⚖️Shields Law🇪🇹 የህግ አገልግሎት / Legal service ⚖️


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: Право


⚖️ Shields Law ⚖️.
ነፃ የህግ የማማከር አገልግሎት፣ የተለያዩ ህጎች፤ አዋጆች፣ ደንቦች፣ መመሪያዎች፣ የውል ፎርሞች፤ መፅሐፍቶች እዚሁ ያገኛሉ። Here on our channel, we provide Free legal Aid. You could alsk get access to laws, cassation decisions, job opportunity updates.
ለማስታወቂያ
👉@alexyoba21

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
Право
Статистика
Фильтр публикаций


የስራ ቅጥር ማስታወቂያ ለአዲስ ተመራቂዎች

ታክስ ይግባኝ ኮሚሽን

የስራ መደብ፦ ረዳት ዳኛ

የትምህርት ደረጃ፦ በሕግ የመጀመሪያ ዲግሪ

የስራ ልምድ፦ 0 ዓመት

የምዝገባ ጊዜ፦ እስከ ሚያዚያ 9 ቀን 2017 ዓ.ም
https://t.me/Shields_Law


አር.ቲ.ዲ. (RTD)
• የተፋጠነ የወንጀል ክርክር ስርዓት
የጉዳዮችን መራዘም ለማስቀረት የተቀየሰው የተፋጠነ የወንጀል አሰጣጥ (RTD) መሰረታዊ ዓላማ በማስረጃ ደረጃ ውስብስብነት የሌላቸውን ጉዳዮች በቀላሉ ለመወሰን አዲስ አሠራር ለመዘርጋት ማስቻል ከሚሆን በስተቀር በሕገ መንግስቱና በሌሎች ተፈጻሚነት ባላቸው ሕጎች የተጠበቁትን የተከሳሽን መብቶች በሚጎዳ አኳኃን ለመተግበር አለመሆኑ ይታወቃል፡፡ በመሆኑም በሕጉ የተጠበቁት መብቶችና የዳኝነት አካሄዶች በሕጉ አግባብ ተተግብረው ዳኝነት ከሚሰጥ በስተቀር አንድ ጉዳይ የተፋጠነ የወንጀል አሰጣጥን (RTD) መሰረት አድርጎ በመቅረቡ ብቻ ቀሪ የሚሆኑ አይደሉም፡፡ የተፋጠነ የወንጀል አሰጣጥ (RTD) አሰራርን መሰረት አድርጎ የሚታይ ጉዳይ የተከሳሹን የመከላከል መብት ለመተው የሚያስችለው ተከሳሹን ይህንኑ መብቱን በማሻያማ አኳኋን የተወው መሆኑን ሲያረጋገጥ ነው፡፡
የተከሳሽ ክስን የመከላከል መብት ሊታለፍ የሚገባው ተከሳሹ መብቱን የማይጠቀምበት መሆኑን በግልፅ ለፍርድ ቤቱ ሲያረጋግጥለት ብቻ ነው፡፡ ተከሳሹ መብቱን ስለመተዉ ባልተረጋገጠበት አግባብ ግን የተከሳሽን የመከላከል መብት ተከሳሹ ትቷል የሚል አገላለፅ በፍርድ ሐተታው ላይ በማስፈር ብቻ ዳኝነት መስጠት ተገቢነት የሌለው አካሄድ ነው፡፡
ሰ/መ/ቁ 100712 ቅጽ 17፣ ኢ.ፌ.ዲ.ሪ. ህገ መንግስት አንቀጽ 9/4/፣ 13/1/ እና /2/፣ 20/4/https://t.me/Shields_Law


ከጋብቻ በፊት የነበረ የግል ቤት በትዳር ዉስጥ ከፍተኛ ወጪ ወጥቶ ማሻሻያ እና ማስፋፊያ ቢደረግለትም የጋራ ንብረት ሊሆን አይገባም፡፡ (የፌደሬሽን ምክር ቤት መስከረም 28-2017 ዓ.ም)‼️

ቀደም ሲል ከጋብቻ በፊት የግል የነበረ ቤት በትዳር ዉስጥ መሰረታዊ በሚባል ደረጃ እድሳት ከተደረገለት ወይም ከፍተኛ ወጪ ወጥቶ ማሻሻያ ከተደረገለት ቤቱ የባልና ሚስት የጋራ ይሆናል በማለት በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ዉሳኔ ተሰጥቶ ነበር፡፡ ይህ የሰበር ሰሚ ችሎቱ ዉሳኔ ሕገ-መንግስቱን ይቃረናል በሚል የሕገ-መንግስት ትርጉም ለፌደሬሽን ምክር ቤት ቀርቦት የነበር ሲሆን  የፌዴሬሽን ምክር ቤቱ መስከረም 28-2017 ዓ.ም  በሰጠዉ ዉሳኔ የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት የሰጠዉን ዉሳኔ በመሻር ተፈጻሚነት የለዉም ብሏል፡፡ፌደሬሽን ምክር ቤት ዉሳኔ ከጋብቻ በፊት የግል የነበር ቤት በጋብቻ ዉስጥ ማሻሻያ እና ማስፋፊያ  መደረጉ ቤቱን የጋራ ንብረት አያደርገዉም፡፡ ቤቱን ለማሻሻል እና ለማስፋፋት የወጣ ወጪ ተጣርቶ ወጪዉ በድርሻ እንዲወስዱ ከሚደረግ በስተቀር ቤቱ የጋራ አይሆንም፡፡

====================
https://t.me/Shields_Law


የፌዴራል መንግሥት በክልሎች ጣልቃ የሚገባበትን ሥርዓት የሚያሻሽለው አዋጅ ፀድቋል።

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው 22ኛ መደበኛ ስብሰባ የፌዴራል መንግሥት በክልሎች ጣልቃ የሚገባበትን ሥርዓት ለመደንገግ የወጣ የማሻሻያ አዋጅን መርምሮ አጽድቋል።

አዋጁ እስከ አሁን በሥራ ላይ የነበረውን አዋጅ ቁጥር 359/ 1995 የሚያሻሽል ሲሆን፤ አዋጅ ቁጥር 1373/2017 ሆኖ በሁለት ድምጸ ተዐቅቦ በአብለጫ ድምፅ ጸድቋል፡፡

አዋጁ የክልል ጊዜያዊ አስተዳደርን የቆይታ ጊዜ የማራዘም ስልጣን፤ ለፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ የሚሰጥ ነው።

አዋጁ የፌደራል መንግስት በክልሎች የሚያቋቁመውን ጊዜያዊ አስተዳደር የስራ ዘመን ለሁለት ጊዜ የማራዘም ስልጣን ለፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ የሚሰጥ ነው።

የአፈ ጉባኤው ውሳኔ በፌዴሬሽን ምክር ቤት መደበኛ ጉባኤ ተቀባይነት ካላገኘ፤ ጊዜያዊ አስተዳደር በተቋቋመበት ክልል “ በአራት ወራት ጊዜ ውስጥ ምርጫ እንዲደረግ “ ያስገድዳል።

ይህ አዋጅ የፌዴራል መንግስት በክልሎች ጣልቃ የሚገባበትን ስርአት ለመደንገግ በ1995 ዓ.ም የወጣውን አዋጅ ያሻሻለ ነው።
https://t.me/Shields_Law


➽አንድ ሰው በአሳዳጊው ስም እንዲጠራ ተብሎ እንዲወሰንለት ለፍርድ ቤት የስም ለውጥ ዳኝነት ሲጠይቅ ህጉ ምን ይላል?
ከጅምሩ አንድ ሰው በአሳዳጊው ስም እንዲጠራ በፍርድ ቤት ዳኝነት የሚያገኝበት የሕግ መሰረት የለም፡፡
በመሆኑም ይህንን አይነት አቤቱታ አቅራቢው ሰው ወላጅ አባቴ ናቸው በማይላቸው ሰው የቤተዘመድ ስም ልጠራ ይገባል በማለት የሚያቀርበው ጥያቄ በሕጉ ስለስም ለውጥ ጥያቄ ማቅረብ ስለሚቻልባቸውና እንዲሁም የዳኝነት አካሉም ለመቀበል መሟላት ከሚገባቸው ሕጋዊ መስፈርቶች ይዘትና ሕጋዊ ውጤት ጋር አብሮ የማይሄድ በመሆኑ ተቀባይነት የሚያገኝበት አግባብ የለም።
በጠቅላላው አንድ ሰው #በወላጅ አባቴ ስም መጠራቴ ቀርቶ #በአሳዳጊዬ ስም እንድጠራ ብሎ የሚያቀርበው የዳኝነት ጥያቄ በሕጉ #ስለስም ለውጥ የተጠቀሱትን ድንጋጌዎች የማያሟላ በመሆኑ ተቀባይነት የሌለው ጉዳይ ስለመሆኑ የፍ/ሕ ቁ.32(1)፣36(1)መሠረት በማድረግ የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በሰ/መ/ቁ. 116977 በቀን የካቲት 25 ቀን 2008 ዓ/ም በዋለው ችሎት አስገዳጅ የህግ ውሳኔ ሰጥቷል።
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 ቅፅ 19


የራሳችሁን አስተያየት ስጡበት እስቲ።።።።።።። አሰብ🇪🇹




ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ለ1446ኛው የኢድ አል-ፈጥር በአል በሠላም አደረሳችሁ !




Vacancy at Federal Supreme court of Ethiopia

Apply before 14th March,2017 E.C

Application:- in person or via email
For additional law vacancy Join us👇👇👇
https://t.me/Shields_Law
https://t.me/Shields_Law




❗አንድ ሰው የወራሽነት የምስክር ወረቀት የያዘ ቢሆንም ንብረቱን ይዞ እስካልተጠቀመ ድረስ የውርስ ንብረቱን በያዘው ሰው ላይ የሚያቀርበው ክስ በፍ/ብ/ሕ/ቁጥር 1000/1/ መሰረት በ3 ዓመት ይርጋ ቀሪ ነው።

የወራሽነት ጥያቄ የጊዜ ገደብ የለውም በሚል ከዚህ በፊት የተሰጡ የሰበር ውሳኔዎችን በመለወጥ በ7 ዳኞች የተሰጠ አዲስ የህግ ትርጉም። የሰ/መ/ቁ 243973 ጥቅምት 06/ 2017 ዓ.ም

የወራሽነት የምስክር ወረቀት የያዘ ሰው በማንኛውም ጊዜ የውርስ ንብረት ጥያቄ ማንሳት ይችላል በማለት ከአሁን በፊት በሰ/መ/ቁ 205248  44237 ቅፅ(10) 38533  ቅፅ(10)  ወዘተ.. የተሰጡ የሰበር ውሳኔዎች በዚህ የሰበር ውሳኔ ተለውጠዋል።

አንድ ሰው የወራሽነት የምስክር ወረቀት የያዘ ቢሆንም ንብረቱን ይዞ እስካልተጠቀመ ድረስ የውርስ ንብረቱን በያዘው ሰው ላይ የሚያቀርበው ክስ በፍ/ብ/ሕ/ቁ. 1000/1/ መሰረት በ3 ዓመት ይርጋ ቀሪ ነው።





Показано 14 последних публикаций.