Фильтр публикаций


ወቅታዊ እና እውነተኛ የመረጃ እጦት ለጋጠማችሁ፣ የቱን ልመን? ብላችሁ ለተወዛገባችሁ፣ እነሆ ሀገራዊ እና አለማቀፋዊ መረጃዎችን ካሉበት አጣርቶና ፈልፍሎ ልምድ ባላቸው ጋዜጠኞች የሚያቀርብ ቻናል ልጠቁማችሁ።

መረጃዎቹ ለየት ያሉ ፈጣን እና እውነተኛ ናቸው።👌""በዚህ ሊንክ ግቡ
👇👇👇
https://t.me/+MGwLfqRVgDsyNGM0
https://t.me/+MGwLfqRVgDsyNGM0
https://t.me/+MGwLfqRVgDsyNGM0


ዳሎል አካባቢ በሬክተር ስኬል 5 ነጥብ 3 የሆነ የመሬት መንቀጥቀጥ ተከሰተ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 24፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በአፋር ክልል ኪልበቲ ዞን ዳሎል ወረዳ ዓዶኩዋ ከተማ አቅራቢያ በሬክተር ስኬል 5 ነጥብ 3 የሆነ የመሬት መንቀጥቀጥ መከሰቱን የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ አስታውቋል።

በዩኒቨርሲቲው የጂኦፊዚክስ፣ ስፔስ ሳይንስና አስትሮኖሚ ተቋም ዳይሬክተር ኤሊያስ ሌዊ (ዶ/ር) ለፋና ዲጂታል እንዳሉት÷ርዕደ መሬቱ ከዓዶኩዋ ከተማ 5 ኪሎ ሜትር በስተደቡብ አቅጣጫ ነው የተከሰተው፡፡

የመሬት መንቀጥቀጡ በትናንትናው ዕለት ቀን 5 ሰዓት 14 ደቂቃ ከ59 ሰከንድ ላይ መከሰቱን ተናግረዋል፡፡

በተጨማሪም በአፋር ክልል ኮናባ ወረዳ ከትናንት በስቲያ በሬክተር ስኬል የተለያየ መጠን ያለው ርዕደ መሬት መከሰቱን አመልክተዋል፡፡

በአካባቢው የተከሰተው ርዕደ መሬት በመኖሪያ ቤቶች እና መሰረተ ልማት ላይ ጉዳት ማድረሱ ነው የተገለጸው፡፡

ሕብረተሰቡ ርዕደ መሬት ጋር ተያይዞ ከክስተቱ በፊት፣ በክስተቱ ጊዜና ከክስተቱ በኃላ ሊወሰዱ የሚገቡ የጥንቃቄ ርምጃዎችን መተግበር እንዳለበት ኤሊያስ ሌዊ (ዶ/ር) አሳስበዋል፡፡

በመላኩ ገድፍ


በሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ላይ ተጥሎ የነበረው እገዳ ተነሳ

የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን “ህግን ተላልፈው ተገኝተዋል” በሚል በሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ላይ ጥሎት የነበረውን የእግድ እርምጃ’፤ “ማስጠንቀቂያ” በመስጠት ከዛሬ ጀምሮ ማንሳቱን አስታወቀ። ባለስልጣኑ እገዳውን ያነሳው፤ ከታገዱት ድርጅቶች ጋር ባደረገው ውይይት “በተፈጠረ መግባባት” እና የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ኮሚሽን ያቀረበውን ምክረ ሃሳብ ከግምት ውስጥ በማስገባት እንደሆነ አስታውቋል።

ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ የዛሬውን ውሳኔ ያስተላለፈው “በታገዱት ሁሉም ድርጅቶች” ላይ መሆኑን ዛሬ ሰኞ የካቲት 24፤ 2017 ባወጣው ጋዜጣዊ መግለጫ አስታውቋል። ተቆጣጣሪ መስሪያ ቤቱ ባለፈው መንፈቅ ዓመት ብቻ በሰባት ድርጅቶች ላይ የእግድ ውሳኔ ማስተላለፉን ባለፈው ጥር ወር መጨረሻ በፓርላማ በተካሄደው የቋሚ ኮሚቴ ስብሰባ ላይ መግለጹ ይታወሳል።

በዚሁ ጊዜ ውስጥ ከታገዱት መካከል አራቱ የሰብአዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች ናቸው። “ከተቋቋሙበት ዓላማ ውጭ ተንቀሳቅሰዋል” በሚል ባለፈው ታህሳስ ወር አጋማሽ የታገዱት እነዚህ ድርጅቶች፤ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ጉባኤ (ኢሰመጉ)፣ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ተሟጋቾች ማዕከል (EHRDC)፣ የመብቶች እና ዴሞክራሲ ዕድገት ማዕከል (CARD) እና የሕግ ባለሙያዎች ለሰብአዊ መብቶች (LHR) ናቸው። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር)

[በዚህ ዘገባ ላይ ተጨማሪ መረጃ ይታከልበታል]


ከአዲግራት ከተማ አቅራቢያ በሬክተር ስኬል 5.2 የተለካ ርዕደ መሬት ተከሰተ

ዛሬ እሁድ ከአዲግራት ከተማ 46 ኪሎ ሜትር በስተምስራቅ ርቀት ላይ በሚገኝ አካባቢ ላይ በሬክተር ስኬል 5.2 የተለካ የመሬት መንቀጥቀጥ መከሰቱን የአሜሪካ የጂኦሎጂካል ሰርቬይ መስሪያ ቤት ገለጸ። ርዕደ መሬቱ የተከሰተው ከቀኑ 5 ሰዓት ከ14 ደቂቃ ላይ መሆኑንም መስሪያ ቤቱ አስታውቋል።

በኢትዮጵያ ካለፈው መስከረም ወር ጀምሮ ተደጋጋሚ የመሬት መንቀጥቀጥ ቢከሰትም፤ በትግራይ ክልል ባሉ ከተሞች አቅራቢያ ርዕደ መሬት ሲመዘገብ ግን በዚህ ዓመት የመጀመሪያው ነው። የዛሬው የመሬት መንቀጥቀጥ በኢትዮጵያ እና ኤርትራ ድንበር ቀጠና የተከሰተ መሆኑን የጠቆመው የአውሮፓ ሜዲትራንያን ሴይስሞሎጂ ማዕከል (EMSC)፤ መጠኑም በሬክተር ስኬል 5.3 የተለካ እንደሆነ አስታውቋል።

በኤርትራ ከአንድ ሳምንት በፊት የደረሰ ርዕደ መሬት በሬክተር ስኬል 4.6 ሆኖ ተመዝግቧል። የመሬት መንቀጥቀጡ የተከሰተው በቀይ ባህር ሰሜናዊ አቅጣጫ ከአስመራ 24 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ባለ አካባቢ ነበር። በሀገሪቱ ባለፈው ታህሳስ ወር አጋማሽም እንዲሁ ተመሳሳይ ርዕደ መሬት ተመዝግቧል።

በሐምሌ 2015 ዓ.ም. በኤርትራ ባህር ዳርቻ ዳህላክ ደሴት አካባቢ የተከሰተው የመሬት መንቀጥቀጥ፤ በትግራይ ክልል የተለያዩ ከተሞች ተደጋጋሚ ንዝረቶች አስከትሎ እንደነበር ይታወሳል። ንዝረቱን በሽሬ፣ አዲግራት፣ አድዋ፣ አክሱም እና መቐለ ከተማ ያሉ ነዋሪዎች መስማታቸውን በወቅቱ ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ገልጸው ነበር። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር)


🌾 ለሶፋ እድሳት ሁነኛ ምርጫዎ ነን🌴

ከውጭ የገቡ ሶፋዎችን ፈረንጆቹ በሰሩበት ማሽኖች እና ሙያዊ ብቃት እንደነበሩ አድርገን መልሰን እናድሳለን 👌

🌻 በውድ የገዙት ሶፋዎት በከፍተኛ ጥራት በማደስ ወደ ቀድሞ አዲስነቱ በመመለስ እናስደንቆታለን

🌻 የ11 አመታት የሶፋ እድሳት የስራ ልምዳችን ጥንቅቅ ያለ ስራ እንድንሰራ አስችሎናል

🌻 የሀገር ውስጥ ሶፋዎችንም ከተለመደው ከፍ ባለ ጥራት ማሳደስ ለምትፈልጉም በራችን ክፍት ነው

🌻 በሀገራችን አሉ የተባሉ ስማቸው ገናና የሆኑ ፈርኒቸር ወይ ሶፋ አምራቾች የሚጠቀሙባቸውን ማሽኖች ይዘን የእድሳት ስራ እንደምንሰራ የሚያውቁ ደንበኞች የዘውትር ምርጫቸው ነን

🌻 ዋጋችን ተመጣጣኝ የስራ ጥራታች ከፍተኛ ነው።

🌻 በአቅራቢያችን ላሉ ሰዎች እንደ ሶፋው የቤት ለቤት እድሳት አገልግሎት ልንሰጥ እንችላለን።

🌻አዳዲስ ሶፋ በፈለጉት ዲዛይን እና በቤትዎ ልክ እንሰራልዎታለን።

🌻የተንጣለለ ወርክሾፖችንን እና ለእድሳት ስራ የምንጠቀማቸውን ማሽኖች መጥተው ይጎብኙ።
አድራሻችን ጃክሮስ ሜታ አካባቢ ለበለጠ መረጃ
0921317125
0938300946
ላይ ይደውሉልን
ድረገፃችንን ይጎብኙ 👇

https://smartsofasolution.com


በትናንትናው ዕለት በ21/06/2017 ከጎንደር ወደ አዲስ ዘመን መስመር ይጓዙ የነበሩ ኤክስፖርት ሰሊጥ የጫኑ ሌሎችም መኪኖች ተኩስ ተከፍቶባቸው ብዙወች በጥይት ጎማቸው የተለያየ የመኪና ክፍላቸው ተመቶባቸው ብዙ መኪኖች መቃጠላቸው የተወሰኑ ሹፌሮች ታፍነው መወሰዳቸውን የሚጠቁም መረጃ ደርሶናል :: ዝርዝር መረጃውን በስፋት የጉዳቱን መጠን ይዘን እንቀርባለን::
©የሹፌሮች አንደበት የፌስቡክ ገፅ እንደዘገበው 👆


ለሞቃዲሾ ምላሽ ይሆን❓👇
በግብፅ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የተመራ የልዑካን ቡድን አስመራን እየጎበኘ ነው።

ፕሬዝዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ በግብፅ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዶክተር ባደር አብዱላህ የተመራውን የልዑካን ቡድን ተቀብለው አነጋግረዋል።

በሱዳን ግጭት እድገትና አቅጣጫዎች፣ በሶማሊያ መንግስት ግንባታ ሂደት እና በአፍሪካ ቀንድ እና በቀይ ባህር አካባቢ ሰላምና ፀጥታን ሊፈታተኑ በሚችሉ ጉዳዮች ላይ መወያየታቸው የሀገሪቷ ሚዲያዎች ዘግቧል።
Ayu Zehabesha


#ቴምር ሪልስቴት
⚠️7ሳይቶችን ስርተን አስረክበናል አሁን ላይ ደግሞ ለሽያጭ ያወጣናቸው ቤቶቾ እና ሱቆች
‼️ፒያሳ (ሊሴ ገ/ማርያም ትምህርት ቤት) ጀርባ
         👉1 መኝታ 66ካሬ=
         10% ቅድመ ክፍያ 693,000ብር
         ሙሉ ክፍያ 6,930,000 ብር
         👉2መኝታ 71ካሬ
        10%ቅድመ ክፍያ 745,000ብር
        ሙሉ ክፍያ 7,455,000ብር
         👉2መኝታ 93ካሬ=
       10% ቅድመ ክፍያ 1,044,000ብር
       ሙሉ ክፍያ 10,044,000ብር
        👉3መኝታ 130ካሬ
      10%ቅድመ ክፍያ 1,365,000ብር
      ሙሉ ክፍያ 13,650,000ብር
        👉ቀሪውን 90% በ17ዙር ከፍለው         የሚጨርሱት
        👉30% እና ከዛ በላይ ለሚከፍል ከከፈሉት ላይ 25% ደረስ የሚደርስ ቅናሽ አዘጋጅተናል
‼️ፒያሳ ሱቅ ሽያጭ 
👉3.9ሚሊዮን 20ካሬ ቅድመ ክፍያ900,000ብር 4ተኛ እና 5ተኛ
👉4.2ሚሊዮን 20ካሬ ቅድመ ክፍያ 1.2ሚሊዮን 3ተኛ
👉4.8ሚሊዮን 20ካሬ ቅድመ ክፍያ 1.5ሚሊዮን 2ተኛ
👉5.5ሚሊዮን 20ካሬ ቅድመ ክፍያ 2ሚሊዮን 1ኛ
👉 7ሚሊዮን 20ካሬ ቅድመ ክፍያ 2.8ሚሊዮን ግራውንድ በውስጥ በኩል
👉10ሚሊዮን 20ካሬ ቅድመ ክፍያ 4ሚሊዮን ግራውንድ በውጪ
ለበለጠ መረጃ ይደውሉ
       👇👇👇👇👇👇
     +251939770177
     +251996856273
https://t.me/TemerRealEstateSalesConsultant
WhatsApp.https://wa.me/251939770177


የኤርትራው ፕሬዝደንት ኢሳያስ አፈወርቂ ከአፍሪካ ህብረት የፖለቲካ፣ ሰላምና ደህንነት ኮሚሽነር ጋር ተወያዩ፡፡ ፕሬዝደንቱ ከኮሚሽነሩ ባንኮሊ አዶዬ ጋር አህጉሪቱ በገጠሟት ፈተናዎች በተለይም በአፍሪካ ቀንድ ዙሪያ ባሉት ወቅታዊ ሁኔታዎች ዙሪያ ጥልቀት ያለው ውይይት ማድረጋቸውን የኤርትራ ማስታወቂያ ሚኒስትሩ አቶ የማነ ገብረመስቀል ገልፀዋል፡፡

በውይይቱ ፕሬዝደንት ኢሳያስ ሲናገሩ ‹‹ምእራባዊያን አፍሪካን የእርስ በእርስ ጦርነቶች ማእከል አድርገው የሚገልፁት በጦርነቶቹ መሀል ጣልቃ ለመግባት ነው›› ማለታቸውን ያስታወቁት አቶ የማነ ይህንን ድርጊት አሳፋሪ በማለት መግለፃቸውንም አስረድተዋል፡፡ ‹‹እንደአለመታደል ሆኖ የአፍሪካ ህብረት እነዚህ አሰራሮች ለማስተካከል እርምጃዎችን መውሰድ አልቻለም›› ያሉት አቶ ኢሳያስ የአፍሪካ ህብረት ጦርነቶችንና ግጭቶችን ለመቆጣጠር ጊዜና ጉልበቱን ከሚያባክል ይልቅ ግጭቶች እንዳይፈጠሩ ማድረግን ቅድሚያ ሊሰጠው እንደሚገባ ማሳሰባቸውን አቶ የማነ አስረድተዋል፡፡

ፕሬዝደንት ኢሳያስ ንግግራቸውን ሲቀጥሉ ‹‹የአፍሪካ ህብረት ያሉበት መዋቅራዊ ድክመቶች ከውጭ ጣልቃ ገብነት ጋር ተዳምረው ድርጅቱ የአፍሪካዊያንን ምኞትና ፍላጎት እንዳያሟላ እንቅፋት ሆነውበታል፡፡ የሚያሳዝነው ደግሞ የአፍሪካ ህብረት አይሆንም የማለት አቅም በማጣቱ የተወሰኑ አገራት ጥቅማቸውን ለማስከበር የሚያደርጉትን ጥረት ቀጥለውበታል›› ያሉ ሲሆን በእሳቸው እይታ የአፍሪካ ልማት ምን መምሰል እንዳለበትም ማብራሪያ እንደሰጡ አቶ የማነ ገልፀዋል፡፡

በተለይም የሱዳንንና የሱማሊያን ጉዳይ በተመለከተ ሀሳባቸውም መግለፃቸውንም አስረድተዋል፡፡ ኮሚሽነሩ ለኤርትራ ቴሌቪዥን በሰጡት አጭር መግለጫ በአፍሪካ ቀንድ በተለይም በሱዳንና በሱማሊያ ጉዳይ የተሰጣቸው ገለፃ ጥልቅና በሳል መሆኑን ተናግረዋል ብለዋል አቶ የማነ


ሰበር ዜና

ሳኡዲ አረቢያ ታላቁ የረመዳን ጾም ነገ ቅዳሜ እንደሚጀምር አስታወቀች።

በሳኡዲ አረቢያ የቴሌስኮፕ ባለሙያዎች አዲስ የረመዳን ጨረቃ ማየታቸውን ገልጸዋል።

በዚህም በዛሬው ዕለት የተራዊህ ሶላት የሚጀመር ሲሆን በነገው ዕለት የረመዳን ጾም የሚጀመር ይሆናል።

¤ሀሩን ሚዲያ ለመላው ሙስሊም ማህበረሰብ እንኳን ለ1446ኛው ዓመተ ሂጅራ የረመዳን ጾም አደረሳችሁ ሲል መልካም ምኞቱን ይገልጻል።


ጠቅላይ ሚኒስተር አብይ በሞቃድሻ ለሶስት ሰዓት ያህል ከቆዩ በኋላ ወዲያው ወደ ኢትዮጵያ መመለሳቸው ተሰማ። በቆይታ መጠን የደህንነት ስጋት እያየለ ሊመጣ ስለሚችል ቆይታቸው አጭር ሆኗል ተብሏል


ጠቅላዩ በዚህ ሰዓት ሶማሊያ ሞቃድሾ ጉብኝት እያደረጉ ነው።


(ዘ-ሐበሻ ዜና) በኳታር አየር መንገድ እየተጓዙ የነበሩ ቻናዊያን በመደባደባቸው አውሮፕላኑ ኬንያ ለማረፍ መገደዱ ተዘገበ፡፡ ከስፍራው እንደተሰራጩ ዘገባዎች ከሆነ አውሮፕላኑ ወደናይጄሪያ ሌጎስ እየተጓዘ የነበረ ሲሆን በአየር ላይ በሁለት ቻይናዊያን መካከል ፀብ ይፈጠራል፡፡

በድብድቡ አንደኛው ቻይናዊ ተጎድቶ በመውደቁ የተነሳ አውሮፕላኑ ጆሞ ኬንያታ አየር ማረፊያ ሊያርፍ መቻሉን ዘገባዎቹ አስረድተዋል፡፡ የተጎዳው ቻይናዊ በአየር ማረፊያው የህክምና እርዳታ የተደረገለት ሲሆን ጥቃት የፈፀመው ቻይናዊ ከአውሮፕላኑ እንዲወርድ ተደርጎ በዚያው መታሰሩ ተገልጿል፡፡

አውሮፕላኑ ለአንድ ሰአት ያህል ከቆየ በኋላ መንገደኞቹን ይዞ ወደሌጎስ ሊበር እንደቻለ ዘገባዎቹ አስረድተዋል፡፡ ይህ ድርጊት የተፈጠረው እሁድ እለት ሲሆን በዚሁ እለት አንድ ሱዳናዊ ደግሞ በኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላን ውስጥ ሲጋራ ሲያጨስ በመገኘቱ መታሰሩን ዘገባዎቹ አስታውቀዋል፡፡

አውሮፕላኑ ከካርቱም ተነስቶ በኢትዮጵያ በኩል አድርጎ ኬንያ የደረሰ ነበር፡፡ ልክ አውሮፕላኑ እንዳረፈ ይህ ሱዳናዊ ሲጋራውን በመለኮስ ህግ መተላለፉን ዘገባዎቹ ገልፀዋል፡፡


ነገ የመጨረሻ ሊሆን ይችላል‼️
Telegram business‼️
ከስር የተቀመጠውን ሊንክ "Start" በማለት ብቻ በነፃ 1,500 stars ይውሰዱ👇👇👇👇
https://t.me/Stars_MeBot/stars?startapp=473382500


በመሬት መንቀጥቀጥ “ከፍተኛ ጉዳት” የደረሰበት የከሰም ስኳር ፋብሪካ፤ ሰራተኞቹን በመጪዎቹ ወራት ሊያሰናብት ነው

ባለፉት ወራት በተደጋጋሚ በተከሰቱ የመሬት መንቀጥቀጦች “ከፍተኛ ጉዳት” የደረሰበት የከሰም ስኳር ፋብሪካ፤ ከአንድ ሺህ በላይ ሰራተኞቹን እስከ መጪው ግንቦት ወር ባለው ጊዜ ውስጥ ለማሰናበት ቅድመ ማስጠንቀቂያ ሰጠ።

የስኳር ፋብሪካው የሰራተኞች ማህበር በበኩሉ ሰራተኞቹ ሳይሰናብቱ ወደ ሌሎች ፋብሪካዎች እንዲበተኑ ለማድረግ ጥረት እያደረገ መሆኑን ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” አስታውቋል።

በስሩ ከአራት ሺህ በላይ ሰራተኞችን የሚያስተዳድረው የከሰም ስኳር ፋብሪካ፤ የቅድመ ማስጠንቀቂያ በመስጠት የሰራተኞቹን የስራ ውል ያቋረጠው ባለፈው ሳምንት ማክሰኞ የካቲት 11፤ 2017 ዓ.ም ባወጣው ማስታወቂያ ነው።

በፋብሪካው የማስታወቂያ ሰሌዳ ላይ የተለጠፈው እና “ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” የተመለከተችው ይህ ማስታወቂያ፤ የስራ ውላቸው የተቋረጠ ከአንድ ሺህ በላይ ሰራተኞችን ስም ዝርዝር የያዘ ነው።

የከሰም ስኳር ፋብሪካ የሰው ሀብት ስራ አመራር እና አቅርቦት ዘርፍ ስራ አስኪያጅ አቶ ዝናቡ ብርሃኑ ፊርማ ያረፈበት ማስታወቂያ፤ ፋብሪካው ከዚህ ውሳኔ ላይ የደረሰው ከታህሳስ 20 ጀምሮ በተደጋጋሚ የተከሰተው ርዕደ መሬት ባስከተለበት “ከፍተኛ ጉዳት” መሆኑን ያስረዳል።

የስኳር ፋብሪካው በዚህ ምክንያት “ስራውን ሙሉ ለሙሉ ያቆመ በመሆኑ”፤ በማስታወቂያው ስማቸው የተዘረዘረ ሰራተኞቹ የስራ ውል ከየካቲት 10፤ 2017 ጀምሮ “በቅደመ ማስጠንቀቂያ” መቋረጡንም አትቷል።

ይሁንና በዚያው ዕለት ፋብሪካው ማስተካከያ በማድረግ በለጠፈው ማስታወቂያ፤ ሰራተኞቹ ከየካቲት 10 ቀን ጀምሮ መሰናበታቸውን በማስቀረት ከዚሁ ቀን ጀምሮ እንደ የአገልግሎት ቆይታቸው ቅድመ ማስጠንቀቂያ የተሰጣቸው መሆኑን ገልጿል።


ለአንድ የስራ መደብ 3ሺህ ሰው ተመዘገበ

አርቲስት ቬሮኒካ አዳነ የግል ፎቶግራፈር እፈልጋለሁ ብላ ባወጣችው ማስታወቂያ ከ3000 በላይ ስራ ፈላጊ እንደተመዘገበ አስታወቀች።
ከአጋሮቼ ጋር በመሆን የመለየት ስራው ተሰርቶ ተፈትኖ በትላንትናው እለት የካቲት 18/2017 ዓም አሸናፊው ተመርጦ ወደ ስራ ገብተናል ብላለች።

በፊት የግል ቦዲ ጋርድ የተለመደ ሲሆን ከለውጡ በኋላ የግል ፎቶ ግራፈር እየተለመደ መጥቷል።

Показано 16 последних публикаций.