Фильтр публикаций


#FulbrightApplications

ለ Fulbright የውጭ ሀገር ተማሪዎች 2025-26 የትምህርት ፕሮግራም ያመልክቱ!

ፕሮግራሙ የማስተርስ ወይም የሦስተኛ ዲግሪዎን በዩናይትድ ስቴትስ በሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች መከታተል ያስችላል፡፡

ተከታዩን ሊንክ በመጫን ያመልክቱ 👇
https://apply.iie.org/ffsp2026

የማመልከቻ ጊዜው የሚያበቃው 👇
አርብ ሚያዝያ 24/2017 ዓ.ም.

@tikvahuniversity

21.3k 0 207 14 75

አዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ የቀድሞ ተማሪዎች ካርኒቫል በሳምንቱ መጨረሻ ያካሒዳል፡፡

ሚያዝያ 17 እና 18/2017 ዓ.ም የሚከናወነው ካርኒቫሉ፤ የቀድሞ ተማሪዎችን ለማገናኘት፣ ትውስታን ለመጋራት እና ኔትወርኪንግ ለመፍጠር አላማ ያደረገ ነው ተብሏል፡፡

የፓናል ውይይቶች እና አዝናኝ ትዕይንቶችን ጨምሮ የተለያዩ ኹነቶች እንደሚከናወኑ ተገልጿል፡፡

የቀድሞ የናዝሬት ቴክኒክ ኮሌጅ፣ የቀድሞ የናዝሬት የቴክኒክ መምህራን ትምህርት ኮሌጅ፣ የቀድሞ የአዳማ ዩኒቨርሲቲ እንዲሁም የአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ምሩቃን ካርኒቫሉን እንደሚታደሙ ይጠበቃል፡፡

@tikvahuniversity

20k 0 11 2 28

3ኛ ዙር የኮምፒውተር ጥገና እና ኔትዎርኪንግ (Computer Maintenance and Networking) ስልጠና በፒያሣ እና በመገናኛ ካምፓስ ምዝገባ ላይ ነን!

👉 ንድፈ ሀሳብን ከተግባር ጋር በማዛመድ የሚሰጥ ስልጠና
👉 የሥራ ላይ ስልጠና (Internship) የተመቻቸለት

የበለጠ ይጠብቁ ...
ሴጅ ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት

☎️ 0906777799 / 0906777755
አድራሻ
ቁ.1: ፒያሣ ቸርችል ጎዳና ኤልያና ሆቴል 2ኛ ፎቅ
ቁ.2: መገናኛ ታሜጋስ ህንፃ 2ኛ ፎቅ

Telegram: https://t.me/sagetraininginstitute
TikTok: https://www.tiktok.com/@sage_training_institute
LinkedIn: https://www.linkedin.com/company/sage-training-institute


#ጥቆማ

5 ሚሊዮን የኢትዮጵያ ኮደሮች ኢንሼቲቭ ነፃ ስልጠናን ለመከታተል ይመዝገቡ።

ዓለም አቀፍ ተቀባይነት ያለው ሰርትፍኬት ማግኘት የሚያስችልዎትን ስልጠና ባሉበት ሆነው ይውሰዱ።

የስልጠና ዘርፎች፦

► ዌብ ፕሮግራሚንግ
► አንድሮይድ ማበልፀግ
► ዳታ ሳይንስ
► አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ፋንዳሜንታልስ

ለመመዝገብ 👇
https://www.ethiocoders.et/

በስምንት ሳምንት ስልጠናውን ሲያጠናቅቁ፥ ዓለም አቀፍ ተቀባይነት ያለው ሰርተፊኬት ይበረከትልዎታል።

@tikvahuniversity

37.4k 0 272 42 156

እንኳን ለጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የትንሳዔ በዓል አደረሳችሁ!

ለክርስትና ዕምነት ተከታዮች በሙሉ መልካም የብርሃነ ትንሣኤ በዓል እንመኛለን። በዓሉ የሰላም፣ የደስታ፣ የፍቅር እና የመተሳሰብ ይሁንልዎ።

የበለጠ ይጠብቁ ...
ሴጅ ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት

☎️   0906777799 / 0906777755
አድራሻ
ቁ.1: ፒያሣ ቸርችል ጎዳና ኤልያና ሆቴል 2ኛ ፎቅ
ቁ.2: መገናኛ ታሜጋስ ህንፃ 2ኛ ፎቅ

Telegram: https://t.me/sagetraininginstitute
TikTok: https://www.tiktok.com/@sage_training_institute
LinkedIn: https://www.linkedin.com/company/sage-training-institute


እንኳን ለብርሃነ ትንሣኤው አደረሳችሁ!

በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የምትገኙና በዓሉን ከቤተሰቦቻችሁ ርቃችሁ እያከበራችሁ ላላችሁ ተማሪዎች መልካም በዓል እንመኛለን።

@tikvahuniversity

36.5k 0 30 325 514

በፌዴራል ተቋማት ላይ በተደረገ ፍተሻ የ129 የመንግሥት ሠራተኞች የትምህርት ማስረጃ ሐሰተኛ ሆኖ ተገኘ።

የትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) የተቋማቸውን የዘጠኝ ወር ሪፖርተር ለህዝብ ተወካዮች ም/ቤት ባቀረቡት ወቅት እንደገለፁት፥ ትምህርት ሚኒስቴር የፌዴራል መስሪያ ቤት ሠራተኞችን የትምህርት ማስረጃ የማጣራት ሥራ እያከናወነ ይገኛል።

በመጀመሪያ ዙር ከ280 የፌዴራል እና ተጠሪ ተቋማት መስሪያ ቤቶች ከሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን የተላከ መረጃን መሠረት በማድረግ የ32,815 ሰራተኞች የትምህርት ማስረጃ ትክክለኛነት መጣራቱን አብራርተዋል።

በዚህም 129 ሐሰተኛ የትምህርት ማሰረጃ የተገኘ ሲሆን፤ የ469 ሰራተኞች መረጃ ያልተሟላ በመሆኑ ለሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ተመላሽ ተደርጓል ብለዋል።

ከ2017 ዓ.ም ጀምሮ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተመራቂዎች የዲግሪ ሰርተፊኬት ህትመት በአንድ ማዕከል ማለትም በትምህርት ሚኒስቴር እንደሚታተም መገለፁ ይታወቃል። #ኢፕድ #GazettePlus

@tikvahuniversity

44.9k 0 48 51 355

#BongaUniversity

ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ ተጠባባቂ ፕሬዝዳንት ተመድቦለታል።

ደገላ ኤርገና (ዶ/ር) ከሚያዝያ 07/2017 ዓ.ም ጀምሮ የቦንጋ ዩኒቨርሲቲ ተጠባባቂ ፕሬዝዳንት ሆነው እንዲሠሩ የተወከሉ መሆኑን በትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) በቀን ሚያዝያ 01/2017 ዓ.ም ተፈርሞ የወጣ ደብዳቤ ያሳያል።

የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት በመሆን ላለፉት ዓመታት ሲያገለግሉ የቆዩት ጴጥሮስ ወ/ጊዮርጊስ (ዶ/ር) ከኃላፊነታቸው የተነሱበት ምክንያት አልተገለፀም።

ጴጥሮስ ወ/ጊዮርጊስ (ዶ/ር) ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ ከምስረታው ጀምሮ አሁን ለደረሰበት ስኬት በርካታ አበርክቶ እንደነበራቸው በመንግሥት ከፍተኛ ባለሥልጣናት ጭምር ከዚህ ቀደም ሲገለፅ እንደነበር አይዘነጋም።

@tikvahuniversity

42.4k 0 56 46 226

ዲላ ዩኒቨርሲቲ ለ2017 ዓ.ም ዕጩ ተመራቂዎች #ሞዴል የመውጫ ፈተና ሰጥቷል።

በዩኒቨርሲቲው የትምህርትና ስነ-ባህሪ ኮሌጅ እና የኢንጂነሪንግና ቴክኖሎጂ ኮሌጅ ዕጩ ተመራቂዎች ሞዴል የመውጫ ፈተና መውሰዳቸወሰ ተገልጿል።

በቀጣይ የዩኒቨርሲቲው ሌሎች ኮሌጆች ለዕጩ ተመራቂዎቻቸው ሞዴል የመውጫ ፈተና ይሰጣሉ ተብሏል።

ቀጣዩ ሀገር አቀፍ የመውጫ ፈተና በሰኔ 2017 ዓ.ም ለሁሉም የመንግሥት እና የግል ዕጩ ተመራቂዎች እንደሚሰጥ ይታወቃል።

ፈተናውን ለመውሰድ ብሔራዊ የዲጂታል መታወቂያ (ፋይዳ) ማውጣት የግድ እንደሆነ መገለፁ አይዘነጋም።

@tikvahuniversity


M-PESA ታላቅ የበዓል ቅናሽ!

የበዓል ግብይታችንን በ M-PESA እንክፈል፣ 10% ተመላሽ እናግኝ!

እና ምን እንጠብቃለን ሸመት ሸመት እናድርግ!

#MPESAEthiopia #MPESASafaricom


ዛሬ በክርስትና ኃይማኖት ተከታዮች ዘንድ ልዮ ቀን ነው። መልካም የጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የስቅለት መታሰቢያ በዓል ይሁንላችሁ።

መልካም በዓል! 

የበለጠ ይጠብቁ ...
ሴጅ ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት

☎️   0906777799 / 0906777755
አድራሻ
ቁ.1: ፒያሣ ቸርችል ጎዳና ኤልያና ሆቴል 2ኛ ፎቅ
ቁ.2: መገናኛ ታሜጋስ ህንፃ 2ኛ ፎቅ

Telegram: https://t.me/sagetraininginstitute
TikTok: https://www.tiktok.com/@sage_training_institute
LinkedIn: https://www.linkedin.com/company/sage-training-institute


✝ እንኳን ለጌታችን ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የስቅለት መታሰቢያ በዓል አደረሳችሁ!!

ዕለቱ መልካም የምናደርግበት፥ የተቸገሩን የምንረዳበት እና አምላካችንን የምናስብበት እንዲሆን ቲክቫህ ዩኒቨርሲቲ ይመኛል።

@tikvahuniversity

39.8k 0 31 388 641

#HaramayaUniversity

ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ በኢትዮጵያና የአፍሪካ ቀንድ ታሪክ የዶክትሬት ዲግሪ ትምህርት መስጠት ሊጀምር ነው።

በሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የኅብረተሰብ ሳይንስና ስነ-ሰብ ትምህርት ኮሌጅ ሦስት አዳዲስ ፕሮግራሞችን ለመጀመር የስርዓተ ትምህርት የውስጥ ክለሳ አካሒዷል።

አዲስ የሚጀመሩ የትምህርት ፕሮግራሞች፦

➫ የኢትዮጵያና የአፍሪካ ቀንድ ታሪክ በዶክትሬት ዲግሪ
➫ የባህልና ቅርስ ጥናት በማስተርስ ዲግሪ
➫ ፖለቲካል ሳይንስና ዓለም አቀፍ ግንኙነት በመጀመሪያ ዲግሪ

በቀጣይ የውጭ ክለሳ በማድረግ በ2018 የትምህርት ዘመን በፕሮግራሞቹ ትምህርት ለማስጀመር እየተሠራ መሆኑ ተገልጿል።

@tikvahuniversity

48k 0 47 26 214

🌐 እጅግ ፈጣን ዋይፋይ በአዲስ ቅመም! ሊያውም ከጉርሻ ጋር!

💨⚡️ እስከ 6 ሰዓት የሚቆይ የባትሪ አቅም ያለውና አዳዲስ የቴክኖሎጂ ትሩፋቶችን ይዞ በአንዴ እስከ 8 ሰው የሚያስጠቅመውን ልዩ ቅመም MIFI ን ገዝተን ፈጣን 4G ኢንተርኔት እንጠቀም!

🍰 ለ30 ቀን ከሚቆይ ነጻ 30ጊባ ዳታ ጉርሻ ጋር!

ከሳፋሪኮም ጋር አንድ ወደፊት⚡️

#SafaricomEthiopia


“ እንዳንማር ነው እንዴ የተፈለገው? ውጤቱ የማይያዝልን ከሆነ ለምን ሪሚዲያል ተፈተንን ?” - የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች

“ ከትምህርት ሚኒስቴር የመጣ መመሪያ ነው” - የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎች ኅብረት
 

የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ አንደኛ ዓመት ጀማሪ የሕግ ተማሪዎች ፊልድ ለመምረጥ የሪሚዲያል ውጤታቸው ብቻ አለመያዙን፣ ሪሚዲያል ከተፈተኑ ከ90 በላይ ተማሪዎች 40 የሚሆኑት ውጤታቸውን ባለማወቃቸው ቅሬታ አሰሙ።

የኢንትራንስ ውጤታቸው ከሪሚዲያል ጋር ተደምሮ ፊልድ ለመምረጥ እንደ መስፈርት መያዙን፣ የሪሚዲል ፈተና ውጤታቸው ከፍተኛ ቢሆንም የኢንትራንሱ በመያዙ ዝቅ ስለሚያደርገው የሚፈልጉትን ፊልድ መምረጥ እንዳልቻሉ ተማሪዎቹ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

በሌላ በኩል፣ ሪሚዲያል ከተፈተኑት 96 የሕግ ተማሪዎች መካከል ውጤት የተለቀቀላቸው የ40ዎቹ ብቻ እንደሆነ፣ ቀሪዎቹ ውጤታቸውን እንዳላወቁ ገልጸዋል።

ተማሪዎቹ አክለው ምን አሉ?

“ለፊልድ መረጣ በ12ኛ ክፍል ውጤት ወይም በሪዛልቱ ሳይሆን መያዝ የነበረበት በሪሚድያሉ ብቻ ነበረበት። በተጨማሪ ውጤቱ የሁላችንም ተማሪዎች ሙሉ መለቀቅ ነበረበት። 96 ተማሪዎች ተፈትነዋል የተለቀቀው የ40ዎቹ ነው። ለምን የሁሉም አልተለቀቀም?።

ማለፍ ወይም መውደቃችንን ለማወቅ ግዴታ የሁሉም ተማሪዎች ውጤት መለቀቅ ይኖርበታል። ባለመለቀቁ ብዙ ተማሪ ችግር ሊያጋጥመው ይችላል። ውጤታችን ሳይለቀቅ ፈተናውን ራሱ በትክክል እንዳረሙትና እንዳላረሙት በምን ልናቀው እችላለን? 

እንዳንማር ነው እንዴ የተፈለገው? ውጤቱ የማይያዝልን ከሆነ ለምን ሪሚዲያል ተፈተንን?” ሲሉ ጠይቀዋል።

የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎች ኀብረት ምን አለ?

ለተማሪዎቹ ቅሬታ የጠየቅነው የዩኒቨርሲቲው ተማሪዎች ኀብረት፣ “ጥያቄው አግባብነት ያለው ጥያቄ ነው ብለንም አናስብም” የሚል ምላሽ ሰጥቷል።

“ምክንያቱም መመሪያ ላይ የነበረ ነገርን ነው እየተገበረ ያለው ሪጅስትራር ስናወራ ያገኘነው ነው። 20% የኢንትራስ ውጤትን 30% ትምርት ክፍል ያዘጋጀው ሲኦሲና 50% ኮምሌቲቭ ጂፒያቸው መሰረት ነው የተወዳደሩት።

ያ ደግሞ ከትምህርት ሚኒስቴር የመጣ መመሪያ ነው በዛ መመሪያ መሰረት ነው ሪጅስትራሉ እየሰራ ያለው” ብሏል።

የ40ዎቹ ውጤት ተለቆ የሌሎቹ ያልተለቀቀውስ ለምንድን ነው? ስንል ላቀረብንለት ጥያቄ በሰጠን ምላሽ፣ “ያለፉት ተማሪዎች ውጤት ነው የሚለቀቀው። እነዚህን ተማሪዎች ተቀብለናል እነዚህ ተማሪዎች አልፈዋል፣ ተብሎ ነው የሚለቀቀው” የሚል ምላሽ ሰጥቷል።

የተፈተኑ ተማሪዎች ወጤቱ ተለቆ ማለፍ/አለማለፋቸው መነገር አልነበረባቸውም? የሚለውን ጥያቄም፣ “ውጤቱን ማየት የሚፈልግ ሪጅስትራል መጥቶ ማየት ይችላል። ያለፉት ተማሪዎች ስማቸው ወደ ኮሌጅ ስለሚተላለፍ ወደምዝገባው ነው የሚቀጥሉት” ሲል መልሷል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia

49.3k 1 62 92 342

የሙስሊም ሴት ተማሪዎች ሂጃብ ጉዳይ

የትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕሮፌሰር) በትምህርት ዘርፍ የዘጠኝ ወራት ዕቅድ አፈጻጻም ላይ በሕ/ተ/ም/ቤት ተገኝተው ማብራሪያ መስጠታቸው ይታወቃል፡፡

የምክር ቤቱ አባላት ሙስሊም ሴት ተማሪዎች ከሂጃብ ጉዳይ ጋር በተያያዘ በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች ችግር እየገጠማቸው መሆኑን አንስተዋል፡፡

በጉራጌ ዞን ጉንችሬ ከተማ፣ በትግራይ ክልል አክሱም ከተማ አንዲሁም በዲላ ዩኒቨርሲቲ ከሂጃብ ጋር በተያያዘ ችግሮች መከሰታቸውን ያነሱት አባላቱ፤ በጉዳዩ ላይ መንግሥት ዘላቂ መፍትሔ እንዲያስቀምጥ ጠይቀዋል፡፡

የትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕሮፌሰር) ምን አሉ?

"የኢትዮጵያ ሕግና ደንቦች፥ በዚህ ጉዳይ ላይ የወጡት ደንቦች ሂጃብ ለብሶ ትምህርት መማርን የሚከለክል የኢትዮጵያ ሕግ የለም፡፡ በሂጃብ ምክንያት፥ ማንም ሂጃብ ለበሰ ተብሎ ትምህርት ቤት መከልከል አይችልም፡፡"

"ኒቃብ ግን የተለየ ነው፡፡ ህጻናቶች፣ ልጆች ባሉበት ትምህርት ቤት የአንድ ሰው ፊት ተሸፍኖ በሚገባ ጊዜ የsecurity risk (የደኅንነት ስጋት) አለው፡፡"

"ከመጅሊስ ሰዎች ጋር ተሰብስበን፣ ተወያይተን፣ ተማምነናል፡፡ በኒቃብ ላይ ሕግ ማስቀየር ካለባችሁ እዚሁ ፓርላማ በማምጣት ማስቀር ነው እንጂ፣ በየጊዜው Issue እየሆነ የግጭት ምክንያት መሆን የለበትም፡፡" "አሁን ያለው ሕግ ግን ሂጃብ በምንም ምክንያት የትም ቦታ መከልከል የለበትም፡፡"

@tikvahuniversity

44.7k 0 37 357 638

በደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲ በ2017 ዓ.ም ሁለተኛ ሴሚስተር በሕግ እና በአይቲ የድኅረ-ምረቃ ትምህርት ለመከታተል ያመለከታችሁ ተማሪዎች ምዝገባ ማክሰኞ ሚያዝያ 14/2017 ዓ.ም መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል፡፡

የአይቲ የድኅረ-ምረቃ ፕሮግራም ትምህርት ሚያዝያ 15/2017 ዓ.ም፤ የሕግ ደግሞ ሚያዝያ 18/2017 ዓ.ም ይጀምራል ተብሏል፡፡

@tikvahuniversity


4ኛ ዙር የፋይናንስ እና ካፒታል ማርኬት ስልጠና በፒያሣ እና በመገናኛ ካምፓስ ምዝገባ ላይ ነን።

🔔 ፈጥነው ይመዝገቡ!

የካፒታል ማርኬት ገበያ በኢትዮጵያ ተጀምሯል። እርስዎም በሴጅ ኢንስቲትዩት የሚሰጠውን የፋይናንስና ካፒታል ማርኬት ስልጠና በመውሰድ በገበያው ለመሳተፍ ራስዎን ያዘጋጁ።

ብቁ በሆኑ መምህራን የሚሰጠውን ስልጠና ይውሰዱና ትግበራውን ይጠባበቁ!

☎️   0906777799 / 0906777755
አድራሻ
ቁ.1: ፒያሣ ቸርችል ጎዳና ኤልያና ሆቴል 2ኛ ፎቅ
ቁ.2: መገናኛ ታሜጋስ ህንፃ 2ኛ ፎቅ

Telegram: https://t.me/sagetraininginstitute
TikTok: https://www.tiktok.com/@sage_training_institute
LinkedIn: https://www.linkedin.com/company/sage-training-institute


#DireDawaUniversity

ዘመናዊ የመልቲ ሚዲያ ስቱዲዮ ግንባታ በተመረጡ የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች እየተከናወነ እንደሚገኝ ይታወቃል።

ስቱዲዮዎቹ የዲጂታል ትምህርትን ለማጠናከር ትልቅ ፋይዳ እንደሚኖራቸው ይታመናል።

የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ መልቲ ሚዲያ ዲጂታል ስቱዲዮ (ምስል ተያይዟል) የምስራቅ ኢትዮጵያ ዩኒቨርሲቲዎች የበይነ መረብ ትምህርት (E-Learning) ሪሶርስ ማዕከል በመሆን ያገለግላል ተብሏል።

@tikvahuniversity


#BongaUniversity

ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በተፈጥሮ ሃብት አያያዝ እና አጠባበቅ ላይ ትኩረት የሚያደርጉ የጥናት ውጤቶች የሚወጡበት ማኪራ ጆርናል (Makira Journal of Natural Resource Management) ህትመት አስጀመረ።

የጆርናሉ ህትመቱ ይፋዊ የማስጀመሪያ ስነ-ስርዓት በዛሬው ዕለት ተካሒዷል።

@tikvahuniversity

Показано 20 последних публикаций.