Фильтр публикаций




የግብጽ ዛቻ ቀጥሏል
ግብጽ የቀይ ባህር አካል ያልሆነ ማንኛውም ሀገር በባህሩ ላይ የባህር ሀይል እንዲያቋቁም አልፈቅድም አለች!!

ካይሮ ይህን ያለችው በውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ የተመራ ልዑክ በኤርትራ ከፕሬዝዳንት ኢሳያስ ጋር ውይይት ካደረገ በኋላ ነው

ወደብ አልባ የሆነችው ኢትዮጵያ በቀይ ባህር የራሷን ወደብ ለማግኘት እና የባህር ሀይል ለመቋቋም እንቅስቃሴ ላይ እንደምትገኝ ይታወቃል

ግብጽ የቀይ ባህር አካል ያልሆነ ማንኛውም ሀገር በባህሩ ዙሪያ የሚያደርገውን ወታደራዊ እንቅስቃሴ እና የባህር ሀይል ለማቋቋም የሚደረግ ጥረት እንደማትቀበል አስታወቀች፡፡

ይህ የተባለው በግብፅ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ባድር አብዳላቲ የተመራ ልዑክ በኤርትራ ከፕሬዝዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ጋር ውይይት ማድረጉን ተከትሎ ነው፡፡

በውይይቱ ሁለቱ ሀገራት የቀይ ባህርን ጨምሮ የጋራ በሚያደርጓቸው ቀጠናዊ እና በተለያዩ መስኮች የሁለትዮሽ ግንኙነቶችን ለማጠናከር ተስማተዋል፡፡

የግብጽ፣ ሶማሊያና ኤርትራ መሪዎች በምን ጉዳይ ላይ ተወያዩ፤ የደረሷቸው ስምምነቶስ ምንድን ናቸው?
የግብፅ ውጭ ጉዳይ ሚንስትር “የቀይ ባህር ደህንነት በተዋሳኝ ሀገራቱ ፍላጎት ላይ ብቻ የተመሰረተ ነው ፤ምንም አይነት ወታደራዊም ሆነ የባህር ሃይል በአካባቢው መገኘትን አንፈቅድም” ብለዋል።

አክለውም “ወደብ አልባ ሀገራት በቀይ ባህር ዙሪያ የባህር ሀይል ማቋቋም የቀጠናውን እና የባህሩን ደህንነት ለመጠበቅ የተደረሰውን ስምምነት ክፉኛ የሚጎዳ ነው” ሲሉ ተደምጠዋል፡፡

የግብፅ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መግለጫ እንዳስታወቀው አብዳላቲ ከፕሬዝዳንት ኢሳያስ ጋር ባደረጉት ውይይት፤ በአህጉራዊ የጋራ ጉዳዮች በተለይም በአፍሪካ ቀንድ አካባቢ ሰላምና ደህንነትን መደገፍ በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ፣ በሶማሊያ ሽብርተኝነትን ለመዋጋት እና ሉዓላዊነቷን በሁሉም ግዛቶቿ ላይ ለማስረፅ የሚያስችል የሃሳብ ልውውጥ ተካሂዷል።

ስብሰባው በሊቢያ እና በአፍሪካ ሳህል አካባቢ ስላለው ሁኔታ እንዲሁም በቀይ ባህር ውስጥ ያሉ ለውጦች እና ማንኛውም ቀይ ባህር አካል ያልሆነ መንግስት በፀጥታ እና በአስተዳደር ውስጥ ተሳትፎን ውድቅ በማድረግ ላይ ትኩረቱን አድርጓል ።

በተጨማሪም በጥቅምት 2024 በኤርትራ ከተካሄደው የመጀመሪያው የመሪዎች ጉባኤ በኋላ ተመሳሳይ የሚኒስትሮች ስብሰባዎችን በሞቃዲሾ እና በአስመራ ለማካሄድ እና በቅርቡ ለሁለተኛው የፕሬዝዳንት ጉባኤ ለመዘጋጀት መምከራቸውን አብዳላቲ ጠቁመዋል።

የኤርትራ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ባወጣው መግለጫ በበኩሉ ትላንት ምሽት ፕሬዝዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ በግብጽ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ባድር አብዳላቲ ከተመራ ልዑካን ጋር በቀጠናዊ ጉዳዮች ላይ ሰፊ ውይይቶች ማድረጋቸውን አስታውቋል፡፡

በሱዳን ሶማሊያ እና በአጠቃላይ በአፍሪካ ቀንድ እንዲሁም በቀይ ባህር አካባቢዎች የሰላም እና የደህንነት ፈተናዎች ላይ ትኩረቱን ያደረገ ውይይት መካሄዱንም መግለጫው አክሏል፡፡

ግብፅና ኤርትራ በሶማሊያ ጉዳይ ማንኛውንም የውጭ ጣልቃገብነት ውድቅ በማድረግ የሞቃዲሾን ሉዓላዊነትና የግዛት አንድነት እንደሚደግፉ በተደጋጋሚ ማስታወቃቸው አይዘነጋም፡፡

ባለፈው አመት መጀመሪያ ላይ ኢትዮጵያ ከራስ ገዟ ሶማሊላንድ ለባህር ሀይል እና ለንግድ የሚሆን 20 ኪሎሜትር የሚሸፍን የባህር ዳርቻ ለመከራየት የመግባብያ ስምምነት መፈራረሟን ተከትሎ በአፍሪካ ቀንድ ከፍተኛ ውጥረት ነግሶ ቆይቷል፡፡

በጥር ወር በቱርክ አደራዳሪነት በአንካራ በሶማሊያ እና በኢትዮጵያ መሪዎች የተደረገውን ስምምነት ተከትሎ ሁለቱ ሀገራት ሙሉ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነታቸውን ወደነበረበት ለመመለስ ተስማማተዋል፡፡

ከዚህ ጊዜ በኋላ የጎረቤታሞቹ ሀገራት ከፍተኛ መሪዎች በሞቃዲሸ እና በአዲስ አበባ የተገናኙ ሲሆን ከሰሞኑም የኢፌድሪ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ በሞቃዲሾ ለመጀመሪያ ጊዜ ይፋዊ የስራ ጉብኝት ማድረጋቸው ይታወሳል፡፡
ዐል ዓይን


‹‹ኤርትራ በግዳጅ ዜጎቿን ለውትድርና መመልመሏን ቀጥላበታለች›› ሲሉ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰብአዊ መብቶች ረዳት ዋና ፀሀፊ ኢልዚ ብራንድስ ተናገሩ፡፡

በተመድ የሰብአዊ መብት ምክር ቤት ዛሬ የኤርትራ ሁኔታ ለግምገማ በቀረበበት ወቅት ዋና ፀሀፊዋ ይህ ጉዳይ አለም አቀፍ የሰብአዊ መብት ድንጋጌዎችን እንደሚጣረስ አስረድተዋል፡፡ ከግዳጅ ወታደራዊ ምልመላ በተጨማሪ ግለሰቦችን በማሰቃየት፣ ፆታዊ ጥቃት በመፈፀምና የጉልበት ብዝበዛ በማድረግ የኤርትራ መንግስት የሰብአዊ መብት ድንጋጌዎችን እየጣሰ መሆኑን የገለፁት ረዳት ፀሀፊዋ በርካታ ኤርትራዊያን ወጣቶች ይህንን በመሸሽ ከአገራቸው እየተሰደዱ መሆኑን አስታውቀዋል፡፡

‹‹ከዚህ ቀደም በዚህ ምክር ቤት ኤርትራ ከዚህ ከድርጊቷ እንድትታቀብ ማሰሰቢያ ተሰጥቷት ነበር›› ያሉት ረዳት ፀሀፊዋ ይሁንና ማሳሰቢያውን ሰምታ ከማስተካከል ይልቅ ብሶባት የመብት ጥሰቱን መቀጠሏን አስረድተዋል፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ በምክር ቤቱ የኤርትራ የሰብአዊ መብት ራፖርተር የሆኑት መሀመድ አብዲሰላም ባቢከር አመታዊ የኤርትራን የሰብአዊ መብት አያያዝ በተመለከተ ይህ ዘገባ በተጠናከረበት ወቅት ማብራሪያ እየሰጡ ይገኛሉ፡፡

የኤርትራ መንግስት እኚህ ራፖርተር ማብራሪያ በሰጡ ቁጥር የተቃውሞ መግለጫ የሚያወጣ ሲሆን ከዚህ ሪፖርት በኋላም ተመሳሳይ መግለጫ እንደሚያወጣ ይጠበቃል፡፡


Репост из: Ahmed Habib Alzarkawi
ስለ ቀይባህር ሲነሳ!!

''የኢትዮጵያን ሰንደቅ አላማ እንኳን እኛ ግመሎቻችን ያውቁታል''

ይህ የአፋር ንጉስ ቢቱወደድ ሱልጣን አሊሚራህ አላህ ይርሀማቸው ታሪካዊ ንግግር ሁሌ ስለ ቀይባህር ሲነሳ አብሮ ይነሳል ምክንያቱም ቢቱወደድ ሱልጣን አሊሚራህ ይህን አይረሴ በሁሉም ኢትዮጽያዊ ዘንድ የሚወደድለት ታሪካዊ ንግግር የተናገሩት ያኔ በሁለት ወንበዴ ቡድኖች ስምምነት የኤርትራ ህዝበ ውሳኔ ሪፈረንደም የቀይ ባህር አፋር በገለለ መልኩ ሲካሄድ። የቀይ ባህር አፋሮች ከኢትዮጵያ መነጠሉን አስመልክቶ የተናገሩት ታሪካዊ ንግግር ነው።

Ahmed Habib Alzarkawi




Репост из: Ahmed Habib Alzarkawi
አሰብ ወደ ባለንብረቷ ኢትዮጵያ ሉዓላዊ ግዛት በቀጥታ እስካልተመለስ ድረስ ኢትዮጵያና ኤርትራ መሀል የሚፈጠር ሽንገላ እንጂ እውነተኛ ሰላም አይኖርም ።

የኤርትራ ቀጣይ ኢኮኖሚና ደህንነት የሚረጋገጠው አሰብ ለኢትዮጵያ በሰላማዊ መንገድ በመመለስ ብቻ ነው። ያ ካልሆነ ኤርትራ ካለፈው 33ዓመታት ነፍስ አልቦነት የከፋ ሁኔታ እንጂ ያነሰ ቀጣይ Future አይኖራትም። ነገር ግን ከትክክለኛውን የሰላማዊ ርክክብ ውጭ በነ ኢሳያስ በኩል የሚመረጥ የጥፋት መንገድ ካለ መጨረሻው የ130 ሚሊየን ባህርበር የተዘጋባቸውን ኢትዮጵያዊያንን ድል ያፋጥናል።

በየትኛው መንገድ አሰብ ወደ ኢትዮጵያ መመለሱ ላይቀር ከጥፋት መንገድ እንዲቆጠብ ሻዕቢያን መምከር ከባድ ቢሆንም ኤርትራዊያንን ማስተማር ማስገንዘብ ያስፈልጋል።

ሊሰመርበት የሚገባው :- ኢትዮጵያ አሰብን በኪራይ አይደለም ምትፈልገው ፤ ወደ ሉዓላዊ ግዛቷ መመለስ እንጂ ፤ " በሊዝ በኪራይ ወዘተ.. ተጠቀሙ" አይነት ማዘናጊያ መቼም ቢሆን ተቀባይነት አይኖረውም።

#asabethiopia


#ሰበር — የሆቢዮ ወደብ ለኢትዮጵያ ቀረበ ❗️

⚓️

የኢትዮጵያ እና ሶማሊያ ተደራዳሪዎች በቱርክ አንካራ ከተማ በኢትዮጵያ የባህር በር የመጠቀም መብት ዙሪያ ቲክኒካዊ ንግግር ላይ ናቸው።

ትናንት በተጀመረውና ሀለተኛ ቀኑን በያዘው ቴክኒካዊ ንግግር ከአምስት ዓመት በፊት በኳታር አማካኝነት እንዲለማ ውል ታስሮበት የነበረውና ሳይለማ ቀርቶ (ለምን የሚለውን ለማወቅ አልቻልኩም) የዛሬ አምስት ወር ገደማ መቀመጫውን ቱርክ ያደረገው ሜታግ ሆልዲግ ካምፓኒ (Metag Holding) $70 ሚሊዮን ዶላር በመመደብ ለማልማት የተዋዋለውን #የሆቢዮ ወደብ (Hobyo Port) ኢትዮጵያ አልምታ እንድትጠቀም ምክረ ሃሳብ አቅርቧል።

በኢትዮጵያ ወገን በኩል ለኢትዮጵያ የሚቀርብና የተሻለ መሰረተ ልማት ያለውን #የቦሳሶ ወደብን ጨምሮ በፑንትላንድ ግዛት ውስጥ ከሚገኙ ወደቦች መካከል የተሻለውን መርጦ በመቀበል አልምታ መጠቀም ትፈልጋለች።

የሁለቱ ወገን ድርድር ነገም የሚቀጥል ሲሆን በአንካራ ሥምምነት መሰረት የመጨረሻው ውሳን April 30/2025 ላይ መጠናቀቅ አለበት።

⚓️

ክብር ኢትዮጵያ የባህር በር ይገባታል ሲል ለሞገተው ታላቁ መሪያችን ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር)


38ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ መካሄድ ጀመረ።

38ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ በአህጉሪቱ መዲና በሆነችሁ በአዲስ አበባ ዛሬ በይፍ መካሄድ ጀምሯል።

ጉባኤው ከ35 በላይ የሀገር መሪዎች፣ አንድ ንጉስ፣ 19 ቀዳማዊት እመቤቶች፣ ሁለት ምክትል ፕሬዚዳንቶች፣ አንድ ጠቅላይ ሚኒስትር እና ሁለት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች እንዲሁም የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ በአዲስ አበባ በአፍሪካ ህብረት ዋና መስሪያ ቤት በጀመረው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ ላይ ተገኝተዋል።

የአፍሪካ ህብረት አባልነታቸው የታገደባቸው 6 ሀገራት ሱዳን፣ኒጀር፣ጋቦን፣ጊኒ፣ቡርኪናፋሶና ማሊ በጉባኤው ያለተሳተፍ ሀገራት ናቸው።

የወቅቱ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ሙሳ ፋኪ ማሃማት '' ተለዋዋጭ ከሆነው የዓለም ፖለቲካና ኢኮኖሚ ጋር በፍጥነት ለመራመድ አፍሪካዊያን በጋራ መቆም እንደሚገባቸው '' ገልፀው ገባኤውን የመክፈቻ ንግግር በማረግ አስጀምረውታል።

በዛሬ ውሎውም የአንጎላ ፕሬዝዳንት ዧው ማኑኤል ጎሳዌስ ሎሬንሶ የሞሪታንያ መሀመድ ኦልድ ጋዙዋንን በመተካት የአፍሪካ ህብረት አዲሱ ሊቀመንበር አድርጎ መርጧል።

አፍሪካ ''በዓለም አቀፍ ደረጃ ያላትን ተገቢ ቦታ እንድታገኝ በተለይ በተመድ በቂ ውክልና እንድታገኝ በትብብር እንደሚሠሩም '' አዲሱ ሊቀመንበር ቃል ገብተዋል።

የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ በአፍሪካ ኅብረት የመሪዎች ጉባዔ ላይ እንደተናገሩት"አፍሪካ በፀጥታ ምክር ቤት ሁለት ቋሚ መቀመጫ እንዲኖራት ተመድ ግፊት ማድረጉን ይቀጥላል'' ሲሉ ተናግረዋል።

የአፍሪካ ህብረት እ.ኤ.አ. በ2030 አህጉሪቱ ላይ የትጥቅ ግጭቶችን ለማስቆም ያለመውን "ጠመንጃዎችን ዝም የማሰኘት" እቅድ የሁለት ዓመት ሪፖርት ላይ ይመለከታል ተብሎ ይጠበቃል።

ከዛሬ ጀምሮ ለሁለት ቀናት የሚመክረው ጉባዔው መሪዎች ለባርነት እና ለቅኝ ግዛት ካሳ አዲስ ግፊት በመጀመር ከገንዘብ ካሳ፣ ያለፉትን ስህተቶች መደበኛ እውቅና መስጠት እስከ ፖሊሲ ማሻሻያዎች ድረስ የባርነት ካሳው ጉዳይ ምን ሊመስል እንደሚችል "የተዋሃደ ራዕይ" ለመቅረጽ እንደሚመክሩ ይጠበቃል።

ሌላው ቁልፍ አጀንዳ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ምርጫ ሲሆን እጩዎች ለሊቀመንበር እና ለምክትል ሊቀመንበርነት ይወዳደራሉ።

የኬንያውን የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር ራይላ ኦዲንጋን፣ የጅቡቲ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማህሙድ አሊ ዩሱፍን እና የማዳጋስካርውን ሪቻርድ ራንድሪያማንድራቶ የወቁቱን የአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር ሙሳ ፋኪ መሐመት ለመተካት ይወዳደራሉ።


Репост из: TIKVAH-ETHIOPIA
“ በ6 ወራት ለ66 ሺህ 741 የማህበረሰብ ክፍሎች የሥነ አዕምሮ ህክምና አገልግሎት ተሰጥቷል ” - አማኑኤል ሆስፒታል

አማኑኤል የአዕምሮ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል በ2017 ዓ/ም፣ “ በ6 ወራት ለ66,741 የማህበረሰብ ክፍሎች የሥነ አዕምሮ ህክምና አገልግሎት ተሰጥቷል ” ሲል ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።

በዚህም 64,256 የተመላላሽ፣ 257 ህፃናት የአዕምሮ፣ 410 ሰዎች የሱስ ህክምና መሰጠቱን የሆስፒታሉ የህዝብ ግንኙነትና ኮሚዩኒኬሽን ስራ አስፈጻሚ አቶ አብዩ የኔአለም ገልጸዋል።

እንዲሁም ለ240 የተሃዲሶ፣ ለ921 የአስተኝቶ፣ ለ1,564 ሰዎች ደግሞ የድንገተኛ የህክምና አገልግሎት መሰጠቱን አቶ አብይ አስረድተዋል።

በተመላላሽ፣ በአስተኝቶና በድንገተኛ የህክምና አገልግሎት ከተሰጣቸው ታካሚዎች መካከል 36,300 የጤና መድን ተጠቃሚዎች መሆናቸው ተመልክቷል።

በተመላላሽና በተኝቶ ህክምና በስድስት ወራት የወንጀልና የፍትሃ ብሔር ተመርማሪ ለሆኑ 413 የህብረተሰብ ክፍሎች የህክምና አገልግሎት መስጠቱም ተገልጿል።

“ በሆስፒታሉ አማካኝ አስተኝቶ የቆይታ ጊዜ በ2016 ዓ/ም ከነበረው 36 ቀናት በ2017 ዓ/ም 6 ወራት ወደ 33 ቀናት ማድረስ፣ የአልጋ የመያዝ ምጣኔም በመጀመሪያ 6 ወራት መጨረሻ ላይ 85.2% መፈጸም ተችሏል ” ተብሏል።

ሆስፒታሉ ከ1930 ዓ/ም ጀምሮ በተኝቶ፣ በተመላላሽ፣ በድንገተኛ፣ የጭንቅላት ምርመራ፣ በኤሌክትሪክ ንዝረት፣ በህፃት የአዕምሮ፣ ከህግ ጋር የተያያዙ የአዕምሮ ህክምናና ምርመራ እንዲሁም የነርቭ ህክምናዎችን እየሰጠ የሚገኝ አንጋፋ ሆስፒታል ነው።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia


190. ዶ/ር ዲላሞ ኦቶሬ ፈረንጄ
191. ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል
192. አቶ መለሰ አለሙ ህርቦሮ
193. አቶ እርስቱ ይርዳው
194. አቶ ሞገስ ባልቻ ገ/መድህን
195. ዶ/ር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ
196. አም/ር ሬድዋን ሁሴን ራህመቶ
197. ዶ/ር ኤርጎጌ ተስፋዬ
198. አቶ አንተነህ ፍቃዱ ወ/ሰንበት
199. አቶ ኡስማን ሱሩር ሲራጅ
200. አቶ ስንታየሁ ወ/ሚካኤል
201. ወ/ሮ እፀገነት መንግስቱ
202. አቶ አክሊሉ ታደሰ
203. ወ/ሮ ሂክማ ከይረዲን
204. ወ/ሮ ነጂባ አክመል
205. አቶ ጃፋር በድሩ
206. አቶ ጥላሁን ከበደ ወልዴ
207. ዶ/ር ተስፋዬ በልጅጌ ዳራ
208. አቶ ታገሰ ጫፎ ዱሎ
209. ወ/ሮ አለምፀሐይ ጳውሎስ አቱሞ
210. ወ/ሮ አስቴር ዳዊት ጦሼ
211. አቶ ገ/መስቀል ጫላ ሞጣሎ
212. አቶ አለማየሁ ባውዲ ሞላ
213. አቶ ንጋቱ ዳንሳ
214. አቶ ኃይለማርያም ተስፋዬ
215. ዶ/ር አበባየሁ ታደሰ
216. አቶ ብርሃኑ ዘውዴ
217. አቶ ወገኔ ብዙነህ
218. ወ/ሮ ሸዊት ሻንካ ሻሽጎ
219. አቶ አዳማ ቴንጳዬ መንገሻ
220. ኢ/ር አክሊሉ አዳኝ
221. አቶ ዳኜ ሂዶ ዋቆ
222. አቶ ጴጥሮስ ወ/ማርያም
223. ዶ/ር ዝናቡ ወልዴ ሀጢያ
224. ኢ/ር ወንድሙ ሴታ ዳጠሞ
225. አቶ ሰለሞን ሶካ ግኛርታ


በብልፅግና ፓርቲ ሁለተኛ መደበኛ ጉባኤ የተመረጡ የምክር ቤት አባላት ዝርዝር
1. ዶክተር ዐብይ አሕመድ
2. አቶ አደም ፋራህ
3. አቶ ተመስገን ጥሩነህ
4. አቶ ሽመልስ አብዲሳ ኡልፋታ
5. አቶ ፍቃዱ ተሰማ
6. ወይዘሮ አዳነች አቤቤ ደሳ
7. አቶ ከፍያለው ተፈራ ይግለጡ
8. ወይዘሮ ጫልቱ ሳኒ ኢብራሂም
9. አቶ አወሉ አብዲ አብዶ
10. አቶ አዲሱ አረጋ ቂጤሳ
11. ዶክተር ዓለሙ ስሜ ፈይሳ
12. አቶ ሳዳት ነሻ አረባ
13. አቶ ነመራ ቡሊ
14. ኢንጅነር ታከለ ኡማ
15. ዶ.ር ቢቂላ ሁሪሳ
16. ዶ.ር ግርማ አመንቴ
17. ዶ.ር ቶላ በሪሶ
18. ዶ.ር ካሳሁን ጎፌ
19. ወይዘሮ ሎሚ በዶ
20. ወይዘሮ ምስኪ መሀመድ
21. ዶ.ር እዮብ ተካልኝ
22. አቶ ታረቀኝ ቡሉልታ
23. አቶ አብዱልሀኪም አልይ
24. አቶ ገመቹ ጉርሜሳ ሲርና
25. ዶ.ር መንግስቱ በቀለ ሁሪሳ
26. ዶ.ር ተሾመ አዱኛ
27. አቶ ቲጃኒ ናስር
28. አቶ ሀይሉ ጀልዴ
29. ወይዘሮ መሰረት አሰፋ ጎዳና
30. ኢንጅነር ሌሊሴ ነሜ
31. አቶ እንዳልካቸው ተፈሪ
32. ወይዘሮ ጀሚላ ሲንቢሩ
33. አቶ ከድር ጀዋር
34. ወይዘሮ ዓለምፀሐይ ሽፈራው
35. አምባሳደር ብርቱካን አያኖ
36. አቶ አለማየሁ እጅጉ
37. ዶ/ር ዮሐንስ ጫላ ወርቁ
38. ዶ/ር ደረጄ ዱጉማ
39. ወ/ሮ ሰዓዳ አብዱራህማን ሃቢብ
40. ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ
41. ዶ/ር ዘላለም ሙላቱ
42. አቶ ደበሌ ቃበታ
43. አቶ መስፍን መላኩ
44. አቶ ከድር ማሞ
45. ዶ/ር ዘለቀ ተመስገን ቦሩ
46. ዶ/ር ኢ/ር ወርቁ ጋቸና ነገራ
47. አቶ ሲሳይ ቶላ
48. ዶ/ር አብዱልአዚዝ ዳውድ
49. አቶ አህመድ እንድሪስ
50. አቶ አለማየሁ አሰፋ ዲሳሳ
51. ዶ/ር ኢፍራህ ወዚር አብዱላሂ
52. ወ/ሮ ኢክራም ጠሃ
53. አቶ አዱላ ህርባዬ ጎላዴ
54. አቶ ኢብራሂም ከድር ጅማ
55. አቶ መኮንን ባይሳ
56. አቶ አብዱልሰላም ዋሪዮ
57. አቶ ድዳ ጉደታ ዳባላ
58. አቶ ጃርሶ ቦሩ ረሮ
59. አቶ አባቡ ዋቆ ቱራ
60. አቶ ክፈለው አዳሬ
61. አቶ ዋቅጋሪ ነገራ
62. አቶ ደንጌ ቦሩ
63. አቶ ሙስጠፋ ሙሁመድ ኡመር
64. አቶ አህመድ ሽዴ መሀመድ
65. ኢ/ር መሀመድ ሻሌ ኢሳቅ
66. አቶ ኢብራሂም ኡስማን ፋራህ
67. አቶ አብዱራህማን ኢድ ጣሂር
68. ወ/ሮ ሰሃርላ አብዱላሂ
69. አቶ መሀመድ ኡመር አህመድ
70. አቶ ፈይሰል ረሺድ ኡመር
71. አቶ መሀመድ ፋታህ መሀመድ
72. አቶ አብዱራህማን አህመድ
73. አቶ መሀመድ አደን እስማኤል
74. ወ/ሮ ከድራ በሽር
75. ወ/ሮ ሀሊሞ ሀሰን መሀመድ
76. ወ/ሮ አያን አብዲ መሀመድ
77. አቶ ኢብራሂም ሀሰን አሊ
78. ወ/ሮ ሂቦ አህመድ ኡመር
79. አቶ መሀመድ ናጂ መሀመድ
80. አቶ መሀመድ አደን ጣሂር
81. አቶ ኢብራሂም ዩሱፍ አህመድ
82. አቶ ጠይብ አህመድ ኑር
83. ዶ/ር አብዱልዋሳ አብዱላሂ በዴ
84. ዶ/ር ሁሴን አብዱላሂ ቃሲም
85. አቶ አረጋ ከበደ ለጋስ
86. አቶ መላኩ አለበል
87. ወ/ሮ አይናለም ንጉሴ
88. አቶ ይርጋ ሲሳይ ቅጣው
89. ዶ/ር አብዱ ሁሴን ኢብራሂም
90. ኢ/ር ሀብታሙ ተገኝ ደስታዬ
91. አቶ ዛዲግ አብርሃ ሻረው
92. አቶ አገኘሁ ተሻገር
93. አቶ ማሞ እስመለአለም ምህረቱ
94. ዶ/ር አህመዲን መሀመድ አህመድ
95. ዶ/ር ድረስ ሳህሉ
96. አቶ ደሳለኝ ጣሰው
97. አቶ ጃንጥራር አባይ ይግዛው
98. ዶ/ር ሙሉነሽ ደሴ አድማሱ
99. አቶ ፍሰሃ ደሳለኝ መኮንን
100. ዶ/ር ዘሪሁን ፍቅሩ መላኩ
101. ዶ/ር ለገሰ ቱሉ
102. ወ/ሮ ፋንቱ ተስፋዬ አለሜ
103. አቶ እንድሪስ አብዱ አህመድ
104. ወ/ሮ ትዕግስት ሀሚድ
105. ወ/ሮ ባንቺአምላክ ገ/ማርያም
106. ወ/ሮ ብርቱካን ሲሳይ እንየው
107. ዶ/ር ሂሩት ከሳ ወንድም
108. ዶ/ር ደመቀ ቦሩ
109. ዶ/ር ጋሻው አወቀ ትኩዬ
110. ዶ/ር ስቡህ ገበያው ታረቅ
111. አቶ ሲሳይ ዳምጤ
112. ወ/ሮ መስከረም አበበ ወርቅነህ
113. አቶ አሸተ ደምለው ተድላ
114. አቶ አሊ መኮንን አስፋው
115. አቶ ሳሙኤል ሞላልኝ ደሳለ
116. አቶ እድሜአለም አንተነህ
117. አቶ ቻላቸው ዳኛው ከበደ
118. አቶ አህመድ አሊ አባአፍሮ
119. አቶ ጎሹ እንዳለማሁ ወንድማገኝ
120. ወ/ሮ ሰላማዊት ካሳ ወዳጄነህ
121. ዶ/ር ኢብራሂም ሙሀመድ እንድሪስ
122. አቶ መካሽ አለማየሁ ግዛው
123. አቶ ኑርልኝ ብርሃኑ አየለ
124. ዶ/ር አማኑኤል ፈረደ አያሌው
125. ዶ/ር ፍሰሃ ይታገሱ ማንበግሮት
126. ወ/ሮ አየለች እሸቴ ወ/ሰማያት
127. ዲ/ን ሸጋው ውቤ አዛገ
128. አቶ ቴዎድሮስ እንዳለው ትኩ
129. ዶ/ር አብርሃም በላይ በርሄ
130. አቶ ታይዜር ገ/ሔር በርሄ
131. ወ/ሮ ያስሚን መሀቢረቢ ሰኢድ
132. አቶ ኦርዲን በድሪ ሀምዶኝ
133. አቶ አሪፍ መሀመድ አዱስ
134. አቶ ካሊድ አልዋን ኢሳቅ
135. አቶ ሙክታር ሳሊህ ኢብራሂም
136. ወ/ሮ አሚና አብዱልከሪም መሀመድ
137. ወ/ሮ አለሚቱ ኡመድ
138. ዶ/ር ጋልዋክ ሮን
139. አቶ አሽኔ አስቲን ቲቶይክ
140. አቶ ቶክ ቾት ቶሃን
141. አቶ ጀሙስ ኞች
142. ወ/ሮ ባንቺአየሁ ድንገታ ነገሪ
143. አቶ አሻድሊ ሀሰን አልአጀብ
144. አቶ ጌታሁን አብዲሳ ሌጮ
145. አቶ ኢሲያቅ አብዱልቃድር ሌጮ
146. ወ/ሮ አስካል አልቦሮ ዲባባ
147. ወ/ሮ አለምነሽ ይባስ ጉቅ
148. አቶ በባክር ሃሊፋ አብደላ
149. ወ/ሪት ምስኪያ አብደላ ሶሶ
150. ወ/ሮ ፍሬህይወት አበበ ጎበና
151. ወ/ሮ ቡዜና አልከድር ሐጂዙሊ
152. አቶ ደስታ ሌዳሞ
153. አቶ አብርሃም ማርሻሎ
154. ዶ/ር ፍፁም አሰፋ አደላ
155. አቶ በየነ በራሳ ባላንጎ
156. ወ/ሮ ፋንታዬ ከበደ
157. ዶ/ር ዳዊት ሀዬሶ
158. አቶ አሸናፊ ኤልያስ
159. ወ/ሮ ሀገረፅዮን አበበ
160. አቶ ጥራቱ በየነ
161. አቶ ሚሊዮን ማቲዎስ
162. አቶ አለማየሁ ጢሞቲዎስ ደቦጭ
163. ወ/ሮ ሰላማዊት ዳዊት
164. ሀጂ አወል አርባ ኡንዴ
165. አቶ መሀመድ ሁሴን አሊሳ
166. አቶ መሀመድ አህመድ አሊ
167. ወ/ሮ ዛህራ ሁመድ አሊ
168. አቶ ወልኦ አይቲሌ
169. አቶ አህመድ መሀመድ ቦዳያ
170. ኢ/ር አይሻ መሀመድ ሙሳ
171. ወ/ሮ አይሻ ያሲን ሀሰን
172. ወ/ሮ ፋጡማ መሀመድ ያሲን
173. አም/ር ሀሰን አብዱልቃድር ባርከት
174. አቶ አብዱ ሙሳ ሁሴን
175. አቶ ኡመር ኑር አርባ
176. ዶ/ር ኢ/ር ነጋሽ ዋጌሾ
177. አቶ ማስረሻ በላቸው ማሞ
178. አቶ ፍቅሬ አማን ጋካ
179. አቶ ነጋ አበራ አጭሶ
180. አቶ በላይ ተሰማ ጅሩ
181. አቶ ፋጂዮ ሳፒ ወትራሻ
182. አቶ አልማው ዘውዴ ግችላ
183. አቶ በየነ በላቸው
184. ወ/ሮ ሄለን ደበበ ወ/ጊዮርጊስ
185. ወ/ሮ መሰረት መስቀሌ አያኖ
186. ወ/ሮ ገነት መኩሪያ ገ/ማርያም
187. አቶ ዳዊት ገበየሁ ገሉ
188. አቶ ሀብታሙ ካፍቲን
189. ዶ/ር እንደሻው ጣሰው


አዲሱ የብልጽግና ፓርቲ ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ በአጠቃላይ 45 አባላት ያለው ሲሆን 10 ሴቶችን አካቷል።

#ኦሮሚያ_ክልል

1. ዶክተር ዐቢይ አህመድ
2. ኦቦ ሽመልስ አብዲሳ
3. ኦቦ አወሉ አብዲ
4. ኦቦ ፍቃዱ ተሰማ
5. አዴ አዳነች አቤቤ
6. አዴ ጫልቱ ሳኒ
7. ኦቦ ሳዳት ነሻ
8. ኦቦ ከፍያለው ተፈራ
9. ዶክተር ተሾመ አዱኛ
10. ዶክተር እዮብ ተካልኝ

#አማራ_ክልል

11. አቶ ተመስገን ጥሩነህ
12. አቶ መላኩ አለበል
13. ወ/ሮ አይናለም ንጉሴ
14. አቶ አረጋ ከበደ
15. አቶ ይርጋ ሲሳይ
16. ዶክተር አብዱ ሁሴን
17. አቶ ጃንጥራር አባይ
18. ዶክተር ሙሉነሽ ደሴ

#ሶማሌ_ክልል

19. አቶ አደም ፋራህ
20. አቶ ሙስጠፌ መሃመድ
21. አቶ አህመድ ሺዴ
22. ወ/ሮ ሃሊማ ዋሽራፍ

#ትግራይ_ክልል

23. ዶክተር አብርሃም በላይ
24. አቶ ታዜር ገብረ እግዚአብሔር

#ሀረሪ_ክልል

25. አቶ ኦርዲን በድሪ
26. ወ/ሮ አሚና አብዱልከሪም

#አፋር_ክልል

27. ሀጂ አወል አርባ
28. መሀመድ ሁሴን አሊሳ
29. መሀመድ አህመድ አሊ

#ደቡብ_ምዕራብ_ኢትዮጵያ_ክልል

30. ዶክተር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ
31. አቶ ፍቅሬ አማን

#ሲዳማ_ክልል

32. አቶ ደስታ ሌዳሞ
33. አቶ አብርሃም ማርሻሎ
34. ዶክተር ፍፁም አሰፋ

#ጋምቤላ_ክልል

35. ወ/ሮ አለሚቱ ኡሞድ
36. ዶዶክተር ካትሏክ ሩን ናቸው።

#ቤኒሻንጉል_ጉሙዝ_ክልል

37. አቶ አሻድሊ ሀሰን
38. አቶ ጌታሁን አብዲሳ

#ማዕከላዊ_ኢትዮጵያ_ክልል

39. አቶ እንዳሻው ጣሰው
40. ወ/ሮ ሙፈሪያት ካሚል
41. ዶክተር ዴላሞ ዶቶሬ

#ደቡብ_ኢትዮጵያ_ክልል

42. አቶ ጥላሁን ከበደ
43. ወ/ሮ ⁠ሸዊት ሻንካ
44. ዶክተር ተስፋዬ ቤልጅጌ
45. ዶክተር አበባየሁ ታደሰ




Репост из: ኢትዮ ኘላስ + Ethio Plus
ሊንደን ጆንሰንን ቃለ መሐላውን ያስፈጸሟቸው ሴት ዳኛ ሲሆኑ እስካሁን በዩናይትድ ስቴትስ ታሪክ ፕሬዝደንትን ቃለ መሐላ ያስፈጸሙ ብቸኛዋ ሴት ዳኛ ናቸው፡፡

ጆንሰን ቃለ መሐላ ላይ ሲፈጽሙ ጎናቸው የቆሙትም ባለቤታቸው በጥይት በተገደሉበት ጊዜ ለብሰውት የነበረውን ያንኑ ልብስ እንደለበሱ ነበር፡፡

ምስሉ ፕሬዝደንቱ በሰው እጅ ለተገደሉበት የአሜሪካ ሕዝብ ተተኪ ፕሬዝደንት መሰየሙን በስተቀር ባልተጠበቀ ምስቅልቅል ሁኔታ ውስጥም ቢሆን የዩናይትድ ስቴትስ መንግሥት ሥራ እንደሚቀጥል እምነት እንዲያድርበት ያደረገም ነበር፡፡

ታዲያ የዩናይትድ ስቴትስ መንግሥት ሥራ ሁልጊዜ ያለ እንከን ይከናወናል ማለት አይደለም፡፡ በታቀደላቸው ስርዐት መሠረት ያልተከናወኑ ብዙ በዓለ ሲመቶች አሉ፡፡

በሥነ ሥርዓት ያልተከናወኑ በዓለ ሲመቶች የወፍ ምስል

ወደ ጥንት ወደ እ አ እ 1829 ዓም መለስ ብለን የአንድሩው ጃክሰንን በዓለ ታሪክን ብንቃኝ ቃለ መሓላቸውን ከፈጸሙ በኋላ በኋይት በነበረው ድግሥ ላይ የታደሙ ደጋፊዎቻቸው እጃቸውን እየጨበጡ ደስታቸውን ለመግለጽ ጓጉተው ሲረባረቡ አዲሱን ፕሬዝደንት ከግድግዳ ጋር አጣብቀው ሊደፈጥጧቸው ምንም አልቀራቸውም ነበር፡፡ ፕሬዝደንቱ በመስኮት ወጥተው እንዳመለጡ ታሪክ ይናገራል፡፡

በ1865 ደግሞ የፕሬዝደንት አብራሃም ሊንከን ምክትል ፕሬዝደንት ሆነው የተመረጡት አንድሩ ጆንሰን በቃለ መሐላ ሥነ ስርዐታቸው ላይ በስካር መንፈስ ንግግር ማድረጋቸው ተመዝግቧል፡፡ አሟቸው ስለነበረ ለህመም ማስታገሻ እንዲሆናቸው የወሰዱት ዊስኪ ነው ያሰከራቸው የሚል ምክንያት እንደተሰጠላቸው ተጽፏል፡፡

በ1873 ዩሊሰስ ኤስ ግራንት በበዓለ ሲመታቸው ድግስ ላይ "በድግሱ ቦታ ሰማያዊ ወፎች ቢበሩልኝ እንዴት ደስ ባለኝ ብለው ነበር" እና ሐሳባቸው ይሙላ ተብሎ ወፎች ለትዕይንት እንዲበሩ ተደረገ፡፡

ክፋቱ ብርዱ ነበር እና ወፎቹን ክንፋቸውን እያደረቀ እንዳረገፋቸው ይነገራል፡፡ የወፍ ነገር ከተነሳ እ አ አ በ1973ም ሪቻርድ ኒክሰን ርግቦች የበዓለ ሲመታቸው የሰልፍ ትዕይንት በሚያልፍበት መንገድ እንዳይገኙ ለማባረር ኬሚካል አስረጭተው ነበር እና የበዐሉ ታዳሚዎች የዋሽንግተኑ ፔንሲልቬኒያ አቨኑ ጎዳና ላይ መደዳውን ኬሚካሉ የገደላቸውን ርግቦች ሬሳ እንዳይረግጡ እየዘለሉ ያልፉ እንደነበር በፕሬዝደንታዊ በዓለ ሲመት ታሪክ ተመዝግቧል፡፡


Репост из: ኢትዮ ኘላስ + Ethio Plus
የአሜሪካ ፕሬዚደንቶች በዓለ ሲመት ታሪክ
-------

በአሜሪካ ፕሬዝደንታዊ በዓለ ሲመት ትልቅ ቀን ነው፡፡ የራሱ የኾነ ወግ እና ሥርዐትም አሉት።

አንዳንዶቹ ከመጀመሪያው ፕሬዝደንት በዓለ ሲመት ጀምሮ የነበሩ የክፍለ ዘመናት ዕድሜ የጠገቡ ወጎች አና ባሕሎች ናቸው፡፡ ታዲያ ሁሉም ፕሬዚደንታዊ በዓላተ ሲመት በሚፈለገው ሥርዓት አና ወግ በታቀደው መሠረት ተከናውነዋል ማለት አይደለም፡፡ እሱም ነው አንዳንዶቹን ከሌሎቹ ይበልጥ አይረሴ የሚያደርጋቸው፡፡

እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር 1789 ዓ.ም የተከናወነው የመጀመሪያው ፕሬዝደንት ጆርጅ ዋሽንግተን በዓለ ሲመት
የመጀመሪያው ፕሬዝደንት ጆርጅ ዋሽንግተን ቃለ መሐላቸውን የፈጸሙት ኒው ዮርክ ከተማ ውስጥ ነበር፡፡

በወቅቱ ኒውዮርክ የአገሪቱ ጊዜያዊ መዲና ስለነበረች ነው፡፡ አሜሪካዊያን ከዚያ በፊት ፕሬዝዳንት ኖሯቸው ስለማያውቅ የምክር ቤት አባላቱ ሥነ ሥርዐቱ እንዴት ቢከናወን ይሻላል በሚል መክረው እስኪወስኑ ጆርጅ ዋሽንግተን አንድ ሳምንት መጠበቅ ነበረባቸው፡፡

ከዚያ በኋላ እ አ አ ሚያዚያ 30 ቀን ላይ ፕሬzደንቱ እና ምክትላቸው እንዲሁም የምክር ቤቱ አባላት የHግ መወሰኛው ምክር ቤት ውስጥ ከተሰባሰቡ በኋላ በረንዳው ላይ ወጥተው ደጅ ለሚጠባበቀው ታዳሚ እጃቸውን በማውለብለብ ሰላምታ ሰጡ፡፡

በመቀጠል ቃለ መሐላውን የሚያስፈጽሟቸው ዳኛ "በዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝደንትነት የተጣለብዎትን ኅላፊነት በታማኝነት ይወጣሉ? ብለው ጠየቋቸው፡፡

ጆርጅ ዋሽንግተን በአዎንታ ቃለ መሐላቸውን ሰጡ፡፡

ይህ ቃለ መሐላ እንዳለ በአሜሪካ ሕገ መንግሥት ውስጥ የተቀመጠ ነው፡፡ ዳኛው ጆርጅ ዋሽንግተን መጽሐፍ ቅዱስ ላይ ምለው ቃል እንዲገቡ ለማድረግ ነበር ያቀዱት፡፡

ነገር ግን የሚከናወንበት ሰዓት ሲቃረብ ዳኛው መጽሐፍ ቅዱስ እንዳላመጡ ባወቁ ጊዜ በጥድፊያ ሰው ተልኮ ከሌላ ቦታ መጽሐፍ ቅዱስ በውሰት መጥቶ ጆርጅ ዋሽንግተን ቃለ መሐላቸው ፈጸሙ፡፡

ዋሽንግተን ቃለ መሐላቸውን ከፈጸሙ በኋላ ያዘጋጁትን ንግግር በሕግ መወሰኛ ምክር ቤቱ አባላት ፊት አነበቡ፡፡

ዊሊያም ማክሌይ የተባሉ ሴኔተር በግል ማስታወሻቸው ላይ ዋሽንግተን ንግግራቸውን ሲያነቡ ተጨናንቀው እጃቸው ይንቀጠቀጥ እንደነበር ማንበብ አስቸግሯቸው እንደነበረም ጽፈዋል፡፡ አዲሱ ፕሬዚደንት ዋሽንግተን ግር ቢላቸውም ሥነ ሥርዓቱ እጥር ጥፍጥ ያለ እንደነበር አክለዋል፡፡

ቶማስ ጀፈርሰን በ1801 ዓ.ም

እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር በ1801 ዓ.ም የሦስተኛው ፕሬዝደንት የቶማስ ጄፈርሰን በዓለ ሲመት ደግሞ ከጆርጅ ዋሽንግተን በዓለ ሲመት ይበልጥ ቀለል ብሎ የተከናወነ ነበር፡፡

ቶማስ ጄፈርሰን ወደ በዓለ ሲመቱ ሥነ ሥርዐታቸው የሄዱት ከሳቸው በፊት እንደነበሩት ሁለቱ ቀደምቶቻቸው በሠረገላ ሳይሆን በእግራቸው ተጉዘው ነው፡፡

የአሜሪካ ምክር ቤት ካፒቶል ሲደርሱ ብዙ ሕዝብ ሲጠብቃቸው ነበር፡፡

ንግግራቸውንም አዘጋጅተው ነበር፡፡ ነገር ግን ድምጻቸው በጣም ድክም ያለ ስለነበረ ንግግራቸውን ሊሰማ የቻለው በጣም ጥቂት ሰው እንደነበር ታሪክ መዝግቦታል፡፡

ቢሆንም ዛሬ ያ የቶማስ ጄፈርሰን የበዓለ ሲመት ንግግር በአሜሪካዊያን ዘንድ በሚገባ ይታወቃል፡፡ በምርጫ ዘመቻው ወቅት በፖለቲካ ፓርቲዎች መካከል የነበረውን አስቀያሚ ጭቅጭቅ ለማርገብ ያደረጉት ንግግር አድናቆት አትርፏል፡፡

ሆኖም የምርጫው ዘመቻው ጭቅጭቅ የተወው አስከፊ ገጽታ ቀጠለ እና ከጄፈርሰን ጋራ የተፎካከሩት ከሳቸው በፊት የነበሩት ፕሬዚደንት ጆን አዳምስ በጄፈርሰን በዓለ ሲመት ላይ ሳይገኙ ቀሩ፡፡ በዓለ ሲመቱ ነገ ሊሆን በዋዜማው ምሽቱ ላይ ጓዛቸውን ጠቅልለው ከዋይት ሐውስ ወጡ እና ወደቦስተን ተመለሱ፡፡

ዊሊያም ሄንሪ ሃሪሰን በ1841 ዓ.ም

እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር በ1841 የዘጠነኛው ፕሬዝዳንት ዊሊያም ሄንሪ ሃሪሰን የቃለ መሐላ ሥነ ሥርዓት ታሪክ ሳይወሳ የአሜሪካ ፕሬዝደንቶች በዓለ ሲመት ታሪክ ተወሳ ለማለት አይቻልም፡፡ ሲመረጡ የ68 ዓመት ሰው የነበሩት ዊሊያም ሃሪሰን በዘመኑ ከነበሩት ፕሬዝደንቶች ሁሉ በዕድሜ ትልቁ ነበሩ፡፡

ታዲያ እንደሚባለው በፕሬዝደንትነት ለማገልገል ጠንካራ መሆናቸውን በጣም ረጅም ንግግር በማድረግ ለማሳየት አስበው ነው ይባላል ኃይለኛ ቅዝቃዜ በነበረበት የበዓለ ሲመታቸው ዕለት ጭንቅላታቸውን በብርድ ቆብ ሳይሸፍኑ ካፖርትም ሳይደርቡ ቆመው ረጅሙን ንግግራቸውን አደረጉ፡፡ ያ በሆነ በወሩ አዲሱ ፕሬዝደንት ዊሊያም ሃሪሰን ታምመው ሞቱ፡፡

ሥልጣን ላይ ሆነው ሕይወታቸው ያለፈ የመጀመሪያ ፕሬዝደንት ናቸው፡፡ ሐኪማቸው ፕሬዝደንቱን ለሕልፈት የዳረጋቸው የሳምባ ምች ወይም ኒውሞኒያ ነው ብለዋል፡፡፡በተለምዶ ግን ብዙዎች ረጅሙ ንግግራቸው የገደላቸው ፕሬዚደንት ይሏቸዋል፡፡

የሐሪሰን አሟሟት እ አ አ በ2014 ምርምር ተደርጎበት ነበር፡፡ ተመራማሪዎቹ ጄን ሜክሂዩ እና ፊሊፕ ሜክውላክ ሃሪሰን የሞቱት በሳምባ ሕመም ሳይሆን በሌላ ምክንያት ነው ይላሉ፡፡ እነሱ እንደሚሉት ሃሪሰን የታመሙት ከበዓለ ሲመታቸው በኋላ ወዲያውኑ ሳይሆን ቆይተው ከሦስት ሳምንታት በኋላ ነው፡፡ የነበራቸውም የሕመም ስሜት ድካም እና ጭንቀት እንጂ ሳምባቸው ላይ እንዳልነበረ ይናገራሉ፡፡

ተመራማሪዎቹ እንዳሉት ከሆነ በጊዜው ዋሽንግተን ዲሲ ጥሩ የፍሳሽ ማስወገጃ አገልግሎት ስላልነበራት የመጸዳጃ ቤት ፍሳሽ ከኋይት ሐውስ በቅርብ ርቀት ሜዳ ላይ ይፈስ ስለነበረ ምናልባት በባክቴሪያ የተበከለ ውሃ ጠጥተው ሳይታመሙ አልቀሩም ሲሉ ተመራማሪዎቹ ድምዳሜአቸውን ኒው ዮርክ ታይምስ ላይ አስነብበዋል፡፡

የ30ኛው ፕሬዚደንት ካልቭን ኩሊጅ በ1923 ዓ.ም

ስለ ፕሬዝደንቶች በዓለ ሲመት ሲወሳ ታዲያ የሁሉም የቃለ መሐላ ሥነ ሥርዐት አይረሴ ነው ማለት አይደለም፡፡ የ30ኛው ፕሬዚደንት ካልቭን ኩሊጅ በዓለ ሲመት ቀዝቀዝ ባለ ድባብ ከተከናወኑት ውስጥ የሚጠቀስ ነው፡፡ ምክትል ፕሬዝዳንት የነበሩት ኩሊጅ እ አ አ በ1923 ነሃሴ ወር ውስጥ ብዙም የሥራ ኃላፊነት ስላልነበረባቸው ቨርሞንት ወደሚኖሩት
ቤተሰቦቻቸው ቤት ለዕረፍት ሄደው ነበር፡፡

አንድ ቀን ሌሊት በተኙበት አባታቸው ይቀሰቅሷቸው እና ቴሌግራም እንደተላከላቸው ይነግሯቸዋል፡፡ ፕሬዚደንቱ ዋረን ሀርዲንግ አርፈዋል የሚል መርዶ የያዘ ቴሌግራም ነበር፡፡ በዚያ ኩሊጅ ፕሬዝደንት ሆኑ፡፡

ኩሊጅ በግል ማስታወሻቸው ላይ ይህንን ባውቅኩ ጊዜ መጀመሪያ ተነስቼ ቆምኩ እና ጸለይኩ፡፡ ከዚያም ከሕገ መንግሥቱ ውስጥ የፕሬዝደንት ቃለ መሐላው ያለበትን አውጥቼ ለአባቴ ያዘው ብዬ ሰጠሁት፡፡ ከዚያም ተመልሼ ጥቅልል ብዬ ተኛሁ ብለው እንደጻፉ ተመልክቷል፡፡

ሊንደን ጆንሰን 1963 ዓ.ም

ቀደም ሲል ከተነገረው በተጻራሪ ድንገተኛ ሐዘን የተመላበትን ሊንደን ጆንሰን 36ኛው ፕሬዚደንት ሆነው ቃለ መሓላ የፈጸሙበትን ቀን አይረሴ ነው፡፡ ጆንሰን ቃለ መሃላ የፈጸሙት ፕሬዚደንት ጆን ኤፍ ኬኔዲ በሰው እጅ በጥይት ከተገደሉ ከአንድ ሰዓት ተኩል በኃላ ነበር፡፡
ጆንሰን በፕሬዝደንታዊው አውሮፕላን ኤር ፎርስ ዋን ውስጥ ቀኝ አጃቸውን ከፍ አድርገው ቃለ መሃላ ሲፈጽሙ የተነሳው ፎቶግራፍ ታሪኩን ይናገራል፡፡ በስተቀኛቸው ባለቤታቸው በስተግራቸው የሟቹ ፕሬዚደንት ባለቤት ጃኪ ኬኔዲ አጅበዋቸው ይታያሉ፡፡


Репост из: ኢትዮ ኘላስ + Ethio Plus
የአሜሪካ ፕሬዚደንቶች በዓለ ሲመት ታሪክ


በከባድ ብርድ ምክኒያት የትረምፕ ቃለ መሐላ ሥነ ሥርዐት በቤት ውስጥ እንዲከናወን ተወሰነ
--------

የአሜሪካ ተመራጭ ኘሬዝደንቶች ከቤት ውጭ በሚካሄድ በዓለ ሲመት ስነስርዓት ነበር ቃለ መሃላ የሚፈፅሙት።

አሁን ግን በዋሽንግተን ባለው ከባድ ብርድ ምክንያት የዶናልድ ትራምኘ የቃለ መሃላ ስነስርዓት በምክር ቤቱ ሕንፃ ካፒቶል ሂል እንዲከናወን ተወሰኗል።

ቃለ መሃለው በሚፈፀምበት የፊታችን ሰኞ በዋሽንግተን እጅግ ከባድ ቅዝቃዜ ይኖራል በመባሉ ነው የተመራጩ ፕሬዚደንት ቃለ መሃላ በምክር ቤቱ ውስጥ እንዲከናወን የተወሰነው።


የኢትዮጵያ ወዳጅ የሆኑት የቀድሞ የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአፍሪካ ጉዳዮች ረዳት ሚኒስትር ቲቦር ናጊ የትራምፕን መምጣት ተከትሎ ወደ አሜሪካ የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት መመለሳቸውን አስታውቀዋል።

ቲቦር ናጊ የሻዕቢያው መሪ ኢሳያስ አፈወርቂ መወገድ አለበት በሚል የሚታወቁ ሲሆን በቅርቡ የሶሪያው መሪ በሽር አልአሳድን መውደቅ ተከትሎ ኢሳያስም የአሳድ እጣፈንታ ይጠብቀዋል በማለት በማህበራዊ ሚዲያቸው መለጠፋቸው ይታወሳል።

የቀድሞ በ ኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ቲቦር ናጊ እንደ ህዳሴው ግድብ በመሳሰሉ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅሞች ላይ በተደጋጋሚ ከኢትዮጵያ ጎን በመሰለፍ የሚታወቁ ለኢትዮጵያ ያላቸውን ውዴታም በአደባባይ የሚገልፁ ጉምቱ የአሜሪካ ዲፕሎማት ሲሆኑ ከወዲሁ ኢሳያስና ግብፅን አጣብቂኝ ውስጥ የከተተ ዜና መሆኑ ተዘግቧል ።


የአሜሪካው ተመራጭ ፕረዚዳንት ዶናልድ ትራንፕ የቀድሞ የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ የአፍሪካ ሌጋሲ ኢንስቲትዩት ልዑካንን በመምራት በበዓለ ስመታቸው እንዲገኙ መጋበዛቸው ተገለፀ።

የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በዓለ ስመት ላይ የምታደሙ የአፍሪካ መሪዎችንና ተፅዕኖ ፈጣሪ ግለሰቦች ስም ዝርዝር በአዘጋጆቹ በኩል ይፋ ተደርጓል።

እንደ ደይሊትራስ ዘገባ ግብዣው በጥር 13 ቀን 2025 ለወጣቱ የናይጄሪያ የንግድ ሥራ መሪ ዶ/ር ኡዞቹክ በተላከ ደብዳቤ “ፕሬዝዳንት ዶናልድ ጄ. ትራምፕን በማክበር የመድብለ ባህላዊ ጥምረት የአሜሪካ ፕሬዚዳንታዊ የምረቃ ቦል አስተናጋጅ ኮሚቴን በመወከል እንዲገኙ ስንጋብዝ በታላቅ ክብር ነው ይላል ብሏል።

ይህ ታላቅ ዝግጅት በጥር 20፣ 2025 በዋሽንግተን የሚካሄድ ሲሆን በማዳም ፍራንያ ኢ ካብራል ሩዪዝ መሪነት ከአፍሪካ ሌጋሲሲ ኢንስቲትዩት በቀረበው ሀሳብ እንደተገለጸው ላበረከቱት ልዩ አስተዋፅዖ እና አመራር እውቅና በመስጠት፣ በዚህ ልዩ ዝግጅት ላይ በመገኘታችን ታላቅ ክብር እንሰጣለን ብሏል።

በዚሁም የወቅቱን የአፍሪካ ሌጋሲሲ ኢንስቲትዩት ልዑካንን በዩኤስ ፕሬዝዳንታዊ የትራምፕ በዓለ ስመት ላይ የሚመሩት የቀድሞ የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ እንደሆኑም ዘገባው ጠቅሷል።
WT


የአሜሪካ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ቲክቶክ የብሔራዊ ጸጥታ አደጋ በመደቀኑ እንዲዘጋ ካልሆነም እዲሸጥ ለሚጠይቀው የፌደራል ህግ ድጋፍ መስጠቱ ተሰማ፡፡
በፍርድ ቤቱ ዛሬ በተካሄደው የቃል ክርክር የቻይናው ባይትዳንስ ንብረት የሆነው ቲክቶክ እንዲታገድ በሙሉ የድምጽ ድጋፍ ማሳለፉን አሶሺየትድ ፕሬስ ዘግቧል።
በአሜሪካ ከ170 ሚሊየን በላይ ተጠቃሚ ያለው ቲክቶክ የተጠቃሚዎችን የግል መረጃ ለቻይና መንግስት አሳልፎ ይሰጣል በሚል ነው እንዲሸጥ ካልሆነም እንዲዘጋ የሚል ክስ የቀረበበት።
ዛሬ በተላለፈው ውሳኔ መሰረት ቲክቶክ ከእሁድ ጀምሮ የሚታገድ ሲሆን እግዱ ተግባራዊ ሲሆን መተግበሪያውን አዳዲስ ተጠቃሚዎች ማውረድ እንደማይችሉ እና ነባር ተጠቃሚዎች ደግሞ ማዘመን (አፕዴት) እንደማችሉ በመረጃው ተገልጿል።
ዶናልድ ትራምፕ የቲክቶክን ጠቀሜታ መገንዘባቸውና ጠቅላይ ፍርድ ቤቱ ውሳኔውን እንዲያዘገይ ጠይቀው የነበረ ሲሆን ጉዳዩን በድርድር እፈታዋለሁ ማለታቸው ይታወሳል።
የአሜሪካ ጠቅላይ ፍርድ ቤት 9 ዳኞች ያሉት ሲሆን የሀገሪቱን ህገ መንግስት የሚጻረሩ ጉዳዮችን የመስማት፣ ለህግ ትርጓሜ የመስጠት፣ የሲቪል መብቶችን የማስጠበቅ፣ በግዛቶች መካከል የተፈጠሩ አለመግባባቶችን የመፍታት፣ ዓለም አቀፍ ስምምነቶችን የሚመለከቱ ጉዳዮች የመምራት ስልጣን አለው፡፡

Показано 20 последних публикаций.