Ethiopian Digital Library


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: Образование


በዚህ ቻናል ስለ
👉ትምህርት፣
👉ሥራ እና
👉ማህበራዊ ጉዳይ
መረጃ ያገኛሉ!
Contact: @ethiodlbot

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
Образование
Статистика
Фильтр публикаций


ነዳጅ በሊትር እስከ 900 ብር እየተሸጠ ነው

በኦሮሚያ ክልል መቱ ከተማ ነዳጅ በሊትር እስከ 900 ብር እየተሸጠ መሆኑ በነዋሪዎች ዘንድ ቅሬታ አስነሳ


የነዳጅ አቅርቦት በማደያዎች ባለመኖሩ በጥቁር ገበያ እየተሸጠ እንደሚገኝ ያነሱት ነዋሪዎቹ፤ በተለይ በትራንስፖርት አገልግሎት ዘርፉ ላይ ጫናው ከፍ ያለ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

የኦሮሚያ ንግድ ቢሮ በበኩሉ "በዚህ መልኩ የተጋነነ የጥቁር ገበያ የለም" ሲል ቅሬታውን ያስተባበለ ሲሆን ሕገ-ወጥ የነዳጅ ንግድን ለመቆጣጠር እየሰራ መሆኑን ገልጿል።

እንደ አሐዱ ሬዲዮ ዘገባ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልልም ተመሳሳይ የሕገ-ወጥ ነዳጅ ሽያጭ መኖሩ ተጠቁሟል። #አሐዱ

@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library




Видео недоступно для предпросмотра
Смотреть в Telegram
ሐኪም እንዴት ቲክቶክ ላይ ይወጣል አሉኝ

@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library


ትናንት ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ አንድ ዶላር 136 ብር የገዙት ባንኮች፤ ዛሬ 1 ዶላር 126 ብር እየሸጡ (እየመነዘሩ) ነው።

እንዴት ነው ነገሩ፤ ባንኮች እየከሰሩ ነው የሚመነዝሩት ማለት ነው? ወይስ ምንድነው?

@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library


ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ዋናው መስሪያ ቤት ነው ብሎ በዚህ ስልክ ደውሎ ጓደኛዬን ሊያጭበረብር ሞከረ ።

አጭበርብሮ መኖርን ቋሚ ስራቸው አድርገውታል።

ስንቱን ዘርፈውት ይሆን!

0973313637
0973313637
0973313637

@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library


መርፌ ቁልፍ

የምታዩት ስዕል እኔ ተወልጄ ባደግሁበት ሰቆጣ መርፌ ቁልፍ እንለዋለን። መርፌ ቁልፍ በገጠር ብዙ አገልግሎት አለው። ብዙ ገጠሬዎች ቢጠቀሙበትም ባይጠቀሙበትም እንደመጠባበቂያ ከኪሳቸው የማይለዩት መሣሪያ ነው። አንዳንድ ሰዎችም መያዣ ሊያበጁለት ይችላሉ። ዋነኛ ስራው ደረት እንዳይገለጥ እንደ አዝራር ለመጠቀም።

በድንገት ቢቀደድ እስኪሰፋ ድረስ ለማያያዝም ይጠቅማል። መርፌ ቁልፍ እሾህ ቢወጋ ወይም የእንጨት ስንጥር በአካል ላይ ቢገባ ለማውጣት ያገለግላል። እግር ወይም እጅ ቆስሎ ምግል ሲይዝም ጫፉ በእሳት ተጠብሶ ይቀዘቅዝና ለማምገል ይጠቅማል። ሞያሌ ወይም ሙጀሌ የሚወጣውም በመርፌ ቁልፍ ነው።

አንዳን ኮረዶች በተሠራ ጸጉራቸው ላይ እንደጌጥ ሲጠቀሙበት የነበሩ ሲሆን ለአገልግሎት ሲፈልጉት አውጥተው ይጠቀሙበትና ተመልሰው ጸጉራቸው ላይ ያደርጉት ነበር።
በነገራችን ላይ በ1950/60ዎቹ አምስት መርፌ ቁልፍ አምስት ሳንቲም፣ 12 ደግሞ በአስር ሳንቲም ይሸጥ ነበር። መርፌም በአምስት ሳንቲም 25፣ በአስር ሳንቲም ደግሞ 50 ይሸጥ ነበር።

መርፌ ቁልፍን የፈጠረው ዋልተር ሃንት የተባለ አሜሪካዊ ሲሆን የፈጠረውም እኤአ 1849 ነው። መርፌ ቁልፉን የፈጠረውም የነበረውን የ15 ዶላር ዕዳ በፍጥነት ለመክፈል ነበር። ሀንት መርፌ ቁልፉን ከሠራ በኋላ ዕዳውን በፍጥነት የከፈለ ቢሆንም የወደፊት ተፈላጊነቱን ሊያጤን አልቻለም። ስለሆነም ጠቃሚነቱን የተገነዘበ ባለሀብት የባለቤትነት መብቶቱን በ 400 ዶላር ገዝቶታል። ቅርጹም ከተፈጠረቀት ጊዜ እስካሁን ሳይለውጥ ቆይቷል።
ምስኪን ሀንት! የተረፈው ስሙ እንጂ ጥቅሙ ሳይሆን ቀረ።

@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library


በጉለሌ ክፍለ ከተማ ውኃ በአቆረ ጉድጓድ ውስጥ ዋና ለመዋኘት የገቡ ሦስት ታዳጊዋች ሕይወት አለፈ

በአዲስ አበባ ጉለሌ ክፍለ ከተማ ውኃ በአቆረ ጉድጓድ ውስጥ ዋና ለመዋኘት የገቡ ሦስት ታዳጊዋች ሕይወት ማለፉን የአዲስ አበባ የእሳት እና አደጋ ስጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን አስታወቀ።

ሁለት የ13 እና አንድ የ16 ዓመት ዕድሜ ያላቸው ታዳጊዎቹ ትላንት እሑድ ኳስ ሲጫወቱ ቆይተው በጉለሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 5 ጉለሌ ዕፅዋት ማዕከል ጊቢ ውስጥ ባለ ውኃ በአቆረ ጉድጓድ ውስጥ ዋና ለመዋኘት ገብተው ሕይወታቸው ማለፉን ነው ኮሚሽኑ የገለጸው።

ጉድጓዱን የቆፈሩ እና በውኃ የሚጠቀሙ አካላት ተገቢውን የአደጋ መከላከል ሥራ የማከናወን ኃላፊነት ያለባቸው በመሆኑ እያጋጠመ ያለውን አደጋ አሰቀድሞ በመከላከል በኩል ግዴታቸውን እንዲወጡ ኮሚሽኑ አሳስቧል።

ወላጆች እና የአካባቢው ማኅበረሰብም ለታዳጊዋች አስፈላጊውን ጥበቃ እንዲያደርጉም ጥሪ አቅርቧል። #EBC

@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library


«ፈተናው እየበዛብኝ ነው ሁላችሁም በፆማችሁ እና በፀሎታችሁ አስታውሱኝ» አብዱ ኪያር

“እማዬ አላህ ነፍስሽን በጀነት ያኑራት። አሁንም አልሓምዱሊላህ።” ድምጻዊ አብዱ ኪያር

«በቀደም ሊፍት ወድቆብን ከከባድ አደጋ ተረፍኩ። ዛሬ ደግሞ የናቴን ሞት ተረዳሁ። ፈተናው እየበዛብኝ ነው።

ሁላችሁም በፆማችሁ እና በፀሎታችሁ አስታውሱኝ።» ብሏል

ነብስ ይማር!

@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library


#Fuuny

ባል ስንመርጥ እራሱ የአርሴናል ደጋፊ ከሆነ አንፈልግም 😂😂 ጨጓራው ያለቀ በሽተኛ ቋሚ አስታማሚ ነው የሚያደርጉን::

አርሰናል ግን...

Helana Oum

@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library

9.5k 0 23 13 87



Видео недоступно для предпросмотра
Смотреть в Telegram
@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library


Khaby Lame - 161.4 million followers - TikTok

2020: 0 Dollar

2023: 16,000,000 Dollar

@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library


ፈተናውን ሙሉ በሙሉ ደፍኖታል

ሳህሌ ነጋሲ የተባለው የ17 አመቱ ታዳጊ በአሜሪካ ኒው ጀርሲ ተማሪ ሲሆን የዘንድሮውን የኮሌጅ መግቢያ ፈተና ወይንም ሳት (SAT) የወሰደ ነው፡፡ በውጤቱም 1600 ነጥብ ማምጣት ችሏል፡፡ ይህም ማለት ፈተናውን ሙሉ በሙሉ ደፍኖታል፡፡

በመላው አሜሪካ በሚሰጠው በዚህ ፈተና እንዲህ አይነት ውጤት እንብዛም አይመጣም፡፡

የሳት ፈተናን መድፈን የሚችሉት ፈተናውን ከወሰዱ ተማሪዎች መካከል ከአንድ ፐርሰንት በታቹ ብቻ ናቸው፡፡ ማለትም በየአመቱ የሚደፍን ተማሪ የማይኖር ሲሆን ከአመታት በኋላ አንድ ተማሪ ደፍኖ ይገኛል፡፡ ሳህሌ ነጋሲ ከእነዚህ ጥቂት ተማሪዎች መካከል ዘንድሮ ተገኝቷል፡፡

በኒውዮርክ ተወልዶ በኒው ጀርሲ ያደገው ይህ ተማሪ ለዚህ ፈተና ዝግጅት ያደረገው በትምህርት ቤት በሚሰጠው ትምህርት ብቻ እንዳልሆነ ገልጿል፡፡ ከኢንተርኔት ላይ በነፃ የሚሰጡ ትምህርቶችን መከታተሉ እንደጠቀመውም አስረድቷል፡፡

በኒውዮርክ ተወልዶ በኒው ጀርሲ ያደገው ይህ ተማሪ ለዚህ ፈተና ዝግጅት ያደረገው በትምህርት ቤት በሚሰጠው ትምህርት ብቻ እንዳልሆነ ገልጿል፡፡ ከኢንተርኔት ላይ በነፃ የሚሰጡ ትምህርቶችን መከታተሉ እንደጠቀመውም አስረድቷል፡፡

በቀጣይነት በሀርቫርድ ዩኒቨርስቲ የህግ ትምህርት የመከታተል ፍላጎት እንዳለው ያስረዳው ሳህሌ ጨምሮም ‹‹ከአስር አመት በኋላ በዚህ ፈተና ካመጣሁት ውጤት የበለጠ ትልቅ ነገር እሰራለሁ›› በማለት ህልሙን አስታውቋል፡፡

የዚህ ተማሪ መረጃ ከትላንት ጀምሮ ይፋ ከሆነ በኋላ አንዳንድ ኢትዮጵያዊያን ተማሪው ኢትዮጵያዊ እንደሆነ እየተናገሩ ይገኛሉ፡፡ ኤርትራዊያን በበኩላቸው ደግሞ የአገራቸው ዜጋ መሆኑን እየገለፁ ናቸው፡፡ #Zehabesha

@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library




ስንት ገባች ከእናንተ ጋር?

@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library


" በዚህ ዓመት 150 ሺህ የሚደርሱ የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ፈተናቸውን በበየነ መረብ (ኦንላይን) ይወስዳሉ " - ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ

@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library


የ2017 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ሁሉም ተማሪዎች በተማሩበት ሥርዓተ ትምህርት ይዘት ይዘጋጃል፡፡

የ2017 ዓ.ም ተፈታኝ ተማሪዎች ከ9ኛ - 10ኛ በነባሩ ሥርዓተ ትምህርት፣ ከ11ኛ - 12ኛ ደግሞ በአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት የተማሩ ናቸው። ነገር ግን በ2015 ዓ.ም በመላ ሀገሪቱ በናሙናነት በተመረጡ ት/ቤቶች የስርዓተ ትምህርት የሙከራ ትግበራ ላይ የተሳተፉ ት/ቤቶች ላይ የነበሩ ተማሪዎች 10ኛ ከፍልን በአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት የተማሩ ናቸው፡፡  በአማራ ክልል በ2016 የትምህርት ዘመን መፈተን ሲገባቸው በጸጥታ ችግር ምክንያት ሳይፈተኑ የቀሩና የ11ኛ ክፍልን በነባሩ ሥርዓተ ትምህርት የተማሩ ት/ቤቶች ላይ የነበሩ ተማሪዎች በ2017 ዓ.ም  የሚፈተኑ አሉ፡፡ በመሆኑም የ2017 ዓ.ም የሁለተኛ ደረጃ መልቀቂያ ፈተና ከላይ የተገለጹትን ሶስቱንም ነባራዊ ሁኔታዎች ከግምት ውስጥ ባስገባ እና ሁሉንም የዘመኑን ተፈታኝ ተማሪዎች በማከለ መንገድ ስታንዳርዱን፣ ደህንነቱንና ሚስጢራዊነቱን ጠብቆ በመዘጋጀት ላይ ይገኛል።

ስለሆነም የፈተና ዝግጅቱ፡-
    1) ከ9ኛ ከፍል ሙሉ በሙሉ ከነባሩ ሥርዓተ ትምህርት፣
    2) ከ10ኛ ክፍል በነባሩና በአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት ላይ ተመሳሳይ ይዘቶች፣
    3) ከ11ኛ ከፍል በነባሩና በአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት ላይ ተመሳሳይ ይዘቶች፣
    4) ከ12ኛ ከፍል ሙሉ በሙሉ ከአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት መሰረት የሚዘጋጅ ይሆናል።

ከላይ የተዘረዘረው የዝግጅት ሂደት በሁሉም የትምህርት ዓይነቶች ላይ እንደተጠበቀ ሆኖ የኢኮኖሚክስ የትምህርት ዓይነት ግን በስርዓተ ትምህርቱ አዲስ የተጀመረ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ በ12ኛ ክፍል ይዘት ላይ ብቻ ተመስርቶ የሚዘጋጅ ይሆናል።

በአጠቃላይ ሁሉም ተማሪዎች ከ9ኛ -12ኛ ክፍል በየተማሩበት የሥርዓተ ትምህርት ይዘት ላይ መመስረት ፈተናው እንደሚዘጋጅ አውቀው ተገቢውን ዝግጅት እንዲያደርጉ መልዕክታችንን እናስተላልፋለን።

ስለሆነም ተማሪዎች አስፈላጊውን ዝግጅት እንዲያደርጉ ወላጆች፣ መምህራንና መላው የትምህርት ማህበረሰብ ተገቢውን ድጋፍ እንዲያደርጉ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን።
                         
የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት!

@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library


#መልካም_ዜና: አሊባባ ከሚቀጥለው ሳምንት ጀምሮ #በኢትዮጵያ_ብር ክፍያ መቀበል እንደሚጀምር አስታወቀ!

አለም አቀፍ የኤሌክትሮኒክስ ግብይት ተቋም የሆነው አሊ ባባ እንደገለፀው ከሚቀጥለው ሳምንት ጀምሮ #በአሊ_ኤክስፕረስ የበርካታ አገራትን ገንዘብ ጥቅም ላይ ያውላል፡፡

ከእነዚህ አገራት መካከል ኢትዮጵያ፣ ናይጄሪያ፤ ግብፅ፣ ኬንያ እና ደቡብ አፍሪካ ይገኙበታል፡፡ የክፍያ መፈፀሚያ ገንዘቦችን ማስፋፋት ያስፈለገው ለአፍሪካ ተጠቃሚዎች በስፋት ተደራሽ ለመሆን በማሰብ እንደሆነ የጠቀሰው አሊ ባባ በተጨማሪም በአለም አቀፍ የክሬዲት ካርዶችና #የውጭ_ምንዛሬ ላይ ያለውን ጥገኝነት ለማስቀረት እንደሆነ አስረድቷል፡፡

የአፍሪካ አገራትን ገንዘብ በግብይቱ ውስጥ ጥቅም ላይ ማዋሉ በአለም አቀፍ የክፍያ ስርአት የተነሳ ለአፍሪካዊያን ትልቅ ማነቆ የሆነውን ችግር ለመቅረፍ ማቀዱንም አስታውቋል፡፡ በዚህም አዳዲስ የአገልግሎቱ ተጠቃሚዎችን እንደሚያገኝ ተስፋ ሰንቋል፡፡

ለዚህ እንዲረዳው በተጠቀሱት አገራት ከሚገኙ የዲጂታል ክፍያ አገልግሎት ሰጪዎች ጋር ጥምረት መፍጠሩን የገለፀው አሊ ባባ ከሚቀጥለው ሳምንት ማለትም #የካቲት_17 ጀምሮ ብርን ጨምሮ የተለያዩ ገንዘቦችን በግብይት ስርአቱ ውስጥ እንደሚያካትት አስታውቋል፡፡

#ለምሳሌ፦ አሊባባ ከቴሌ ብር ጋር ለመስራት ቢስማማ ከአሊ ኤክስፕረስ ላይ ኦንላይን/Online እቃ ለመግዛት ቴሌ ብር ተጠቅሞ መክፈል ይቻላል ማለት ነው!

@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library


በ2017 የትምህርት ዘመን ከ50ሺ በላይ ተማሪዎች የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተናን ለመውሰድ ተመዝግበዋል

በአዲስ አበባ በማህበራዊና በተፈጥሮ ሳይንስ የትምህርት መስኮች የ2017 ዓመት 50ሺ 807 ተማሪዎች የ12ኛ ክፍል ፈተና እንደሚወስዱ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ አስታውቋል።

በ2017 የትምህርት ዘመን  የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተናን በከተማ አስተዳደሩ በበይነ መረብ ኦን ላይን በውጤታማነት ለመስጠት በሚያስችል ስራ እየተሰራም መሆኑን የቢሮው ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ ሳምሶን መለሰ ለብስራት ሬድዮ እና ቴሌቪዥን ተናግረዋል።

የ2017 የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና በከተማ አስተዳደሩ በበይነ መረብ በውጤታማነት ለመስጠት እንዲቻል ከወዲሁ የተለያዩ የቅድመ ዝግጅት ተግባራት ለማከናወን እቅድ መዘጋጀቱንና ወደ ስራ መገባቱን አንስተዋል። ፈተናው ኦን ላይን እንደመሰጠቱ ኮምፒውተሮችና እና መሟላት የሚገባቸውን መሰል ግብዓቶች የመለየት ስራ ተጀምሯል።

ለፈተናው አስፈላጊ የሆኑ ግብአቶችን የማዘጋጀት ተግባራት ከወዲሁ በመጀመር ፈተናው በታቀደለት መርሃ ግብር እንዲሰጥ በትኩረት መስራት ይገባል ተብሏል።

@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library

17k 1 24 6 37

በ1929 የካቲት 12 ቀን የተፈጸመውን ግፍ ደራሲ ተመስገን ገብሬ በአይኑ የተመለከተውን እንደሚከተለው ከትቦ አስነብቧል

"ቀኑ ብርቱ ፀሐይ ነበር፡፡ በዚያ እስር ቤት በማዘጋጃ ቤት ሜዳ ነበርና ብርቱ ክቢያ ተከበን ታላቅ ፍርሃት ነበር፡፡ ውሃና መብልም አላገኘንም፡፡ በሦስተኛው ቀን ጊዜውም ስድስት ሰዓት ሲሆን አስራ ሰባት ሰዎች በውሃ ጥማቱ ሞቱ፡፡ ይህም ቀን ጨለመ፡፡ እህልና ውሃ ሳናገኝ ሦስተኛው ቀን ነበርና ገንዘብም እየተቀበሉ በኰዳቸው ጣሊያኖች ለእስረኞች ውሃ መሸጥ ጀመሩ፡፡

"ሕይወታችንም በዚህ ስቃይ ውስጥ ታንቃ ስንጨነቅ መሸ፤ እንጂ ለቀን ቀኑ ረጅም ነበር፡፡ ከዚያ ረሐብና ውሃ ጥማት እንዲገድሉን መርጠን ነበር፡፡ ይህንንም ከልክለውን ሁለት ካሚዮን አምጥተው ከዚህ ወደሚሰፋ እስር ቦታ ሊወስዱን እየቆጠሩ ስሙን እየፃፉ 30ውን አሳፈሩት፡፡ እንደተናገርኩት እኔ በጽህፈት ቤቱ በር አጠገብ ስለነበርኩ እስረኛውን አየቆጠሩ አያሳፈሩ መጓዝ የጀመሩ ከወዲያ በኩል ነበርና ስለዚህ የኔ መሄዴ ዘግይቶ ነበር፡፡ ብዙ የሚያሳዝን ቁም ነገሮች በመዘግየቴ አየሁ፡፡

"ሦስት ሴቶች በወሊድ ተጨንቀው ኖረዋል፡፡ ሊወልዱም ቦታ አላገኙምና በአስረኛው ግፊ ተጨፍልቀው ሞተዋል፡፡ ሦስቱም ከትንንሽ ህፃናቶቻቸው ጋር ሬሳቸው ወድቆ አየሁት፡፡ በውሃ ጥማትና በረሃብ እነርሱም በቦምብ ከገደሉት ከሞተው ሰውና ከሬሳው ብዛት የተነሳ እኒህን በወሊድ የሞቱትን ያስተዋላቸው አልነበረም፡፡ እኔንም ሊገድሉኘ ስሜን በሊስት ይዘው ይፈልጉኝ ነበርና ስሜን ፅፈው ሊያሳፍሩኝ ሲሉ ሌላ ስም ነገርኳቸው፡፡ በካሚዮንም እስረኛውን ወደወሰዱበት ስፍራ አጓዙን፡፡

"በመንገድም የካሚዮኑ መብራት በሚወድቅበት እንመለከት ነበር፡፡ መንገዱ ሁሉ ሬሳ ተሞልቶ ነበር፡፡ በገደሏቸው በሐበሾች ሬሳ ተሞልቶ ነበር፡፡ ዝም ብለው በላዩ ይነዱበት ነበር፡፡ በሬሳው ብቻ አይደለም፡፡ ነገር ግን ሬሳውን ደግሞ በካሚዮናቸው በጨፈለቁት ወቅት በሰው ሬሳ መንገዱ ተበላሽቶ ያስጸይፍ ነበር፡፡ ከመንገዱም ዳር የወደቁትን ሬሶች የካሚዮኑ ብርሃን በወደቀባቸው ጊዜ ድመቶች ጐንጫቸውን ነክሰው ጺማቸውን እያራገፉ ሲበሏቸው አየሁ፡፡"
ገጽ 94-95

ተመስገን ገብሬ ህይወቴ (ግለ-ታሪክ)

ክብር ለየካቲት 12 ሰማዕታት !!

@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library

Показано 20 последних публикаций.