Ethiopian Digital Library


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: Образование


በዚህ ቻናል ስለ
👉ትምህርት፣
👉ሥራ እና
👉ማህበራዊ ጉዳይ
መረጃ ያገኛሉ!
Contact: @ethiodlbot

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
Образование
Статистика
Фильтр публикаций


የዩኒቨርሲቲ መውጫ ፈተና ከ177 ሺህ በላይ ተማሪዎች ተፈትነው ያለፉት 47,790 (27%) ብቻ ናቸው ::

#Exit_Exam_Result

@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library


Top 10 Countries in Africa with highest literacy levels

1. Seychelles🇸🇨,95.9%
2. South Africa 🇿🇦,95.0%
3. Sao tome and Principe 🇸🇹94.8%
4. Namibia🇳🇦,92.3%
5. Mauritius🇲🇺,92.2%
6. Cape verde,🇨🇻,
7. Cote d'ivoire 🇬🇳,89.9%
8. Zimbabwe🇿🇼,89.7%
9. Eswatin 🇸🇿88.4%
10. Zambia🇿🇲86.7%

@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library


በአዲስ አበባ በ239 የሽማቾች ልኳንዳ ቤቶች
1 ኪሎ ስጋ - ከ460 ብር እስክ 520 ብር እንዲሸጥ ተመን ተቀምጦለታል::
የአዲስ አበባ ህብረት ስራ ኮሚሽን

@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library


የscholarship እድል የሚያስገኘው የALX Pathway ፕሮግራም ምዝገባ ሊያልቅ 4 ቀን ብቻ ቀረው!

የALX ‘Pathway’ ፕሮግራምን በመውሰድ፣ የአለምአቀፍ ዲግሪ እና ሙሉ ስኮላርሺፕ እድል ለማግኘት ይመዝገቡ። የዚህ ስኮላርሺፕ እድል በጥቅሉ በአመት የ85,000 አሜርካን ዶላር፣ ወይም የ11 ሚሊዮን የኢትዮጵያ ብር፣ ተመጣጣኝ ዋጋ አለው።

ALX ከ14 በላይ ታዋቂ ዓለም አቀፍ ዩኒቨርሲቲዎች ጋር የትብብር ስምምነት አለው። አብዛኛዎቹ ዩኒቨርሲቲዎች የሚገኙት America ሲሆን፣ በEurope እና South Africa የሚገኙም አሉ።

የዚህ የትብብር ስምምነት ዋና ይዘት፣ የALX Pathway ኘሮግራምን በስኬት የሚጨርሱ ልጆች፣ በእነዚህ ታዋቂ ዩኒቨርሲቲዎች ተቀባይነት እና የስኮላርሺፕ እድሎች የሚያገኙበትን መንገድ ማስፋት ነው።

የምዝገባውን ሂደት ደረጃ በደረጃ ማብራሪያ ለማየት፣ እንዲሁም ምዝገባውን በተሳካ ሁንያ ለማጠናቀቅ፣ ይህንን የቴሌግራም ቻናል ተቀላቀሉ፡- https://t.me/ALXScholarship2ndBatch.

ወደ ምዝገባው ቀጥታ ለመሄድ ይህንን ተጫኑ - https://www.alxafrica.com/join-pathway/


ሁሌ የሚገርመኝ ስለ ዩኒቨርሲቲ መምልራን አንድ መረጃ ሲለቀቅ የሃይስኩል/ የፕሪፓራቶሪ መምህራን (ሁሉም ማለቴ አይደለም) ይመጡና የዩኒቨርሲቲ መምህር ደግሞ በppt እያስተማረ ገለመሌ ይላሉ።

እንዲህ የሚያደርጉት ብዙ ጊዜ ነው እኔም አይቼ አልፍ ነበር አሁን አሁን እየበዛ ስለሆነ ማስጠንቀቁ ልክ ነው።

የዩኒቨርሲቲ አስተማሪ ከ30 በላይ የተለያዩ ኮርሶችን እንዲያስተምር ይደረጋል። ለዚህ ደግሞ ቴክኖሎጂ (ፕሮጀክትር እና የመሳሰሉትን ) ይጠቀማል።

በቾክ እየፃፉ ማስተማር እየቀረ ነው ። ባይሆን በማርከር መፃፍ ይመረጣል።

ሲጠቃለል እንዲህ አይነት ኮሜንት የሚፅፍ ሰው ብሎክ የሚባል ቅጣት ይጠብቀዋል እና ይጠንቁቅ።

@Ethiopian_Digital_Library


Видео недоступно для предпросмотра
Смотреть в Telegram
የዩኒቨርሲቲ መምህር ነኝ ደሞዜ 99 ዶላር ነው:: ይህ ደሞዝ ዝቅተኛ ብቻ ሳይሆን ኢምሞራላዊም ነው! መምህራን ለልጆቻቸው መሆን አልቻሉም! ኢምሞራላይዝድ የሆነ መምህር ይዘህ ነገ በአለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ የሆኑ ተማሪዎችን ያፈራሉ ብሎ መጠበቅ ሞኝነት ነው::

@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library

10.9k 0 25 15 131



ዩቲዩብ ላይ ብዙ ብር የሚከፈላችሁ ምን አይነት ቪድዮ ስትሰሩ ነው?

https://www.youtube.com/watch?v=Cl-Ho0irwUs

@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library


“በዱቤ ወደ ውጭ ሀገር እንልካለን” በሚል በተለያዩ ታዋቂ ሰዎች፣ አርቲስቶች እና ቲክቶከሮች ማስታወቂያ የተታለሉት

በኢትዮጵያ በርካታ ተቋማት ሕጋዊ ፈቃድ ወስደው ወደ ተለያዩ ሀገራት የሥራ ስምሪት ላይ እየሠሩ ይገኛሉ። በዚያው ልክ ግን “ዜጎችን ወደ ውጭ እንልካለን” በሚል ስም ገንዘብ ሰብስበው አድራሻ የሚቀይሩ እንዳሉ በተደጋጋሚ የሚሰማ ጉዳይ ነው።

ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ደግሞ “ወደ ውጭ ሀገራት እንልካለን በሚሉ ተቋማት ተጭበርብረናል” የሚሉ ሰዎች በማኅበራዊ ሚዲያ አማራጮች ቅሬታዎቻቸውን እያሰሙ ይገኛሉ።
ወጣት ተመስገን ሰለሞን ከእነዚህ ሰዎች መካከል አንዱ ሲሆን “AIM ULTRA CONSULTANCY” በተባለ ድርጅት ደርሶብኛል ስላለው በደል ለኢቢሲ ዶትስትሪም በዝርዝር ተናግሯል።

እሱ እንደሚለው “በዱቤ ወደ ውጭ ሀገር እንልካለን” በሚል በተለያዩ ታዋቂ ሰዎች፣ አርቲስቶች እና ቲክቶከሮች የሚነገረውን የድርጅቱን ማስታወቂያ በመመልከት ሂደቱን ጀመረ።
ሂደቱን በሚጀመርበት ጊዜም ‘በዱቤ’ በሚል የተዋወቀው ነገር ቀርቶ ‘ለተለያየ ሥራ ማስኬጃ’ በሚል ክፍያዎችን ተጠይቆ ከፍሏል። በዚህ ድርጅት እሱን ጨምሮ ከ56 ሺህ እስከ 700 ሺህ ብር የተጭበረበሩ ሰዎች እንዳሉ ነግሮናል።

የድርጅቱ ባለቤት “ቤተልሔም ታደሰ” እንደምትባል እና “ጉዳያችሁን አስጨርስላችኋለው፤ በእኔ ላይ ጣሉት” በማለት በተደጋጋሚ የኤምባሲ እና ተያያዥ ክፍያዎችን እንዳስከፈለቻቸው፣ እሱም መተዳደሪያው የነበረችውን ባጃጅ ሽጦ እና የቤተሰቡን መሬት አስይዞ በመበደር የተጠየቀውን ቀሪ ክፍያ መፈጸሙን ነው የነገረን።

Credit: EBC

@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library


ሰሙነ ሕማማት እና የቀናት ስያሜዎች

የዐብይ ጾም የመጨረሻው ሳምንት ከሰኞ እስከ ቅዳሜ ያሉት ቀናት ሰሙነ ሕማማት ይባላሉ። በነዚህ ቀናት የኢየሱስ ክርስቶስ ሕማም የሚታሰብ ሲሆን፤ ካህናትና ምእመናን በቤተክርስቲያን ቅጥር ግቢ ተሰብስበው የሕማሙን ነገር የሚያወሳውን ዜማ በማዜም ቀኑን ሙሉ በስግደትና በጸሎት ያሳልፋሉ።

ካህናተ ቤተክርስቲያን ጥቁር ልብስ ይለብሳሉ፤ ምክንያቱም ጌታችን የደረሰበትን መከራና ስቃይ እንዲሁም የሰው ልጅ አምስት ሺህ 500 ዘመን በጨለማ ግዞት ይኖር እንደነበር ለማዘከርም ጭምር ነው። በዚህ ሳምንት ከክርስቶስ ልደት በኋላ የመጡት የድኅነት ምልክቶች አይደረጉም። ከሰኞ እስከ ትንሳኤ ዋዜማ ያሉት ስድስቱ የሰሙነ ሕማማት ዕለታትም ትርጉም ተሰጥቷቸው ይታሰባሉ፡፡

☄️ ሰኞ:- ርግመተ በለስ እና አንጽሖተ ቤተመቅደስ ትባላለች።

በዚህ ዕለት ኢየሱስ ክርስቶስ ከቢታኒያ ሲወጣ ተራበ። ቅጠል ያለባትን በለስ ተመልክቶ ወደ በለሲቱ ቢቀርብ ከቅጠል በቀር ምንም ነገር ባለማግኘቱ “ከአሁን ጀምሮ ለዘላለም ምንም ካንቺ ፍሬ አይበላ” በማለት ስለረገማት መርገመ በለስ የተፈጸመበት ሰኞ ይባላል። ጌታ ወደ ቤተመቅደስ ሄዶ በቤተመቅደሱ የሚሸጡትን እና የሚለውጡትን “ቤቴ የጸሎት ቤት ትባላለች” በማለት ከቤተመቅደስ ገርፎ ያስወጣበት ዕለት ነው።

☄️ ማክሰኞ:- የጥያቄና የትምህርት ቀን ትባላለች።

ሰኞ ዕለት በቤተመቅደስ ሲሸጡ እና ሲለውጡ የነበሩትን ሁሉ እየገረፈ በማባረሩ ምክንያት ለሰው ልጅ ሹመትንና ስልጣንን የሰጠ ጌታ በምን ስልጣን ይህንን ታደርጋለህ? ተብሎ በፈሪሳውያን ተጠይቋልና የጥያቄ ቀን ይባላል። በዕለተ ማክሰኞ በቤተመቅደስ ረጅም ትምህርት ስላስተማረ የትምህርት ቀንም ትባላለች።

☄️ ረቡዕ፡- ምክረ አይሁድ፣ የመልካም መዓዛ እና የእንባ ቀን ይባላል። ረቡዕ እለት የአይሁድ ሊቃነ ካህናትና ጸሐፍት ጌታን እንዴት መያዝ እንዳለባቸው የመከሩበትና ውሳኔ ያሳለፉበት ቀን በመሆኑ ምክረ አይሁድ ይባላል።

የመልካም መዓዛ ቀንም መባሉ ደግሞ በለምጻሙ በሰምዖን ቤት ተቀምጦ ሳለ መላ ሕይወቷን ለዝሙት አስገዝታ ትኖር የነበረችው ማርያም እንተ እፍረት (ባለሽቶዋ ማርያም) ዋጋው እጅግ ውድ የሆነ የአልባጥሮስ ሽቱ አምጥታ በራሱ ላይ በማርከፍከፍ ስለቀባቸው ነው።
ባለሽቱዋ ሴት (ማርያም እንተ እፍረት) ኃጢአቷን ይቅር እንዲላት እየለመነች በእግሩ ስር ተደፍታ በእንባዋ እግሩን አርሳለችና ማየእንባ ቀን ይባላል።

☄️ ሐሙስ:- ፀሎተ ሐሙስ፣ ህጽበተ ሀሙስ፣ የምስጢር ቀን፣ የሐዲስ ኪዳን ሐሙስ እና የነጻነት ሐሙስ ይባላል።

ፀሎተ ሐሙስ ጌታ ለአይሁድ ተላልፎ ከመሰጠቱ በፊት በጌቴሴማኒ የአትክልት ስፍራ ሲጸልይ በማደሩ ጸሎተ ሐሙስ ይባላል። ጌታችን የደቀመዛሙርቱን እግር በፍጹም ትህትና ዝቅ ብሎ ያጠበበት ዕለት በመሆኑም ሕጽበተ ሐሙስ ይባላል። የምስጢር ቀን ይባላል፡- ከሰባቱ ምስጢራት አንዱ የቅዱስ ቁርባን ምስጢር በዚህ ዕለት ተፈጽሟልና የምስጢር ቀን ይባላል። የሐዲስ ኪዳን ሐሙስ ይባላል፡- መሥዋዕተ ኦሪት /በእንስሳት ደም የሚቀርብ መሥዋዕት/ቀርቶ ለአለም ድኅነት ራሱን ያቀረበበት ቀን በመሆኑ የሐዲስ ኪዳን ሐሙስ ይባላል። የነጻነት ሐሙስ ይባላል፡- ለኃጢአትና ለዲያቢሎስ ባሪያ ሆኖ መኖር ማብቃቱን እንዲሁም የሰው ልጅ ያጣውን ክብር መልሶ ማግኘቱ የተረጋገጠበት ቀን ስለሆነም የነጻነት ሐሙስ ይባላል።

☄️ ዓርብ:- የስቅለት ዓርብ እና መልካሙ ዓርብ ይባላል።

ኢየሱስ ክርስቶስ ለአዳምና ለልጆቹ ሁሉ ቤዛ ሆኖ በመልዕልተ መስቀል ላይ ተሰቅሎ የዋለበት ዕለት ነውና የስቅለት ዓርብ ይባላል። ከጌታ ስቅለት በፊት በተለይም በሮማውያን ህግ የወንጀለኛ መቅጫ ምልክት የነበረውን መስቀል ጌታ በደሙ ቀድሶ የምህረት፣ የሕይወት አርማ፣ የዲያቢሎስ ድል መንሻ ስላደረገው፤ በሞቱ መልካሙን ሕይወት ስላገኘን መልካሙ ዓርብ ይባላል።

☄️ ቅዳሜ:- ቅዳም ስዑር፣ ለምለም ቅዳሜ እና ቅዱስ ትባላለች።

ይህች እለት ከድሮ በተለየ መልኩ የጌታችንን መከራ በማሰብ በጾም ታስባ ስለምትውል የተሻረች ቅዳሜ ትባላላች። ካህናቱ ለምእመናን ለምለም ቀጤማ የሚያድሉበት ዕለት በመሆኑም ለምለም ቅዳሜ ይባላል። ምዕመናንም ይህንን ለምለም ቀጤማ እስከ ትንሣኤ ሌሊት በራሳቸው ላይ ያስሩታል። ቅዱስ የሆነው እግዚአብሔር በጥንተ ተፈጥሮ ፍጥረታትን አከናውኖ ያረፈበት ቀን ሲሆን፤ በዘመነ ሐዲስ ደግሞ የማዳን ስራውን ሁሉ ፈጽሞ በሥጋው በመቃብር ሲያርፍ በነፍሱ ወደ ሲዖል ወርዶ ሲኦልን በርብሮ ባዶዋን ሲያስቀራት በዚያ የነበሩትን ነፍሳት የዘላለም ዕረፍትን ያወረሰበት ዕለት ስለሆነ ቅዱስ ቅዳሜ ይባላል።

Credit: GazettePlus

@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library

8.7k 0 91 1 101



Репост из: Digital Lottery Ethiopia
በኢትዮጵያ የመጀመሪያው ዲጂታል ሎተሪ ይፋ ሆነ

በገበያ ላይ ካሉት የወረቀት ሎተሪዎች በተጨማሪ በዲጂታል መልክ በተለያዩ ቋንቋዎች የተዘጋጀው የመጀመሪያው ዲጂታል ሎተሪ ይፋ ሆነ፡፡

የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ፣ የኢትዮጵያ ሎተሪ አገልግሎትና የታምኮን ሶፍትዌር ሶሉሽን የሥራ ኃላፊዎች ዲጂታል ሎተሪውን በይፋ አስጀምረዋል፡፡

ገበያ ላይ ካሉ የወረቀት ሎተሪዎች በተጨማሪ በድረገጽ፣ በሞባይል አፕሊኬሽንና በኤስ ኤም ኤስ አማካኝነት ሕብረተሰቡ ዕድሉን በመሞከር የሚሸለምበት መሆኑን የኢትዮጵያ ሎተሪ አገልግሎት ዋና ሥራ አስፈጻሚ ቤዛ ግርማ ገልጸዋል፡፡

የዲጂታል ሎተሪው ለወጣቶች የሥራ ዕድልና ለሀገር ውስጥ የቴክኖሎጂ ኩባንያዎች እድገት ምቹ ሁኔታን በመፍጠር ረገድ አዎንታዊ ሚና እንዳለው የታምኮን ሶፍት ዌር ሶልሸንስ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ሰለሞን ከበረ አስታውቀዋል።

ኤፍ ኤም ሲ

@digital_lottery_ethiopia


ዘንድሮ 150,000 ተማሪዎች 12ኛ ክፍል በኦላይን (online) ይፈተናሉ :: የፈተናው ጊዜ አንድ ወር ተኩል አካባቢ ይቀረዋል:: 84,000 መምህራን በክረምት ስልጠና ይወስዳሉ::

Prof. Birhanu Nega

@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library


🚨 Exciting News from Bahir Dar University! 🚨

BDU is proud to announce Bahir Dar University, Ethiopia, is now an #ETS Certified Test Administrator (CTAS) for the #TOEFL iBT®! 🎉📚

🌍 As an official TOEFL iBT® test center, we’re here to empower your global ambitions! Whether you’re aiming for higher education, career advancement, or scholarships, the TOEFL iBT®—the world’s most recognized English proficiency test—opens doors to 13,000+ institutions worldwide.

Why take the TOEFL iBT® at BDU?
✅ Globally trusted for academic, professional, and visa purposes
✅ Flexible testing options tailored to your schedule
✅ State-of-the-art facilities at our #TOEFL Center, Peda Campus

📢 Online registration opens soon!
Stay tuned for details on securing your seat and joining thousands who’ve achieved their dreams with TOEFL iBT®.

📌 Get in touch:
📞 +251 911 816 361
📧 toefl.center@bdu.edu.et
📍 TOEFL Center, Peda Campus, Bahir Dar University, Ethiopia

#TOEFL #BahirDarUniversity #FacultyofHumanities #EnglishTest #ETS #HigherEducation




ኢትዮጵያውያን ተማሪዎች በቻይና የሁዋዌ ቴክፎርጉድ ግሎባል ውድድርን አንደኛ በመሆን አሸነፉ

የኢትዮጵያ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የሁዋዌ ሲድስ ፎር ዘ ፊውቸር ቴክ ፎር ጉድ ግሎባል ውድድርን አንደኛ በመሆን አሸንፈዋል።
ውድድሩ ከመጋቢት 29 እስከ ሚያዝያ 9 ቀን 2017 ዓ.ም በሚቆየውና በቻይና ቤጂንግ እና ሼንዘን የሚገኙ የቴክኖሎጂ ማዕከሎችን ጉብኝትና የተግባር ስልጠናዎችን ካካተተው ዝግጅት ጋር የተካሄደ ሲሆን ውጤቱ ይፋ የተደረገው ሚያዝያ 3 ቀን 2017 ዓ.ም ነው።

በስድስት ተማሪዎች የተወከለው የኢትዮጵያ ቡድን ተማሪዎቹን ከአዲስ አበባ፣ ሃራማያ፣ ጅማ፣ ወልቂጤ እና አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርስቲዎች አሰባስቧል። በውድድሩም ከሞሮኮ፣ ደቡብ አፍሪካ፤ አርጀንቲና አየርላንድ፣ ማላዊ፣ ቬትናም፣ አረብ ኤምሬትስ እና ሌሎችንም ጨምሮ ከዓለም ዙሪያ ከተውጣጡ 12 ልዩ ቡድኖች ጋር ተወዳድሯል። የሲድስ ፎር ዘ ፊውቸር ግሎባል አምባሳደር የሆነችው ኢትዮጵያዊቷ ተማሪ አሲያ ከሊፋም በዝግጅቱ በእንግድነት ተገኝታለች።

ተማሪዎቹ የእንስሳትን ህመሞች አስቀድሞ ለመለየት በተዘጋጀውና በአርተፊሻል አስተውሎት በጎለበተው ኤርሊ ቬት (EarlyVet) በተሰኘው ፕሮጀክታቸው የተወዳደሩ ሲሆን በዚህም ትኩረት ለመሳብ ችለዋል።
ይህ የፈጠራ ፕሮጀክት ከተባበሩት መንግስታት የዘላቂ ልማት ግቦች (SDGs) በተለይም ግብ 2 "ዜሮ ርሃብ" እና ግብ 15 "ህይወት በምድር" ከሚለው ጋር የተጣጣመ መሆኑና በግብርና እና በእንስሳት ጤና ላይ ያሉ ወሳኝ ተግዳሮቶችን ይፈታል ተብሎ እንደሚታመን በውድድሩ ተብራርቷል።

የሁዋዌ ኢትዮጵያ የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር ሚስተር ሊሚንግ ዬ በቡድኑ ስኬት የተሰማቸውን ደስታ ገልጸው ድሉ የኢትዮጵያውያን ወጣቶች ልዩ ችሎታ እና ፈጠራ የታየበት ነው ብለዋል። አክለውም መጪው ትውልድ ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ በመጣው የቴክኖሎጂ ገጽታ ውስጥ እንዲበለጽግ በሚያስፈልገውን ድጋፍ እና እድሎች ማመቻቸቱን ለማስቀጠል ሁዋዌ ቁርጠኛ መሆኑን ገልጸዋል።

ቡድኑ ለዓለም አቀፋዊ ውድድር እድል ያገኘው በግንቦት 2016 ዓ.ም በኤሳውራ ሞሮኮ በተካሄደው የክፍለ አህጉራዊ የቴክፎርጉድ (Tech4Good) ውድድር ወቅት ከ17 የአፍሪካ ሀገራት ከተውጣጡ 28 ቡድኖች ጋር ተወዳድሮ አንደኛ በወጣበት ወቅት መሆኑ ይታወሳል፡፡

በዓለም አቀፍ ደረጃ እ.ኤ.አ. በ2008 የተጀመረው የሁዋዌ ሲድስ ፎር ዘ ፊውቸር ፕሮግራም በአገር ውስጥ ያለውን ውድድር ከኢትዮጵያ ትምህርት ሚኒስቴር ጋር በመተባበር የሚያዘጋጅ ሲሆን ለተሳታፊ ተማሪዎች ከውድድር ባለፈ የሰዉ ሰራሽ አስተዉሎት (AI)፣ ክላዉድ ኮምፒዉቲንግ፣5ኛ ትውልድ: ሳይበር ደህንነት፣ አይኦቲ እና ቢግ ዳታን ጨምሮ በቴክኖሎጂዎች ላይ አጠቃላይ ስልጠና የሚወስዱበት እድል ያመቻቻል።

#MoE

@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library


በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ተቀጥረው የሚሰሩ የአንዳንድ የህንድ ዜጎች ፎርጅድ ዶክመንት ሲዳሰስ
"ቅጥር ለማግኘት ለዩኒቨርስቲው ሰራተኞች የሁለት ወር ደሞዝ የሚሰጡ አሉ"


የአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ተቀጥረው የሚሰሩ አንዳንድ የህንድ ዜግነት ያላቸው አስተማሪዎች ሀሰተኛ የትምህርት ማስረጃ እንዳላቸው እና ይህ እንዳይታወቅ ከአንዳንድ የዩኒቨርስቲው አመራሮች ጋር እንደሚሰሩ መረጃዎች እየወጡ ይገኛሉ።

መሠረት ሚድያ የተመለከታቸው እና በአንዳንድ የህንድ አስተማሪዎች ጭምር እውነትነታቸው የተረጋገጠ እነዚህ መረጃዎች እንደሚጠቁሙት በወር በሺዎች የሚቆጠር ዶላር የሚከፈላቸው አንዳንድ ህንዳውያን የትምህርት ማስረጃቸው ወይ ሀሰተኛ ነው ወይም ያልተማሩትን የዶክትሬት ዲግሪ እንደተማሩ ሀሰተኛ ማስረጃ አቅርበው ተቀጥረዋል።

"አንዳንዶቹ የክህሎት እና የትምህርት ማረጋገጫ ሂደትን ግልፅ ባልሆነ መልኩ አልፈው ተቀጥረው ይገኛሉ፣ ይህ ደግሞ እየተደረገው በዩኒቨርስቲው ጥቂት አመራሮች ተሳትፎ ጭምር ነው" የሚሉት የአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ የቀድሞ መምህር የነበሩት ዶ/ር ሱረሽ ኩማር ናቸው።

አንዳንድ ህንዳውያን ግዜያቸውን እና ሙያቸውን በመጠቀም ለውጥ ለማምጣት ጥረት እያረጉ ቢሆንም እነዚህ ሀሰተኛ ዶክመንቶችን ይዘው እየመጡ የሚቀጠሩ ህንዳውያን ችግር እየሆኑ እንደመጡ ዶ/ር ሱረሽ ያስረዳሉ።
"ሀሰተኛ ዶክመንት ይዘው የሚመጡ እነዚህ ግለሰቦች የኢትዮጵያን የትምህርት ስርዐት እየገደሉት ነው" የሚሉት ዶ/ር ሱረሽ የእነዚህን ህንዳውያን ስም በዝርዝር ያቀረቡበትን ዶክመንት መሠረት ሚድያ ተመልክቷል።

አንዳንዶቹ ህንዳውያን ህገወጥ ዶክመንታቸውን ይዘው መጥተው ቅጥር ለማግኘት ለዩኒቨርስቲው ሰራተኞች የሁለት ወር ደሞዝ እንደሚሰጡ ታውቋል።
ከእነዚህ ህንዳውያን መሀል እስከ 14 አመት በኢትዮጵያ ያስተማሩ እንደሚገኙ የተጠቀሰ ሲሆን በዚህ ዙርያ የተሰጠ ማብራርያ የለም።

"አንዳንዶቹ ይባስ ብሎ ከሁለት ዩኒቨርስቲ ደሞዝ ይቀበላሉ፣ አንዳንዶቹ የስራ ፈቃድ የላቸውም ወይም ፈቃዳቸው ተቃጥሏል፣ ይህ ጉዳይ በአስቸኳይ ተጣርቶ እርምት ካልተደረገበት በሀገር ሀብት እና በተማሪዎች ትምህርት መቀለድ ነው" ያሉት ስማቸው እንዲጠቀስ ያልፈለጉ አንድ የዩኒቨርስቲው ኢትዮጵያዊ መምህር ናቸው።
ከዩኒቨርስቲው ምላሽ ካገኘን ይዘን እንመለሳለን።

መሠረት ሚድያ

@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library


የመቃብር ሪል እስቴት (Memorial Estate) - ኢንጅነር ደሳለኝ ከበደ

ከሪል እስቴት ቢዝነሶች ውስጥ አንዱ የመቃብር ሪል እስቴት (Memorial Estate ) ይገኝበታል። በእኛ ሀገር ያለ ነገር ግን እንደ ቢዝነስ እንዳይሆን ከምመኘው አንዱ የሪል እስቴት አይነት ነው።

የዚህ የሪል እስቴት ዘርፍ ተዋንያን የሚከተሉትን ስራዎችን ማከናወን የንግድ ስራቸውን ያከናውናሉ:-
፩) የራሳቸው ለቀብር ስራ ማከናወኛ መሬት ገዝተው ሸንሽነው በአጸድና የውስጥ መንገዶች አስውበው የቀብር ቦታዎችን ያከራያሉ ይሸጣሉ ...ያስተዳድራሉ።
፪) የተለያዩ የመታሰቢያ ሃውልቶችን ዲዛይን ሰርተው ገንብተው ይሸጣሉ በትዕዛዝም ይሰራሉ
፫) የተለያዩ የጋራ መቃብር ህንጻዎችን (ፉካ ያለባቸው) ይገነባሉ ያከራያሉ የቀብር ስርዓት ያስፈጽማሉ ቦታውን ያስተዳድራሉ።
፬) ከቀብር ቦታዎች ውጪ ለተለያዩ ታላላቅ ሰዎችና የሀገር ባለውለታዎችን መታሰቢያ የሚሰሩ መታሰቢያ መናፈሻ ቦታዎችንና ሀውልቶችን (Memorial Parks ) ይገነባሉ ያስተዳድራሉ

በንጽጽር በሀገራችን የመቃብር ስፍራዎች (የዘላቂ ማረፊያ) የአስተዳደር ሲስተም በጣም ጥሩ የሚባልና የህብረተሰቡን ሀይማኖታዊ እሴቶችን አስጠብቆ የቀጠለ ነው ማለት ይቻላል። የውጮቹ ዓላማው ዘላቂ ማስታወሻ ማስቀመጥ ሲሆን የእኛ ዘላቂ ማረፊያ ነው ።

ይህ በእንዲህ እንዳለ ሰሞኑን በወጡ መረጃዎች ለቀብር የሚሆን ፉካ ክፍያ በአንዳንድ ቦታዎች ለሰባት ዓመታት 170 ሺህ ብር አካባቢ እንደ ደረሰ ሰምቼ የፈራሁት ነገር መድረሱን ተረዳሁ። ይህ የሚሆነው በመንግስት በሚተዳደሩ የዘለቄታዊ ማረፊያ ቦታዎች ሳይሆን በእምነት ተቋማት የሚተዳደሩ የመቃብር ስፍራዎች መሆኑ ገራሚ ነው 🙁 ። ያም ዘላቂ ሳይሆን ለኪራይ 🙁

በዚህ ከቀጠሉ ያላቸው ቦታ እያለቀ መሄዱን ተከትሎ ተኝተን ሳይሆን በቁም እንደችካል ሊቀብሩን ሁሉ መሞከራቸው የሚቀር አይመስለኝም። በመደበኛው አቀባበር በአማካኝ 1x2ሜ አካባቢ ማለትም 2 ካሬሜ ሲያስፈልግ በቁም መቃብሮች 0.6x0.3ሜ 0.18ካሬሜ በቂ ነው። እነዚህ የመቃብር ሪል እስቴት ቢዝነስ አከናዋኝ እየሆኑ የመጡት የእምነት ተቋማት ይህንንም አያደርጉትም ተብሎ አይታሰብምና ከወዲሁ መልክ ቢይዙ መልካም ነው።

አላማቸው ሰው ኑሮ ተወደዱብኝ ብሎ መሞት የማያዋጣ መሆኑን ለማሳየት ከሆነ ደግ ነው። ለማንኛውም ወገኔ መሞት የማያዋጣበት ጊዜ ላይ እየደረሰን ይመስላል 🙂 ጤናችንን እየጠበቅን ከሚመጣብን ከፍተኛ ድንገተኛ ወጪ ራሳችንና ቤተሰባችንን እድራችንንም እንጠብቅ 🙂
ከእምነት ተቋማት ውጭ ለሆኑ ለዘላቂ መታሰቢያ መናፈሻ ቦታዎች ግን የግል የ Memorial Estates ቢኖሩን ሸጋ ነው።

@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library


የሚመለከታችሁ ሁሉ

መረጃውን ለማግኝት ይህንን ሊንክ ይጫኑ

https://forms.gle/N8uPaW7uXYTEZWQC8

@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library


የውጭ አገር የትምህርት ዕድል ያገኘውን ጓደኛውን በመርዝ ገደለ

በአዲስ አበባ ዩንቨርስቲ የዘንድሮ ተመራቂ የነበረው ውብሸት አስቤ ከአሜሪካ ፊሊድያ ዩንቨርስቲ ነፃ የትምህርት እድል አግኝቶ ለጉዞ እየተዘጋጀ ባለበት የቅርብ ጓደኛው ዶርም ውስጥ #በመርዝ እንደተገደለ የአስክሬን ውጤቱ ያሳያል።

ወጣት ውብሸት እጅግ በጣም ትሁትና ታታሪ መሆኑን ብዙዎች ይመሰክራሉ። ይሁን እንጂ በጉብዝናውና በመልካም እድሎቹ ላይ በመቅናት እጅግ በሚከረፋ መርዝ ህይወቱን ነጠቁት።

በአረብ ሀገር እየለፋች ያስተማረችው እህቱ በወንድሟ ፅኑ ተስፋ የነበራት ቢሆንም በምቀኝነትና በክፋት ተነሳስተው የወንድሟን ነፍስ ፣ ህልሙንና ተስፋውን በማጨናገፋቸው ከመሞት ያልተናነሰ ተስፉ መቁረጥ ውስጥ ትገኛለች። እጅግ ከባድ የመንፈስ ስብራት ደርሶባታል።

በጣም የሚያሳዝነው ደግሞ ይህንን ከባድ ወንጀል የፈፀመው ተጠርጣሪ ጓደኛው የህግ ጠበቃ ይዘው የተከራከሩ ሲሆን በሟች ቤተሰብ በኩል "ቸልተኛ" አቃቤ ህግ ብቻ በመሆኑ #ገዳይ ከእስር ሊፈታ ጫፍ ደርሷል።

የሟች ቤተሰብ ተስፋና ማረፊያቸው የነበረውን ወጣት ልጃቸውን መነጠቃቸው ሳይበቃ ጭራሽ የልጃቸው ገዳይ በነፃ መፈታቱ የእግር እሳት የሆነ ህመምና ለልጃቸውም ሁለተኛ ሞት ነው።

Sentayehu Hailu

@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library

Показано 20 последних публикаций.