በነገራችን ላይ… የምዝገባ ቀን ዛሬ ስላለፈ እህቶቻችን ያልፋቸዋል ማለት አይደለም። ይሄ'ኮ ቀነ ገደቡም፣ ህጉም ሰው ሠራሽ እንጂ የማይሻርና የማይሻሻል መለኮታዊ ህግ አይደለም። ፍትሕ ካለና ሃገሪቱ ይበልጥ ወደ ኋላ እንዳትጓዝ የሚፈልግ አንፃራዊ ሰው ካለ፤ እህቶቻችን አይደለም ዛሬ ጥር፤ ፈተናው ሐምሌ 01 የሚሰጥ ከሆነ ሰኔ 20 መመዝገብ ይቻላሉ።
ስለዚህ እነርሱ ያወጡት ቀኑ ባለፈ ብለን ተስፋ ሳንቆርጥ ትግላችን ሳይቀዘቅዝ እስከ ድል ደጅ ይቀጥል። ሲጀመር ለሁሉም ለተወሰነ ቀነ የመጨረሻ ቀን ብለው ያራዝሙት ይሆናል። ካልሆነም ችግሩ የልጆቹ ሳይሆን የከልካዮቹ ስለሆነ በልዩ ምክንያት ጉዳያቸው ይታያል።
የትግል ስልትን እንደየሁኔታው እየቀያየሩ መወጠር ነው።
||
t.me/MuradTadesse