Фильтр публикаций


ይህንን Online ስራ ያልጀመራችሁ ቶሎ ግቡና ስሩበት
https://www.lendlease-et.com/#/register?code=49826


ባያችሁት አትሰበሩ!
፨፨፨፨//////፨፨፨፨
ውጪውን እያያችሁ፣ ሌላውን ሰው እየተመለከታችሁ፣ ሶሻል ሚድያውን እየበረበራችሁ በንፅፅር ዓለም ለምትባክኑ፣ ሳታቁት ራሳችሁን ንቃችሁ ሌላውን የምታከብሩ፣ ባለማስተዋል ራስን መሆንን ተጠይፋችሁ ሌላ ሰው መሆንን ለምትናፍቁ፣ በተደጋጋሚ በሙላት እየኖራችሁ እንዳልሆነ ለሚሰማችሁ፦ የእናንተ ዓለም ይሔ አይደለም፣ ህይወታችሁን ልትመሩት የሚገባው በዚህ መንገድ አይደለም። አውቃችሁና ፈልጋችሁ እዚህ ሁኔታ ውስጥ አልገባችሁም፣ ብትጠየቁም ምርጫችሁ እንዳልሆነ ትናገሩ ይሆናል። ነገር ግን የማይወደውን ህይወት የሚኖር፣ የማይፈልገው ስፍራ የሚገኝ፣ የማይገባውን ተግባር የሚፈፅም ሰው እናንተ ብቻ አይደላችሁም። ብዙ ሰው እንደነገሩ ይኖራል፣ ካለበትም የከፋ እንዳለ እያሰበ ይፅናናል። እርግጥ ነው ከፈጣሪው በቀር ያለበትን ችግር የሚረዳው የለምና ራሱን ከማፅናናት በቀር አማራጭ የለውም። መጨከን ካለባችሁ ህይወት ላይ ጨክኑ እንጂ ራሳችሁ ላይ አትጨክኑ። ህይወት ብዙ ክፉ ነገር ብታሳያችሁም እናንተ በፍፁም ባያችሁት ነገር እንዳትሰበሩ፤ ዓለም ብዙ ብትፈትናችሁም እናንተ ግን በፍፁም ፈጣሪያችሁን እንዳታማርሩ። ጭፍን አማኝ፣ ጭፍን ተስፈኛ መሆንን ልመዱ። የመጣው ይምጣ እንደ አመጣጡ ተመልሶ ይሔዳል።

አዎ! ባያችሁት አትሰበሩ! ሁን ተብሎም ተደረገ በአጋጣሚ ተከሰተ አሁን አሁን የምታዩት ብዙ ነገር አስፈሪ፣ የምትሰሙትም ነገር እንዲሁ አስደንጋጭ ሊሆንባችሁ ይችላል። ነገር ግን ብትፈሩም እንዳትሰበሩ፣ ብትደነግጡም ተስፋ እንዳትቆርጡ። በራሳቸው ሃይል ሊያሸንፏችሁ የማይችሉ አካላት ድክመታችሁን አጥብቀው ይፈልጋሉ፣ እንድትረጋጉና ራሳችሁን ችላችሁ እንድትቆሙ የማይፈልጉ አካላት በብዙ ትብታብ ሊያስሯችሁ ይፈልጋሉ። ደካማ ሰው ብርታቱ አይታየውም፣ ሰነፍ ሰውም በራሱ ጥንካሬ አይተማመንም። ማንኛውም የሰው ልጅ ትኩረት ማድረግ ከቻለ ምንም ማድረግ እንደሚችል አስተውሉ። ትኩረታችሁ በብዙ መንገድ ተሰርቆ፣ የሚረባውንም የማይረባውንም ወደ አዕምሯችሁ እያስገባችሁ፣ አገኘን ብላችሁ ነፃ የሆነ ነገር እያሳደዳችሁ፣ አጥፊያችሁ ይሁን አልሚያችሁ እንደሆነ ሳትረዱ ያያችሁትን ሁሉ እየተመኛችሁ ከሆነ ዓለም አዙሪት ውስጥ ከታ አቅላችሁን ሳታስታችሁ በፍጥነት ወደ ራሳችሁ ተመለሱ። አትዘናጉ፣ ልባችሁ ሲሰረቅ ዝም ብላችሁ አትመልከቱ።

አዎ! ጀግናዬ..! ያበቃ ቢመስልህም ገና አላበቃም፣ የተሸወድክ፣ የተሸነፍክ፣ የወደክ፣ የተጣልክ ቢመስልህም ጊዜው ገና ነው። ዳግም መነሳት ትችላለህ። በውድቀትና በሽንፈት መሃል የተማርከውን ትምህርት እየኖርክ ዳግም ራስህን ማብቃት ትችላለህ። ሸሩን ለሸረኛ፣ ጎጡን ለጎጠኛ፣ ሰበቡንም ለሰበበኛ ትተህ አንተ ራስህን አድን። የተባለው ሁሉ እውነት እንዲሆን አትጠብቅ፣ የተነገረህን ሁሉ ማመን አቁም። የትኛውንም በነፃ የምታገኘውን ነገር ከመጠቀምህ በፊት እርሱ ሊጠቀምብህ እንዳልሆነ በሚገባ መርምር። አንዳንድ ሁነቶች መግቢያቸው በጣም ሰፊ ነው፣ መውጫቸው ግን እጅጉን ጠባባ ነው። ቦሃላ "ምነው እጄን በሰበረው" ከማለትህ በፊት አገኘው ብለህ ሁሉ ነገር ውስጥ እጅህን አትክተት። አብዛኛው ብልጭልጭና አጓጉዊ ነገር ወጥመድ ነው። በሰዓቱ ያልጠበከውን ደስታ ይሰጥሃል ቦሃላ ግን መቀመቅ ውስጥ ይከትሃል። ሰው ያደረገውን ሁሉ አታድርግ፣ ሰው በተራመደበት መንገድ ሁሉ አትራመድ። አስተዋይነትህን ተጠቀም፣ ስብራትህንም ቀድመህ አስቀረው።


ማንነት ይቅደም!
፨፨፨/////////፨፨፨
ከምንም በፊት የተገነባ ማንነት አለት ላይ እንደተገነባ ህንፃ ነው፤ ማንም ቢመጣ ሊነቀንቀው አይችልም። "ገንዘብ ሳገኝ ማንነቴ ላይ እሰራለሁ" ብትል ገንዘቡ ሲጠፋ የገነባሀው ማንነትም ቀስ በቀስ ሲሸረሸር ትመለከተዋለህ፤ ፍቅር ስጀምር ማንነቴን እገነባለሁ ብትል ፍቅርህ እክል ሲገጥመው በፍቅር ህይወትህ ላይ የተገነባው ማንነትም እንደ ሸክላ ሲፈረካከስ ትመለከተዋለህ፤ እኔነቴን በቤተሰቤ ሀብትና ስልጣን፣ በእራሴ ዝናና ንብረት ላይ እመሰርታለሁ ብትል መሰረቶችህን ሁሉ የጊዜ ማዕበል ጠራርጎ ሲወስዳቸው ከተገነባው ማንነት በላይ አንተነህን አጥተህ ባዶ እጅህን እያጨበጨብክ ትቀራለህ። የትኛውም ምድራዊ ቁስ ጠፊ ነው፤ የትኛውም የሰው ልጅ ግኝት ጊዜያዊ ነው። በጠፊውና ጊዜያዊው ንብረት ላይ የተመሰረተ ማንነትም ከንብረቱ ጋር መጥፋቱና መክሰሙ አይቀርም። የምትችለው ምንድነው? ብትባል "የምችለው እራሴን መሆን፣ እራሴን መገንባትና እራሴን ማብቃት ነው።" ብለህ በኩራት ተናገር።

አዎ! ጀግናዬ..! ማንነት ይቅደም፤ ስብዕናህ ላይ አስቀድመህ ስራ፤ በመጀመሪያ ወሰኝ የህይወት መርህ ይኑርህ፤ አስቀድሞ የአስተሳሰብ እርከንህን አስፋ፤ ቆራጥነትህን አጠንክር። እራሱ የታላቅነት ጉዞህ፣ የምትጓዝበት የእድገት መንገድ የሚገነባው ማንነት ይኖራል። እርሱም እስከሞከርክና ሂደቱን እስከተከተልክ ድረስ በምንም ምክንያት የሚቀር አይደለም። በቅድሚያ ግን የማይናወጠውን የእራስህን ማንነት ከአምላክህ ፍቃድ፣ ከእራስህ ፍላጎትና ከህይወት አላማህ አንፃር ገንባ። ለፍርድ መቸኮል፣ ስም ማጥፋት ተስፋ እንደመቁረጥ በቀለለበት፣ ትቺትና ነቀፋ ባህል በሆነበት ዓለም እየኖርክ አስቀድሞ የተገነባ ፅኑ ማንነት ከሌለህ ለከፋው ውድቀት በጣም ቅርብ እንደሆንክ እወቅ። ስኬትን ስትመኝ በትንሽዬ እንቅፋት ተንኮታኩተህ የነበርክበት ትመለሳለህ፣ ለሰው ስታስብ ለእራስህም መሆን ያቅትሃል።

አዎ! ማንም የሚመለከትህ በእራሱ መነፅር የጥራት መጠን ነውና የሚሰጥህን የማንነት ልኬት ተቀበል፣ ነገር ግን ውስጥ ለውስጥ የምትፈልገውን ማንነት መገንባት እንዳታቆም፤ ማንም ሃሳብ የሚሰጥህ ከመረዳት አቅሙ ተነስቶ ነውና ሃሳቡን አክብርለት፣ ነገር ግን ከምንም በፊት አንተ ለእራስህ ስለምትሰጠው ሃሳብ በጥልቀት አስብ። ብዙዎች የተጎዱት በሌላ ሰው እንደሆነ ያስባሉ፣ በሚያሳዝን ሁኔታ ግን ከገዛ እራሳቸው በላይ የጎዳቸው፣ ከገዛ አስተሳሰባቸውና ለእራሳቸው ከሚሰጡት ቦታ በላይ የተጫወተባቸው ሰው የለም። ለእራሳቸው ፍቅር ሳይኖራቸው የሚያፈቅራቸውን ሰው ያስሳሉ፣ ለእራሳቸው ውለታ መዋል አልቻሉም ሰዎች ግን ውለታ እንዲውሉላቸው ይፈልጋሉ፣ እራሳቸውን የመቀበል አጣብቂኝ ውስጥ ገብተዋል ነገር ግን ሌሎች እንዲቀበሏቸው ያለማቋረጥ ይወተውታሉ። ቀዳሚው የቤትስራ ማንነትን ማብቃት፣ እራስን መቻልና ለእራስ መሆን መቻል ነውና አስቀድመህ እውነተኛውን ማንነትህን ገንባ፤ በመጀመሪያም ለእራስህ ሆነህ ተገኝ።


ልጁን ግደሉት!
፨፨፨//////፨፨፨
እስከ መቼ ያማረውን ሁሉ እንድታመጡ የሚያስገድዳችሁን ልጅ እየተለማመጣችሁ ትኖራላችሁ? እስከመቼ በልቶ የማይጠግበውን፣ ጠጥቶ የማይረካውን፣ አይቶ አምሮቱ የማይወጣውን ልጅ እያስታመማችሁ ትዘልቃላችሁ? እስከ መቼ በትንሹም በትልቁም የሚበሳጨውን፣ በትንሽ ውድቀት ተስፋ የሚቆርጠውን ህፃን እያባበላችሁ ትኖራላችሁ? እስከ መቼ? የህፃኑና የእናንተ መለያያ ጊዜ መቼ ነው? ይህን ህፃን ውጪ አትፈልጉት፣ ይህ ህፃን ትልቅ ቦታ ይዞ ውስጣችሁ ተቀምጧል። የራሱ ጊዜ አለው፣ በሰዓቱ ካቀረቀረበት ቀና ይላል፣ በጊዜው ወጣ ማለት ይጀምራል፣ ማመዛዘን የሚባለውን ነገር ይተዋል ትናንሽ ነገሮችን መከተል ይጀምራል፣ ጫወታ ያታልለዋል፣ ብልጭልጭ ይሸውደዋል፣ መናገር የፈለገውን ይናገራል ማንን ሊያስቀይም እንደሚችል ግን አያውቅም፣ ያሻውን ነገር ዛሬውኑ ማግኘት ይፈልጋል ራሱንም ያለልክ ያስጨንቃል። ይሔን በቅጡ ያላደገውንና ብስለት የጎደለውን ህፃን በቶሎ ካልገራችሁት ህይወታችሁ ሁሌም እቃቃ ጫወታ መሆኑ አይቀርም።

አዎ! ልጁን ግደሉት፣ ስሜቱን ብቻ የሚከተለውን፣ "ያልኩት ካልሆነ ሞቼ እገኛለሁ" የሚለውን፣ አርቆ መመልከት የተሳነውን፣ ትዕግሥትና ፅናት ያልፈጠረበትን፣ ሩጫ የሚወደውን ብሎም ሲወድቅ ለረጅም ጊዜ የሚያዝነውን ህፃኑን ማንነታችሁን ከውስጣችሁ አስወግዱት። ማንኛውም ህፃን ተግሳፅ ይፈልጋል፣ የትኛውም ህፃን መማርና መገራት ያስፈልገዋል፣ ከፊት ሆኖ የሚመራውን ያሻል። የራሳችሁን ህፃንም በሚገባ አስተምሩት፣ ገስፁት፣ የሚፈልገውን ሳይሆን የሚያስፈልገውን፣ የሚጠቅመውን አቅርቡለት፣ ያለቀሰለትን ሳይሆን የሚገባውን ስጡት፣ ከፊት ሆናችሁ ምሩት፣ መንገዱን አሳዩት። በማይረባ ትንሽ ነገር ራሳችሁን እየደለላችሁ ከሆነ፣ ከቁብነገር ቀልድና ጫወታን እያስበለጣችሁ ከሆነ፣ በወረተኝነት እየተጠቃችሁ ከሆነ፣ ስሜታችሁ እየሰለጠነባችሁ ከሆነ፣ ውስጣችሁ ብርታትና ጥንካሬ እያጣ ከሆነ ህይወት ንቃትና ብስለታችሁን አጥብቅ እየፈለገች እንደሆነ እወቁ። ልጅነታችሁ ብዙ ያሳጣችኋል፣ ከእናንተ የማይጠበቅ ስህተት ያሰራችኋል፣ ሰርቶና ለፍቶ ገንዘብ ከመስራትና ንብረት ከማፍራት ይልቅ ጊዜን በዋዛ ፈዛዛ በከንቱ እንድታሳልፉ ያደርጋችኋል።

አዎ! ጀግናዬ..! ህይወት ላይ ቁብነገረኛ ለመሆን እድሜህ እስኪገፋ አትጠብቅ። ሁሉም ነገር ጊዜ ዓለም። በዕድሜ በሰል ስትል ሰውነትህ ይዝላል፣ ጎልመስ ማለት ስትጀምር ሃላፊነቶችህ እየጨመሩ ይመጣሉ፣ ለራስህ የሚሆን ጊዜ ታጣለህ፣ ትኩረትህ በየቦታው ይበታተናል፣ አንዳንዴም ህፃኑ ማንነትህ ሰው ፊት አሳንሶ ያሳይሃል። ከእድሜህ በፊት መብሰል ትችላለህ፣ ህፃኑ ማንነትህ እንዳለ ስሜትህ ላይ መንገስ ትችላለህ። ያላዳመጥከው ስሜት እንዴትም መውጣት አይችልም፣ ትኩረትና ቦታ ያልሰጠሀው ፍላጎት በምንም መንገድ መገለጥ አይችልም። ይጥቀመው አይጥቀመው፣ ጉዳት ይኑረው አይኑረው ሳያውቅ ያማረውን ሁሉ ለማድረግ የሚነሳው ክፉና ደጉን ያልለየው ህፃን ልጅ ብቻ ነው። ሚዛናዊ መሆንን ልመድ። ስለራበህ ብቻ የቀረበልህን ምግብ ሁሉ አትመገብም፣ ስላለህ ብቻ ያማረህን ሁሉ አትገዛም። ከህፃን ከፍ ያለ የበሰለ እይታ ያስፈልግሃል፣ በትንሹም ቢሆን በራሱ ላይ መራር ውሳኔዎችን መወሰን የሚችል ጠንካራ ማንነት ያስፈልግሃል። የልጅነት አመለካከት ማራመድ አቁም፣ ህፃንነትህን ባለበት አስቀረው፣ ለስንፍና ቦታ አትስጠው፣ ታላቁን ብርቱ ማንነትም ገልጠህ አሳየው።


የመጀመሪያዎቹ ሁኑ!
፨፨፨፨////////፨፨፨፨
መውደቅ ብርቅ አይደለም ነገር ግን ብርቅ ቢሆን እንኳን እስኪ የመጀመሪያዎቹ ሁኑ፤ መሸነፍ ለማንም አዲስ አይደለም ነገር ግን አዲስ ቢሆን እንኳን እስኪ የመጀመሪያዎቹ ሁኑ፤ መተቸት መሰደብ ብርቅ አይደለም ነገር ግን ብርቅ ቢሆን እንኳን እስኪ ለመጀመሪያ ጊዜ ተተቹ ተሰደቡ። ምን ይመጣል? ምን ታጣላችሁ? ምንስ ይጎድላችኋል? ለአንዳንድ ሁነቶች መፍትሔው ድፍረትና ድፍረት ብቻ ነው። መምጣት ያለበት መምጣቱ ላይቀር እንዲሁ በረጅም ገመድ እንደ ታሰረች አህያ ራሳችሁን በፍረሃት አትሰሩት። ከዚህ በፊት ማንም ላይ ያልተከሰተ ነገር አይከሰትባችሁም ቢከሰትባችሁም እንኳን የሞትና የሽረት ጉዳይ አይደለም። በደምብ አስባችሁት ከሆነ ትልቅ ቦታ ከሰጣችሁት ዓለም ላይ የማያስፈራ ነገር የለም። ቦታ በሰጣችሁት ልክ ሊቆጣጠራችሁ የሚፈልገው ነገር ብዙ ነው። አዲስ ነገር ለመሞከር የመጀመሪያ ከሆናችሁ ለማሳካቱም የመጀመሪያዎቹ የምትሆኑት እናንተ ናችሁ። ርቆ መሔድ ስጋትን ይደቅናል፣ እዛው በነበሩበት መቆየትም ጭንቀትን ያመጣል፤ ለየት ማለት አይን ውስጥ ያስገባል፣ ተመሳስሎ መኖርም ያስረሳል። በዚህም አላችሁ በዛ ጭንቀት ሁሌም አለ። የጭንቀታችሁን ምክንያት መምረጥ ግን ትችላላችሁ።

አዎ! የመጀመሪያዎቹ ሁኑ! ከፊት ቅደሙ፣ ብትከስሩም ብታተርፉም ጥቅሙ የእናንተ ነው። ዓለም የምትሸልመው አሸናፊዎችን ነው፣ አሸናፊዎች ደግሞ በመሞከርም ሆነ በመጀመር የመጀመሪያዎቹ ናችሁ። ቆማችሁ ከሆነ ትልቁ ሃሳባችሁ መጀመር ብቻ ይሁን፣ ጀምራችሁም ከሆነ ዋናው ግባችሁ መጨረስ ይሁን። የሰው ልጅ የመጀመሪያ መሆንን ይፈራል፣ ከፊት ሆኖ ነገሮችን አስቀድሞ መጋፈጥ ያስጨንቀዋል፣ ሃላፊነት የበዛበት ነገር ላይ ለመሳተፍ አይፈርድም። ፊትለፊት የማይወጣና ራሱን በአሉታዊ ንግግሮች ያላስገረፈና ቆዳውን ያላጠነከረ ሰው ደግሞ አንድ እርምጃ ወደፊት ፈቀቅ ያለ ህይወት አይኖረውም። ነገሮች ይደጋገማሉ፣ ሃሳቦች ይደራረባሉ ነገር ግን እነዚህ ለረጅም ጊዜ የተደራረቡ ነገሮች ለብዙ ሰዎች አዲስ ናቸው። እናንተ ሰው እየጠበቃችሁ ከሆነ ጊዜ ግን አይጠብቃችሁም፣ እናንተ ወቅታዊ አጀንዳን እያሳደዳችሁ ከሆነ ዓለም ጥላችሁ እየሔደች ነው። ሞኝ ብልጦች መሓል ሲገባ ብልጥ የሆነ ይመስለዋል። ከገባው ግን ቶሎ ሞኝነቱን ተረድቶ ከሁሉም የላቀ ብልጥ ሆኖ መገኘት ይችላል።

አዎ! ጀግናዬ..! ከፊት ተሰለፍ፣ ከአብዛኛው ሰው ቀድመህ ተገኝ፣ ብዙ ሰው ለማያገኘው እድል ራስህን አዘጋጅ። በየትኛውም ውድድር አስቀድመው የጀመሩት ሁሉ አያሸንፉም፣ ነገር ግን ካልጀመሩት ሰዎች በተለየ ከፍተኛ የማሸነፍ እድል አላቸው። ደፋር እንደሆንክ የምታስብ ከሆነ ብዙ ሰው በሚሸሸው ወሳኝ ጉዳይ ላይ ከፊተኞቹ ተርታ የማትመደብበት ምክንያት አይኖርም። ፈሪ ዓለሙ ፍረሃት ነው፣ ደፋር ዓለሙ እውነት ነው። ፈርተህ አትቁም ይልቅ በድፍረት ከፊት ተፋለም፣ ተጨንቀህ እድልህን አትግፋው ይልቅ ነቃ ብለህ በርህን ክፈትለት። አንተ ካልተቀየርክ የትም ብትሔድ ስጋትህ አይቀየርም፣ አንተ ካልነቃህ ምንም ብታደርግህ ፍረሃትህ በውጤትህ ይገለጣል። እርግጥ ነው ለማውራት የቀለለ ሁሉ ሲደረግም ቀላል ሊሆን አይችልም። አንተን ግን የሚያስፈልግህ ቅለቱ ወይም ክብደቱ ሳይሆን ማድረጉ ብቻ ነው። ኮተት አታብዛ፣ ምክንያት አትደርድር። ፍላጎቱ ካለህ ቀድመህ ተራመድ፣ ከማንም ቀድመህ ከመዳረሻው ድረስ፣ የሚገባህን ውጤትም በእጅህ አስገባ።


//•• ኢጎአችን እና አይምሮ •• //

የሰው ልጅ ለደረሰበት ስልጣኔ እና ብዙ ሳይንሳዊ እውቀቶች ምክንያት አእምሮዉን በሚገባ መጠቀሙ መሆኑ ግልፅ ነው። ነገር ግን አእምሮአችን በጣም አስፈላጊ የመሆኑን ያህል አውዳሚም ሊሆን ይችላል። እንዴት?

አእምሮ በውስጡ ወደ 100 ቢሊየን የሚጠጉ ኒውሮኖች ይገኛሉ። በዚህም ምክንያት የሰው ልጅ በቀን (24ሰአታት) ውስጥ ከ 40,000 እስከ 60,000 ሀሳቦችን ያስባል። ከነዚህ ሀሳቦች ውስጥ 75% የሚሆኑት መጥፎና አውዳሚ (negative thoughts) ሲሆኑ 95% ደግሞ ተደጋጋሚ (repetitive thoughts) ናቸው። ስለዚህ ከነዚህ ሁሉ ምናስባቸው ሀሳቦች ውስጥ ቀና እና መልካም (positive thoughts) የሚባሉት 5%ቱ ብቻ ናቸው።

ተመስጦ (meditation) የማድረግ ልምድ ካላችሁ ይህንን መረዳት ትችላላችሁ። አእምሮአችን በአብዛኛው ምንም ለህይወታችን ፋይዳ በሌላቸው ሀሳቦች ሲባክን ይውላል። ነገር ግን ይህን ለመረዳት መጀመሪያ አእምሮአችሁን መታዘብ መጀመር አለባችሁ። ይህንን ካላደረጋችሁ ግን የምታስቡት እናንተ እንጂ አእምሮአችሁ ላይመስላችሁ ይችላል። አብዛኛው ሰዉ የሚያስበው አእምሮ መሆኑን አይረዳም፤ የሚያስበው፣ የሚያስታውሰው፣ የሚያሰላስለው አእምሮአችሁ እንጂ እናንተ አይደላችሁም። ይህንን ለማረጋገጥ ጭንቅላቱ ላይ አደጋ የደረሰበትን ሰው መመልከት በቂ ነው፤ ጭንቅላታቸው የተጎዱ ሰዎች ያለፈ የህይወት ታሪካቸውን እና ያከማቹትን እውቀት የሚረሱበት አጋጣሚ አለ።

አእምሮአችን እንድናስብበት እና እንዲያገለግለን የተሰጠን ድንቅ ገፀ በረከት ቢሆንም በተቃራኒው እኛ እራሳችን የአእምሮአችን ባርያ ነን። ነገር ግን አእምሮን በአግባቡ ከተጠቀምንበት መጥፎ ጌታ ከመሆን ይልቅ ጥሩ ባርያ ማድረግ እንችለላለን። አእምሮአችን ማስላት ይወዳል፤ እራሱን ከሌሎች ያነፃፅራል።

አእምሮ የኢጎ ማእከል ነው። ኢጎ እራስን በሆነ አይነት ማንነት ለሰዎች ለመግለፅ መሞከር እና ከሌሎች የተሻለ መሆኑን ለማሳየት የሚሞክርበት መንገድ ነው። ለምሳሌ ፦ የብሔር ማንነትን፣ የትምህርት ደረጃን፣ የቆዳ ቀለምን፣ ሀይማኖትን፣ ግለሰባዊ አመለካከትን እንደ ራስ ማንነት በመቁጠር ከሌሎች የተሻሉ መሆንን ለማሳየት የሚደረግ ጥረት የኢጎ የተለያየ ገፅታ ነው። አንድ ሐኪም ለሙያው ካለው ፍቅር የተነሳ የሚሰጠው የህክምና አገልግሎት ጤናማ ቢሆንም፤ የህክምና እውቀት መያዙ ከሌሎች ሰዎች የተሻለ እንደሆነ እንዲሰማዉ የሚያደርገው ከሆነ እና በየአጋጣሚው ስለሱ የሚያወራ ከሆነ ግን ይህንን ኢጎ ልንለው እንችላለን።

ኢጎ ራስን ከሁለንተና የመነጠል ውጤት ነው። አእምሮአችሁ ከሁለነተና ጋር አንድ እንድትሆኑ አይፈልግም። ምክንያቱም ከሁለንተና (universe) ጋር አንድ ከሆናችሁ ከአእምሮ በላይ ትሆናላችሁ፤ ማሰብ በምትፈልጉበት ሰአት ታስባላችሁ ካልፈለጋችሁ ደግሞ አእምሮን እንዳያስብ ማድረግ (shutdown) ትችላላችሁ። አሁን ግን እየሆነ ያለው የተገላቢጦሽ ነው፤ አእምሮአችን በያንዳንዷ ሰከንድ ያለኛ ፍላጎት ያስባል። ይህም ማለት እጃችን ያለኛ ፍላጎት ቢንቀሳቀስ ማለት ነው፤ አእምሮአችን ግን ይህንን ያደርጋል። ሰዎችም ይህንን የአእምሮአቸውን ጫጫታ ለመርሳት በተለያዩ የአልኮል እና አደንዛዥ እፆች እራሳቸውን ይጠምዳሉ።

እዉነታው ግን እኛ ከሁለንተና የተለየን አይደለንም። አእምሮአችን ከእውነተኛ ውስጣዊ ተፈጥሮአችን በታች ነው። ይህንን ውስጣዊ ተፈጥሮአችንን ለማግኘት ከኢጎ (አእምሮ) የበላይነት መላቀቅ ይኖርብናል። አእምሮ ማለት ምንም ሳይሆን ያለፈ እና የወደፊት ህይወታችን የሀሳብ ጥርቅም ማለት ነው። ከአእምሮአችን ቁጥጥር ለመላቀቅ አሁንን መኖር ይኖርብናል፤ ምክንያቱም አሁን(now) የጊዜ አካል አይደለም። ሀሳብ እንዲኖር ያለፈ ወይም የወደፊቱ ጊዜ መኖር አለባቸው ።


ቆሻሻውን ተጠየፉ!
፨፨፨፨//////፨፨፨፨
ፀዴ ሁኑ፤ ንፅት ፅድት በሉ። የቆሸሸውን የጥላቻ አስተሳሰብ ተጠየፉ፣ ለጆሮ የሚጎረብጠውን የዘረኝነት አቋም ራቁት፣ ሰላም የማይሰጠውን የጎጠኝነትን አስተምህሮ ከአካባቢያችሁ አስወግዱ። አዕምሯችሁ በማይረባ የንቀትና የጥላቻ አመለካከት ተሞልቶ ከላይ ንፁህና ፅዱ ልብስ ብትለብሱ ምንም ዋጋ የለውም። አሁን አሁን በዚህ መንገድ የሚያምታቱ ሰዎች በዝተዋል። አለባበሳቸው ነጭ ነው አስተሳሰባቸው ግን ከጥላሸት የከፋ ጥቁር ነው፤ ሲታዩ ዘናጭ ይመስላሉ ንግግራቸው ግን እንደ ሬት ይመራል፣ ገፅታቸው በፈገግታ ተሞልቷል ቀርበው ሲታዩ ግን ውስጣቸው በክፋትና በጥላቻ ተተብትቧል፤ ከውጭ ለሚያያቸው ሀይማኖተኛ ጿሚ ፀላይ አስቀዳሽ ይመስላሉ ለቀረባቸው ግን ነውራቸው እጅግ የከፋ ነው። በጥሩ ልብስና ቁስ ሰውን ማታለል በጣም ቀላል ነው፣ ልብና ኩላሊትን የሚመረምረውን ፈጣሪ ግን መቼም ማታለል አይቻልም። ስለማንኛውም የሰው ልጅ ስለምታስቡት ሃሳብ ደጋግማችሁ ተመልከቱ፣ ስላለመመረዙና ስላለመቆሸሹ እርግጠኛ ሁኑ። የአስተሳሰባችሁ ጤንነት የህይወታችሁ ጤንነት ነው፤ የእያንዳንዱ አቋማችሁ ትክክለኝነት የስኬታችሁ ዋንኛ ምክንያት ነው። በቆሸሸ አመለካከት ላይ ቤት አትስሩ፣ በተመረዘ አካሔድ ወደፊት ለመጓዝ አትሞክሩ።

አዎ! ቆሻሻውን ተጠየፉ፣ መርዙን ወደ ህይወታችሁ አታስገቡ፣ በወደቀ አስተሳሰብ አትመሩ። ከምር ራሳችሁን የምታከብሩ ከሆነ ማንም በቂቤ የተለወሰ ምላስ ያለው ሰው የሚያቀብላችሁን የጥላቻ ሃሳብ አትቀበሉም፣ የእውነት የአዕምሮ ጤናችሁና የውስጥ ሰላማችሁ የሚያሳስባችሁ ከሆነ ቆሻሻውን መርዘኛ አስተምህሮ ለመጠየፍ ጊዜ አታጠፉም። ሀሳቡ አልሚም ይሁን አጥፊ፣ ጠቃሚም ይሁን ጎጂ፣ የጥላቻም ይሁን የፍቅር ማንኛውም ሰው የራሱ ሃሳብ አለው፣ ይህን ሀሳቡን የሚጭንበት ተቀባይም ይኖረዋል። ስንዴና እንክርዳዱን መለየት እየቻላችሁ፣ ዋናውን ሰብልና አረሙን እያወቃችሁ ማንም ራሱን እንደ አዋቂና ተመራማሪ ቆጥሮ የሚነዛውን አጥፊ አቋም እንደወረደ መቀበል አቁሙ። ሁሉም ሰው ነፃ ሃሳብ እንዳለው ሁሉ እናንተም ነፃ ሃሳብ አላችሁ፣ ሁሉም ሰው የመምረጥ አቅም እንዳለው እናንተም የሚበጃችሁን የመምረጥ አቅሙ አላችሁ። የትኛውም ስቃያችሁ የሚያበቃው እናንተ ልታስቆሙት ፍቃደኛ ስትሆኑ ብቻ ነው፤ ማንኛውም ሰው አስተሳሰቡን ሊጭንባችሁ የሚችለው እናንተ ስትቀበሉት ነው። ለይስሙላ አትኑሩ፣ ሰው ምን ይለኛል ብላችሁ ጠባብና አጥፊ አመለካከት ውስጥ አትዘፈቁ።

አዎ! ጀግናዬ..! የራስህ ሚዛናዊ አመለካከት ይኑርህ። ልክ እንዳየህ የምትፈርድ፣ የሰማሀውን ሁሉ የምታምን፣ ለጥሩውም ለመጥፎውም ጆሮህን የምትከፍት፣ ጠዋት ፅድቅ ቦታ ማታ ርካሽ ስፍራ የምትገኝ፣ እያወክ ወገንህን የሚያሸብር ዜና የምታሰራጭ ወይም የምትከታተል ሰው አትሁን። ከቆሻሻ ውስጥ ንፁህ ነገር አይወጣም፣ ከመጥፎ ተግባርም መልካም ውጤት አይገኝም። አውቀህና ፈልገህ እስካልገባህበት ድረስ ህሊናህ የእያንዳንዱን ነገር ትክክለኛነትና ስህተት መሆን በሚገባ ይነግርሃል። ጨላው በየት እንደሆነ፣ ብረሃኑም በየት እንደሆነ በሚገባ ይነግርሃል። ህሊናህን ማዳመጥ ያንተ ፋንታ ነው። ማሰብ እየቻልክ ከሚያስብ ሰው የማይጠበቅን የወረደ የጭፍን ጥላቻና የትምክህተኝነት አስተምህሮ የሚያስተላልፍ ሰው አትከተል። ተናጋሪ ሁሉ ትክክል አይደለም፤ ዝምተኛ ሁሉም ስህተት አይደለም። ማንም የፈለገውን ቢናገር ሰሚ አያጣም፣ ማንም ምንም ቢሰራ ተመልካች አያጣም። ምን እንደምትሰማ፣ ምን እንደምታይ በሚገባ አስበህ ወስን። ንፁ ሀሳብ እያለህ፣ ፅድት ያለ አቋም ኖሮህ የማንንም የቆሸሸና የረከሰ አስተሳሰብ ወደ ውስጥህ አታስገባ።


ለሰው አታሳዩ!
፨፨፨////፨፨፨
ህይወታችሁ ውስጥ ምን እየተካሔደ ነው? እናንተ ምን ደረጃ ላይ ናችሁ? ምን አግኝታችሁ ምን አጥታችኋል? የምትንሰፈሰፉለት ነገራችሁ ምንድነው? ሰው ባየልኝ ብላችሁ የምትመኙት ነገርስ ምንድነው? ምንም ላይ ድረሱ፣ ምንም አይነት ትልቅ ነገር አድርጉ፣ የትኛውንም አጓጉዊ ተግባር ፈፅሙ በፍፁም ለሰው አታሳዩ፣ እንዴትም ሰው እንዲያውቅ አታድርጉ። በህይወታችሁ ደስተኛ ናችሁ? ለሰው አታሳዩ፣ በህይወታችሁ ደስተኛ አይደላችሁም? ለሰው አታሳዩ፣ የምትፈልጉትን ነገር አግኝታችኋል? ለሰው አታሳዩ፣ በዛሬ ስኬታችሁ ትኮራላችሁ? ያፈራችሁት ንብረት ያስደስታችኋል? ያላችሁ ቤተሰብ ያሳሳችኋል? የትምህርት ደረጃችሁ በራስመተማመናችሁን ጨምሮታል? የሚያስቀና የፍቅር ወይም የትዳር ህይወት አላችሁ? ለሰው አታሳዩ። አስደሳችም ሆነ አሳዛኝ፣ አዎንታዊም ሆነ አሉታዊ ሁኔታ ውስጥ ብትሆኑ ለራሳችሁ ደህንነትና ውስጣዊ ሰላም ብላችሁ ሁኔታችሁን ለሰው አታሳዩ። ደስተኛ እንደሆናችሁ ለሰው ሁሉ ካላሳያችሁ ማን ደስታችሁን በሃዘን ይቀይረዋል? ሀዘናችሁን ለሰው ሁሉ ካላሳያችሁም ማን ድክመታችሁን ያውቃል? የሚያያችሁ ሰው ሁሉ ወዳጃችሁ እንደሆነ አታስቡ፣ በጊዜው ድርጊታችሁን የሚያደንቅ ሁሉ ከልቡ እንደሆነ አታስቡ።

አዎ! ለሰው አታሳዩ! ስኬታችሁን ለሰው አታሳዩ፣ ከፍታችሁን ለሰው አታሳዩ፣ ውድቀታችሁን፣ ስህተታችሁን፣ ድክመታችሁን ለሰው አታሳዩ። የእውነት መሻሻልና ማደግ ከፈለጋችሁ፣ የምር ከልብ የተረጋጋና ሰላማዊ ህይወት መኖር ከፈለጋችሁ በፍፁም ትልቅም ይሁን ትንንሽ ጉዳያችሁን ለሰው አታሳዩ። ሰው ስላየው ነገር ይጠይቃል፣ ያወቀውን ነገርም ይመረምራል፣ ከምርመራው ቦሃላ የራሱን የግል ፍርድ ይሰጣል። ብዙዎች በሚገባ የሚያውቁትን ትልቅ አጀንዳ ቤታቸው አስቀምጠው በጨረፍታ ስላዩትና ስለሰሙት የሰው ጉዳይ በመተንተን ጊዜያቸውን ያጠፋሉ። የተሸፈነ ነገር ይበስላል እንደሚባለው ህይወታችሁን ሸፈን ሸሸግ አድርጉት። ሁለመናችሁን አደባባይ አውጥታችሁ ነፃነት የሚባል ነገር እንደማይኖራችሁ እወቁ። "ሰው እንዲ ይለኛል፣ ሰው እንደዛ ይለኛል" ብላችሁ ከምትጨነቁ ገና ከጅምሩ ሰው የሚለውን ለማሳጣት ደበቅ ብላችሁ ኑሩ። ለአንድ ሰሞን ታይቶ መነጋገሪያ ሆኖ ማለፍ የሰው ምላስ ውስጥ ከመክተት ውጪ ምንም የሚጠቅማችሁ ነገር የለም። በአጉል ፉክክር ተወጥራችሁ ያላችሁን ነገር ሁሉ ለሰው ስላሳያችሁ የበለጣችሁ እንዳይመስላችሁ።

አዎ! ጀግናዬ..! አንተ ማን እንደሆንክ ታውቃለህ፣ ኬት እንደተነሳህ፣ አሁን የት እንዳለህ፣ ወዴት እንደምትሔድም በሚገባ ታውቃለህ። ስለራስህ ያለህ እውቀት ላንተ ይጠቅምሃል፣ ሌላ ሰው ግን ስላንተ ሁሉንም ነገር ማወቁ ለአንተም ሆነ ለሰውዬው የሚጠቅመው ነገር የለም። በቅርበት የሚያዩህ ሰዎች ያዩሃል፣ የሚያወቁህም ያውቁሃል። እይታና እውቀታቸው ግን በልክ ሊሆን ይገባል። ስራ መጀመረህን ዓለም ማወቅ የለበትም፣ ፍቅረኛ መያዝህን ወዳጅ ዘመዱ ሁሉ ማየት አይኖርበትም፣ ማግባትህ በየሚድያው መተላለፍ የለበትም፣ ቤት መኪና መግዛትህን የምታውቀው ሰው ሁሉ ማየት የለበትም። ያገኘሀው የትኛውም ነገር እንዲበረክትልህ ከፈለክ ከሰው አይን ሸሽገው፣ ትኩረት እንዳይበዛበት ዞር አድርገው። በለበስከው ውድ ልብስ ከመሰናከል ራስህን ጠብቅ፣ በገነባሀው ትልቅ ህንፃ ከመውደቅ ራስህን ጠብቅ። በሰው ፊት በንብረትህ ትለካለህ በፈጣሪህ ፊት ግን በልብህ ትለካለህ። የትኛው እንደሚበልጥ አንተ ታውቃለህ። ራስህን የመጠበቅ ግዴታ አለብህ፣ ራስህን ከምትጠብቅበት ዋና መንገድ ውስጥም አንደኛው ከሰው ተደብቆ በነፃነት መኖር ነው። ባንተ ዙሪያ የሚነሱ አጀንዳዎችን ቀንስ፣ የጫጫት መንስኤ ከመሆን ታቀብ፣ ዞር ብለህ ዓለምህ በደስታ ቅጭ።


በዝግጂት ንቁ!
፨፨፨/////፨፨፨
ጦርነት ውስጥ ናችሁ። ጦርነቱ ከራሳችሁና ከሌሎች ሰዎች ጋር ነው። ይህን ጦርነት የምታሸንፉበት አንድና አንድ መንገድ ብቻ አላችሁ። እርሱም ዝግጂት ይባላል። ከጦርነቱ በፊት ራስን ማሰልጠን፣ ራስ ላይ መስራት፣ የምታደርጉትንና የምትናገሩትን አስቀድማችሁ ማወቅ፣ ከሁኔታዎች የቀደመ ንቃትና ብርታን መላበስ። ከእኔ ይሻላሉ ብላችሁ የምታስቧቸውን ሰዎች ተመልከቱ። በምን በለጧችሁ? በምን ከእናንተ ተሻሉ? እነርሱ ሲበዛ ጠንቃቃና ለነገሮች ዝግጁ ናቸው። ሀሳብ ቢኖራቸው እንዴት ሊፈፅሙት እንደሚችሁ አስቀድመው ይመረምራሉ፣ ህልም ቢኖራቸው ህልማቸውን ደጋግመው ከመናገር በላይ ደጋግመው ለማድረግ ይዘጋጃሉ። አብዛኛው ሰው ሰው ፊት ሲቆም የሚያስበው ስለሚናገረው ነገር ወይም ስለሚያደርገው አይደለም፣ ይልቅ ሀሳብና ጭንቀት የሚሆንበት ከንግግሩና ከድርጊቱ ጀርባ የሚመጣበት ግብረመልስ ነው። ከዚህ በፊት የተበለጣችሁበትንና አንሳችሁ የተገኛችሁበትን ሁኔታ አስታውሱ፣ ምክንያታችሁን መርምሩ። በንቃትና በዝግጂት ማነስ ወደኋላ አትቅሩ።

አዎ! በዝግጂት ንቁ፣ ጦራችሁን አዝምቱ፣ ሁሌም ለአሸናፊነት የተዘጋጃችሁ ሁኑ። ሁሌም ራሳችሁን ለማስታመም አትሞክሩ፣ ሁሌም ደረጃችሁን ለማሳነስ አትጣሩ፣ ሁሌም በሃሳብና በጨንቀት ብቻ ጊዜያችሁን አታጥፉ። የምትፈልጉት ነገር አለ፣ ምኞት አላችሁ፣ ያስደስተኛል ብላችሁ የምታስቧቸው ነገሮች አሉ። ነገር ግን እስካሁን እንዴት በእጃችሁ እንደምታስገቧቸው ምንም እውቀቱ የላችሁም፣ ሲበዛ በጣም ቸልተኛ ሆናችሁባቸዋል፣ ከማሰብ ውጪ ምንም እርምጃ አልወሰዳችሁባቸውም። እጃችሁን የያዛችሁ ማነው? ንቃተ ህሊናችሁን የወሰደባችሁ ምንድነው? ተነሳሽነት ያሳጣችሁ፣ ስሜት አልባ ያደረጋችሁ፣ ሁሌም የሽንፈትን ፅዋ እንድትጎነጩ ያደረጋችሁ ነገር ምንድነው? ለደርጊት ዝግጁ አይደላችሁምን? ለጦርነቱ አልሰለጠናችሁምን? ሀሳባችሁን ለመኖር ብርታቱ የላችሁምን? ቅዱስ መፅሐፍ እንኳን ይሔን ይላል፦ ተዘጋጅታችሁ ኑሩ።" ዝግጁ ካልሆናችሁ ዓለም ታመልጣችኋለች፣ ዝግጁ ካልሆናችሁ ብቻችሁን ትቀራላችሁ። እያንዳንዱ ውሳኔዎቻችሁ ውጤት ይዘው ይመጣሉ፣ እያንዳንዱ ተግባሮቻችሁ የሚያደርሷችሁ መዳረሻ አላቸውና ተዘጋጁ።

አዎ! ጀግናዬ..! ባታስተውልም የሀሳብ ጦርነት ውስጥ ነህ፣ ትኩረት ባትሰጠውም ለውድቀት እየተዘጋጀህ ነው፣ አሁን ባይገባህ በቆምክበት ብዙ ነገር እያመለጠህ ነው። ተኩረትህ ሲበተን ዝም ብለህ ትመለከታለህን? በአንዴ በብዙ ነገር ስትወጠር አሁንም ዝም ብለህ ትመለከታለህ? ከየአቅጣጫው የሚረብሹህ ዜናዎች ሲመጡ ዝም ብለህ ትሰማለህን? በእርግጥም በነዚህ ሁኔታዎች ውስጥ ከሆንክ አዕምሮህን ሰብስበህ፣ ወደ ውስጥህ ተመልክተህ፣ ተረጋግተህ ትልቅ ነገር ለማድረግ በእጅጉ ትቸገራለህ። አንተን ብሎ የሚመጣ ነገር ሁሉ የሚጠቅምህ እንዳልሆነ ተገንዘብ። በተረበሸና በተመሰቃቀለ ከባቢ ውስጥ ለሚመጡልህ እድሎች ዝግጁ ሆነህ ልትኖር አትችልም። ጦርነቱን ተፋልመህ ማሸነፍ ከፈለክ ሌላ አማራጭ የለህም። ትኩረትህን የሚበትኑ ነገሮችን አስወግድ፣ ወደ አዕምሮህ የሚገቡ የማይረቡ ነገሮችን አስወግድ። ከባድ ቢሆንም ሁሌም ለተለየ ነገር ዝግጁ ሁን፣ ሁሌም ለከፋው ነገር ዝግጁ ሁን። የግልና የዓለም ጦርነትህን የምታሸንፍበት ብቸኛው መንገድ ሁሌም ንቁና ዝገጁ ስትሆን ብቻ እንደሆነ እወቅ።


ማንም አያቆመኝም!
፨፨፨፨/////////፨፨፨፨
ከእራስ ጋር ንግግር፦ "መሆን ያለበት ይሆናል፣ መገፋት በላብኝ እገፋለሁ፣ መተቸት ባለብኝ እተቻለሁ፣ በየጊዜው የሚዘባበትብኝ አይጠፋም፣ የግል ችግሬ ፋታ ነስቶኛል፣ ውጫዊ ጫናዎች በርትተውብኛል፣ በስራዬ ደስተኛ አይደለሁም፣ ውስጤ ምቾት ማግኘት አልቻለም ነገር ግን ምንም ቢከሰትብኝ ማንም አያቆመኝም። ገና በጠዋቱ ስጀምር ለምን እንደጀመርኩ አውቃለሁ፣ ገና ወደ ጥረት ስገባ ምን እንደሚጠብቀኝ አውቃለሁ፣ ወዴትም ጉዞ ስጀምር አስቀድሜ ከእራሴ ጋር ተማክሬያለሁ፣ መነሻዬ ለማቆም አይደለም፣ ልፋት ትጋቴ በቀላሉ ተስፋ ለመቁረጥ አይደለም። ማንም የማያቆመውን ማንነት በሂደት እየገነባው ነው፤ ይሉኝታ የማይሰብረውን፣ ስድብና ማሳነስ የማይሸረሽረውን ስብዕና እያቋቋምኩ ነው። ምንም እንኳን ጉዞዬ አልጋ በአልጋ ባይሆን፣ ምንም እንኳን በፈለኩት ጊዜ የፈለኩትን ውጤት ማግኘት ባልችልም፣ ምንም እንኳን ያልጠበኩት ውድቀት አደናቅፎ ቢጥለኝም ያሰብኩትን ከማሳካት ግን ምንም አይገታኝም።

አዎ! ማንም አያቆመኝም! እራሴን ማወቅ ባለብኝ ልክ ለማወቅ፣ ፍላጎቴን አንድ አቅጣጫ ማስያዝ ባለብኝ ፍጥነት ለማስያዝ እጥራለሁ። በአምላኩ ስጦታ የሚተማመን፣ በእራሱ ትጋት የሚያምን ማንነትን እየገነባው እገኛለሁ። የሚመጣ ሁሉ እንደሚሔድ አውቃለሁና፣ የተባልኩትን በሙሉ አይደለሁምና፣ ሃሳቤ ሁሉ እኔን አይደለምና ከአምላኬ ጋር በምንም እንደማልሸበር ለእራሴ ደጋግሜ እነግረዋለሁ። እኔን የሚታየኝ ለማንም አይታይም፣ የእኔ የልብ መሻት፣ የእኔ ፍላጎት የማንም የልብ መሻት፣ የማንም ፍላጎት አይደለም። ስለዚህ ለህልሜ እስከመጨረሻው እፋለማለሁ፤ ለመሻቴ መክፈል ያለብኝን ዋጋ ለመክፈል ሁሌም ዝግጁ ነኝ። እንደሚባለው ሁሉ "የማቆመው ሳሸንፍ ነው፤ ወደኋላ የምመለሰው ግቤን ስመታ ነው፤ ምላሽ የምሰጠው በስራዬ ብቻ ነው።" ይህን የማደርገው ለእራሴና ለሚያምኑብኝ ሁሉ ነው።"

አዎ! ጀግናዬ..! ለምንም ለማንም የማይበገር፣ ከስሙ በላይ የውስጥ ፍላጎቱ የሚያስጨንቀው፣ ከውጫዊ ትቺትና ነቀፋ በላይ የእርሱ ያለአላማ መኖር የሚያሳስበው፣ ከሚታየው ውጤት በተሻለ በማይታየው ውስጣዊ እድገትና ብስለት የሚያምን ማንም የማያቆመውን ማንነት መፍጠር ተለማመድ። ክብርን ፍለጋ ለማንም የምታጎበድድበት ምክንያት አይኖርም፤ በሌሎች ለመወደድ ብለህ የእራስህ ጠላት የምትሆንበት፣ አንቱታና ውዳሴን ለማግኘት ወሬ አድማቂ ሆነህ የምትቀርበት ምክንያት አይኖርም። ከጉዞህ ሊያደናቅፉህ ከሚያብሩብህ ሰዎች ጋር ምንም ህብረት የለህም፤ ያንተን ስኬት መመልከት ከማይፈልጉት ጋር ምንም አይነት ስምምነት አይኖርህም። ለእራስህ ካልሆንክ ለማንም እንደማትሆን አስታውስ። በምናብህ የምትታይህ የስኬት ጭላንጭል ከምንም በላይ ሃይል እንደሚኖራት እወቅ። ላልታየህ ነገር እንቅልፍ አጥተህ አታድርም፤ ያለምንም ምክንያት ያለማቋረጥ አትጥርም። የምታልመውን አይነት ህይወት መኖር ሳትጀምር በፍፁም እንዳታቆም፤ የታየህ ከፍታ ላይ ሳትደርስ በጭራሽ ወደኋላ እንዳትመለስ።


ስራህ ምንድነው?
፨፨፨/////////፨፨፨
ለዓመታት የፈራሀውን ተግባር በድፍርት ጀምረሃል፣ ውስጥህ የነበረውን ስጋት ቀስበቀስ ቀንሰሃል፣ መሰናክሎችህን በየጊዜው እየተጋፈጥክ አስወግደሃል፣ ለአላማህ እንደቀረብክ፣ ግብህን ለመምታት እንደተዘጋጀህ ውስጥህ ይነግርሃል። በስቃይህ ውስጥ ትርጉምን ትመለከታለህ፣ በመረጥከው ውጣውረድ ውስጥ ለውጥና እድገትህን ታስተውላለህ፣ ማን መሆንህን በጊዜ ሂደት ውስጥ ለእራስህና ለሌሎች ታስመለክታለህ። ሁለት ተመጣጣኝ ምርጫ አለህ፦ አንድም የእራስህ ደግፊ መሆን ወይም የእራስህ ነቃፊ መሆን። የሚበጅህን ልብህ ያውቀዋል፣ የሚያሻግርህን ውስጥህ በሚገባ ይረዳል። እራስህን ስትነቅፍ በየትኛውም ስራህ እንደማትደሰት ግልፅ ነው፤ እራስህን ስትደግፍ ግን በትንሿ እርምጃህ ትነቃቃለህ፣ በትንሿ እንቅስቃሴህ ውስጥህን ታበረታታለህ።

አዎ! ጀግናዬ..! ስራህ ምንድነው? ለእራስህ ብለህ ምን እያደረክ ነው? አሁን ያለህበትን ደረጃ ለማሻሻል ምን እየፈፀምክ፣ ምንስ እየከወንክ ነው? ለእራስህ ብለህ እራስህን እየወደድክ ወይስ ለሌሎች ብለህ እራስህን እየጠላህ? ለእራስህ ብለህ እራስህን እያበረታህ ወይስ ለሌሎች ብርታትና ንቃት ብለህ እራስህን እየጎዳህና እራስህን እየጣልክ? ስራህን የመምረጥ ሙሉ መብት እንዳለህ አስታውስ፣ ባሰኘህ መንገድ ያሰኘህ ስፍራ መድረስ እንደምትችል አስተውል። ጀምሮ የማቆም ምርጫ አለህ፣ በቀላሉ ተስፋ የመቁረጥ፣ የመጠራጠርና ህልምህን ችላ የማለት ምርጫ አለህ። በምትኩም መጠበቅ፣ ተስፋ ማድረግ፣ ማመን፣ የህልምህን እውንነት በጉጉት መጠባበቅን የዘወትር ተግባርህ አድርገህ ትርፋማ መሆን ትችላለህ።

አዎ! ሁሌም በሮች ለሚሰሩ ሰዎች ክፍት ናቸው፣ በተለይ ስራዬ ከሚሉት ነገር በላይ እራሳቸው ላይ ለሚሰሩት፣ እራሳቸው ላይ በየጊዜው ኢንቨስት (Invest) ለሚያደርጉት የውጤታማነት በር ክፍት ነው፤ የስኬት በር ክፍት ነው፤ የእደገት በር ክፍት ነው። በተስፋህ ብዛት የዛሬ መሰናክልህን ተሻገር፣ በፅናት ላመንክበት ጉዳይ እራስህን ስጥ፣ የወረደውን የአሁን ደረጃህን መመልከት አቁም፣ የአሁን ሁኔታህ የዘላለም እንደሆነ መቀበል አቁም። ባለህ ግበዓት የመጠቀምን ድፍረት ገንባ፣ ስራህን በአግባብ በስረዓት የመምረጥ ድፍረት ይኑርህ፣ ከባዱን የህይወት ጎዳና መሸሽ አቁም በምትኩ በከባዱና ተስፋ አስቆራጭ ጉዞ ውስጥ እራስህን ገንባ፣ የመረጥከውን ወሳኝ ተግባር በወጥነት ፈፅመው። ዓለምን ተፋለም፣ መጥፎ ልማድህን አሸንፍ፣ መልካሟን የህይወት ገፅህንም አጉልተህ አሳይ።


ከባዱን ተሻገር!
፨፨፨//////፨፨፨
ተሰብሮ መኖር ከባድ ነው፤ ይቅርታ አለማድረግ ከባድ ነው፤ ስራ ማጣት ከባድ ነው፤ ወገን ማጣት፣ ረዳት ማጣት እጅግ ከባድ ነው። ነገሮች እንዳሰቡት ሳይሆኑ ሲቀሩ፣ እቅዶች አልሳካ ሲሉ፣ መንገዶች ሁሉ ምቾት ሲያጡ፣ ሸክሞች ሲበዙ፣ ጫናዎች ሲያይሉ ተስፋ አስቆራጭ ከባድ የህይወት ከስተቶች ከፊታችን ይደቀናሉ። ለአመታት የለፋንበት ትምህርት በቀናት ወይም በወራት ውስጥ ፍሬ አፍርቶ መመልከት እንፈልጋለን። ለረጅም ጊዜ አብሮን የነበረ ሰው በአንዴ ሲለየን በቅፅበት ልንረሳው እንሞክራለን፤ የፈተናዎችን እድሜ ማሳጠር፣ ችግራችንን ወዲያው መቅረፍ የሁልጊዜ ምኞታችን ነው።

አዎ! የደስታ ሰዓታት ቢረዝሙ፣ የፈተና ጊዜያት ቢያጥሩ መልካም ነበር። ነገር ግን ከባዱም ቀላሉም ነገር የእራሱ ቀነ ገደብና የተመጠነ ጊዜ አለው። ገፍተህ ወይም ሸውደህ የምታልፈው የፈተና ወቅት የለም፤ ይዘህ የምታቆየውም የደስታ ጊዜ አይኖርም። እጅጉን በብዙ ጥበቃህን የፈተነ፣ እንቅልፍህን ያሳጠህ ነገር ካለ የትኩረት አቅጣጫህን ቀይረው፤ እርሱ ካለሆነ ብለህ በጥበቃ ብዛት ሰውነትህን አታዝለው። ብዙ አሻጋሪ አማራጭ መንገዶች እንዳሉ ተመልከት። ቀጥተኛ መንገድ ባለሙያ አሽከርካሪ እንደማይፈጥር ሁሉ የተስተካከለና የተመቻቸ አካሄድም ሊያጠነክርህና ሊያሻሽልህ እደማይችል አስብ።

አዎ! ጀግናዬ..! ከባዱን ተሻገር! በፅናት ተፋለመው፤ በትግስት ተጋፈጠው፤ እራስህን አበርታ። ከባድ መሆኑን እንደማይታለፍ አትቁጠረው፤ አስቸጋሪ መሆኑ እንደማያልፍ አይሰማህ። የማያልፍ የለም፤ የማይረሳ፣ የማይዘነጋ ጊዜ አይኖርም። አስጨናቂ ሰዓታት ይረዝማሉ ምክንያቱም ሙሉ ትኩረታችን ጉዳዩ ላይ ስለሆነ፤ አስደሳች ጊዜያት ያጥራሉ ምክንያቱም ቅፅበቷን ከማጣጣም ይልቅ የማለቂያዋን ጊዜ ስለምንጠብቅ። አንተ ጋር የመጣ ሁሉ የሚታለፍ፣ የሚረሳ ነውና በቶሎ እጅ አትስጥ፤ ለመሰበር አትጣደፍ፤ ካንተ የቀረ ከሌለ አምላክህ የሚያስብልህን ጠብቅ፤ የእርሱ ምርጫ እንደሚስማማህ አትጠራጠር፤ በፅናትና ትዕግስትህም ተማመን።


ጅል ሁን!
፨፨///፨፨
አንዳንዴ በጣም የሚገርም የጥበበኞች አስቂኝ ጨዋታ...
እንደ ጅል- ጅል ለመሆን ብልሃት ከትግስት ጋር ጥበብ ነው። በጣም የሚያስቀው ነገር፣ አንተን እያጃጃሉህ እንደሆነ ለሚስሉ ሰዎች ማጃጃላቸውን እንዳላወቀ ሆነህ ስታጃጅላቸው ለብቻህ ጊዜ ሳቅ።
አንዳንዴ- ሰዎች እንደተመቀኙህ አውቀህ ምቀኝነታቸውን እንዳላወቀ በወጥመዳቸው ሊያስገቡህ ሲቸኩሉ አምልጠህ ስታያቸው፣ የራሳቸው ወጥመድ አጥምዷቸው ስታይ ለብቻህ ጊዜ ሳቅ።

አንዳንዴ- የሚጠሉህ እንደሚውዱህ አይነት ሲተውኑ አጨብጭብላቸው። ለብቻህ ጊዜ ግን ሳቅ።
አንዳንዴ- በላይህ ላይ የደረበች ሴት እወድሃለሁ፣ ማሬ፣ ወተቴ ስኳሬ ስትልህ (ስታጃጅልህ) እንዳላወቀ የሁል ጊዜ ፈገግታህን አሳያት ከዛ የምታገባትን ታማኝ ሴት አስበህ። ለብቻህ ጊዜ ሳቅ።

አንዳንዴ- ሊያጭበረብሩህ የባጥ የቆጡን ለሚቀባጥሩ ነጋዴዎችን አሃ ብለህ እንዳላወቀ በትኩረት ስማቸው። ከዛም በልብህ እንደማትገዛቸው በማወቅ ደስ ይበልህ።
አንዳንዴ የምታውቀውን እንደማታውቅ እንደሚያውቅ አድርጎ የሚያወራ ሰው ሲያጋጥምህ እዋቀቱን እንዳላዋቂ አድንቅለት። ለብቻህ ጊዜ ግን ሳቅ።

አየህ አንዳንዴ ሁሉም ቦታ ላይ እንደባነንክ ማስባነን የለብህም። ለጅል እንደ ጅል የምትሆንበት የግድ ጊዜ አለ። አንዳንዴ ጠላትህ ጠላቱ እንደሆንክ ማወቅህን ካወቀ ደህንነትህ ስጋት ያጋጥመዋል። እስከ ጊዜው ለተዋናዮች ማጨብጨብና ለገጸባህሪያቸው መስታወት መሆን ያስፈልጋል።


ቀጥታ ከህይወት...!
፨፨፨፨፨///////፨፨፨፨
እራስህን አዘጋጅተህ፣ የሚያስፈልግህን አሟልተህ፣ በአካል፣ በጊዜ፣ በስነልቦና ብቁ ሆነህ መደበኛውን ትምህርት ትማራለህ። በእርግጥ ወደሀውና አምነህበት ከሆነ አስገራሚውን ተዓምር እንድትፈጥር ያልችልሃል፤ ነገር ግን በተቃራኒው ተገደህና ሳታምንበት የተማርከው እንደሆነ ጊዜህን የሚበላ፣ ውስጥህን የሚያውክ፣ የቁጪትህ መንስዔ ሆኖ ታገኘዋለህ። እውነታን ብትሸሸውም አታመልጠውም። ብዙ የትምህርት ዘርፍ ስለተማርክ፣ ትልቁን መዓረግ ስለተሸከምክ ብቻ ህይወትን አታሸንፍም። ህይወት የእድሜህን እኩሌታና ከዛ በላይ ከበላው ዲግሪ፣ ማስተርስና ፒኤችዲ በብዙ እጥፍ ትበልጣለች። መደበኛውን ትምህርት ብትማር በተወሰኑ ዘርፎች ባለሙያ ልትሆን ትችላለህ በተቀሩት ግን ከእውቀት የራክ አላዋቂ ትሆናለህ። በብዙ አቅጣጫ ያልተሳለና የእውቀት ዘርፉን ያላሰፋ ሰው ደግሞ ውስን አማራጭ ብቻ ይኖሩታል፣ ብቃቱ በተወሰኑ ዘርፎች ብቻ ይሆናል፣ እራሱን ይገድባል፣ የህይወት ዘመኑን በሙሉ አንድን ነገር ደጋግሞ በመስራት ያሳልፈዋል።

አዎ! ጀግናዬ..! ከአሰልቺ ህይወት ለመላቀቅ፣ እራስህን ለማሳደግ፣ የዘረፈ ብዙ ሙያ ባለቤት ለመሆን ቀጥታ ከህይወት ተማር፤ ቀጥታ ተግባራዊ የህይወት ዘርፎች ላይ ጠንክር፣ ከሚያጋጥሙህ እያንዳነዱ ተግዳሮቶች ትምህርትን ቅሰም። ከማንም የማታገኘውን እውቀት በተግባር ከህይወት ተማር፣ ማንም የማያስረዳህን የህይወት ሚስጥር እየኖርክ እወቅ፤ በሂደት ተረዳ። በመኖር ውስጥ ከምታሳልፋቸው ሁኔታዎች በላይ የስኬትህ ቁልፍ ሚስጥራት፣ የለውጥህ ወሳኝ ምክንያቶች አይኖሩም። ህይወት ስትገባህ እርምጃህ በእውቀት ይሆናል፣ ጉዞህ በብቃት ይከወናል። ከፊትህ የማይደፈር የሚመስል ትልቅ ገደል ቢኖርም እንዴት እንደምታለፈው በሚገባ ታውቃለህ።

አዎ! እየኖርክ ነውና ህይወት በየዘርፉ፣ በየአቅጣጫው ትፈትንሃለች፣ ወደ ትግሉ ሜዳ ትመራሃለች፣ ከተለያዩ ተጋጣሚዎችህም ታገናኝሃለች። አንተም ሁሌ በተሸናፊነት አትኖርም፣ ሁሌም እያማረርክ አትቀጥልም። ከሽንፈትህ ትማራለህ የምሬት ምክንያቶችህንም ትቀርፋለህ። ጥሩ ተማሪ ለማሸነፍ ጊዜ አይወስድበትም፤ ህይወትን የተረዳ ሰው እርምጃዎች ሁሉ ይቀሉታል፤ ከነገሮች በላይ የገዘፈ ማንነት ይኖረዋል፤ መራመድ ሲፈልግ ይራመዳል፣ መቆም ሲኖርበትም ይቆማል። ቻይነትን፣ አስተዋይነትን፣ ብርታትን፣ ጥንካሬን፣ ማስተዋልን ከህይወት ይማራል። ጠባሳውን የሚሽርበት፣ እራሱን የሚጠግንበት ብርቱ አቅም አለው። ከመሸሽ በላይ መጋፈጥን፣ ከመደበቅ በላይ ከፊት መውጣትን ይመርጣል። መማርህ ካልቀረ የህይወት ዘመን ትምህርት ተማር፣ ማወቅህ ካልቀረ የህይወት ሚስጥራትን እወቅ። የመረጥከውን ህይወትም በሙላት፣ በአግባብና በብቃት ኑር።


ፍላጎትህን አቃና!
፨፨፨////////፨፨፨
ቀላል ህይወት እንዲኖርህ ከፈለክ፣ ቀላል የህይወት መርህ ያስፈልግሃል። አንደኛውም መርህ ከሰዎች የምትጠብቀውን ነገር ይዳስሳል። ማንም መወደድን የሚጠላ፣ ተቀባይነትን የሚጠየፍ፣ መከበርን የሚገፋ ሰው የለም። ነገር ግን ፍላጎቱ ስህተት መሆን የሚጀምረው ያየው ሰው ሁሉ እንዲወደው፣ ስራውን የተመለከተው ሰው ሁሉ እንዲያደንቀው፣ የሰማው ሁሉ እንዲከተለው መፈለግ የጀመረ እለት ነው። ይህን መርህ ይዘህ ከህመም በቀር ምንም ልታተርፍ አትችልም። ምክንያቱም አንተ እራስህ የማትተገብረውን ነገር ከሰዎች እየጠበክ ነውና ነው። ማንም ብትሆን የእራስህ ስሜትና ፍላጎት አለህና ሁሉንም ሰው ልትወድ፣ ሁሉም ሰው የሚናገረውን ልታዳምጥ፣ የሁሉም ሰው አድናቂና ተከታይ ልትሆን አትችልም። የምትወደው ሰው እንደመኖሩ የማይመችህና ምርጫህ ያልሆነ ሰው አለ። ይህም በሰውነቱ ሳይሆን በተግባሩ ነው።  ስለዚህ ከፍላጎትህ ጋር የሚሄደውን፣ ለአላማህ የሚጠቅምህን፣ ንግግሩ ፍሬ ነገር የሚሰጥህን ሰው ትሰማለህ፣ ትወዳለህ፣ ትቀበላለህ ሌላውን ትተዋለህ።

አዎ! ጀግናዬ..! ፍላጎትህን አቃና! ምኞትህን ፈር አስይዝ፤ የህይወት መመሪያህን ከአቋምህ ጋር አስኪድ፤ ከተግባርህ ጋር አጣጥም። አንተ የማትፈፅመውን ተግባር ሌሎች እንዲፈፅሙልህ አትጠብቅ፤ እራስህ የማትሆንላቸውን ገፀባህሪ እነርሱ እንዲሆኑ አታስገድዳቸው። አንተ ስትፈልግ ቀላልና መደረግ ያለበት ግዴታ፣ ሌሎች ሲፈልጉ ደግሞ በፍላጎትህ ልክ በምርጫ የምታልፈው ነገር የለም። ከሌሎች የምትጠብቀውን ነገር ሌሎች ካንተ እንደሚጠብቁ ብታውቅ ምንያክል ልታደርግላቸው ዝግጁ እንደሆንክ እራስህን ጠይቅ። እራስህ ባስቀመጥከው ሚዛናዊ ያልሆነ መርህ አትሸነፍ፤ መልሶ አንተኑ በሚያጠቃህ አቋም እራስህ አትገድብ።

አዎ! ለደስታህ ሲባል መርሆችህ በሙሉ ደጋፊህና ከገሃዱ አለም እውነታ ጋር የሚሔዱ ሊሆኑ ይገባል። ሰዎች እንደማያደርጉልህ እያወክ ስለምን ደጋግመህ እነርሱን እየጠበክ እራስህን ትሰብራለህ? በፍላጎቶችህ ከደብ ማጣት ስለምን ለጭንቀትና ብሶት እራስህን ታጋልጣለህ? ከውጭ የምትፈልገው ነገር ቢኖር ቅድሚያ ውጥህ እንደሌለና ለእራስህ እንዳላደረክ እርግጠኛ ሁን። እግዚአብሔር ከሚሰጥህ፣ አምላክ ከሚያድልህ ነገር በቀር አንዱም ከሰዎች የሚመጣ ነገር አብሮህ አይቀርም። ውጫዊ መሻትህን ገድብ፤ ከእራስህ የምትጠብቀው ነገር ላይ አተኩር፤ መሬት ላይ ባለው ተጨባጭ እውነታ አንፃር ህይወትህን ቀለል አድርገህ ኑር።


አንዱን ብቻ አድርጉ!
፨፨፨፨////////፨፨፨፨
በሙዚቃው ዘርፍ ትልቁን አሻራ አሳርፎ ያለፈው Mozart በትኩረትና ብዙ ነገሮችን በቶሎ ስለማገባደድ የተናገረውን ንግግር ላንሳላችሁ። "ብዙ ነገሮችን የማከናወኛው አጭሩ መንገድ በአንድ ጊዜ አንድ ነገር ላይ በማተኮር ብቻ ማድረግ ነው።" ብዙ አማራጭ እንዳለን እያሰብን በኖርን ቁጥር በእራሳችንና በስራችን ከመተማመን በላይ ባሉን አማራጮች ላይ ይበልጥ እምነት ይኖረናል፤ አንዱ ነገር እንደሚሳካ ከማሰብ ይልቅ አንዱ ባይሳካ አንዱ ይሳካል እያልን እንዘናጋለን። የጀመርናቸው ብዙ የጀጨረስናቸው ግን ጥቂቶች ይሆናሉ። ብዙ ነገር በአንዴ ማድረግ ቢቻል ጥሩ ነበር ነገር ግን የምንሰራውን ስራ በጥራት ለመስራት ብቸኛውም ያለን አማራጭ በአንዴ አንድ ነገር ብቻ ማድረግ ነው።

አዎ! በየቦታው እራስን በትኖ፣ ብዙ ነገር ላይ አተኩሮ፣ ይህንንም ያንንም ጀምሮ የትኛውንም ስራ በጥራትና በፍጥነት ማጠናቀቅ አይቻልምና በሰዓቱ ወሳኙንና በጣም አስፈላጊውን አንዱን ብቻ አድርጉ። ለእራሳችሁና ለቤተሰባችሁ እንኳን ጊዜ እስክታጡ ድረስ እራሳችሁን Busy ከማድረጋችሁ በፊት የምርም ትርፍ ላለውና ህይወታችሁ ላይ እሴት ለሚጨምር ነገር በየአቅጣጫው እየባከናችሁ እንደሆነ እርግጠኛ ሁኑ። አሁን እጃችሁ ላይ ብዙ ስራ ካለባችሁና ሁሉንም በተመሳሳይ ሰዓት ጨርሳችሁ ለማለፍ እየሞከራችሁ ከሆነ ቅድመተከተለ አስቀምጡና ዋናውን ስራችሁን አስቀድማችሁ አገባዱ። ቢቻልና በአንዴ በሁሉም ዘርፍ ስኬትንና አንቱታን ማግኘት የሚጠላ ሰው የለም። ነገር ግን አዕምሯችን በአንዴ ማተኮር የሚችለው አንድ ነገር ላይ ነውና አንዱን ስትጨርሱ ሌላውን የመጀመር ልማድን አዳብሩ።

አዎ! ጀግናዬ..! ፈለክም አልፈለክም፣ ጠበከውም አልጠበከውም ትኩረትህን የሚወስድ፣ ውስጥህን የሚረብኝ፣ መረጋጋት የሚነሳህ ሃሳብም ሆነ ተግባር በየትኛውም ሰዓት ሊመጣብህ ይችላል። የአፈፃፀም ደረጃህና የስራህ ጥራትም የሚፈተነው በዚህ ሰዓት ነው። አንድ አስፈላጊ ነገር በጀመርክ ቅፅበት ሌሎች አስፈላጊ ነገሮችም እንዳሉ ሊታዩህ ይችላሉ፣ የታየህን ሁሉ ለማድረግ ስትጥርም አንዱንም በስረዓት ሳታደርገው ጊዜና አቅምህን ትጨርሳለህ። በሰዓቱ መስራት ያለብህን አንድ ነገር ስራ፤ በጣም አንገብጋቢ ለሆነው ጉዳይ ትኩረት ስጥ። ብዙ ነገሮችን በአጭር ጊዜ ማገባደጃው ብቸኛ መንገድ በአንዴ አንድ ነገርን ብቻ ማድረግ እንደሆነ ተረዳ።


ህመሙን ተቀበሉት!
፨፨፨፨////////፨፨፨፨
የትኛውም ውሳኔ የራሱ ተመጣጣኝ ዋጋ አለው፤ የትኛውም ተግባር የራሱ ግብረመልስ፣ የራሱ ውጤት አለው። ለውሳኔያችሁ መታመን፣ ተግባራችሁን እስከመጨረሻው ማስኬድ፣ ጥረታችሁንም መቀጠል አምናችሁ መቀበል ላለባችሁ ህመም ያጋልጣችኋል። ህመሙን እንደ ጥፋት፣ ስቃዩንም እንደ ቅጣት የምትመለከቱ ከሆነ ግን ዳግም አዲስ ውሳኔ መወሰንና እንደገና አዲስ ተግባር የመሞከር ድፍረት እያጣችሁ ትመጣላችሁ። የምትችሉት አንድ ነገር ነው፦ ጥፋቱን ሳይሆን ህመሙን መቀበል፣ ውጣውረዱን እንደ ቅጣት ሳይሆነ ነገ ውጤት ሊያመጣ እንደሚችል ግበዓት መውሰድ። የሞከራችሁት ነገር በሙሉ ባልተሳካ ቁጥር እራሳችሁን ጥፋተኛ ማድረግ ተነሳሽነታችሁን እየገደለ፣ አቅማችሁን እያሳነሰና ዋጋ እያሳጣችሁ እንደሚመጣ አስተውሉ።

አዎ! ጥፋቱን ተውት ህመሙን ተቀበሉት! የሚያሳድጋችሁን ህመም፣ የሚቀይራችሁን ህመም፣ ደረጃችሁን የሚጨምረውን ህመም ተቀሉት። ሃሳባችሁ ትልቅ ሲሆን ህመማችሁም ትልቅ ይሆናል፣ ተግባራችሁ ፈታኝ ሲሆን ጥረታችሁና ድካማችሁም እንዲሁ ፈታኝ ይሆናል። በጥረታችሁ መሃል የምታጠፉትን ጥፋት፣ የሚያጋጥማችሁን ውድቀት፣ የሚደርስባችሁን ጫና፣ የምታጡትን ሰውና የምትከስሩትን ገንዘብ እንደመማሪያ እንጂ እንደ ሌላ የስጋት ምንጭ አትውሰዱት። ምንጊዜም የጥፋተኝነት ስሜት እስረኛ ያደርጋችኋል፤ በስህተታችሁ በተፀፀታችሁ ቁጥር ወደፊት መጓዝ ያቅታችኋል፣ ሃሳባችሁ እንዲሁ ያስፈራችኋል፣ ምኞታችሁ ከንቱ ሆኖ ይቀራል፣ የራሳችሁ እንቅፋት እራሳችሁ ትሆናላችሁ፣ ሳታውቁት ለዘመናት በተመሳሳይ አስተሳሰብ ተመሳሳይ ስፍራ እራሳችሁን ታገኙታላችሁ።

አዎ! ጀግናዬ..! ጥፋቱ እንደጥፋት፣ ስህተቱም እንደስህተት ይቀመጥ፣ ይልቅ ከጥፋቱ ቦሃላ ከደረሰብህ ህመም፣ ከስህተቱ ቦሃላ ካጋጠመህ ስቃይ በሚገባ ተማር። ትሞክራለህ ትሳሳታለህ፣ አዲስ ነገር ትጀምራለህ ታጠፋለህ፣ ነገር ግን በሂደቱ ውስጥ መማር ከቻልክ ነገሮች ሁሉ የማይቀየሩበት ምክንያት አይኖርም። በህመም ውስጥ ተምሮ መውጣት፣ በስቃይ መሃል እራስን ፈልጎ ማግኘት መቻል የትልቁ አላማህ አካል መሆን ይኖርበታል። ስቃይ የመኖር እጣፋንታ ነው፣ ህመም የህይወት አንድ አካል ነው። ነገር ግን ለምን እየተሰቃየህ ነው? ለምን ብለህ እየታመምክ፣ ዋጋ እየከፈልክ ነው? የሰዎችን ኢምፓየር ለመገንባት ወይስ የእራስህን ለመመስረት፣ ሰዎችን ለማበልፀግ ወይስ እራስህን ከእስር ነፃ ለማውጣት? ምክንያትህን በሚገባ እወቀው፣ ባወከው ልክ ለላቀቀው ህመም እራስህን አዘጋጅ፣ ሁሌም ከርሱ ተማር፣ እራስህንም አብቃበት።


በርታ በል!
፨፨////፨፨
መድሃኒት ቀማሚው ለመድሃኒትነት የሚያገለግሉትን ግብዓቶች ፍለጋ ወደ ጫካ ይገባል፤ አትክልቶችንም ያስሳል። አሰሳው መድሃኒት ለመቀመምና ታካሚውን ከህመሙ ለማዳን እንዲሁም ለማሳረፍ ነው። ጥረቱ ግን አልጋ በአልጋ አልነበረም፤ የሚያገኛቸው ቅጠሎች ሁሉ ለፈለገው መድሃኒት የሚሆኑ አልነበሩም ነገር ግን ትከክለኛውን ቅጠልና ሌሎች ግብዓቶችን ፍለጋ ማሰሱን አላቆመም። ጥረቱም መና እንዳይቀር፣ ታካሚውም እንዲፈወስ የሚጠበቅበትን ሁሉ ለማድረግ እራሱን በይበልጥ አዘጋጅቶ ጥረቱን ቀጥሏል። በእርሱ ድካም ታካሚው ቢያመልጠው ቁጪትና ፀፀቱ የህይወት ዘመን ቁስሉ ነው። ነገር ግን ስለበረታ የታካሚውን ህይወት መታደግ ቻለ። አንተም ሁሌም ደስተኛ ላትሆን ትችላለህ፣ ህይወት ፊቷን ልታዞርብህ እድልም ጀርባ ልትሰጥህ ትችላለች፣ ቀኑ ሰጨልምብህ ተስፋ ለመቁረጥ ልታቀርብህም ትችላለች። ነገር ግን ካደረካቸው በላይ ባላደረካቸው እየተቆጨህና እየታመምክ ከምትኖር አሁን በርታ በል። የምታየው ሁሉ የሚያነቃህ፣ የምትሰማው ሁሉ የሚያበረታታህ፣ የምትሰራው ሁሉ ለውጤት የሚያበቃህ ላይሆን ይችላል። አንተ በፈለከው ጉጉት ልክ ብዙዎች አይሳኩም፤ መንገድህ አይቀናም፤  ሃሳብህ አይሞላም። ካልጠነከርክ ግን ሁሉም ያበቃል።

አዎ! ጀግናዬ..! በርታ በል! በመኖርህ የምታዝን ሳትሆን ስላለህ ብቻ፣ አምላክህ ፊት በመቆምህ ብቻ ህያዊት ነፍስህን በተስፋ የምትሞላ ሁን። ጠንካራ ነህና ቀላል ነገር አይሰብርህም፤ ብርቱ ነህና በጥቃቅን ክፍተት ተስፋ አትቆርጥም። ከባዱ ሊሰብርህ ቢመጣም እንዳትበገር፤ እጅህን ለመስጠት አትፋጠን። ተስፋህ ውስጥ ገና ያልኖርከው፣ ያላጣጣምከው፣ ያልተነካ ሙሉ ህይወት አለ። በእራሰህ አዝነህ ተስፋ ስላጣህ ከምንም የከፋውን ምንም ሳታገኝ ምንም ታጣለህ፤ እራስህን ትጥላለህ፤ በእራስህ ትከፋለህ፤ መልካሟን የህይወት ገፅም ወደ ክፉ፣ አስደሳቿንም ወደ አሳዛኝ ትቀይራታለህ። ያለፈው ጊዜ ቢያሳምምህ፣ ቢያሰቃይህ፣ ቢያቆስልህም ከበረታህ ከአሁን ጀምሮ ያለው ጊዜ ግን ይጠግንሃል፤ ያክምሃል፤ ያሳርፍሃል።

አዎ! ደጋግመህ በእራስህ ከማዘን ተቆጠብ፤ በእራስህ ከመጨከን ተመለስ። የማይደክም፣ የማይዝል፣ የማይታመም ሰው የለም። ሲስቅ የምታየው ሁሉ የሚያለቅስበት ጊዜ ነበር፤ ሲደሰት የተመለከትከው ሁሉ በህይወት አጋጣሚ ለአሳዛኝ ክስተት የሚጋለጥበት ጊዜ ይኖረዋል። ኑሮ ስለከበደህ ህይወትህን እንደ እርግማን አትቁጠራት፤ ችግር ስለተደራረበብህ በብሶት አንገትህን አትድፋ። የጨለመችው ጀንበር ጎህ ለምትቀደው ብረሃን ቦታ የምትለቅበት ጊዜ ይመጣል፤ መቼም ጨልሞ አይቀርም። የምታምነው አምላክ ሁሌም ከጎንህ ነውና መቼም ብቻህን እንደሆንክ አይሰማህ። ከተሰባሪው ሰው በላይ በማይበገረው ፅኑ ድጋፍህ በሆነው በፈጣሪህ ተማመን። በምክንያት የሆኑት ሁሉ በምክንያት ያልፋሉ፤ ያስደመመህን ለውጥ በሰዎች ላይ እንዳየሀው አትቀርም፤ ከበረታህ፣ በተስፋ ከተሞላህ፣ ካመንክ፣ በእምነትህ ልክ ከጣርክ ያለጥርጥር ያንን ለውጥ በአንተም ህይወት ሲከሰት ትመለከተዋለህ።


ቀላሉን እርሱት!
፨፨፨//////፨፨፨
ስለ ቀላሉ ገንዘብ መስሪያ መንገድ ብዙ ሲባል ሰምታችኋል፣ ስለ ቀላሉ ስራ ብዙ ተብላችኋል፣ ስለ አቋራጩ ሃብት ማከማቻ መንገድ፣ ስለ ተለመደው የቁማር ጫወታ ከብዙም ብዙ ሰምታችኋል፣ ከመስማትም በላይ ደጋግማችሁ ሞክራችሁታል። ነገር ግን ምን አገኛችሁ? እድሜን ከማባከን፣ ስሜትን ከመረበሽና እንቅልፍን ከማጣት በቀር ምን አተረፋችሁ? ምንም። ሁሌም የሰነፎች መገለጫ አቋራጭ መንገድ ነው፤ ሌቦች አምታተው ማትረፍ የሚፈልጉ ናቸው። ለማንም ያልሰራውን መስጠት እንደማትፈልጉ ሁሉ ባልሰራችሁትም ለመሸለም አትሯሯጡ። ቀላሉን መምረጥ ቀላል እንደሚያደርጋችሁ አስታውሱ፣ አቋራጩን መምረጥ ብኩን እንደሚያደርጋችሁ ተረዱ። ለሰነፎች ቦታ የማትሰጥ፣ በቀላሉ የማታበለፅግ፣ በአጭሩም ትርፋማ የማታደርግ ዓለም ላይ እንደምትኖሩ እወቁ።

አዎ! ቀላሉን እርሱት፣ አቋራጩን አቁሙ፣ ማምታታቱ ይቅርባችሁ፣ እራሳችሁም አትወናበዱ። ሰው ያደረገውን ማድረግ ትችላላችሁና ለከባዱ ፈተና እራሳችሁን አዘጋጁ፣ ውስብስቡን ለማለፍ፣ ከባዱን ለመጋፈጥ፣ ፍረሃታችሁን ለማሸነፍ፣ የወደፊት ህይወታችሁን ለማስተካከል፣ ልባችሁን ለማሳረፍ፣ እራሳችሁን ከድህነት ወለል ነፃ ለማውጣት መንፈሳችሁን አጠንክሩ፣ ስሜታችሁን አድሱ፣ ወኔያችሁን አነሳሱ። ከማንም ሳታንሱ ከማንም ያነሰ ህይወት ለመኖር አትንደርደሩ። ማንም ብትሆኑ ያለማቋረጥ የምትሰሩት ስራ የማይከፍላችሁ መንገድ አይኖርም። ተፈጥሮ የምትመራው በአንድ ህግ ብቻ ነው። "ከባዱ ምርጫ ከባድ ባለድል ያደርጋል፣ ቀላሉምርጫ ልፍስፍስ ደካማ ያደርጋል።" ከህጉ ዝንፍ ማለት ለህይወት ዘመን ከባድ ፀፀት ይዳርጋል።

አዎ! ጀግናዬ..! ቀላሉን ማሳደድ አቁመ እራስህን ፈትነው፣ እያወክ ዋጋ አስከፍለው፣ አቀርቅሮ አሰንዲሰራ አድርገው፣ ሳያቋርጥ እንዲተጋ አድርገው። ሰው የሚጠቁምህን ቀላል ስራ ሁሉ አትመን፣ የተባልከውን ሁሉ በመጀመር ጊዜ አታጥፋ። ዋጋህ የሚጨምረው ልክ እንደብረቱ በእሳት ስትፈተን እንደሆነ አስታውስ። አጭሯን እድሜ በልፍስፍሶች መንገድ እየተጓዝክ ይበልጥ አታሳጥራት፣ ውዷን ህይወትህን ትርጉም በማይሰጡ ጥቃቅን ተግባራት እርባና ቢስ አታድርጋት። ጨከን በል፣ ፈተና ያለውን ምርጫ በልበሙሉነት ምረጥ፣ ላሰኘህ ሳይሆን ለሚጠቅምህ፣ ለቀለለህ ሳይሆን ከብዶ ለሚያከብድህ እራስህን አሳልፈህ ስጥ። ጠንክረህ ተፋለም፣ እስከመጨረሻው ታገል፣ መቼም ተስፋህን አትጣ፣ ለከባዱ የህይወት ምርጫም የሚመጥን ማንነትን ገንባ።


ጨለማው አብቅቷል!
፨፨፨፨/////////፨፨፨፨
አዎ! ጠለማው አብቅቷል እናም ድጋሜ አይመለስም፣ አሳፋሪው ወቅት፣ አስፈሪው ጊዜ አልፏል እናም ድጋሜ አትመለከተውም። ከልክ በላይ ማሰብ፣ ለሚሆነውም ለማይሆነውም መጨነቅ፣ በየትኛውም ስፍራ አቀርቅሮ መጓዝ፣ ለከባዱ የህይወት አጋጣሚ አስቀድሞ መንበርከክ፣ ሰዎች ባስቀመጡት ክብ ደጋግሞ መመላለስ፣ በራስ አለመተማመን፣ በራስ ማፈር፣ እራስን ማሸማቀቅና ማጎሳቆል ሁሉ አብቅቷል። ለእራስህ የምትኖርበት ጊዜ መጥቷል፣ እራስህን የምታኮራበት፣ ከጨለማው አስተሳሰብ፣ ከውድቀት አቋም እራስህን ነፃ የምታወጣበት ጊዜ አሁን ነው። ብዙዎች ስለወደፊት ያወራሉ፣ ብዙዎች በትናንትናቸው ታስረዋል አንተ ግን ዛሬ አሁን የውሳኔ ሰው ሆነህ ተገኝ፣ ዛሬውኑ ህይወትህን ወደመቀየር ተሸጋገር። ለራስህ የገባሃቸው መሰረተ ቢስ ቃላቶች፣ የሚገባህን ህይወት መኖር ያልቻልክበት ጊዜ እንዲያበቃ አድርግ።

አዎ! ጀግናዬ..! ጨለማው አብቅቷል፣ የብረሃን መንገድ ተጀምሯል፤ የኋሊቱ ጉዞ ቆሟል ወደፊት መራመድ ጀምረሃል፤ በራስ ማዘን አብቅቷል በማንነት መኩራት ተጀምሯል። ማስመሳል፣ እራስን ማታለል፣ ለታይታ መኖር ለእይታ መመላለስ፣ እራስን በየአቅጣጫው ማድከም፣ ህይወትን ማክበድ ቀርቷል። ብዙዎች እውነታን መጋፈጥ ይፈራሉ፣ ብዙዎች ሪስክ መውሰድ ይፈራሉ፣ ብዙዎች በስንፍና ታስረዋል፣ በእምነት ማጣት በጥርጣሬያቸው እየተበዘበዙ ነው፣ ብዙዎች ከተግባር በራቀ ሃሳብ፣ እርምጃ ባልተወሰደበት ህልም፣ ከዛሬ ነገ ተንከባሎ በመጣ እቅድ በጭንቀት ይኖራሉ። ከብዙዎቹ አንዱ እንደሆንክ ከተሰማህ እርምጃ የምትወስደው እንደለመድከው በሃሳብ ወይም በእቅድ ወይም በወሬ ሳይሆን በተግባር እንደሆነ አስታውስ።

አዎ! ህይወት ለማን ቀላል ሆና ታውቃለች? ኑሮ ለማን አልጋባልጋ ሆኖ ያውቃል? ለማንም። ማንም ህይወቱን ወዶ ተመችቶት ለመኖር የግድ ማድረግ ያለበት ነገር ይኖራል። በተመሳሳይ የለውጥ አመለካከት፣ በተለመደው የህይወት መረዳት፣ በአንዳይነት የግል አቋም አንዳች የሚፈጠር ነገር የለም። የጨለማው ዘመን ያበቃ ዘንድ ህልምህን መሞከር ይኖርብሃል፣ ከቀደመው ችግር ለመውጣት አዲስ አደጋን መጋፈጥ የግድ ነው፣ ትናንትህን ለማደስ ዛሬ እንቅስቃሴ መጀመር ይጠበቅብሃል። ያለ ተግባር የሚገፈፍ ጨለማ፣ ያለጥረትም የሚመጣ ለውጥ የለም። የምርም ህይወትህን ከወደድከው ይበልጥ ትደሰትበት ዘንድ በምትፈልገው መንገድ መቀየር ይኖርብሃል። ቀስበቀስ ነገር ግን በእርግጥም ነገሮችን ትቀይራለህ፣ በሂደት ነገር ግን የምርም የምትመኘውን ህይወት መኖር ትጀምራለህ። በተስፋህ ተማመን በከባዱ መንገድም ህይወትህን አሻሽል።

Показано 20 последних публикаций.