፈጽሙ የሚያስገድድ ረቂቅ አዋጅ ቀረበ


ባንክና ኢንሹራንስን ጨምሮ በበርካታ አገልግሎቶች ላይ ክፍያ ይፈጸማል
የሚጠበቅባቸውን ክፍያ በወቅቱ ገቢ የማያደርጉ ወለድና ቅጣት ይከፍላሉ

የኢትዮጵያ አደጋ ሥጋትና ሥራ አመራር ኮሚሽን ራሱን የቻለ የፌዴራል መንግሥት አስፈጻሚ አካል ሆኖ እንዲቋቋም በቀረበው ረቂቅ አዋጅ፣ የመንግሥትና የግል ድርጅት ተቀጣሪ ሠራተኞች ከሚከፈላቸው የተጣራ የወር ደመወዝ ላይ ክፍያ እንዲፈጽሙ የሚያስገድድ ድንጋጌ ተካተተ፡፡
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ትናንት መጋቢት 9 ቀን 2017 ዓ.ም.  ባደረገው መደበኛ ስብሰባ የምክር ቤት አባላት በረቂቁ ላይ ለስምንት ደቂቃ ያህል ከተወያዩበት በኋላ፣ ለምክር ቤቱ የውጭ ግንኙነትና ሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ለዝርዝር ዕይታ ተመርቷል፡፡
በረቂቅ አዋጁ ማብራሪያ ላይ በቅድመ አደጋ፣ በአደጋና በድኅረ አደጋ ወቅቶች ለሚወሰዱ የአደጋ ሥጋት ቅነሳ፣ ምላሽና መልሶ ማቋቋም የሚሆን የኢትዮጵያ አደጋ ሥጋት ምላሽ ፈንድ መቋቋሙ ተገልጿል፡፡...

ተጨማሪ ያንብቡ: https://www.proworksmedia.com/139426/


የአሜሪካ ድምፅ ሬዲዮ ሥርጭት መቆሙ አማራጭ ድምፆች እንዳይደመጡ የሚያደርግ ውሳኔ ነው ተባለ

ከተመሠረተ 83 ዓመታት ያስቆጠረውና በኢትዮጵያ የሚነገሩትን ጨምሮ ከ50 በላይ ቋንቋዎች ሲሠራ የነበረው የአሜሪካ ድምፅ ሬዲዮ (ቪኦኤ) ሥርጭቱን እንዲያቆም መደረጉ፣ አማራጭ ሚዲያ ያጡ የሕዝብ ድምፆች እንዳይሰሙ ያደርጋል ተባለ፡፡
ከባለፈው ቅዳሜ መጋቢት 6 ቀን 2017 ዓ.ም. ጀምሮ የአሜሪካ ድምፅ ሬዲዮ (ቪኦኤ) የሰው ሀብት ዳይሬክተር ለተቋሙ ቋሚ ሠራተኞች አስተዳደራዊ እረፍት እንዲወስዱና ሥራ እንዲያቆሙ ደብዳቤ የላከላቸው ሲሆን፣ በሁሉም ቋንቋዎች ይሠራጩ የነበሩት ፕሮግራሞችም ወዲያውኑ ሥርጭታቸውን አቁመዋል፡፡  የሚዲያ ተቋሙ በኢትዮጵያ በ1974 ዓ.ም. በአማርኛ፣ እንዲሁም በ1988 ዓ.ም. ደግሞ በኦሮሚኛና በትግርኛ ቋንቋዎች ሥርጭት መጀመሩን መረጃዎች ያስረዳሉ፡፡
የሬዲዮ ጣቢያውን ከሥርጭት የማስቆም ውሳኔ በዶናልድ ትራምፕ  ፕሬዚዳንታዊ ትዕዛዝ አማካይነት ነው፡፡ ከዚህ ውሳኔ በኋላ የአሜሪካና የምዕራባዊያኑ ያመዘነ እሴት እንደሆነ የሚነገርለትን የሚዲ...

ተጨማሪ ያንብቡ: https://www.ethiopianreporter.com/139402/


በኦሮሚያ ክልል በሕዝብ ማመላለሻ አውቶቡሶች ላይ ጥቃት መድረሱና ተሳፋሪዎች መታገታቸው ተሰማ

በኦሮሚያ ክልል በተለምዶ ዓሊ ዶሮ በሚል ስያሜ በሚጠራው አካባቢ ሰኞ መጋቢት 8 ቀን 2017 ዓ.ም. ታጣቂዎች በሕዝብ ማመላለሻ አውቶብሶች ላይ ጥቃት በመፈጸም ወደ 50 የሚገመቱ ሰዎችን ማገታቸው ተሰማ። የሪፖርተር ምንጮች በአንድ ግለሰብ ላይ ግድያ መፈጸሙንና ሌላ ግለሰብ ደግሞ በጥይት ተመተው አዲስ አበባ የሕክምና ዕርዳታ እየተደረገላቸው እንደሚገኝ ገልጸዋል።
በሳምንቱ መጀመሪያ ከአዲስ አበባ በኦሮሚያ ክልል አቋርጠው ወደ አማራ ክልል ደብረ ማርቆስ ከተማ እየተጓዙ በነበሩት በፈለገ ግዮን፣ በዓባይና በሐበሻ አውቶቡሶች ላይ በታጣቂ ኃይሎች በተከፈተ ድንገተኛ ጥቃት መድረሱን ሪፖርተር ከምንጮች መረዳት ችሏል።
ጥቃቱ ሲፈጸም በአካባቢው የነበሩ አንድ ግለሰብ ስለሁኔታው ሲያስረዱ፣ ‹‹ጥቃቱ የተለመደ ነው፣ በኦሮሚያ ክልል ውስጥ ከገርበ ጉራቻ አልፎ በተለምዶ ዓሊ ዶሮ የሚባል ቦታ የተፈጠረው ነገር አዲስ አይደለም። በየቀኑ ለማለት በሚቻል ሁኔታ ዕገታና ግድያ አለ።...

ተጨማሪ ያንብቡ: https://www.ethiopianreporter.com/139414/


የብሔርተኝነት ፖለቲካ ጡዘትና በአገር ላይ የሚደቅነው አደጋ

በነገደ ዓብይ
ከአንድ ዓመት በፊት በሪፖርተር ዕትም “እኔ እምለው” ዓምድ ላይ፣ “ብሔር ተኮር ፌዴራሊዝሙ ረጅም ርቀት ይወስደናልን?” በሚል ርዕስ በአንድ ጸሐፊ የተሰናዳ አንድ ወቅታዊ ጽሑፍ ማንበቤን አስታውሳለሁ፡፡ ይህንን ጽሑፍ ያስታወስኩት ዛሬ ርዕስ የማላደርገውን ነገር ግን፣ አሁን ላለንበት ምስቅልቅል የዳረገን ሕወሓት የገባበትን ቀውስ ስታዘብ ነው፡፡ እውነት ለመናገር አለመታደል ሆኖብን እንጂ፣ በአገራችን ወቅታዊ ሁኔታ ላይ ሙግትና ምክክር ማድረግ የሚያስፈልገው በእንዲህ ያለው መሠረታዊ ዕሳቤ ላይ መሆን ነበረበት፡፡ በጠቀስኩት ጽሑፍ የጸሐፊውን ሥጋትና አገራዊ ችግር እኔም የምጋራ በመሆኑ፣ የብሔር ፖለቲካው መለጠጥና መክረር ከፓርቲ ሽኩቻ አልፎ የእርስ በርስ ጦርነቱን እንዳያባብሰው፣ እንዲሁም አገርን የማያባራ ቀውስ ውስጥ እንዳይከት ያለኝን ግላዊ ሥጋት ለመሰንዘር እፈልጋለሁ፡፡
ሕወሓት መራሹ የኢሕአዴግ አገዛዝ በአገራችን አስከፊ ውጤት እያስከተለ ያለው...

ተጨማሪ ያንብቡ: https://www.ethiopianreporter.com/139467/


ዘወትር ዕረቡ የሚጠብቁት የሪፖርተር ጋዜጣ የተለያዩ መረጃዎችን ይዞ በገበያ ላይ ይገኛል
በድረገጻችን https://www.ethiopianreporter.com/ ላይም ያገኙታል።

----------||----------
የሪፖርተር ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን ይቀላቀሉ
ፌስቡክ↠ https://bit.ly/2Iv9bZB
ትዊተር↠ https://bit.ly/35qeNwV
ቴሌግራም↠ https://bit.ly/3Qb4N1M
ዩቲዩብ ↠ https://bit.ly/3p0jUQY
ቲክቶክ ↠ https://bit.ly/3Ruxsyv

የ ስራ ማስታወቂያዎች ↠ EthiopianReporterJobs.com


አሜሪካ ያቋረጠችው ድጋፍ ተፅዕኖ እንዳላሳደረበት የኅበረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ተናገረ

የአሜሪካ መንግሥት ባቋረጠው የፋይናንስ ድጋፍ ምክንያት በሥራው ላይ ተፅዕኖ እንዳልደረሰበት፣ የኢትዮጵያ ኅብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት አስታወቀ፡፡
ወደ ሥልጣን ከመጡ ስድስት ሳምንታት ያስቆጠሩት ፕሬዚዳት ዶናልድ ትራምፕ ወደ ነጩ ቤተ መንግሥት በገቡ የመጀመሪያዎቹ ጥቂት ቀናት፣  የአሜሪካ ዓለም አቀፍ ተራድኦ ድርጅት (ዩኤስኤአይዲ) ለአገሮች ሲያደርገው የነበረው ድጋፍ እንዲቋረጥ ማድረጋቸው ይታወሳል፡፡ የትራምፕ ውሳኔ በአፍሪካ ጤና አጠባበቅ ላይ ከፍተኛ ተፅዕኖ ማምጣቱ በስፋት እየተነገረ ነው፡፡ አሜሪካ አ.ኤአ. በ2024 ወደ 4.5 ቢሊዮን ዶላር ለአፍሪካ የጤና ዘርፍ ብቻ ዕርዳታ ማቅረቧን መረጃዎች ያሳያሉ፡፡
በአሜሪካ ለጤናው ዘርፍ ይቀርብ የነበረው ድጋፍ በመቋረጡ፣ ወሳኝ የሚባሉ አገልግሎቶች ላይ አስቸጋሪ ሁኔታ እንደሚፈጥር የጤና ዘርፍ ተዋንያን እየገለጹ ነው፡፡
ይህንን በተመለከተ ሪፖርተር ጥያቄ ያቀረበላቸው የኢትዮጵያ ኅብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ዋና ...

ተጨማሪ ያንብቡ: https://www.ethiopianreporter.com/139300/


Видео недоступно для предпросмотра
Смотреть в Telegram
#ማስታወቂያ

#ቴምር ሪልስቴት

‼️ፒያሳ ሱቅ ሽያጭ 

👉3.9ሚሊዮን 20ካሬ ቅድመ ክፍያ900,000ብር 4ተኛ እና 5ተኛ
👉4.2ሚሊዮን 20ካሬ ቅድመ ክፍያ 1.2ሚሊዮን 3ተኛ
👉4.8ሚሊዮን 20ካሬ ቅድመ ክፍያ 1.5ሚሊዮን 2ተኛ
👉5.5ሚሊዮን 20ካሬ ቅድመ ክፍያ 2ሚሊዮን 1ኛ
👉 7ሚሊዮን 20ካሬ ቅድመ ክፍያ 2.8ሚሊዮን ግራውንድ በውስጥ በኩል
👉10ሚሊዮን 20ካሬ ቅድመ ክፍያ 4ሚሊዮን ግራውንድ በውጪ
ለበለጠ መረጃ ይደውሉ
       👇👇👇👇👇👇
     +251911010170
     +251951574515
TemerRealEstateSalesConsultant


Видео недоступно для предпросмотра
Смотреть в Telegram
#ማስታወቂያ

ይቆጥቡ፤ የበለጠ ያግኙ!
የውጭ ሐዋላ የቁጠባ ሂሳብ
***
ደንበኞች ከውጭ ሀገራት የተላከላቸውን ገንዘብ ወይም በባንኩ የሚመነዝሩትን የውጭ ሀገር ገንዘብ የሚያስቀምጡበት የቁጠባ ሂሳብ ነው፡፡

• ከፍተኛ የወለድ መጠን ያስገኛል፤
• ደንበኞች ገንዘብ ከውጭ ሀገራት ሲላክላቸው ወይም በባንኩ ሲመነዝሩ የአየር ሰዓት ስጦታ ያገኛሉ፤
• የሂሳቡ ባለቤቶች ለውጭ ሀገር ጉዞ የውጭ ምንዛሪ ፍላጎታቸው ቅድሚያ ይሰጣቸዋል፡፡
***
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
ሁሌም የሚተማመኑበት ባንክ!
#cbe #banking #ethiopia #foreigncurrencies


#ማስታወቂያ

ሕብረት ባንክ እንኳን ለ1446 ዓ.ሒ የሐጅ ጉዞ በሰላም አደረሳችሁ እያለ፤ የሐጅ ጉዞ ክፍያዎን በአቅራቢያዎ በሚገኙ ቅርንጫፎቻችን በልዩ መስተንግዶ እንዲፈጽሙ በአክብሮት ይጋብዛል፡፡

በዚህ አጋጣሚ የሸሪዓውን መርህ መሰረት ያደረገ ሕብር ሀቅ የተሰኘ ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎታችን ተጠቃሚ ይሁኑ፡፡

ሐጀን መብሩር!

ሕብር ሀቅ
ሕብረት ባንክ
በሕብረት እንደግ!

📞 ለበለጠ መረጃ ወደ 995 ነፃ የጥሪ ማዕከል ይደውሉ፡፡
🤳 በቀላሉ አዳዲስ መረጃዎች እንዲደርስዎ የቴሌግራም ገፃችንን አሁኑኑ ይቀላቀሉ፡፡ https://t.me/HibretBanket
🌐 ሌሎች የማህበራዊ ገፆቻችንን እና ድህረ ገፃችንን linktr.ee/Hibret.Bank ይጎብኙ፡፡


የነገው ሰው እንዴት ይታነፅ?

በሳህሉ ባዬ
በዚህ መጣጥፍ የምንመለከተው ዓብይ ነጥብ ጨዋታ በሕፃናት አስተዳደግ ላይ መሠረታዊ መማሪያ መድረክ መሆኑንና የማሰብ ችሎታቸው እንዲዳብር፣ የግንዛቤ አድማሳቸው እንዲሰፋ፣ የቋንቋ ክህሎታቸው እንዲጠናከር፣ ጥበብን እንዲካኑና የእጅ ሥራ ዕውቀታቸው እንዲጎለብት የጨዋታ መድረኮችን ማመቻቸት በእጅጉ አስፈላጊ ጉዳይ መሆኑን ማሳየት ነው፡፡ በመሆኑም የዛሬዋ መጣጥፌ የምታተኩረው በሕፃናት አስተዳደግ ሒደት ላይ ጨዋታ ስላለው ጤናማና አይተኬ አስተዋጽኦ ይሆናል፡፡  
በሕፃናት አስተዳደግ ሒደት ላይ ጥናት ያደረጉ ባለሙያዎች የጨዋታን ጠቀሜታ እንደሚከተሉት አስፍረውታል፡፡ ሕፃናት በአካል፣ በአዕምሮ፣ በስሜትና በማኅበራዊ ለጋና ታዳጊ ስለሆኑ የሚያዩት፣ የሚሰሙት፣ የሚዳስሱትና የሚያሸቱት ሁሉ ከህልውናቸው ጋር በፍጥነት ይዋሃዳል፡፡ ሕፃናት መንቀሳቀስ የሚወዱና በአንድ ሥራ ላይ ብቻ ለረዥም ጊዜ ተጠምደው መቆየት የማይችሉ ናቸው፡፡ ጨዋታ ይወዳሉ፡፡ ጨዋታ ሲባል ቧል...

ተጨማሪ ያንብቡ: https://www.proworksmedia.com/139317/


የጫኑትን በመጠራጠር ተሽከርካሪዎችን ለወራት እንዳይንቀሳቀሱ ማገድ ሕጋዊ ዕርምጃ ሊባል አይችልም

ሰሞኑን ከተሰሙ መረጃዎች መካከል አንዱ ከጂቡቲ የተለያዩ ሸቀጣ ሸቀጦችንና ምግብ ነክ ምርቶችን የጫኑ ከ150 ያላነሱ ተሽከርካሪዎች በአፋር ክልላዊ መንግሥት ሰመራ ውስጥ ተይዘው እንዳይንቀሳቀሱ መደረጉን ያመለክታል፡፡ ከእነዚህ ተሽከርካሪዎች ውስጥ ብዙዎቹ ከአንድ ወር በላይ የቆዩ ሲሆን፣ አንዳንዶቹ ደግሞ ወደ ሁለት ወራት የተጠጋቸው ስለመሆኑም ተሰምቷል፡፡ እንደ መረጃው ከፌዴራል ጉምሩክ በተላለፈ መመርያ መሠረት ተሽከርካሪዎቹ ወደ መሀል አገር እንዳይገቡና እዚያው ባሉበት ቦታ እንዲቆዩ ሆነዋል፡፡ ተሽከርካሪዎቹ ከጫኑት ስንዴ፣ ዘይት፣ ዱቄትና ሌሎች ሌሎች ምግብ ነክ ምርቶችን የጫኑ ናቸው፡፡ ሌሎች ሸቀጣ ሸቀጦችንም የጫኑ ተሽከርካሪዎች ስለመኖራቸው ተጠቅሷል፡፡ ባልተለመደ ሁኔታ ተሽከርካሪዎቹ ተይዘው እንዲቆዩ ለምን እንደተወሰነባቸው ግልጽ ሳይደረግላቸው ቆይቶ በኋላ ላይ ግን ከፍራንኮ ቫሉታ ጋር በተያያዘ ተፈጠረ በተባለ ችግር መሆኑ ተሰምቷል፡፡ ዕቃዎቹን ካስጫኑ ድ...

ተጨማሪ ያንብቡ: https://www.proworksmedia.com/139260/


የኩላሊት ንቅለ ተከላ ሕክምና ችግር ከፍተኛ ደረጃ ላይ መድረሱ ተገለጸ

በቅዱስ ጳውሎስ አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ብቻ እየተሰጠ የሚገኘው የኩላሊት ንቅለ ተከላ ሕክምና ‹‹አለ›› ሊባል በማይቻልበትና በከፍተኛ ችግር ውስጥ እንደሚገኝ ተገለጸ፡፡
የኢትዮጵያ የኩላሊት ንቅለ ተከላ ማኅበር ፕሬዚዳንት አቶ ቢንያም አበራ ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ የኩላሊት ሕመምና ንቅለ ተከላ እንዲደረግላቸው የሚፈልጉ ታማሚዎች ቁጥር ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ ነው፡፡ ሆኖም በቅዱስ ጳውሎስ አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ብቻ በመሰጠት ላይ የሚገኘው የንቅለ ተከላ ሕክምና በሚፈለገው ልክ ነው ለማለት አያስደፍርም ብለዋል፡፡
‹‹የኩላሊት ሕመምና ሕክምናውን የሚፈልገው ሰው ቁጥር ጨምሯል፡፡ ንቅለ ተከላው ግን አለ የሚባልበት ደረጃ ላይ አይደለም፡፡ ሙሉ ለሙሉ ቆሟል ለማለትም የሚቸግር ነው፤›› የሚሉት ፕሬዚዳንቱ፣ ከባለሙያ እጥረት፣ ከመድኃኒት አቅርቦትና ከሕክምና ግብዓት ችግሮች ጋር በተያያዘ ምክንያት አጥጋቢ አገልግሎት እየሰጠ አይደለም ብለው እንደሚያም...

ተጨማሪ ያንብቡ: https://www.proworksmedia.com/139288/


በአዲስ አበባ ከተማ በኢ-መደበኛ ንግድ መሰማራት የሚችሉት የከተማዋ ነዋሪዎች ብቻ እንዲሆኑ የሚደነግግ ደንብ ወጣ


ደንቡ ደረሰኝ የመቁረጥ ግዳጅ ጥሏል

በሃይማኖት ደስታ
በአዲስ አበባ ከተማ መደበኛ ባልሆነ ንግድ መሰማራት የሚችሉት የከተማዋ ነዋሪዎች ብቻ መሆናቸውን የሚደነግግ ደንብ መፅደቁ ታወቀ፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ በ4ኛ ዓመት 8ኛ መደበኛ ስብሰባው ተወያይቶ ካፀደቃቸው ረቂቅ ደንቦች መካከል፣ ‹‹መደበኛ ያልሆነ የጎዳና ላይ ንግድን ሥርዓት ለማስያዝ›› ይረዳ ዘንድ እንደተዘጋጀ ለማወቅ ተችሏል፡፡
‹‹መደበኛ ያልሆነ የጎዳና ላይ ንግድን ሥርዓት ለማስያዝ›› ደንብ ቁጥር 184/2017 ሆኖ ከፀደቀው ሕግ አጠቃላይ ይዘት ጋር በተገናኘ፣ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፍትሕ ቢሮ ኃላፊ አቶ ተክሌ በዛብህን ሪፖርተር አነጋግሯቸው፣ ‹‹ካቢኔው ያፀደቀው አዲሱ ደንብ በመዲናዋ አንድ ግለሰብ መደበኛ ባልሆነ ንግድ ላይ ሊሰማራ የሚችለው፣ የአዲስ አበባ ከተማ መታወቂያ ካለውና የከተማዋ ነዋሪ ከሆነ ብቻ ሊሆን እንደሚገባ አስገዳጅ መሥፈርት አስቀምጧል፤››...

ተጨማሪ ያንብቡ: https://www.proworksmedia.com/139308/


የክልሉን ሕዝብ ሥጋት ላይ የጣለው የሕወሓት አመራሮች ውዝግብ

የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዚዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ ሐሙስ መጋቢት 4 ቀን 2017 ዓ.ም. በአዲስ አበባ በሰጡት መግለጫ፣ በትግራይ ክልል ያለውን ወቅታዊ ሁኔታ ተጠቅመው ትግራይን ማጥፋት የሚፈልጉ ኃይሎች እንዳሉ በመጥቀስ፣ ‹‹ጥቂት ከፍተኛ አመራሮች ከኤርትራ መንግሥት ጋር እየሠሩ ነው፤›› የሚለውን ጨምሮ ካቀረቧቸው ማብራሪያዎች በኋላ፣ በደብረ ጽዮን ገብረ ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራው ሕወሓት ክንፍ ምላሽ ሰጥቷል፡፡
በሁለቱ የሕወሓት ክፍሎች መካከል ያለው የፖለቲካ ውጥረት መካረርን ተከትሎ 24 የምዕራቡ ዓለም አገሮችና የአውሮፓ ኅብረት ወደ ግጭት መመለስ እንደማይገባ ማሳሰቢያ ሲሰጡ፣ በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ምክትል ፕሬዚዳንት ሌተና ጄኔራል ታደሰ ወረደ የሚመራው የሰላምና ፀጥታ ካቢኔ ቢሮ በበኩሉ፣ የፌዴራል መንግሥት ጣልቃ እንዲገባ የቀረበው ጥያቄ ኃላፊነት የጎደለው ነው ሲል ወቅሷል።
በጊዜያዊ አስተዳደሩ ፕሬዚዳንት የሚመራውን የፖለቲካ ድርጅቱ...

ተጨማሪ ያንብቡ: https://www.ethiopianreporter.com/139304/


ጠቅላይ ሚንስትር ዓብይ አህመድ(ዶ/ር) ሐሙስ መጋቢት 11 ቀን 2017 ዓ.ም በፓርላማ ተገኝተው ከምክርቤት አባላት ለሚቀርቡላቸው ጥያቄዎች ማብራሪያ ሊሰጡ ነው።


ኑሮና ብልኃቱ አልሳካ ያለው የጉርስና የመጠለያ ነገር

በገነት ዓለሙ
በኢትዮጵያ ውስጥ ያለው የኑሮ ውድነት የጠያቂ መብዛትንና የሸቀጥ ማነስን አድምጦ ዋጋ ለመተኮስ የሚፈጥን፣ ለአቅርቦት መብዛትና ለፍላጎት መቀነስ ግን ጆሮ የሌለው፣ የዓለም የነዳጅ ዋጋ መውደቅ እንኳ ከቅጠላ ሊገታው ያልቻለ ዓይን አውጣ ነው፡፡ የዋጋ አቀጣጠሉ ደግሞ ያው በደርግ ዘመን እንደለመደው ባለሁለት አቅጣጫ ነው፡፡ መሸጫ ተመን ከፍ በማድረግና የሚሸጠውን ነገር መጠን/ሚዛን፣ ጥራት ወይም ውፍረት በመቀነስ፡፡
ከሚገዙ/ከሚሸጡ ነገሮች የብዙዎች ጭንቅ የሆኑት የመሠረታዊ ፍላጎት አቅርቦቶች ናቸው፡፡ ከመሠረታዊ ፍላጎት ውስጥ ልብስ አሮጌ በማሳደስም ሆነ በመግዛት የሚሸፈን ‹‹ትርፍ ነገር›› ሆኗል፡፡ የልጅ ትምህርት ቤትም ጊዜ ይሰጣል፡፡ ዕድሜ ሲደርስ እንደምንም አንድ የደንብ ልብስ ገዝቶ መንግሥት ትምህርት ቤት መስደድ ነው፡፡ ሕክምናም ከአገረ ሰብ መድኃኒት፣ ከጠበልና ከመሳሰለው ካለፈ ያው ጤና ጣቢያ እንዳደረገ ይኮናል፡፡ ሞት አንደኛውን ከመጣም...

ተጨማሪ ያንብቡ: https://www.ethiopianreporter.com/139255/

Показано 20 последних публикаций.