በአዲስ አበባ የሚገኙ
35 ትምህርት ቤቶች ለ2017 የትምህርት ዘመን ምዝገባ እንዳያካሒዱ ዕገዳ ተጣለባቸው።
በከተማዋ የሚገኙ
35 የቅድመ አንደኛ እና አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለ2017 የትምህርት ዘመን ምዝገባ እንዳያካሒዱ ማገዱን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን አሳውቋል።
ትምህርት ቤቶቹ በዋናነት በትምህርት ፖሊሲ ጥሰት፣ በትምህርት ስታንዳርዱ መሰረት ከ
75 በመቶ በታች ያመጡ እንዲሁም የትምህርት ጊዜ ሰሌዳን በአግባቡ አለመጠቀም የታየባቸው በመሆኑ ዕግዱ እንደተጣለባቸው ባለስልጣኑ ገልጿል።
ዕግዱ ከተጣለባቸው ትምህርት ቤቶች መካከል የጊብሰን ትምህርት ቤቶች፣ የቅዱስ ሚካኤል አምስት ትምህርት ቤቶች እና የካ አፖሎ ትምህርት ቤት እንደሚገኙበት የባለስልጣኑ ዋና ሥራ አስኪያጅ ዳኛው ገብሩ ተናግረዋል።
ዕገዳ በተጣለባቸው ትምህርት ቤቶች ይማሩ የነበሩ ተማሪዎች በመኖረያ አቅሪያቢያቸው በሚገኙ የግል እና የመንግሥት ትምህርት ቤቶች ያለምንም ተጨማሪ ክፍያ እንዲስተናግዱ ይደረጋል ብለዋል።
ሌሎች
41 ትምህርት ቤቶች በራሳቸው ጊዜ መቀጠል ስላልቻሉ ፈቃዳቸው መሰረዙን የገለፁት ኃላፊው፤ የ
150 ትምህርት ቤቶች ጉዳይ በሒደት ላይ እንደሆነና ወደፊት እንደሚገለፅ ተናግረዋል።
በ2017 የትምህርት ዘመን በአዲስ አበባ ተማሪዎችን መዝግበው እንዲያስተምሩ ፈቃድ የተሰጣቸው ትምህርት ቤቶች
1,332 መሆናቸውን ጠቁመዋል።
@tikvahuniversity