"ቤተ ማርያም መንፈሳዊ ሚዲያ💒


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: Религия


🌹«ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን
/አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ።♥ https://t.me/Orthodoxtewahdoc

ሐምሌ 3 በ2014 ዓ°ም ተከፈተ።
📌እግዚአብሔር ቢፈቅድ የቅዱሳኑን ታሪክ እንመማርበታለን ብለን ከፈትነው ቅዱስ እግዚአብሔር ይፍቀድልን አሜን‼
❤የእመ ብርሃን ልጅ🤗

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
Религия
Статистика
Фильтр публикаций


አያምርብኝ ብዘነጋው ታሪኬን
ሚካኤል ነው ያስጌጠልኝ ህይወቴን
አረሳብኝ እርሱ አትርሳብኝ ያልኩትን
ለካስ ሰምቶ ይኖራል የልጅነት ፀሎቴን!!

🥰የመንገድ መሪየ ጠባቂዬ መልአከ ምክሩ አባቴ ቅዱስ ሚካኤል ሰላም ያሳድረን❤️


✥•••••●◉ ✞ ◉●•••••✥
✍️"የሚሰማኝ ግን በእርጋታ ይቀመጣል ከመከራም ሥጋት ያርፋል"📖ምሳ 1፥33☦📚
        
✥•••••●◉ ✞ ◉●•••••✥
📗ስንክሳር ዘወርኃ ሚያዝያ ፲፪/12

ወለተ ሥላሴ ብላችሁ በጸሎታችሁ አስቡኝ
https://t.me/Orthodoxtewahdoc
🌹የያዕቆብ ሌሊት ይሁንልን🕊




🔉ተግባራዊ ክርስትና (ለወጣቶች)ምዕራፍ አራት)

👂ስለ ትውስታዎችና ስለ ፈጠራ ስራዎች📚

🌷በፈንታነሽ ወለተ ሥላሴ


መፅሐፈ ሲራክ ምዕራፍ ፬--፮📚

የእግዚአብሔር ቸርነቱ ብዙ ነው እያልክ በኃጢአት ላይ ኃጢአት አትሥራ።ቸርነትም መቅሠፍትም ከርሱ ዘንድ ይመጣልና።

🩷እንደምን አመሻችሁ🌷


«ነገኮ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል ነው ወቶ ከመቅረት ቅዱስ ሚካኤል አባቴ ይጠብቀን።🙏

🌹በስደት ያለነውን ለሀገራችን ያብቃን ።አሜን🙏❤

1.3k 0 10 20 86

"አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አሜን ሚያዝያ 12- ዳግመኛም በዚኽች ዕለት የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤልን እግዚአብሔር ወደ ነቢዩ ኤርሚያስ ላከው፡፡ ነቢዩ ኤርሚያስን ጠባብና ረግረግ ከሆነ እሥር ቤት ንጉሥ ሴዴቅያስ ባሠረው ጊዜ የንጉሡ ባለሟልና የጭፍራ አለቃ የሆነው ኢትዮጵያዊው አቤሜሌክ አውጥቶታል፡፡ ያንጊዜም የኢየሩሳሌምን ጥፋት እንዳያይ መራራ ምርኮንም እንዳይቀምስ ነቢዩ ኤርሚያስ መረቀው፡፡ እንደመረቀውም ሆነለትና ኢትዮጵያዊው አቤሜሌክ 66 ዓመት ተኝቶ ኖረ፡፡ ከእርሱም ጋራ ወይንና በለስ ነበረ፣ ነገር ግን አልተለወጠም ነበር፡፡ የእስራኤልም ልጆች ከምርኮ እስኪመለሱ ድረስ የኢየሩሳሌምንም ጥፋት እንዳያይ እግዚአብሔር በመልአኩ በቅዱስ ሚካኤል አማካኝነት ጠብቆታል መግቦታልም፡፡
+ ፡፡ ረድኤት በረከታቸው ይደርብን፣ በጸሎታቸው ይማረን!
+ + + + +
ቴሌግራማችንን ይቀላቀሉ

https://t.me/Orthodoxtewahdoc


📘#ተአምር አባ ሳሙኤል ዘዋልድባ🌹

📕☞ወር በገባ በ12 የአባታችን የበርሃው መናኝ የአባ ሳሙኤል (ዘዋልድባ)ወራሒው መታሰቢያው ነው፡፡☞ህግን የሚጠብቅ ትእዛዝን የሚፈጽም የነብያትና የሐዋርያት ወገን በሽተኞችን የሚፈውስ የነፍሳት መድኃኒት የእግዚአብሔር ሰው የማር አባ ሳሙኤል ታምር ይህ ነው፡፡

☞የከበራችሁ አሕዛብ ሆይ አባታችን ብጹአዊ ማር አባ ሳሙኤል ከተማሪዎቹ ጋር አርብ ቀን በገዳም ውስጥ ሲመላለስ እግዚአብሔር ያደረገውን እነግራችሁ ዘንድ በማስተዋልና በጥበብ ስሙ፡፡
☞ምሽት በሆነ ጊዜ በአለት መካከል አደሩ፤ የሚመገቡትም አጡ፡፡ አባታችን
ብቻውን ራቅ አለ፡፡ ☞እጆቹን ዘርግቶ አይናቹን አንጋጦ ወደ አምላኩ፤ወደ እግዚአብሔር ጸለየ፡፡ እንዲህም ብሎ አቤቱ ሰውን የምትወድ የምሕረት አምላክ ፍጥረትን የምትወድ የምህረት አምላክ ፍጥረትን ሁሉ የምትመግብ በበረሃ አረባ ዘመን ሳይዘሩ ሳይሰበስብ እስራኤል የመገብካቸው አሁንም ለተቸገሩት ለእነዚህ አገልጋዮች ምግባቸውን ስጣቸው፡፡

☞እንደዚህ ከጸለደ በኀላ ተማሪዎቹ ወደ አሉበት የእግዚአብሔር ስልጣን ይዞ
ተመለሰ በአደሩበት በዚያች እለት ላይ ሦስት ጊዜ ባረከ ከትልልቅ አሳዎች ጋር
በእርሱ ውኃ ፈለቀ፡፡
☞ብጹአዊው ከእስራኤል ልጆች ወገን የሆኑ ልጆቹን ይህች ዉኃ ከዚህ ዓሣ ጋር
ተሰጠኝ በይቅርታው ብዛት ይህን ስለሰጠን እግዚአብሔር እያመሰገናችሁ
ለቀዳሚት ሰንበትና ለእሁድ የሚያበቃንን ያዙ አላቸው፡፡ ቸርና ሰው ወዳጅ ነውና፡፡
☞ከእርሱ ይህንን ነገር በሰሙ ጊዜ አባታችን ብጹአዊ ማር ሳሙኤል ያደረገውን
ተአምር አይተው ፈጽመው ተደሰቱ፡፡ እግዚአብሔርንም አመሰገኑት፡፡
☞እንደ አዘዛቸው አደረጉ፡፡ ለሁለት ቀኖች ያህል ከሰበሰቡት እየተመገቡ
ተቀመጡ፡፡
☞ሁለተኛ ቀን ሰኞ በነጋ ጊዜ የተረፈውን ምግባቸውን ይሰበስቡ ዘንድ
ተማሪዎቹን ዳግመኛ አዘዛቸው በዚያምች ውሃና ተይዘው በተበሉት በእነዚያም
አሣዎች ላይ ባረከ እንደ መጀመሪያውም ሕያው ሆኑ ወደ ዚያች ዐለትም ገቡ፡፡
ተዘጋጅ እንደ ቀድሞም ሆነች፡፡
☞ስም አጠራርህ መልካም የሆነ የእስራኤል ወገን ምሁር የስድሳ ነገስታት ወገን
ለልጆችህ ምግብ ከዓሣ ጋር ከደረቅ ዐለት ውሃን ያፈለቅህ ብጹአዊ አባት አባ
ሳሙኤል (ዘዋልድባ) ጸሎትህ ሀጥያታችንን በደላችንን የሚያስተሰርይልን
ይኹነን፡፡ ለዘላለሙ አሜን
☞(ገድለ አቡኑ ሳሙኤል ዘዋልድባ)
☞ሲራክ ተክለጻዲቅ የተዋህዶ ልጅ https://t.me/Orthodoxtewahdoc




📕#ቅዱስ_ላሊ_በላ🌹

📘☞ወር በገባ በ12 ታስቦ የሚውለው ቅድስናን ክንግስና ጋር ንግስና ከቅድስና ጋር አስተባብሮ የያዘ ቅዱስ ላሊበላ ያደረገው ተዓምር ይህ ነው፡፡
☞ከዕለታት በአንድ ቀን ቅዱስ ላሊበላ እራት ሊበላ ሲዘጋጅ እንዲህ ሆነ፡፡
☞ሦስት ሰዎች በቤተ መንግሥቱ አዳራሽ አቅራቢያ እርሱ ወደ ተቀመጠበት
መጡ፡፡ እነዚህ ሦስት ሰዎች አቤቱ ጌታችን ምንበላው ሥጠን ዛሬ የምንበላው
የለንምና ብለው ለመኑት አንዱ ይህን በአለው ጊዜ ቅዱስ ላሊበላ ሊጎርስ በእጁ
የያዘውን አንዱ ጉርሻ ሠጠው፡፡
☞ሁለተኛም እንደዚያ ለመነው፡፡ለእርሱም ሁለተኛውን ጉርሻ ሰጠው፡፡
ሦስተኛውም እንደዚያ ለመነው ሦስተኛውን ጉርሻ ለሦስተኛው እንዲሰጠው
ረዱን አዘዘው፡፡
☞ቅዱስ ላሊበላ ሲመገብ ያለ ሶስት ጉርሻዎች አይበላም ነበርና ሦስቱም
ፈጽሞ ተሠጠ ረዱ የቅድስ ላሊበላ ምግብ እንዳለቀ ባየ ጊዜ የእንጀራውን
ጠርዝ ወስዶ በጎመን ለውሶ እንዲበላ ሠጠው፡፡
☞ቅዱስ ላሊበላ የምበላው ሰሦስቱን ጎርሻ ለተቸገሩት ከሰጠሁ በኃላ ሌላ
ቁራሽ እመገባለሁ ብሎ እምቢ አለ፡፡ ይህንን የሰጠህኝንማ ከበላሁ ስለ ሰጠሁት
ፈንታ ሌላውን ብበላ እንዳልሰጠሁ መሆኔ ነው ብሎ፡፡ ይህን ተናግሮ ቅዱስ
ላሊበላ ጾሙን አደረ፡፡
☞ይኸውም የእግዚአብሔር ቃል ነው፡፡ ከራሳችሁ ይልቅ ባልንጀራችሁን ውደዱ
የምትለዋን በሐዋርያው አንደበት የተነገረችውን ቃል ፈጽሟታልና፡፡
☞ይህችው ቃል በቅዱስ ላሊበላ ተፈጸመች፡፡ራሱ ተርቦ ሌሎዎችን
እንዲያጠግብ፡፡ራሱ ተጠምቶ ሌሎችን እንዲያረካ፡፡ ጌታ በወንጌል ስለ ጽድቅ
የሚረቡ የሚጠሙ ንዑዳን ናቸው እነሱ ደስ ይሰኛሉ ይጠግቡማል እንዳለ፡፡ ማቴ
ም 5፡፡ ይህችንም ቃል ለመፈጸም ቅዱስ ላሊበላ እራሱ የሚመገባቸውን ሦስት
ጉርሻዎች ሰጠ፡፡
☞ ንጉሥ ሲሆን የሚሠጠው አጥቶ አይደለም በእግዚአብሔር ዘንድ ዎጋ
እንዲያገኝ ምግቡን ሠጠ እንጂ፡፡
☞ከዚህም በኃላ ለሦሥቱ ሰዎች ረዱን ሌላ የሚበላ የሚጠጣ ተራቁተውም
ሲያይ ልብስ እንዲሠጣቸው አዘዘው፡፡
☞አገልጋዩ ረዱም በወጣ ጊዜ እኒዚያ ሦስቱ ሰዎች ወደ ሰማይ ሲያርጉ
አያቸው፡፡
☞ወደ ገብረ መስቀል(ቅዱስ ላሊበለ) እንዲጎበኙትና ቸርነቱን ለመፈተን የመጡ
መላእክት ናቸውና፡፡
☞ጌታችንም እንግዳ ተቀባዮችን ራሱ እንግዳ ሆኖ ይጎበኛቸዋልና፡፡ ከአብርሃም
ቤት እንግዳ ሆኖ እንደገባ ዘሩንና እሱን እንደባረካቸው፡፡
☞ቅዱስ ላሊበላ በዘመነ መንግሥቱ ከሦስቱ ጉርሻ በስተቀር ሌላ
አልተመገበም፡፡ ከአንዲት ጽዋ ውሃ ሌላ አይጠጣም ነበርና፡፡
☞ጸሎት ልመናው ተራዳይነቱ በዚህ በቅዱስ እና በንጉሥ ላሊበላ በጸሎቱ
ለምታምኑ ይሁን፡፡
☞( ገድለ ቅዱስ ላሊበላ)
https://t.me/Orthodoxtewahdoc




✝እንኳን አደረሳችሁ✝
††† እንኳን ለነቢየ እግዚአብሔር ቅዱስ ኤርምያስ ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን። †††

††† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! †††

††† ቅዱስ ኤርምያስ †††

††† ታላቁ ነቢይ ቅዱስ ኤርምያስ ከዐበይት ነቢያት አንዱ ሲሆን ቅድመ ልደተ ክርስቶስ በ600 አካባቢ የነበረ ነቢይ ነው:: አባቱ ኬልቅዩ ይባላል:: ከካኅናተ እስራኤል አንዱ ነበር::

እግዚአብሔር ኤርምያስን የጠራው ገና በሕጻንነቱ ነበር:: "ከእናትህ ማሕጸን ሳትወጣ መርጬሃለሁ: ቀድሼሃለሁ" ሲልም በገሃድ መስክሮለታል:: (ኤር. 1:5)

ከቅዱሳን ነቢያት እንደ ኤርምያስ የተሰቃየና ያለቀሰ የለም:: ከ70 ዘመናት በላይ ስለ ወገኖቹ አልቅሷልና:: ሊቃውንት "ነቢየ ብካይ" (ባለ እንባው ነቢይ) ይሉታል::

ዘመኑ ዘመነ ኃጢአት (ዘመነ ዐጸባ) ነበር:: እሥራኤላውያን ከመሪዎቻቸው ከነ ሴዴቅያስ ጋር በክፋት ተባብረውም ነበርና ኤርምያስን አልሰሙትም:: ይልቁኑ ክፉ ቦታ ውስጥ አስረው አሰቃዩት:: እግዚአብሔር ግን በኢትዮዽያዊው አቤሜሌክ አማካኝነት ከመከራው አዳነው::

የተሰበከላቸውን የንስሃ ጥሪ አልሰሙምና ስልምናሦር የሚባል የአሕዛብ ንጉሥ መጥቶ አሥሩን ነገድ ማርኮ አሦር (ነነዌ) አወረዳቸው:: በሁዋላ ደግሞ በኃይለኝነቱ የታወቀው የባቢሎን ንጉሥ ይማርካቸው ዘንድ ወደ ሁለቱ ነገድ ኢየሩሳሌም ደረሰ:: ኤርምያስ ወደ ከተማዋ ዳር ወጥቶ ስለ ኢየሩሳሌምና ስለ እግዚአብሔር ቤተ መቅደስ አለቀሰ::

ከቤተ መቅደስ ንዋያት እኩሉን ለምድር አደራ ሰጣትና ሸሸገችው:: ነቢዩ የተናገረው አይቀርምና ንጉሡ ናቡከደነጾር እኩሉን ገድሎ: እኩሉንም ማርኮ: ኢየሩሳሌምን አቃጥሎ: የአሕዛብ መዘባበቻ አድርጐ ባቢሎን አወረዳቸው::

ቅዱስ ኤርምያስን ግን ትሩፋን (ከመከራው የተረፉት) ይዘውት ወደ ግብፅ ወረዱ እንጂ አልተማረከም::

በዚያም ተአምራትን አድርጐ አራዊትን አጥፍቷቸዋል:: ትንሽ ቆይቶ ግን እውነተኛ አባት: ነቢይ: መምሕርም ነውና ወደ ሕዝቡ (ወደ ባቢሎን) ወረደ:: በዚያም ትንቢትን እየተናገረ: ሕዝቡን ከ70 ዓመታት በሁዋላ ወደ ሐገራቸው እንደሚመለሱ እያስተማራቸው በባቢሎን ቆይቷል:: ያለ በደሉም በመከራቸው ተካፋይ ሆኗል::

ሰባው ዘመን ሲፈጸም እግዚአብሔር እንደ ቃል ኪዳኑ በኤርምያስ መሪነት እሥራኤል ወደ ኢየሩሳሌም ተመለሱ:: አሁንም ግን ክፋታቸውን ይተው ዘንድ ፈቃደኞች አልነበሩምና ኤርምያስ ገሠጻቸው::

በዚህ ተበሳጭተው ሊወግሩት ሲሉ ጸጋ በዝቶለት: ምስጢርም ሰፍቶለት ስለ ነገረ ሥጋዌ (ስለ ክርስቶስ የማዳን ሥራ) አምልቶና አጉልቶ ትንቢት ተናገረ:: አንዴ ልቡናቸው ታውሮ ኤርምያስ ነው ብለው ድንጋዩን በድንጋይ ሲወግሩት ውለዋል:: ዘግይቶ ግን ኤርምያስ ራሱን ገለጠላቸው:: ስለ እነርሱ ሲል 70 ዘመን ያለቀሰውንና ምትክ የሌለውን አባታቸውን ወግረው ገደሉት::

ታላቁ ነቢይ ቅዱስ ኤርምያስ 52 ምዕራፎች ያሉት ሐረገ ትንቢት ተናግሯል / ጽፏል:: ዜና ሕይወቱ ከራሱ የትንቢት መጽሐፍ በተጨማሪ በተረፈ ኤርምያስ: በመጽሐፈ ባሮክ: በገድለ ኤርምያስ: በዜና ብጹዐን: በመጽሐፈ ስንክሳርም ተጽፏል::

በዚህች ዕለት ንጉሡ ሴዴቅያስ ቅዱስ ኤርምያስን አስሮት እያለ ኢትዮዽያዊው ቅዱስ አቤሜሌክ ያስፈታበት (ከረግረግ ያወጣበት) ይታሰባል::

††† ቸር እግዚአብሔር በኤርምያስ ምልጃ ሃገራችንን ከጥፋት: ሕዝቦቿን ከስደትና ከመቅሰፍት ይሰውርልን::

††† ሚያዝያ 12 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
1.አቡነ ሳሙኤል ዘቆየጻ (ኢትዮዽያዊ)
2.ቅዱስ ኤርምያስ ነቢይ
3.ቅዱስ አቤሜሌክ ኢትዮዽያዊ
4.ቅዱስ ባሮክ
5.ቅዱስ እለእስክንድሮስ ዘኢየሩሳሌም

††† ወርሐዊ በዓላት
1.ቅዱስ ሚካኤል ሊቀ መላዕክት
2.ቅዱስ ማቴዎስ ሐዋርያ
3.ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ
4.ቅዱስ ቴዎድሮስ ምሥራቃዊ (ሰማዕት)
5.ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ
6.አቡነ ሳሙኤል ዘዋልድባ
7.ቅዱስ ድሜጥሮስ

††† "ኢየሩሳሌም ሆይ ነቢያትን የምትገድል: ወደ እርሷ የተላኩትንም የምትወግር: ዶሮ ጫጩቶቿን ከክንፎቿ በታች እንደምትሰበስብ ልጆችሽን እሰበስብ ዘንድ ስንት ጊዜ ወደድሁ! አልወደዳችሁምም:: እነሆ ቤታችሁ የተፈታ ሆኖ ይቀርላቹሃል:: እላችሁአለሁና: በጌታ ስም የሚመጣ የተባረከ ነው እስክትሉ ድረስ እንግዲህ ወዲህ አታዩኝም::" †††
(ማቴ. 23:37-39)

††† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †††

https://t.me/zikirekdusn
💠"መንግሥተ ሰማያት ቀርባለችና ንስሐ ግቡ::"💠    /ማቴ ፫:፫/
🔷ዝክረ ቅዱሳንን ተማሩ ብለን እንለምናችኋለን!!

❇️ዝክረቅዱሳን (ማኅበረ ቅዱስ ዳዊት)❇️

" 🔶ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን"::/የቅዱሳንን ዜና(ታሪክ) እንድመሰክር ፍቅር ያስገድደኛል::🔸
       አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ /መጽሐፈ ምሥጢር/
https://t.me/zikirekdusn




በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ
           አሜን

✍️ "በበጎ ሥራ ሁሉ ፍሬ እያፈራችሁ በእግዚአብሔርም እውቀት እያደጋችሁ፥
ለጌታ እንደሚገባ ትመላለሱ ዘንድ እንለምናለን"
📖ቆላስይስ 1፥10-11

           ቀናችንን በጸሎት እንጀምር

       ✥••┈┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈┈••✥
ወዳጄ ሆይ እስኪ ንገረኝ ለምንድነው የምታዝነው❓
       ✥••┈┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈┈••✥

ድሃ ስለሆንክ ነውን❓

❖ ይልቁንስ በዚህ ምክንያት በማዘንህ ልታዝን ይገባሃል፤ ማዘን የሚገባኽ ድሃ ስለሆንክ ሳይሆን ከእግዚአብሔር ሐሳብ ምን ያህል እንደራቅክ በማሰብ ልታዝን ይገባሃል፡፡

❖ ሐሳብህን ከጊዜአዊው ገንዘብ አንሥተህ ሰማያዊውን አክሊል ሽልማትህን ባለማሰብህ ልታዝን ልትተክዝ ይገባሃል፡፡

❖ ቅዱስ ጳውሎስ በየቀኑ ይገደል ነበር፤ ነገር ግን አላዘነም፤ አላለቀሰም፤ ደስ ይለው ነበር እንጂ፤ ብዙ ጊዜ በረሃብ አለንጋ ይጠበስ ነበር፤ ነገር ግን አላዘነም፤ አላጉረመረመም፤ ይከብርበት ነበር እንጂ፤ ታድያ አንተ የዓመት ቀለብ የለኝም ብለህ ታዝናለህን “እኔ እኮ የቤተሰብ አባወራ ነኝ፤ ልጆችን አሳድጋለሁ፤ ሠራተኛ አለኝ፤ ሚስት አለችኝ፡፡

❖ ቅዱስ ጳውሎስ ግን ቢያስብ ለራሱ ብቻ ነው” ልትለኝ ትችላለህ፤ እኔም እንዲህ ብዬ እመልስሃለሁ ቅዱስ ጳውሎስ ያስብ የነበረው ለራሱ ብቻ አይደለም፤ ለዓለም ኹሉ እንጂ፤ አንተ አንድን ቤተሰብ ለማስተዳደር ትጨነቃለህ፤ ርሱ ግን ዓለምን ሁሉ ለማስተዳደር ይጨነቅ ነበር፤ በኢየሩሳሌም ለነበሩ ድሆች ይጨነቅላቸው የነበረው ርሱ ነው፡፡

❖ በሜቄዶንያ ለነበሩት ያስብላቸው የነበረው እርሱ ነው፤ በየቦታው ለነበሩ ድኾች ይጨነቅላቸው የነበረው ርሱ ነው፤ ያስተዳድራቸው ከነበሩት ሰዎች ከሚሰጡት ይልቅ የሚረዱ ይበዙ ነበር፡፡

❖ ለዓለም ሁሉ ማሰቡ በሁለት ወገን ነበር፤ በአንድ ወገን እንዲሁ የሚበሉት አጥተው እንዳይጐዱ፤ በሌላ ወገን ደግሞ በመንፈሳዊ ሕይወታቸው ባለጸጐች እንዲሆኑ፤ ስለዚህ አንተ ለልጆችህ ከምታስበው በላይ ቅዱስ ጳውሎስ ለዓለም ሁሉ ያስብ ነበር ብዬ እነግርሃለሁ፡፡

❖ ቅዱስ ጳውሎስ ያስብ የነበረው ለሚያምኑት ልጆቹ ብቻ እንዳይመስልህ፤ ለማያምኑትም ጭምር ይጨነቅላቸው ነበር እንጂ፤ እነርሱ ድነው እርሱ በነርሱ ፈንታ እንዲረገም ይመኝ ነበር፤ እነርሱ የዘለዓለም ሕይወት አግኝተው ርሱ ገሃነም እንዲገባ ይመኝ ነበር።
📖ሮሜ 9፥1-3

❖ አንተ ግን ምንም ዓይነት ቁጣ ቢመጣም “እኔ ልራብልህ” ብለህ ስለወንድምህ አትሞትም፤ አንተ ለአንዲት ሚስትህ ብቻ ትጨነቃለህ፤ ቅዱስ ጳውሎስ ግን “ዕለት ዕለት የሚከብደኝ የአብያተ ክርስቲያናት ሁሉ ሐሳብ ነው” እንዳለ፤ ይጨነቅ የነበረው በዓለም ሁሉ ላሉት አብያተ ክርስቲያናት ነው፡፡
📖2ኛ ቆሮ 11፥28

❖ ወዳጄ ሆይ ታድያ ለምንድነው ከቅዱስ ጳውሎስ በላይ እንደምታስብ አድርገህ ራስክን የምትመለከተው❓

❖ በምን ያህል ርቀት እንዳለህስ አታስተውልምን❓

❖ ስለዚህ ማዘን፣ ማልቀስ የሚገባን በድህነት ውስጥ ስላለን አይደለም፤ ማልቀስ ማንባት የሚገባን በኃጢአት ማጥ ውስጥ ስንገባ ነው፤ የሚገባ ኀዘን ይኸው ነው፤ ከኃጢአት በቀር ለሌላ ማዘን እንዲሁ ተራ ነገር ነው ብዬ በእውነት ያለ ሐሰት እነግርሃለሁ፡፡

✍️"የሚሰማኝ ግን በእርጋታ ይቀመጣል ከመከራም ሥጋት ያርፋል"
📖ምሳ 1፥33


📌ምንጭ
✍ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ


🔔 ከመምህራን የማንን ትምህርት ማግኘት ይፈልጋሉ?
👇👇👇

ነካ ያድርጉት

┏━━━━━━━━━━━━━━┓
🔔 መምህር ምሕረተአብ አሰፋ
┗━━━━━━━━━━━━━━┛
┏━━━━━━━━━━━━━━┓
🔔 መምህር ዘበነ ለማ
┗━━━━━━━━━━━━━━┛
┏━━━━━━━━━━━━━━┓
🔔 መምህር ሄኖክ ኃይሌ
┗━━━━━━━━━━━━━━┛
┏━━━━━━━━━━━━━━┓
🔔 መምህር ዮርዳኖስ አበበ
┗━━━━━━━━━━━━━━┛
┏━━━━━━━━━━━━━━┓
🔔 አባ ገብረ ኪዳን
┗━━━━━━━━━━━━━━┛
┏━━━━━━━━━━━━━━┓
🔔 መምህር ያረጋል አበጋዝ
┗━━━━━━━━━━━━━━┛
┏━━━━━━━━━━━━━━┓
🔔መጋቢ ሐዲስ እሸቱ አለማየሁ
┗━━━━━━━━━━━━━━┛
┏━━━━━━━━━━━━━━┓
🔔 መምህር እዮብ ይመኑ
┗━━━━━━━━━━━━━━┛
┏━━━━━━━━━━━━━━┓
🔔መምህር ገብረ እግዚአብሔር
┗━━━━━━━━━━━━━━┛
┏━━━━━━━━━━━━━━┓
🔔መምህር አባ ገብረ ኪዳን
┗━━━━━━━━━━━━━━┛

🔗የሁሉንም መምህራን ትምህርት ለማግኘት🔔
🫧🫧🫧🫧JOIN🫧🫧
🫧🫧


🌷እንደምን አደራችሁ ቤተሰብ 🥰

"ወዳጆቼ ከልባችን ኦርቶዶክስ ከሆንን እንደ ኤሳው ብኩርናችንን በምስር አንሽጥ እምነት ሀገራችንን ቅድስት ቤተክርስቲያናችንን በቻልነው መጠን አናስደፍር እንጠብቅ ወላጆቻችንን አናክብር።📍

❤መልካም ዕለተ አርብ ይኹንልን ቸሩ መድኃኔዓለም ከክፉ ነገር ይሰውረን አሜን ✝🙏


🌷መልክአ ቅዱስ ያሬድ📚

አቤቱ አምላከ ቅዱስ ያሬድ እግዚአብሔር ሆይ! እኔን ወለተ ሥላሴን ይልቁኑ ሙሉ ህዝበ ክርስቲያን ከመከራ ስጋ ከመከራ ነፍስ ጠብቀን ቤተሰባችንንና ልጆቻችንንም በጤናና በህይወት ምላቸው ቅድስት ሃገር ኢትዮጵያንም በረድኤት ጎብኛት ዛሬም ዘወትርም ለዘለዓለሙ አሜን🤲🌷


✥•••••●◉ ✞ ◉●•••••✥
✍️"የሚሰማኝ ግን በእርጋታ ይቀመጣል ከመከራም ሥጋት ያርፋል"📖ምሳ 1፥33☦📚
        
✥•••••●◉ ✞ ◉●•••••✥
📗ስንክሳር ዘወርኃ ሚያዝያ ፲፩/11

ወለተ ሥላሴ ብላችሁ በጸሎታችሁ አስቡኝ
https://t.me/Orthodoxtewahdoc
🌹የያዕቆብ ሌሊት ይሁንልን🕊




🌷አርብ የፍቅር ቀን❤

ጌታ ሆይ ስለ ሰው ልጆች ፍቅር ስትል በዕለተ አርብ በቆረስከው ስጋህ ባፈሰሰከው ደምህ ብለህ አቤቱ  ማረን ይቅርም በለን፡፡🙏

Показано 20 последних публикаций.