Murad Tadesse (Official Channel)☪️🇪🇹


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: Религия


ትክክለኛው ኢስላማዊ አስተምህሮ፦
1) ከቁርኣን፣
2) ከሐዲሥ፣ [በሰለፎች አረዳድ]
3) ከታማኝ ዑለማዎችና
4) ከትክክለኛ ቂያስ ተጠናቅሮ ይቀርብበታል።
√ አዳዲስና ወቅታዊ ኢስላማዊ የሆኑ ጉዳዮችም ይዳሰሳሉ።
√ አላማዬ በዲኔ ላይ ያለውን የመረጃ ክፍተት መሙላት ነው።
ማንኛውም አስተያዬት ሲኖራችሁ @Murad_Tadesse ላይ አስፍሩት።
ስህተትም ባያችሁ ጊዜ አርሙኝ።
ጀዛኩሙል`ሏህ ኸይራ!

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
Религия
Статистика
Фильтр публикаций


Репост из: Mizan Tv - ሚዛን ቲቪ 🇪🇹
Видео недоступно для предпросмотра
Смотреть в Telegram
የምሽት ስንቅ ለቀልብዎ❤️

[Part: ⓵⑦∅⑥]👌


#ቁርኣን


ከመጥፎ ጎረቤት፣ የወላጆቹን ሐቅ ከማይጠብቅና መልካም ስነ ምግባር ከሌላት ሴት ኑሮህን አርቅ።
ذكر ابن عبد البر رحمه الله :

كدر العيش في ثلاث :

الجار السوء
والولد العاق
والمرأة السيئة الخلق

📚الآداب الشرعية لابن مفلح

6k 0 18 29 117

ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የሃገራችን የትምህርት ስርዓት የበለጠ ተበክሏል።

ዋነኛ መነስዔው በዘርፉ ብቃት የሌላቸው አካላት ወሳኝ ወሳኝ ቦታዎች ላይ መቀመጣቸው ነው። በመማር ማስተማር ስርዓቱ እንዝህላልነት የተነሳ ቆፍጠን ብሎ የሚማር ተማሪም እየጠፋ ነው። ተስፋ ሰንቆ የሚማር፣ ትምህርት ይጠቅማል ብሎ አስቦ እንደ ተማሪ የሚጠበቅበትን ኃላፊነት የሚወጣ ትውልድ እየጠፋ ነው።

በተለይም ከካሪኩለሙ ኋላ ቀርነት በተጨማሪ ፈተና የሚያወጡት አካላት ኃላፊነት የማይሰማቸው ግዴለሾች እንደሆኑ የሚያሳዩ ነገሮችን እየታዘብን ነው። እንዲህ ግራ የገባው፣ ተማሪውን ዕውቀቱን የማይፈትሹ ተራና ጥቅም አልባ ጥያቄዎችን እያወጡ እያወዛገቡ፤ በኋላ ይህን ያክል % ተማሪ ወደቀ ብሎ በሚዲያ መለፈፍ ትርጉም የለውም።

ለዚህ መፍትሄው፤ ከመምህራን ጀምሮ ብቃታቸውን መፈተሽ፣ ከትምህርት ሚኒስተር ጀምሮ በሁሉም የፌዴራል፣ የክልል፣ የዞን፣ የወረዳ፣ የከተማ አስተዳደሮች… ላይ ያሉ አካላትን ብቃት መፈተሽ ያስፈልጋል። ብቁ ሰዎች ከተመደቡ ዘመናዊው ዓለም ጥሎት ካለፈ 20 አመታትን ያስቆጠሩ ሃሳቦች ለታሪክነት ካልሆነ በስተቀር ገበያው ላይ ያሉ ይመስል መካተት የለባቸውም። በምትኩ ገበያው ላይ ያሉ ሃሳቦች ይካተቱ። ካሪኩለሙ ሞዲፋይ ይደረግ።

ትውልድ አትግደሉ! ትልቅ የትምህርት ተቋም ሆኖ በአንድ የፈተና አይነት ላይ ብቻ በርካታ የሃሳብ፣ የቃላትና የፊደላት ግድፈት መታየቱ አሳፋሪ ነው። በዘመድ አዝማድ ስልጣን ከፈለጋችሁ በሌላው መስክ እንደለመዳችሁት ተጫወቱ እንጂ በትምህርት ግን አታስቡት! ፕሊስ!

||
t.me/MuradTadesse

7.4k 0 14 15 122



Репост из: STEM with Murad 🇪🇹
ቴክኖሎጂ ተማሩ ብያለሁ።
በሉ! በነዚህ ዘርፎች ዕውቀቱ ያላችሁ ለሥራ ኢቫንጋዲ ቴክ ላይ አመልክቱ።

«ከዚህ በታች በተዘረዘሩት የሥራ መስኮች፣ አዲስ አበባ ኢትዮጵያ ውስጥ ለሚገኝው የኢቫንጋዲ ቴክ ቢሮ፣ 14 ሰዎችን አወዳድረን ለመቅጠር ስለምንፈልግ፣ የሚፈለገውን መስፈርቶች የምታሟሉ ባለሙያዎች በዌብሳይታችን evangaditech.com ላይ ያለውን መረጃ በመከተል፣ ማመልከቻችሁን እንድትልኩና ኢቫንጋዲን እንድትቀላቀሉ ተጋብዛችሗል።

ለበለጠ መረጃ
https://www.youtube.com/watch?v=_n0Fm8GGtaE 

የሥራ መስኮቹ፥
  1. DATA ENGINEER
  2. AWS CLOUD ENGINEER
  3. MULESOFT DEVELOPER
  4. SHAREPOINT DEVELOPER
  5. MS SQL DBA SYSTEMS DEVELOPER
  6. SOFTWARE TESTER
  7. ENGLISH INSTRUCTOR» ብለዋል።


ይህ ነገር ግን እውነት ነው?
««ለፈገግታ »

የሐጅ ስነ ስርአት ሲፈፅሙ ከሑጃጆች የሰማውን ፈገግ የሚያደርግ ገጠመኞች የሳዑዲ ወታደር እንዲህ ያወጋል፦

1) ሴትየዋ የሑጃጆችን ብዛት እያየች በመገረም እጇን አንስታ "ያ ረብ! እነሱን ተዋቸው፤ ከኔ ጋ ሁን!"

2) ሰውየው ጠዋፍ እያደረገ "ያ ረብ! በጀነት ከተበሰሩት አስሩ አድርገኝ!" ይላል። ይህን የሰማው አብሮት የነበረው ጓደኛው "ማንን አውጥቶ ነው አንተ ምትገባው?"

3) ጀመራት ላይ ሴትዮዋ በንዴት እየተሳደበች ጠጠር ትወረውራለች። ወታደሩ "ያ ሐጃ! እንዲህ ማለት አይፈቀድም! ሲላት፤ "ምን አገባህ? ኢብሊስ ዘመድህ ነው?!"

4) አንዱ ደግሞ "ያ ረብ! ያ ረብ! ባንተ ምርጫ ቆንጆ ነገር እፈልጋለሁ!"»

8.4k 0 139 24 284

«የፍቅር መድኃኒቱ፤ ያፈቀርካትን ሴት ማግባት ነው!» ብለዋል ኢብኑ-ል-ቀይዩም።

እንጂ በስልክና በቴክስት አሊያም በሶሻል ሚዲያ አሊያም በየ ሻይ ቤቱ በመዞር በመጀናጀን አይደለም። እምቢ ካለች ደግሞ አሲድ በመድፋት አይደለም። ሌላውን ተውና ከጓሮ ለጓሮ በመውጣት ወደ ሐላሉ አምጡት!

11.9k 0 129 166 321

Видео недоступно для предпросмотра
Смотреть в Telegram


Репост из: ሐላል ድጅታል ኔትወርክ (Halal Digital Network -HDN) 🇪🇹
ዛሬ ሰኔ 15/10/16 ከቀኑ 9 ሰዓት ገደማ በምስሉ ላይ የምትመለከቱት ዶልፊን መኪና የታርጋ ቁጥር ኦሮ 03702 የሆነ መኪና ከቤተል ተቅዋ መስጂድ ጀርባ ተሰርቆብናል። መኪናውን ያያችሁ በተከታዮቹ ስልክ ቁጥሮች እንድትጠቁሙን በትህትና እንጠይቃለን ።

0919297989 ኻሊድ
0995010856/ሙሐመድ ሐሰን


በጣም በርካታ የህዝብ ጭንቅንቅ ብሎ ባለበት ክራውድድ ቦታ ላይ አንድት ኒቃቢስት እናት ልጇ ጠፋት። ስሙን እየጠራች ትፈልገው ጀመር። ሰዎች «ኒቃብሽን አውልቂው፣ በቀላሉ አይቶሽ ወዳንቺ እንዲመጣ!» አሏት።

እርሷም «የጠፋው ልጄ እንጂ ሐያኤ አይደለም!» አለቻቸው።

በርግጥ! ለእንዲህ አይነቷ እናት አላህ በቀላሉ ከልጇ ጋር ያገናኛታል። እንዲህ አይነት ጀግኖች አሉን። እና ሳይቸገሩ የሚገላለጡና ተሸፍነውም ሐያእ ያጡ እንስቶች ምን ይሉ?

||
t.me/MuradTadesse

13.8k 0 45 21 336

«ወደ ነፍስህ መመልከት ከፈለግክ፤ ጭብጥ አፈር ያዝ፤ ከርሱ ነው የተፈጠርከው፣ ወደርሱም ትመለሳለህ፣ ከርሱም ትወጣለህ።»





13.4k 0 17 21 165

ሐጅ ላይ ላላችሁ… በአያመ ተሽሪቅ የመጨረሻው ቀን ልክ ጀመራትን ጨርሳችሁ ከሚና ወደ መካ እንደተመለሳችሁ፤ ከ14ኛው ቀን ጀምሮ ወደ ሃገራችሁ የመመለስ ፍላጎታችሁ ይጨምራል። የሆነ ዒባዳን አጠናቃችሁ ረፍት ላይ ያላችሁ አይነት ስሜት አለው፤ የምትሠሩት ታጣላችሁ።

ዞሮ ዞሮ እንደ አካሄዳችሁ ወረፋ ነው የምትመለሱት ስለተባለ፤ ከወረፋችሁ ቀድማችሁ መምጣት የምትችሉበት ነገር ከሌለ ወረፋችሁ እስኪደርስ ድረስ እንደት ማሳለፍ እንዳለባችሁ ልጠቁማችሁ።

ጥቂት የማይባል ሰው ጀማዓህ ሶላት ራሱ እዛው ሆቴል አካባቢ ባለ መስጅድ ወይም ሆቴል ውስጥ ይሰግዳል እንጂ ሐረም ለመመላለስ ሲዘናጋ ይስተዋላል። እናንተ አላህ መርጧችሁ የተከበረው ቤቱን ዚያራ ወፍቋችሁ ሳለ፤ ሰው እንደት ወደዛ በሄድኩ እያለ እናንተ ከዚያ ለመውጣት አትቸኩሉ። ስለዚህ ወደሃገራችሁ እስከምትመለሱ ድረስ፤ የሥራና የቤተሰብ ጭንቀቱ እንዳለ ቢሆንም ያላችሁን ቆይታ አጣጥሙት።

ፈጅር ላይ ቀደም ብላችሁ ከእንቅልፋችሁ ተነሱና ወደ ሐረም ሂዱ፤ ተሃጁዳችሁንና ዊትራችሁን ሰጋግዳችሁ፣ እዛው ፈርዱን ከሰገዳችሁ በኋላ ጸሐይ እስከምትወጣ ድረስ እዛው እየቀራችሁና ዚክር እያደረጋችሁ በማሳለፍ ሹሩቃችሁን ሰግዳችሁ ወደ ሆቴል በመመለስ ቁርስ ብሉና እስከ ዙህር ተኙ። ዙህር ላይ ምሳ ብሉና ወደ ሐረም በማቅናት ዙህራችሁን ሰግዳችሁ እስከ ዒሻእ እዛው አሳልፉ። በመሃል እንቅልፍ ካለም ከዙህር እስከ ዐስር ባለው የሆነች ያክል አረፍ በሉ። ከዐስር በኋላና ከመጝሪብ በኋላ ሙሐደራዎችና ደርሶች ስለሚኖሩ ዐረብኛ የምትችሉ ዘወር ዘወር ብላችሁ አዳምጡ። በ74 ቁጥር ግራውንድ ላይ ብትገቡም ተመዝገቡና ከጠዋት እስከ ማታ የቁርኣን ሒፍዝና ሐለቃ ስላለ ተሳተፉ። ብዙ አስተማሪ ዶክተሮች አሉ። ከዚያ ዒሻእን ሰግዳችሁ ወደ ሆቴል መጥታችሁ ራት በልታችሁ እስከ ፈጅር ለጥ ማለት ነው።

ከዐስር በኋላና በመሳሰሉት ወቅቶች ሲመቻችሁ ጠዋፍ እያደረጋችሁ፣ ካዕባን በዓይናችሁ ብሌን በቀጥታ በምታዩበት ቦታ ላይ በመሆን እያጣጣማችሁ፣ ቁርኣናችሁን እየቀራችሁ፣ ዚክርና ዱዓችሁን እያደረጋችሁ ብታሳልፉ፤ እመኑኝ ያ ቶሎ ወደ ሃገሬ በገባሁ እያለ መሄጃ ቀኑ የናፈቀው ልባችሁ ጭራሽ ሃሳቡን ቀይሮ መሄጃ ቀኔ ደረሰ እያለ ይጨነቃል።


ሞክሩት'ማ!
ደግሞ አንድ ሰው አንድን ዒባዳህ ሲያጠናቅቅ፤ የዛ ዒባዳው ተቀባይነትና ፍሬ ማፍራቱ የሚታየው ከዚያ በኋላ ባለው ጥንካሬና ድክመቱ ነው።

አላህ ያግዛችሁ፤ ይቀበላችሁም።

||
t.me/MuradTadesse

14.4k 1 63 11 183



ፍሪጅ ውስጥ እየገቡ አገር የሚያጠፉ ህፃናትን እንደት አድርገን አደብ እናሲዛቸው?


Репост из: Mizan Tv - ሚዛን ቲቪ 🇪🇹
Видео недоступно для предпросмотра
Смотреть в Telegram
የማለዳ ስንቅ ለቀልብዎ❤️

[Part: ⓵⑦∅⑤]👌


#ቁርኣን

13.5k 0 53 19 121

Репост из: Mizan Tv - ሚዛን ቲቪ 🇪🇹
Видео недоступно для предпросмотра
Смотреть в Telegram
የምሽት ስንቅ ለቀልብዎ❤️

[Part: ⓵⑦∅④]👌


#ቁርኣን


ባለፈ ፈተና ያመለጣችሁ ካላችሁ ነገ ቅዳሜ ተፈተኑ ተብሏል።


አንዳንድ ሰው ሲያገኝ አያቅበትም።
ባለሃብት ሲሆን ከአላህም ጋር፣ ከአላህ ፍጡሮችም ጋር የሚጣላ አለ። በተለይ አጥቶ ያገኘ ሰው፤ አላህን ማመስገን ሲገባው የነበረበትን ረስቶ ሌላ ሙድ ውስጥ ይገባል።

እንኳን ሚስኪኖችን እንደ ድልዲይ ሆነው ወንዙን በማሻገር ለዚህ ሰበብ የሆኑትን ሰዎች እንኳ ዘወር ብሎ አያይም። ያኔ አላህን እያለቀሰ ይማፀን እንዳልነበር፤ ዛሬ ግን የታጠረው ሱሪ ይረዘማል፣ ያሳደገው ጺም ይላጫል፣ መስጅድ ለጀማዓህ ሶላት ይመላለስ የነበረው ቤቱ ውስጥ ለመስገድም በግድ ነው… የኩራቱን ነገር'ማ ተውት።


በአጭሩ ምን ልላችሁ ነው፦
አላህን የገንዘብ ሪዝቅ ስንጠይቀው፤ «ገንዘብ ስጠኝ!» ብቻ አንበለው። ይልቁንም ጠቃሚ ገንዘብ እንዲሰጠን፣ ከርሱ የሚያርቀንና እርሱን ከማውሳት ቢዚ የሚያደርገን ሳይሆን ወደርሱ የሚያቃርበን ገንዘብ እንዲሰጠን እንማፀነው።

ከአላህ ከሚያርቅ ባለሃብትነት ይልቅ ወደ አላህ የሚያቃርብ ድህነት የተሻለ ነው።

ዱንያን'ኮ የፈለገ ብንቸገር እንኳ በሞት እንገላገላታለን። አኺራችን ከተበላሸ ግን ምን ማምለጫ አለን? ምን መገላገያ መፍትሄ አለን? መዝገቡ ከታጠፈና ቀለሙ ከደረቀ በኋላ ከቁጭት ውጭ ምን አማራጭ አለን? ምንም!

ሰዎች ቢያስተውሉ ኖሮ፤ ዛሬ ላይ የሚጠፋ የማይመስላቸውና እንኳን ለነርሱ ለዘመድ አዝማድ እስከ ዕለተ ሞታቸው ድረስ ቢከፋፈል የማያልቅ የሚመስላቸው ረብጣ ገንዘብ፤ አላህ ከወሰነ በአንድ ሌሊት እንዳውም በአንድት ቅፅበት ከነርሱ እጅ መውጣት የሚችል ነው።

ትናንት ዘካ አሰልፈው ሲሰጡ የነበሩ፤ ዛሬ ላይ በተራቸው ተሰልፈው ዘካ ለመቀበል የሚቸገሩ ሰዎችን አልታዘብንም ወይ? የነ ቃሩን ታሪክስ ምን ነበር?

ይልቅ አላህ ለዱንያችንም ለአኺራችንም የሚጠቅመንን ሪዝቅ ይለግሰን።


اللهم ارزقني رزقًا واسعًا حلالًا طيبًا من غير كدٍّ.. واستجب دعائي من غير رد.. وأعوذ بك من الفضيحتين: الفقر والدّين، اللهم يا رازق السائلين، يا راحم المساكين، ويا ذا القوة المتين، ويا خير الناصرين، يا ولي المؤمنين، يا غيّاث المستغيثين، إياك نعبد وإيّاك نستعين، اللهم إن كان رزقي في السماء فأنزله، وإن كان رزقي في الأرض فأخرجه، وإن كان بعيدًا فقرّبه، وإن كان قريبًا فيّسره، وإن كان كثيرًا فبارك فيه يا أرحم الراحمين، اللهم صلّ على محمد وآل محمد، واكفني بحلالك عن حرامك، وبطاعتك عن معصيتك، وبفضلك عمّن سواك يا إله العالمين، وصلّى الله على محمد وعلى آله وصحبه وسلم።

||
t.me/MuradTadesse

15.7k 0 52 15 217
Показано 20 последних публикаций.