Murad Tadesse (Official Channel)☪️🇪🇹


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: Религия


ትክክለኛው ኢስላማዊ አስተምህሮ፦
1) ከቁርኣን፣
2) ከሐዲሥ፣ [በሰለፎች አረዳድ]
3) ከታማኝ ዑለማዎችና
4) ከትክክለኛ ቂያስ ተጠናቅሮ ይቀርብበታል።
√ አዳዲስና ወቅታዊ ኢስላማዊ የሆኑ ጉዳዮችም ይዳሰሳሉ።
√ አላማዬ በዲኔ ላይ ያለውን የመረጃ ክፍተት መሙላት ነው።
ማንኛውም አስተያዬት ሲኖራችሁ @Murad_Tadesse ላይ አስፍሩት።
ስህተትም ባያችሁ ጊዜ አርሙኝ።
ጀዛኩሙል`ሏህ ኸይራ!

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
Религия
Статистика
Фильтр публикаций


Видео недоступно для предпросмотра
Смотреть в Telegram
😢

8.5k 0 24 18 142

አዛዥና ታዛዥ የሌለበት ክልል → ትግራይ

የአክሱም ከተማ ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ፀጋ የአክሱም ከተማ ፍርድ ቤት ያስተላለፈውን የእግድ ውሳኔ እንደማይቀበሉ መግለፃቸው ተሰማ!

▣ ሶስት ት/ቤቶች የፍርድ ቤቱን ውሳኔ ፈርመው መቀበላቸው ተገልጿል።



የአክሱም ከተማ ወረዳ ፍርድ ቤት አስተዳደራዊ ጥሰት በፈጸሙ ትምህርት ቤቶች ላይ ተግባራቸው ህጉን የጣሰ መሆኑን ገልጾ እግድ መጣሉ ይታወቃል።

የአክሱም ከተማ ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ፀጋ የአክሱም ከተማ ፍርድ ቤት ያስተላለፈውን የእግድ ውሳኔ እንደማይቀበሉ መግለፃቸውን ሀሩን ሚዲያ ከስፍራው የደረሰው መረጃ ያመላክታል።

ሙስሊም ሴት ተማሪዎቹ ዛሬ ከሒጃባቸው ጋር ተመሳሳይ የሆነ ዩኒፎርም ለብሰው ለማማር ወደ የትምህርት ቤቶቻቸው ሂደው የነበሩ ቢሆንም ዛሬም እንዳይገቡ መከልከላቸውን ገልፀዋል።

የ12ኛ ክፍል ተማሪዎቹም ፎርም የመሙላት እድል ይኖራል ብለው ዛሬ ጠይቀው የነበረ ቢሆንም ጊዜው እንዳበቃ ተነግሯቸው ፎርሙን ሳይሞሉ መመለሳቸውን ተናግረዋል።

ሁለት ትምህርት ቤቶች የፍርድ ቤቱ የእግድ ደብዳቤ አንቀበልም ብለው መልሰዋል። ሌሎቹ ትምህርት ቤቶች የእግድ ደብዳቤውን ፈርመው እንደተቀበሉ ለማረጋገጥ የቻልን ሲሆን ይሁንና ተማሪዎችን ማስገባት አለመጀመራቸው ተሰምቷል።

የአክሱም ተማሪዎች የሂጃብ ጉዳይ ትምህርት ሚንስትር መድረሱ የተገለፀ ሲሆን የትምህርት ሚኒስትር በጉዳዩ ዙሪያ ከሰሞኑ መፍትሔ ይሰጣል ተብሎ ይጠበቃል።

-የዚህን ዜና ሙሉ መረጃ በምሽት በሚኖረን የመረጃ ሰኣት ወደናንተ እናደርሳለን!

©: ሀሩን ሚዲያ

10k 0 5 32 192

እኔ ብቻ ነኝ ግን የቡና ሐጃ የሌለብኝ? ገና ከመልኩ ጀምሮ! ምን ጣፍጧችሁ እንደምትጠጡት'ኮ ነው ግራ 'ሚገባኝ¡

በተለይ ደግሞ ወተት ላይ ቡና ጨምራችሁ የምታበላሹት ምን አስባችሁ ነው¿ ወተትን ያክል ነገር!

ጭራሽ ደግሞ ቡና ያነቃናል… ምናምን

13.2k 0 62 305 436

ወላሂ በየትኛውም!

14.1k 0 10 21 329

አላህን ይህን ሐላል ልብስ በቅርቡ ይወፍቃችሁ!

13.7k 0 24 94 294

ታላቅ የ"ነሲሓ ኮንፈረንስ" በሚሊኒየም አዳራሽ


ዝግጁ⁉️

13.9k 0 21 64 288

ወጣትነት እና ስኬት


በሸይኽ ኢልያስ አሕመድ


الله يعلم ما نشكو من الألم
وما نعانيه من ضيقٍ ومن سقَم
لكن لنا فيه ظن لا يخيبنا
حاشاه أن ترجِع الأيدي بلا نِعم....

14.3k 0 26 14 119

Репост из: Mizan Tv - ሚዛን ቲቪ 🇪🇹
Видео недоступно для предпросмотра
Смотреть в Telegram
የማለዳ ስንቅ ለቀልብዎ❤️

[Part: ②①①⑨]👌


#ቁርኣን


Репост из: Mizan Tv - ሚዛን ቲቪ 🇪🇹
Видео недоступно для предпросмотра
Смотреть в Telegram
የምሽት ስንቅ ለቀልብዎ❤️

[Part: ②①①⑧]👌


#ቁርኣን


Видео недоступно для предпросмотра
Смотреть в Telegram

14.7k 0 19 47 167

Видео недоступно для предпросмотра
Смотреть в Telegram
የዛ የቤት ነገር አሁንም ፋይሉ አልተዘጋም¡

ማነህ ወይ መድረሳ ነበር በልልኝ¡

14k 0 27 38 237

ይቺን ነገር አዳምጧት። ደስ ብላኛለች ገለፃዋ!

||
t.me/MuradTadesse


በአንድ ወቅት ያጋጠመኝን ልንገራችሁ…

አንድ ወንድም ብዙ መልዕክት በውስጥ ልኮ፤ በተደጋጋሚ አላየሁለትም ነበር መሰል። ከዛ እንደዚህ ለተቸገሩ ሰዎች ሳስተባብር ለአንዱ የሆነች ትንሽ ብር ላከ። ደረሰኝ ላኩ እላችሁ የለ! ከዛ ደረሰኙን ለማየት ገብቼ አየሁለት።

ከዛ ምን ቢለኝ ጥሩ ነው… «የብር ነገርማ ስትሆን ሩጠህ ታያታለህ!» የሚል ይዘት ያለው መልዕክት ላከልኝ። ከዛ «ያው ወደኔ አካውን አይደለምኮ የሚገባው!» ብዬው ተሳስቀን እግረ መንገዱን ጉዳዩንም ነግሮኝ ተለያየን። ግን ያው የላካት ብር ለማናገር መግቢያ ሰበብ ሳይሆን ኢንሻ አላህ ለመሰደቁም ብሎኝ ነበር።


በዚሁ አጋጣሚ ከታች Users ላይ እንደምታዩት 9999+ በላይ ያልተነበበ መልዕክት አለ። የማላነበው ከምታስቡት በላይ ቢዚ ስለምሆን እንጂ ለክፋት አይደለም!

በሉ! ደግ እደሩ!


ላመሰግናችሁ ነው የመጣሁት። ትናንትና ዛሬ አግዟት ያልኳችሁትን እህት ጉዳይ ፋይል ዘግተናል። ፖስቶቹንም አጥፍቻቸዋለሁ። በራሱ ተነሳሽነት ማገዝ የፈለገ ማገዝ ይችላል። እጅግ በጣም አላህ ይስጣችሁ። ለአንድ ሰው ብቻውን ትልቅ ሸክም የሆነን ነገር ለየብቻ ተረባርበን ስንካፈለው ምንም አይመስለንም። አላህ በጀነት ያበሽራችሁ። ዱንያችሁን ከነ ቤተሰባችሁና ወዳጅ ዘመዳችሁ ያሳምርላችሁ። በዓፊያ፣ በጤና፣ በኢማን፣ በሰላም ኑሩልኝ!


የደብዳቤው ትርጉም‼
================
«የአክሱም ሙስሊም ተማሪዎች ሂጃብ ለብሰው የመማር ክልከላ ታገደ
~~~~~
ሰሞኑን የበርካታ መገናኛ ብዙሃን፣ ማህበራዊ ሚዲያዎች፣ የሀይማኖት ተቃማት፣ አግባብ ያላቸው አካላትና ግለሰቦች አጀንዳ የነበረው በአክሱም የሙስሊም ተማሪዎች ሂጃብ ጉዳይ በፍርድ ቤት ጊዜያዊ ውሳኔ አግኝቷል።

በአክሱም ከተማ የሚገኙ አምስት ትምህርት ቤቶችና የከተማዋ ትምህርት ጽ/ቤት የሙስሊም ተማሪዎችን ህጋዊ፣ ሰብአዊና ሀይማኖታዊ መብት በመጣስ ሂጃብ ለብሰው እንዳይማሩ ከልክለው እንደነበር ይታወሳል።

ክልከለውን በመቃወም በተለያዩ መንገዶች ሲቀርብ ለነበረው ጥያቄና ተቃውሞ የትምህርት ቤቶቹና የትምህርት ጽ/ቤቱ ኃላፊዎች አዎንታዊ ምላሽ ባለመስጠታቸው ጉዳዩ ወደ ፍርድ ቤት አምርቶ ነበር።

በመሆኑም በትግራይ ክልል የእስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የክስ አቤቱታ ቀርቦለት የነበረው የአክሱም ወረዳ ፍርድ ቤት ጉዳዩን በዝርዝር ተመልክቶ ዛሬ ጊዜያዊ ውሳኔ ሰጥቷል።

በዚህም መሰረት የክስ ክርክሩ ውሳኔ እስኪሰጥ ክልክላው ቢዘልቅ በተማሪዎቹ ላይ የማይቀለበስ የመብት ጥሰት ሊያስከትል እንደሚችል የጠቀሰው ፍርድ ቤቱ ተማሪዎቹን ለማገድ የተላለፈው አስተዳደራዊ ውሳኔ እንዲታገድ አዟል።

እግዱ የክስ ሂደቱ ውሳኔ እስኪያገኝ ወይም ተለዋጭ ትእዛዝ እስኪሰጥ ድረስ እንደሚፀና የጠቀሰው ፍርድ ቤቱ ተማሪዎቹ ሂጃብ ለብሰው የመማር መብታቸው እንዲከበር እና በክልከላው ምክንያት የምዝገባ ጊዜ አልፏቸው የነበሩት የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች በነገው እለት በልዩ ሁኔታ እንዲመዘገቡ ወስኗል::

ለተፈጻሚነቱም ክልከላውን ለፈጸሙት ትምህርት ቤቶች በአድራሻ የፍርድ ቤቱ የእግድ ውሳኔ እንዲደርሳቸው ተደርጓል::

በተጨማሪም ተከሳሾች የፊታችን ጥር 16/2017 በአካል ችሎት ተገኝተው በቃል ሀሳባቸውን እንዲያቀርቡ ፍርድ ቤቱ አዟል::»

Hanan እንደተረጎመችው።

14.7k 0 18 28 355

Видео недоступно для предпросмотра
Смотреть в Telegram
ለነገ ቀን ሙሉ እንዲመዘገቡ ተፈቅዷል እያሉ ነው እነዚህ ልጆች!

14.1k 0 15 27 150

በነገራችን ላይ… የምዝገባ ቀን ዛሬ ስላለፈ እህቶቻችን ያልፋቸዋል ማለት አይደለም። ይሄ'ኮ ቀነ ገደቡም፣ ህጉም ሰው ሠራሽ እንጂ የማይሻርና የማይሻሻል መለኮታዊ ህግ አይደለም። ፍትሕ ካለና ሃገሪቱ ይበልጥ ወደ ኋላ እንዳትጓዝ የሚፈልግ አንፃራዊ ሰው ካለ፤ እህቶቻችን አይደለም ዛሬ ጥር፤ ፈተናው ሐምሌ 01 የሚሰጥ ከሆነ ሰኔ 20 መመዝገብ ይቻላሉ።

ስለዚህ እነርሱ ያወጡት ቀኑ ባለፈ ብለን ተስፋ ሳንቆርጥ ትግላችን ሳይቀዘቅዝ እስከ ድል ደጅ ይቀጥል። ሲጀመር ለሁሉም ለተወሰነ ቀነ የመጨረሻ ቀን ብለው ያራዝሙት ይሆናል። ካልሆነም ችግሩ የልጆቹ ሳይሆን የከልካዮቹ ስለሆነ በልዩ ምክንያት ጉዳያቸው ይታያል።

የትግል ስልትን እንደየሁኔታው እየቀያየሩ መወጠር ነው።
||
t.me/MuradTadesse


የአክሱም ወረዳ ፍርድ ቤት ሒጃብ መልበስ የሚከለክለው መመሪያ ላይ ዕገዳ ጥሏል‼
====================

(በሒጃብ ምክንያት ተማሪዎችን ያገዱ ትምህርት ቤቶች ፍርድ ቤት እንዲቀርቡ አዟል!)

||



✍ የትግራይ ክልል እስልምና ጉዳዮች ምክርቤት በአክሱም ሙስሊም ሴት ተማሪዎች ሒጃብ ለብሰው እንዳይማሩ አስተዳደራዊ እግድ ባደረጉ 5 ትምህርት ቤቶች ላይ ክስ መመስረቱ ይታወቃል።

ጉዳዩ በዛሬው ዕለት የአክሱም ከተማ ወረዳ ፍርድቤት ላይ ቀርቦ ውሳኔ ተስጥቶበታል። ፍርድ ቤቱ አስተዳደራዊ እግድ ባደረጉ ትምህርት ቤቶች ላይ እግድ ጥሏል።

ጉዳዩ በተማሪዎቹ ላይ የማይቀለበስ የሰብአዊ መብት ጉዳት ሊያደርስ ስለሚችል ተማሪዎቹ ሒጃባቸውን ለብሰው ወደ ትምህርት ገበታቸው እንዲመለሱ የሚል ውሳኔ አስተላልፏል።

በሒጃብ ምክንያት ተማሪዎችን ያገዱ ትምህርትቤቶቹ ለጥር 16/2017 ፍርድ ቤት ቀርበው ቃላቸውን እንዲሰጡ ትእዛዝ ተሰጥቷል።

በተያያዘ ዜና የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት በሰጠው ማሳሰቢያ ፥ የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ምዝገባ ዛሬ ጥር 6/2017 ዓ.ል ከቀኑ 11፡00 ሰዓት ላይ ተጠናቋል።

የአክሱም ሁለተኛ ደረጃ ሙስሊም ሴት ተማሪዎች የ12ኛ ክፍል አገር አገር አቀፍ ፈተና ለማሳተፍ የሚያስችላቸው ፎርም ሳይሞሉ የተሰጠው የምዝገበ ቀነ ገደብ ዛሬ አልቋል።

© ሀሩን ሚዲያ

15.2k 0 10 24 374

Ministry of Education Ethiopia
እና

FBC (Fana Broadcasting Corporate S.C.)

ሒጃብና ኒቃብ ከስኬት አያግድም ስንላችሁ የማትሰሙ የደናቁራን ክምችት ናችሁ።

ይሄው እህታችን በመማሯ ከራሷ አልፋ ሃገሯን ወክላ በዓለም አቀፍ መድረክ ስማችሁን እያስጠራች ናት።

ነገር ግን ሒጃብ ለብሶ መማር አይቻልም ሲሉ የድንጋዩ ዘመን የአክሱም ጭራቆች ምንም አልተነፈሳችሁም።

እጅግ በጣም ኋላ ቀር፣ ድንዙዝ፣ ትምክህተኛና ጠባብ ስለሆናችሁ እንጂ፤ ቢገባችሁ ኖሮ 159 ተማሪ ከትምህርት ለአንድ አመት እንኳ ማገድ ትውልድንና ሃገርን አንድ እርምጃ ወደ ኋላ እንደመገተት ነው።

ግን እናንተ ሙስሊሙን ካጠቃችሁ ሃገር ብትጎዳም አይገዳችሁ።

ማፈሪያዎች! ደግሞ ወዳጅ መስላችሁ ሲሳካላቸው ትዘግባላችሁ። ውስጥ ውስጡንና በይፋ በሒጃባቸው ምክንያት የምትሠሩትን ሴራ ማን ይዘግብላችሁ እነ ነውር ጌጡ‼

Показано 20 последних публикаций.