እውን መረጃ


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: Музыка


📌#ቀዳሚ_ምርጫዎ ➠ ፈጣን እና ተዐማኒ መረጃ ➠ወቅታዊ መረጃዎች ➠ልዩ ልዩ ዘገባዎች የምታገኙበት ቻናል
📌ጥቆማ ለመስጠት እና Cross
👉 @Ewenmereja_bot
#እውነተኛ እና #ትኩስ #መረጃዎች
#እውንነት

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
Музыка
Статистика
Фильтр публикаций


የእስራኤል አየር ኃይል በደቡባዊ ሊባኖስ ሻኪፋ አቅራቢያ በምትገኘው የአርኖን ከተማ የተለያዩ አካባቢዎች ጭካኔ የተሞላበት የአየር ጥቃት መፈፀሙን ሪፖርቶች አመላከቱ

@Ewun_Mereja1
@Ewun_Mereja1


አስገራሚ ዜና

ይህ ዜና የሚለው ኔዘርላንድ ወስጥ በ1987 የባዮሎጂ የመውጫ ፈተና የተፈተኑ ተማሪዎች በድጋሜ እንዲፈተኑ ሊጠሩ ነው ነው። የተሰጠው ምክንያት ደግሞ የባዮሎጂ ፈተና መሰረቁ ተረጋግጧል  የሚል ነው።  ይህ እንግዲህ የተረጋገጠው ከ38 ዓመት በኋላ ነው።  የያኔዎቹ ተማሪዎች ዛሬ እድሜያቸው 55 ደርሷል ።

ባለስልጣኑ ለሁሉም ጥሪ እንደሚደረግና ፈተናውን በድጋሜ እንደሚወስዱ ገልፀው ፣ ካልወሰዱ ግን ዲፕሎማቸው ሙሉ እንደማይሆን አስጠንቀቀዋል ።

ከ38 ዓመት በኋላ በድጋሜ ተፈተኑ ብትባሉ ምን ትላላችሁ?

@Ewun_Mereja1
@Ewun_Mereja1


ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች እንኳን ለትንሳኤ በዓል በሰላም አደረሳችሁ!

መልካም በዓል ይሁንላችሁ፣ ይሁንልን።

@Ewun_Mereja1
@Ewun_Mereja1


በፑቲን የታወጀው የትንሣኤ ተኩስ አቁም ተግባራዊ ሆነ

የሩሲያ መከላከያ ሚኒስቴር ኪዬቭ የተኩስ አቁሙን የምታከብር ከሆነ የሩሲያ ወታደሮችም ተግባራዊ ያደርጉታል ብሏል።

የተኩስ አቁሙ በልዩ ወታደራዊ ዘመቻው  ከረዥም ጊዜ በኋላ የታወጀ የመጀመሪያው የተሟላ የተኩስ አቁም ነው።

በመጋቢት ወር ለ30 ቀናት የኃይል መሠረተ ልማት የተኩስ አቁም ቢደረስም ዩክሬን ስምምነቱን እንደጣሰች የሩሲያ መከላከያ ሚኒስቴር በተደጋጋሚ ማስታወቁ የሚታወስ ነው።

@Ewun_Mereja1
@Ewun_Mereja1


የብር የመግዛት አቅም መዳከም የዘንድሮውን ፋሲካ ለሸማቾች ፈታኝ እንዳደረገው ገለፁ

የዘንድሮ 2017 ዓ.ም. የፋሲካ በዓል በሸማቾች ዘንድ ከፍተኛ ፍላጎት ያላቸው እንደ ዶሮ እና በሬ ያሉ የእንስሳት ምርቶች ዋጋ በከፍተኛ ሁኔታ መጨመሩ የብር የመግዛት አቅም ማሽቆልቆል ጋር ተዳምሮ በበዓሉ ወጪ ላይ ከፍተኛ ጫና መፍጠሩን ተናግረዋል።

በተለይም ባለፈው ዓመት በዚሁ ወቅት በአማካኝ እስከ 1300 ብር ይሸጥ የነበረው ዶሮ በዚህ ዓመት ዋጋው በእጥፍ ጨምሮ እስከ 2500 ብር እየተሸጠ ይገኛል ይህም 92 በመቶ አከባቢ ጭማሪ ተደርጎበታል።

የዘርፉ ነጋዴዎች ለዚህ ከፍተኛ የዋጋ ጭማሪ ምክንያት የሆነው ለዶሮ እርባታ የሚውለው የመኖ ዋጋ በከፍተኛ ሁኔታ መጨመሩ እንደሆነ ይገልጻሉ።

በተመሳሳይ የእንቁላል ዋጋም በከፍተኛ ሁኔታ በመናር አንድ እንቁላል ከ 20 ብር እስከ 25 እየተሸጠ መታየቱ የብዙዎችን ስጋት ጨምሯል።

የእርድ ከብት (በሬ) ዋጋም ከዶሮው ባልተናነሰ መልኩ የዋጋ ጭማሪ አሳይቷል። ባለፈው 2016 ዓ.ም የፋሲካ በዓል ወቅት በአማካኝ እስከ 60 ሺህ ብር ይሸጥ የነበረ አንድ በሬ በዚህ ዓመት ዋጋው ከ 80 ሺህ እስከ 90 ሺህ ብር እየተሸጠ ይገኛል።

ይህ ሁኔታ የብር የመግዛት አቅም ከኑሮ ውድነቱ ጋር ተዳምሮ በበዓሉ ወጪ ላይ ከፍተኛ ተፅዕኖ ማሳደሩን ሸማቾች ለካፒታል ተናግረዋል።

@Ewun_Mereja1
@Ewun_Mereja1


ፖሊስ የአዲስ ስታንዳርድ ጋዜጠኞችን ለእስር መዳረጉን እና የኤሌክትሮኒክስ ንብረቶችን መውሰዱን በተመለከተ የተሰጠ መግለጫ

በእስር ላይ የነበሩ የተቋማችን ሰራተኞች ምሽት ላይ ከተለቀቁ በኋላ ንብረቶቻችሁ ከማክሰኞ ሚያዚያ 14 ቀን 2017 ዓ.ም በኋላ ሊመለሱላችሁ ይችሉ ይሆናል ተብለናል።

ተቋማችን አዲስ ስታንዳርድ ሚዲያ በግልጽ ለህዝብ ማሳወቅ የሚፈልገው የተቋማችን ዋነኛ የዲጂታል መገልገያችን (main digital credentials) ምንም አይነት ጥቃት እንዳይደርስበት በአስተማማኝ ሁኔታ እንዲገኝ ያደረግን መሆኑን ነው።

ነገር ግን ከዚህ ውጭ ፖሊስ ባካሄደው ብርበራ በግዳጅ ከተወሰዱብን የኤሌክተሮኒክስ እቃዎች በተለይም ከስልኮቹ እና ኮምፒዩተሮቹ በተናጠል የሚላኩ ማናቸውም መልዕክቶች፣ ኢሜይሎች እንዲሁም ግንኙነቶች ተቋማችንን እንዲሁም ሰራተኞቻችንን የማይወክሉ መሆናቸውን ነው።

በተቋማችን ላይ ፖሊስ ብርበራ ካካሄደ በኋላ ባሉት ጊዜያት እነዚህ ኮምፒዩተሮች እና ስልኮች የሚገኙት በጸጥታ ሀይሎቹ እጅ ሲሆን በእነዚህ ኮምፒዩተሮች እና ስልኮች ምን እየተከናወነባቸው እንደሆነ የተረጋገጠ ነገር መግለጽ አንችልም።

ሆን ተብሎ በፋሲካ ዋዜማ እንዲህ አይነት ድርጊት በተቋማችን ላይ የተፈጸመው አፋጣኝ ምላሽ እንዳንሰጥ እና ሰራተኞቻችን ግራ እንዲጋቡ ለማድረግ መሆኑን መረዳት አያዳገትም።

በዚህ አጋጣሚ ህጋዊ እና ሰላማዊ የሆነ አካሄድን አሟጦ በመጠቀም የሰራተኞቻችን ደህንነት እና የኤሌክተሮኒክስ ንብረቶቻችንን ያለምንም ጥቃት መመለስ ለማረጋገጥ እንደምንሰራ ለማሳወቅ እንወዳለን።

በዚህ ፈታኝ ጊዜ የሚዲያ ተቋማችን ወዳጆች ሁኔታዎቹን እንድትረዱልን እያሳሰብን፣ ቀጣይነት ላለው ድጋፋችሁ ምስጋናችንን እናቀርባለን።

በየጊዜው የሚኖሩ ሁኔታዎችን እየተከታተልን እንደምናሳውቅ እንገልጻለን።


"ከሩሲያ እና ዩክሬን ድርድር ልንወጣ እንችላለን" አሜሪካ

በሩሲያ እና ዩክሬን እየተደረገ ያለው የሰላም ድርድር ለውጥ የማያመጣ ከሆነ አሜሪካ ከድርድሩ ልትወጣ እንደምትችል የአሜሪካው ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርክ ሩቢዮ ተናገሩ ፡፡

ማርክ ሩቢዮ ዋሽንግተን የሚጠበቅባትን አድርጋለች ከዚህ በኋላ ጦርነቱ የእኛ አይደለም (it’s not our war) ብለዋል፡፡

ሩቢዮ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ አሜሪካ የሩሲያ እና ዩክሬን ጦርነት በሰላም እንዲቋጭ እስካሁን ድረስ ያልተቋረጠ ድጋፍ ያደረገች ሲሆን፤ ከዚህ በኋላ ሀላፊነት አንወስድም፤ ጦርነቱን እኛ አልጀመርነውም ሲሉ ተናግረዋል፡፡

የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ የሞስኮ እና ኬቭን ጦርነት ለማስቆም ለ87 ቀናት ያህል ደክመዋል፤ ያሉት ሩቢዮ መጨረሻ ላይ የራሳችንን ውሳኔ ማስቀመጣችን አይቀርም ብለዋል፡፡

@Ewun_Mereja1
@Ewun_Mereja1


"ባለትዳሮቹ.. ቀድመው ይስተናገዳሉ" የባሕር ዳር ከተማ አሥተዳደር

የባሕር ዳር ከተማ አሥተዳደር የመኖሪያ ቤት መሥሪያ ቦታ ለመስጠት ነዋሪዎችን በማኅበር የማደራጀት ሥራውን ሊጀምር መኾኑን ማሳወቁ ይታወሳል።

ከሚያዝያ ስድስት ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ ደግሞ የመንግሥት ሠራተኞችን፣ የጸጥታ ሃይሎችን እና የከተማ ነዋሪዎችን እንደ ቅደም ተከተላቸው የምዝገባ እና የማደራጀት ሥራ እየሠራ ነው።

ነዋሪዎች በማኅበር ሲደራጁ የሚያጋጥሙትን ችግሮች ለመቅረፍ እና ሥራውን ለማቀላጠፍ ከተማ አሥተዳደሩ ባለ ትዳር ኾነው የሚደራጁትን እንደሚያበረታታ እና ቅድሚያ እንደሚሰጥ ተገልጿል።

በባሕር ዳር ከተማ አሥተዳደር የኅብረት ሥራ ማኅበራት ማስፋፊያ ጽሕፈት ቤት ኀላፊ አብርሐም ወርቁ በሰጡት ማብራሪያ ለመደራጀት የሚመጡ ሰዎች በሀሰት ፍቺ ወይም ላጤነት የመቅረብ ዝንባሌዎች መኖራቸው ተገምግሟል ብለዋል።

የሚደራጁ ሰዎች ኹኔታ በዝርዝር ከተገመገመ በኋላ ትዳር እና ልጅ ያላቸውን ግለሰቦች ችግራቸውን ለመቅረፍም ሲባል ትዳር ያላቸውን ማበረታታት ተገቢ ነው ብለዋል አቶ አብርሐም።

ለባለትዳሮች ቅድሚያ ይሰጣል ማለት የሌሎችን ለማጣራት የሚወስደውን ያህል ጊዜ አይወስድም ማለት መኾኑንምም ገልጸዋል።

ትክክለኛ ጋብቻ የሌላቸው እና በትክክለኛ ፍች የፈጸሙት እስኪረጋገጥ በጋብቻ ላይ ያሉት እንዳይጉላሉ የተወሰደ መፍትሄ ነው ብለዋል።

ሲጣራ በትክክልም ላጤ የኾኑ (በትዳር ላይ ያልኾኑ) ይኖራሉ፤ የነሱ መብትም እንደተጠበቀ ነው ብለዋል።

ተቋማት ትክክለኛ መረጃ የመስጠት እና የቤት ሥራ ማኅበራትም ተገቢ ያልኾኑ ተደራጂዎችን የመታገል ውስንነቶች እንዳሉባቸው አቶ አብርሐም ጠቅሰዋል።

መረጃ ሰጪ ተቋማት ትክክለኛ መረጃ የመስጠት እና ማኅበራትም በውስጣቸው የሚደራጅን ሰው መስፈርት አውቀው የማደራጀት ኀላፊነት እንዳለባቸውም ገልጸዋል።

የባሕር ዳር ከተማ መሬት የሕዝቡ የጋራ ሀብት ነው ያሉት ኀላፊው ይህንን ሀብት በፍትሐዊ መንገድ ለመጠቀም ሁሉም ኀላፊነቱን ሊወጣ እንደሚገባ ነው የገለጹት።

በማደራጀት ሥራው ከሚታዩ ዝንባሌዎች ውስጥ አንዱ የሀሰት ላጤነት ነው ብለዋል። ይህንን ለመከላከል በሚደረግ የማጣራት ሂደት እውነተኞቹ እንዳይጉላሉ ባለትዳሮቹ ቀድመው የሚያገኙበትን አሠራር ነው የተቀመጠው ብለዋል።

በላጤነት የሚደራጁትን ደግሞ ከተቋማቸው እና ከማኅበራቸው ጋር  መረጃ በማጥራት ትክክል ኾነው ሲገኙ ተደራጅተው ቦታ ያገኛሉ ነው ያሉት።

Via:አሚኮ

@Ewun_Mereja1
@Ewun_Mereja1


የጀኔራሎቹ እግድ ተነሳ

አዲሱ የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት ሌ/ጀኔራል ታደሰ ወረደ በቀድሞው የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ፕ/ት በአቶ ጌታቸው ረዳ ጊዚያዊ እግድ የተላለፈባቸውን ሦስት ከፍተኛ ወታደራዊ አዛዦችን ከሚያዝያ 7/2017 ዓ.ም ጀምሮ እግዱ መነሳቱን ከሦስት ቀን በፊት በቀን 08/08/2017 ዓ.ም በተጻፈ ደብዳቤ አሳውቀዋል።

በቀድሞው የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር የተጣለባቸው ጊዚያዊ እግድ የተነሳላቸው ሦስቱ ከፍተኛ ወታደራዊ አዛዦች ስም ዝርዝር፦

1.ሜጀር ጄነራል ዮወሃንስ ወልደጊዮርጊስ፣
2. ብርጋዴር ጄነራል ምግበይ ሃይለ እና
3. ሜጀር ጄነራል ማሾ በየነ ናቸው።

@Ewun_Mereja1
@Ewun_Mereja1


በደብረጺዮን ገብረሚካኤል የሚመራው ሕወሓት፣ ፌደራል መንግሥት የትግራይ ግዛቶችን በኃይል የያዙ የታጠቁ ኃይሎችን ባስቸኳይ እንዲያስወጣ ዛሬ ባወጣው መግለጫ ጠይቋል።

ቡድኑ፣ የትግራይን መሬት በኃይል የተቆጣጠረው አካል "የተከዜ ዘብ" የሚላቸውን አዳዲስ ታጣቂዎች እያስመረቀ በትግራይ ላይ "የጦርነት ነጋሪት እየጎሰመ ይገኛል" በማለትም ከሷል። ይህ ዓይነቱ ድርጊት የፕሪቶሪያውን የግጭት ማቆም ስምምነት ሙሉ በሙሉ የሚጻረርና ዘላቂ ሰላም እንዳይመጣ እንቅፋት የሚፈጥር ነው በማለትም ቡድኑ አስጠንቅቋል። የአፍሪካ ኅብረት ፓናል ባፋጣኝ ተሰብስቦ በፕሪቶሪያው የግጭት ማቆም ስምምነት አጠቃላይ አፈጻጸም ላይ እንዲወያይም ቡድኑ ጠይቋል። ስምምነቱ ሙሉ በሙሉ ተግባራዊ ባለመኾኑ፣ የሕዝብ ሞት፣ ሥቃይና ሠቆቃ እንደቀጠለ ይገኛል ብሏል። የፕሪቶሪያው ስምምነት ባለፉት ሁለት ዓመታት ለትግራይ ሕዝብ ትርጉም ያለው ለውጥ አላመጣም ያለው ፓርቲው፣ የታጠቁ ኃይሎች በኃይል በያዟቸው የትግራይ ግዛቶች አኹንም ወገኖቻችን እየተገደሉ፣ እየተፈናቀሉ፣ እየታሠሩና እየተሠቃዩ ይገኛሉ ብሏል። ቡድኑ፣ የፕሪቶሪያው ስምምነት ተደራዳሪዎችና ዓለማቀፉ ማኅበረሰብ ተፈናቃዮች ወደቀያቸው እንዲመለሱ አስቸኳይ ርምጃ እንዲወስዱም ጥሪ አድርጓል።

@Ewun_Mereja1
@Ewun_Mereja1


ብሄራዊ ተሃድሶ ኮሚሽን፣ በትግራይ ተቋርጦ የቆየውን የመጀመርያው ምዕራፍ የቀድሞ ተዋጊዎችን ትጥቅ የማስፈታት፣ የመበተንና መልሶ ከኅብረተሰቡ ጋር የመቀላቀል መርሃ ግብር ትናንት እንደገና አስጀምሯል።

በክልሉ በኅዳር የተጀመረው የትጥቅ ማስፈታትና መልሶ መቀላቀል ሂደት በ"ቴክኒክ" እና "ፖለቲካዊ" ምክንያቶች ከታኅሳስ ጀምሮ ተቋርጦ ነበር። የትግራይ የሰላምና ጸጥታ ቢሮ ሃላፊ ጀኔራል ፍስሃ ኪዳኑ፣ በትግራይ ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍን የፕሪቶሪያው የግጭት ማቆም ስምምነት ሙሉ በሙሉ ተግባራዊ መኾን አለበት በማለት በትናንቱ የመርሃ ግብሩ ድጋሚ ማስጀመሪያ ስነ ሥርዓት ላይ ተናግረዋል። ጀኔራል ፍስሃ፣ የግጭት ማቆም ስምምነቱና የትጥቅ ማስፈታትና መልሶ መቀላቀሉ መርሃ ግብር እንዲሳካ ፌደራል መንግስቱ በግጭት ማቆም ስምምነቱ የገባባቸውን ግዴታዎች መወጣት እንዳለበት አሳስበዋል። የተሃድሶ ኮሚሽን ኮሚሽነር ተመስገን ጥላሁን በበኩላቸው፣ ኮሚሽኑ ለመርሃ ግብሩና ለስምምነቱ ትግበራ ከፌዴራል መንግሥቱና ከአዲሱ ጊዜያዊ አስተዳደር ጋር በትብብር እንደሚሠራ ቃል ገብተዋል።

@Ewun_Mereja1
@Ewun_Mereja1


አዲስ ስታንዳርድ መጽሄት፣ ፌደራል ፖሊስ ዛሬ አዲስ አበባ ወደሚገኘው ቢሮው በመግባት የድርጅቱንና የጋዜጠኞችን ንብረቶች እንደወሰደ ማምሻውን ባወጣው መግለጫ አስታውቋል።

ፖሊስ ጋዜጠኞቹን ጭምር በቁጥጥር ሥር አውሎ እንደነበር የገለጠው መጽሄቱ፣ ዘግየት ብሎ ግን የታሠሩ ባልደረቦቹ እንደተለቀቁ ጠቅሷል። ኾኖም ፖሊስ የወሰዳቸውን የቢሮና የጋዜጠኞች ላፕቶፖች፣ ሞባይል ስልኮችና ሃርድ ዲስኮች እስከ ምሽት ድረስ እንዳልመለሰ፣ ይህም በሥራው ላይ ተጽዕኖ እንደፈጠረና በጋዜጠኞቹ ደኅንነት ላይ ስጋት እንደደቀነ መጽሄቱ ገልጧል።

@Ewun_Mereja1
@Ewun_Mereja1


በድሬዳዋ የእስልምና ኃይማኖት ተከታዮች ከስግደት ለሚመለሱ ክርስቲያን ምዕመናን ማዕድ አጋሩ

በድሬዳዋ የእስልምና ኃይማኖት ተከታዮች ከስግደት ለሚመለሱ የክርስትና እህት ወንድሞቻቸው ማዕድ አጋርተዋል።

የስቅለት በዓል ዛሬ ከማለዳው ጀምሮ በድሬዳዋ በሚገኙ የክርስትና ኃይማኖት ተከታዮች ዘንድ በስግደት፣ በዝማሬ፣ በፀሎት እና በንስሃ ታስቦ ውሏል።

የእስልምና ኃይማኖት አባቶችና ተከታዮች በየአብያተ ክርስቲያናቱ ደጃፎች ከስግደት ለሚመለሱ የክርስትና እህት ወንድሞቻቸው ማዕድ በማጋራት አብሮነታቸውን አሳይተዋል።

በማዕድ ማቋደሱ ሥነ-ሥርዓት ላይ በድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከድር ጁሃር የተመራና የአስተዳደሩን ካቢኔ አባላት ያካተተው ቡድን መሳተፉ ተመላክቷል፡፡

@Ewun_Mereja1
@Ewun_Mereja1


የለማ መገርሳ ቤተሰብ አባላት መታሰራቸውን ፖለቲከኛው ጃዋር አረጋግጬአለሁ አለ። ከፖለቲካ ውጭ የሆኑ ቤተሰቡ መታሰራቸው ነውር ነው ብሏል። ለማ ለምን ዝም አለን ተብሎ እንዴት ቤተሰቡ ይታሰራሉ ብሏል።

@Ewun_Mereja1
@Ewun_Mereja1


የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ በሦስት አጀንዳዎች ላይ ውሳኔ አሳለፈ


የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ ባካሄደው 4ኛ ዓመት 10ኛ መደበኛ ስብሰባ በሦስት አጀንዳዎች ላይ ውሳኔ አሳልፏል።

አጀንዳዎቹም፤

1ኛ. ተቋርጦ የነበረው የመኖርያ ቤት ህብረት ሥራ ማህበራት አገልግሎትን ለማስቀጠል ተጠንቶ የቀረበ የውሳኔ ሀሳብ ላይ የመልካም አስተዳደር ጥያቄን ሊፈታ በሚችል አግባብ የውሳኔ ሀሳብ አሳልፏል።

2ኛ. የብርሃን ዓይን ሰውራን፣ የመነን እና የገላን ቦርዲንግ ትምህርት ቤቶች ካላቸው ልዩ ስምሪት፣ የጥራት ደረጃ እና ከሚያንቀሳቅሱት ሀብትና ንብረት አስተዳደር አንፃር ህጋዊ ሰውነት ኖሯቸው እንዲተዳደሩ እና ተጠሪነታቸው በቀጥታ ለከተማው ትምህርት ቢሮ እንዲሆን የቀረበውን ደንብ መርምሮ አጽድቋል፡፡

3ኛ. ሀገራዊ ፋይዳ ባላቸው ፕሮጀክቶች የቀረበ የመሬት ማስፋፊያ ጥያቄዎች ላይ ተወያይቶ ተገቢነት ያለው መሆኑን በማረጋገጥ ማጽደቁን የከንቲባ ጽሕፈት ቤት መረጃ ያመለክታል።

@Ewun_Mereja1
@Ewun_Mereja1


ኢትዮጵያ ወደ ሩሲያ የምትልከውን ቡና ለማሳደግ ከፍተኛ ፍላጎት እንዳላት ገለፀች

የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር አዱኛ ደበላ ከሩሲያው ሜይ የቡና ኤክስፖርተር ጋር ተወያይተዋል።

ኩባንያው ፋሃም ከተባለ የኢትዮጵያ ቡና ላኪ ድርጅት ቡና እንደሚገዛ ከኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለሥልጣን የተገኘው መረጃ ያሳያል።

ኩባንያው ባለፉት አምስት ዓመታት ከኢትዮጵያ የሚያስገባው ቡና መጠን እንደጨመረና በየወሩ በአማካኝ 10 ኮንቴይነር ቡና እንደሚገዛ ኃላፊዎቹ ገልጸዋል።

የባለሥልጣኑ ዋና ዳይሬክተር በሩሲያ ያለው የኢትዮጵያ ኤምባሲ የሀገሪቱን ቡና በሩሲያ ለማስተዋወቅና ገበያውንም ለማስፋት ጥረት እያደረገ ነው ብለዋል። በተጨማሪም ኢትዮጵያ ወደ ሩሲያ የምትልከውን ቡና ለማሳደግ ከፍተኛ ፍላጎት እንዳላት ገልፀዋል።

@Ewun_Mereja1
@Ewun_Mereja1


በአማራ ክልል ለምክክር ኮሚሽን አጀንዳቸውን ያቀረቡት ከፋኖ ውጪ ያሉ ታጣቂዎች ናቸው ተባለ

የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በአማራ ክልል ባካሄደው አጀንዳ ማሰባሰብ ከፋኖ ውጪ ያለ ታጣቂ ቡድን ለውይይት እና ምላሽ ለማግኘት አጀንዳ መስገባቱን የኮሚሽኑ ሰብሳቢ ለቢቢሲ ተናገሩ።

ፕሮፌሰር መስፍን አርአያ እንዳሉት ታጣቂ ቡድኑ ወደ ትጥቅ ትግል ያስገቡትን ምክንያቶች የምክክር አጀንዳ ጥያቄዎች በማድረግ ወደ ምክክር ኮሚሽኑ ማምጣታቸውን ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በአማራ ክልል ከመጋቢት 27 አስከ ሚያዝያ 4/2017 ዓ.ም. በባሕር ዳር ከተማ ባካሄደው የአጀንዳ ማሰባሰብ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የመንግሥት አካላት፣ ታዋቂ ግለሰቦች፣ የማኅበረሰብ ወኪሎች እና የተለያዩ ተቋማት እንዲሁም የማኅበራት ተወካዮች መሳተፋቸው ተገልጿል።

በዚህ ሂደት ላይ በክልሉ ውስጥ የሚንቀሳቀስ አንድ ታጣቂ ቡድን ለብሔራዊ ምክክር ኮሚሽኑ ጥያቄዎቹን የያዘ አጀንዳ ማስገባቱን ሰብሳቢው ፕሮፌሰር መስፍን አርአያ ተናግረዋል።

ሰብሳቢው በአማራ ክልል ከሚንቀሳቀሱ ታጣቂ ቡድኖች መካከል አንዱ ነው ያሉት ይህ ቡድን ያሉት ጥያቄዎች በአጀንዳነት ለኮሚሽኑ ያቀረበው "በትክክል ውይይት ተደርጎ መግባባት የሚደረስበት ከሆነ የትጥቅ ትግሉን ማቆም ይቻላል በሚል እምነት" መሆኑን ለቢቢሲ ገልጸዋል።

ፕሮፌሰር መስፍን አክለውም ታጣቂ ቡድኑ ያቀረበው አጀንዳ "በሕገ መንግሥቱ ማዕቀፍ ውስጥ ሊጠየቁ የሚገባቸውን ጥያቄ የያዘ" መሆኑን ጠቁመው በታጣቂ ቡድኑ የቀረበውን አጀንዳ አሁን ከመግለጽ ተቆጥበዋል።

ታጣቂ ቡድኑ በርካታ ታጣቂዎች ያሉት ነው ያሉት ፕሮፌሰር መስፍን አርአያ፣ በክልሉ ውስጥ የሚንቀሳቀሰው "የፋኖ ቡድን አካል" አለመሆኑን ተናግርዋል።ethio fm

@Ewun_Mereja1
@Ewun_Mereja1


የካሊፎርኒያ ግዛት በትራምፕ ላይ ክስ መሰረተች

ከአሜሪካ ግዛቶች ሁሉ ከፍተኛ ኢኮኖሚ የምታንቀሳቅሰው እንዲሁም የግዙፍ ፋብሪካዎች እና እርሻዎች መገኛ የሆነችው የካሊፎርኒያ ግዛት፤ የዶናልድ ትራምፕን ታሪፍ በመቃወም ክስ መሰረተች።

የካሊፎርኒያ ግዛት አስተዳዳሪ ጋቪን ኒውሶም የፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕን ታሪፍ በመቃወም ክስ መመስረታቸውን ይፋ አድርገዋል።

ዶናልድ ትራምፕ በዓለም አቀፍ አገራት ላይ የጣሉትን ታሪፍ በመቃወም ለመጀመርያ ጊዜ በተመሰረተው የግዛቲቱ ክስ፤ ትራምፕ ይህንን ፕሬዝዳንታዊ ትዕዛዝ ለማስተላለፍ የተጠቀሙትን ሕግ ተቃውሟል።

ካሊፎርኒያ ከየትኛውም የአሜሪካ ግዛቶች በመቅደም በዓለም አምስተኛዋ ግዙፍ ኢኮኖሚ ያላት ግዛት ነች።
በግዛቲቱ ውስጥ ግዙፍ የማኑፋክቸሪንግ ኩባንያዎች እና ሰፋፊ እርሻዎች ይገኛሉ።

@Ewun_Mereja1
@Ewun_Mereja1

Показано 18 последних публикаций.