AddisWalta - AW


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: Новости и СМИ


This is Walta Media and Communication Corporate’s official Telegram channel.
For more updates please visit https://shorturl.at/ehosX https://www.youtube.com/c/WaltaTV/featured

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
Новости и СМИ
Статистика
Фильтр публикаций


የገንዘብ ሚኒስትሩ ከአሜሪካ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ጋር ተወያዩ

ሚያዝያ 17/2016 (አዲስ ዋልታ) የገንዘብ ሚኒስትር አሕመድ ሺዴ ከተለያዩ የአሜሪካ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ጋር በወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ተወያይተዋል፡፡

የ2024 የዓለም ባንክ እና አይኤም ኤፍ ስብሰባዎች ጎን ለጎን በሚኒስትር አሕመድ ሺዴ የሚመራው ልዑክ ከአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የአፍሪካ ጉዳዮች ረዳት አምባሳደር ሞሊ ፊ፣ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ አምባሳደር ማይክል ሀመር እና የአሜሪካ የዓለም አቀፍ ጉዳዮች ግምጃ ቤት ምክትል ፀሐፊ ጄይ ሻምባህ ጋር ተወያይቷል፡፡

ውይይቱ የኢትዮጵያን ወቅታዊ ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ ሁኔታ እንዲሁም የሀገሪቱን የማክሮ ኢኮኖሚ ማዕቀፍ ለማሻሻል በሚደረጉ ማሻሻያዎች ላይ ያተኮረ እንደሆነ ተገልጿል።

ሁለቱ ወገኖች በዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም (አይኤምኤፍ) እና የዓለም ባንክ በኩል የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ የሚያገግምበትን ሁኔታ ለመፍጠር፣ ሀገራዊ ትስስር እና ቀጣናዊ መረጋጋትን ለማስፈን በሚያስፈልገው ሁሉን አቀፍ ድጋፍ ላይ መወያየታቸውን በአሜሪካ የኢትዮጵያ ኤምባሲ መረጃ ያመላክታል፡፡


አጓጊው ደሞ አዲስ መጪው እሁድ ከቀኑ 9 ሰዓት ጀምሮ #በቀጥታ ስርጭት ለእናንተ ለተመልካቾቻችን ተወዳዳሪዎቹን ይዞላችሁ ይቀርባል።

በቀጥታ ስርጭትም ዳኞችና ተወዳዳሪዎች በተመልካቾች ድምፅ ይዳኛሉ።  በዕለቱም የተሰጣቸውን ኮድ በማስቀደም በ8970 SMS ድምጽ ይስጡ!

ያሬድ አበበ - B1
ታረቀኝ ረጃው - B3
እንግዳው አስፋው - B5
ኃይለኢየሱስ ታደገ - B6

#ደሞ_አዲስ #አዲስ_ዋልታ #music #idol

እሁድ ከቀኑ 9 ሰዓት ጀምሮ በቀጥታ ስርጭት ይጠብቁን 🎼


“የሊቢያ ጠቅላይ ሚኒስትር አብዱልሃሚድ አልዳባቢያን በመቀበሌ ደስታ ተሰምቶኛል። በውይይታችን ወቅት በቀጣናዊ የሰላም እና መረጋጋት፣ የኢኮኖሚ ትብብር፣ የሰው ኃይል ልውውጥ እና በሌሎች የጋራ ፍላጎት ጉዳዮችን አንስተናል።” - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ


የሚኒስትሮች ምክር ቤት ባካሄደው መደበኛ ስብሰባ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳለፈ

ሚያዝያ 17/2016 (አዲስ ዋልታ) የሚኒስትሮች ምክር ቤት በዛሬው ዕለት ባካሄደው 31ኛ መደበኛ ስብሰባ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳልፏል፡፡
በዚህም፡-

1. ምክር ቤቱ በቅድሚያ የተወያየው የወጪ ንግድ የቀረጥ ማበረታቻ ሥርዓት አዋጅን ለማሻሻል የቀረበው ረቂቅ አዋጅ ላይ ነው፡፡ ለኢንደስትሪ ልማትና ኢንቨስትመንት የሚያስፈልገውን የውጭ ምንዛሪ ግኝት ለማሳደግ፣ በወጪ ንግድ ሥራ ላይ የተሰማሩ ባለሀብቶች በማበረታታት ረገድ የታዩ ውስንነቶችን ለመቅረፍ እና የዘርፉን ተዋንያን የሚያበረታታ ሥርዓት በመዘርጋት ተወዳዳሪነት ማላቅ ይቻል ዘንድ ረቂቅ ማሻሻያ አዋጅ ተዘጋጅቶ ቀርቧል፡፡ ምክር ቤቱም ረቂቅ ማሻሻያ አዋጁ ላይ ከተወያያ በኋላ ግብዓቶችን በማከል ወደ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲተላለፍ በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡

2. በመቀጠል ምክር ቤቱ የተወያየው የፌዴራል ህብረት ስራ ኮሚሽን ለሚሰጣቸው አገልግሎቶች የሚያስከፍለውን የአገልግሎት ክፍያ ለመወሰን በቀረበ ረቂቅ ደንብ ላይ ነው፡፡ ኮሚሽኑ የሚሰጣቸውን አገልግሎቶች ማስፋት፣ የአገልግሎቶቹን የጥራት ደረጃ ማሻሻል፣ ብሎም የተጠቃሚውን ማህበረሰብ አቅም ባገናዘበ መልኩ አገልግሎት ለመስጠት ያወጣውን ወጪ በከፊል መሸፈን የሚያስችል ስርዓት መዘርጋት በማስፈለጉ ረቂቅ ደንቡ ተዘጋጅቶ ለምክር ቤቱ ቀርቧል፡፡ ምክር ቤቱም በረቂቅ ደንቡ ላይ ከተወያየ በኋላ ግብዓቶችን በማከል በነጋሪት ጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በስራ ላይ እንዲውል በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡
👇👇
https://shorturl.at/rsJV1


ውበት የሚያበቃበት ቀን የለውም የምትለው የ60 ዓመቷ ቁንጅና ተወዳዳሪ

የ60 ዓመቷ የሕግ ባለሙያ እና ጋዜጠኛ አሌጃንድራ ማሪሳ ሮድሪጉዝ በቅርቡ የሚስ ቦነስ አይረስን ውድድር በማሸነፍ ለሚስ አርጀንቲና የቁንጅና ውድድር ብቁ ሆናለች። ውበት የሚያበቃበት ቀን የለውም የምትለው አሌጃንድራ ማሪሳ የ2024 ሚስ ዩኒቨርስ አሸናፊ ለመሆንም ቆርጣ ተነስታለች።

እንደ አውሮፓዊያን አቆጣጠር 1958 ጀምሮ በውድድሩ መሳተፍ የሚችሉት ከ18 እስከ 28 ዓመት የዕድሜ ክልል ውስጥ ያሉ ሴቶች ብቻ ነበሩ፡፡ ባለፈው ዓመት ግን የዕድሜ ገደቡ ተነሳ። ይህ ለአርጀንቲናዊቷ የ60 ዓመት ቆንጆ “ሁኔታው ለእኔ ተመቸኝ” የሚያስብል ሆነና ተሳተፈች።

አርጀንቲናዊቷ ተወዳዳሪ ከበርካታ ወጣት ቆነጃጅት ሴቶች ጋር ተወዳድራ የሚስ ቦነስ አይረስን ማዕረግ ካሸነፈች በኋላ በማኅበራዊ ሚዲያ ላይ አነጋጋሪ ሆናለች።

ውድድሩን ማሸነፏን ተከትሎ በመድረክ ላይ ንግግር ስታደርግ ለሁሉም ሴቶች ውበት እድሜ እንደሌለው እና እንቅፋቶችን ማፍረስ እንደምንችል ማሳየት እፈልጋለሁ ብላለች።
👇
https://shorturl.at/pxBGX


አየር መንገዱ ወደ ካሜሩን ዱዋላ ከተማ የሚያደርገውን ሳምንታዊ በረራ ወደ 11 አሳደገ

ሚያዝያ 17/2016 (አዲስ ዋልታ) የኢትዮጵያ አየር መንገድ የካሜሩን የንግድና የኢኮኖሚ ማዕከል ወደ ሆነችው ዱዋላ ከተማ የሚያደርገውን ሳምንታዊ በረራ ወደ 11 ማሳደጉን ገለጸ።

በዚህም ከግንቦት 26/2016 ዓ.ም ጀምሮ በረራውን ወደ 11 ከፍ እንደሚያደርግ አስታውቋል።

አየር መንገዱ በአሁኑ ወቅት ወደ ከተማዋ 7 ጊዜ ሳምንታዊ በረራዎችን እያደረገ እንደሚገኝ ተገልጿል።


"የአፍሪካ ዋንጫን በ2029 ወይንም በ2031 ለማዘጋጀት እየሰራን ነው" የባሕልና ስፖርት ሚኒስትር ቀጄላ መርዳሳ - አሁን 👇

https://shorturl.at/hOT48




235 ሰዎችን የሚይዘው አሳንሰር (ሊፍት)
#ቴክኖ_ቅምሻ

በፊንላንድ ሊፍት ኩባንያ ኮን በ2022 በህንድ ሙምባይ በሚገኘው ጂዮ ወርልድ ሴንተር ህንፃ ውስጥ በዓለማችን የመጀመሪያ የሆነውን 235 ሰዎችን የሚይዘው አሳንሰር (ሊፍት) ገጥሞታል።

ይህ ትልቁ የመንገደኞች ሊፍት የስቲዲዮ አፓርታማ ያክላል የተባለ ሲሆን 16 ቶን የሚመዝንና በ9 የብረት ኬብሎች የተደገፈ ነው፡፡ አሳንሰሩ ሰዎችን ከማጓጓዝ በተጨማሪ ለሰርግና ለአርት ኤግዚብሽን ማሳያ እንዲሆን ተደርጎ የተሰራ ሲሆን 25.78 ስኩየር ሜትር ስፋት ያለውና ለተመልካች ውብ የሆነ እይታና የአትክልት ቦታ ያካተተ ነው።

አሳንሰሩ 18 ትላልቅ ፑሊዎች፣ 9 የብረት ኬብሎች እና በብረት ዓምዶች ላይ የተስተካከሉ ሀዲዶችን ባቀፈ አዲስ የፑሊ ጨረር ሲስተም ላይ የተሰራ ነው ተብሏል።

የዓለማችን ትልቁ የመንገደኞች አሳንሰር (ሊፍት) ልዩ ባለ አራት ፓነል የመስታወት በር፣ የመስታወት ግድግዳዎች ፓኖራሚክ እይታዎችን እና ክሪስታል-የተጣበበ ጣሪያን ያሳያል። በአምስት ፎቆች መካከል ብቻ የሚጓዝ ቢሆንም በሴኮንድ 1 ሜትር ፍጥነት በመጓዝ ሪከርድ ሰባሪው ሊፍትም ሆኗል።

ሊፍቱ ውስጥ ተጓዦች ሲደክማቸው አረፍ የሚሉበት 2 ምቹ ሶፋዎችም አሉት፡፡

የኮን ማኔጂንግ ዳይሬክተር ኢሚት ጎሳይን የዓለማችንን ትልቁን የህዝብ ማመላለሻ አሳንሰር (ሊፍት) ለደንበኞቻችን ችግር ፈች የሆነ ፕሮጀክት በመስራታችን ኩራት ይሰማናል ብለዋል፡፡
👇
https://shorturl.at/rT679


በወቅታዊ ሀገራዊ የደህንነትና ፀጥታ ጉዳዮች ዙሪያ በመምከር ከብሔራዊ የደኅንነት ምክር ቤት የተሰጠ መግለጫ

የተከበራችሁ የሀገራችን ሕዝቦች፣
ኢትዮጵያ በረጅም ዘመን የሀገረ መንግሥትነት ታሪኳ፣ የፖለቲካ ልዩነቶችን፣ አለመግባባቶችን እና ግጭቶችን በሰላማዊ መንገድ፣ በንግግር፣ በውይይት እና በሕጋዊ አግባብ የመፍታት ልምምድ የላትም። እንደ አለመታደል ሆኖ ፖለቲካችን የዜሮ ድምር ፖለቲካ ነው። በሀገራችን የተለመደው በጉልበት አሸንፎ ሥልጣን የያዘ ኃይል፣ በጉልበት ተሸንፎ ሥልጣን እስኪለቅ ድረስ ሁሉንም ጠቅልሎ የሚቆጣጠርበት እና የፈቀደውን የሚያደርግበት የፖለቲካ ባህል ነው።

የለውጡ መንግሥት ወደ ሥልጣን የመጣው በጉልበት አይደለም። ይሄም አዲስ የፖለቲካ ባህል ነው። ይሄን አዲስ የፖለቲካ ምእራፍ የሚያጸና ሌላ ሰላማዊ የፖለቲካ ባህል ደግሞ በዴሞክራሲያዊ ምርጫ የሕዝብ ይሁንታ አግኝቶ መንግሥት በመመሥረት አሳይቷል። ከዚህም በመሻገር ልዩ ልዩ የፖለቲካ ፓርቲዎች አመራሮችና አባላትን በመንግሥት ኃላፊነት በመመደብ፣ ኢትዮጵያ የጋራ ቤት መሆንዋን አስመስክሯል።

ሰላማዊ የፖለቲካ ሽግግር ብቻውን ግብ አይደለም። ሌሎች ግቦችን ለማሳካት መሣሪያ እንጂ። የኢትዮጵያ ችግር የአሁኑን አካሄድ በማስተካከል ብቻ አይፈታም። በታሪክ ውስጥ የወረስናቸውን ስብራቶች መጠገንም የግድ ይለናል። እነዚህን የታሪክ ስብራቶች ለመጠገን ሦስት ዓይነት መፍትሔዎች ተቀምጠዋል።
👇👇
https://www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate/posts/pfbid0of2Sg3MfVug4AugqUtVmeV4NE9fCrsoiscuKqwnHhjN6jzdaranZH7Dk7Y5cN4a2l


የመኖሪያ ቤት ተደርምሶ ባደረሰው አደጋ የ7 ሰዎች ሕይወት አለፈ

ሚያዝያ 16/2016 (አዲስ ዋልታ) በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ በግንባታ ላይ የሚገኝ የመኖሪያ ቤት ተደርምሶ በጀርባ በሚገኝ ሌላ መኖሪያ ቤት ላይ በማረፉ የ7 ሰዎች ሕይወት አለፈ፡፡

አደጋው የተከሰተው በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ወረዳ 12 ልዩ ስሙ ጠሮ መስጊድ ተብሎ በሚጠራ አካባቢ መሆኑን የክፍለ ከተማው ዋና ስራ አስፈፃሚ አይዳ አወል ለአዲስ ዋልታ ዲጂታል ሚዲያ ገልጸዋል።

በግንባታ ላይ የነበረው የግለሰብ መኖሪያ ቤት ተደርምሶ በጀርባ በሚገኝ ሌላ መኖሪያ ቤት ላይ በማረፉ በቤቱ ውስጥ ለነበሩ ሰባት ነዋሪዎች ሕይወት ማለፍ ምክንያት መሆኑን ተናግረዋል።

አደጋው ሌሊት ከ10፡30 በኋላ የተከሰተ መሆኑን የገለጹት ዋና ስራ አስፈፃሚዋ እስካሁን የሰባት ሰዎች ሕይወት ማለፉን ጠቁመዋል።

አደጋ ለደረሰባቸው የቤተሰብ አባላት መጽናናትን ተመኝተው ኅብረተሰቡ ላይ መሰል አደጋዎች እንዳይደርሱ በህንፃ ግንባታዎች ላይ ጥንቃቄ ሊደረግ እንደሚገባ አመልክተዋል፡፡

በአድማሱ አራጋው


የጨረታ ማስታወቂያ

የጉምሩክ ኮሚሽን ተሽከርካሪዎች፣ ጥሬ ዕቃዎች፣ ተንቀሳቃሽ እና የሚገጠሙ ፎርክ ሊፍቶች፣ የዳይፐር ማምረቻ ማሽኖች እና መለዋወጫዎች፣ የቢሮ መገልገያ ቁሳቁሶች እንዲሁም በሼድ ውስጥ የሚገኙ ሌሎች ዕቃዎችን በሙሉ ባሉበት ሁኔታ በጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል።

የጨረታ መነሻ ዋጋው 315 ሚልዮን 671 ሺሕ 341 ብር ከ14 ሣንቲም ነው።

ተጨማሪ መረጃ ሐዋሳ ጉምሩክ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት በስልክ ቁጥር 0462125396 በመደወል ማግኘት ይችላሉ፡፡


በእንግሊዝ ፕሪሚዬር ሊግ አርሰናል ከቼልሲ ዛሬ ምሽት ይጫወታሉ

ሚያዚያ 15/2016 (አዲስ ዋልታ) በእንግሊዝ ፕሪሚዬር ሊግ ዛሬ ምሽት 4 ሰዓት ላይ አርሰናል በኤምሬትስ ስታዲዬም ከቼልሲ ጋር ወሳን ጨዋታ ያካሂዳሉ።

አርሰናል በ33 ጨዋታዎች በሊጉ የደረጃ ሰንጠረዥ በ74 ነጥብ አንደኛ ደረጃ ላይ የተቀመጠ ሲሆን በተመሳሳይ 74 ነጥብ ሁለተኛ ደረጃ ላይ ከሚገኘነው ሊቨርፑል በጎል ክፍያ ነው የሚለያዩት።

ለአርሰናል የዛሬ ምሽቱ ጨዋታ የዋንጫ ፉክክሩን ለማጠናከር በጥንቃቄ እንደሚጫወት ሲጠበቅ በጥሩ መነቃቃት ላይ የሚገኘው ቸልሲ ዘንድሮ ከታላላቆቹ የሊጉ ቡድኖች ጋር ጠንክሮ በመታየቱ የምሽቱን ጨዋታ አጓጊ ያደርገዋል።

ቼልሲ 31 ጨዋታዎችን አድርጎ በ47 ነጥብ 9ኛ ደረጃ ላይ የተቀመጠ ሲሆን የዛሬ ምሽቱን ጨዋታ ካሸነፈ ደረጃውን ወደ 7ኛ ከፍ ሊያደርግ የሚችልበት እድል ያገኛል።


#ከተሞቻችን
አዲግራት

በ14ኛው ክፍለ ዘመን እንደተቆረቆረች የሚነገርላት ታሪካዊቷ የአዲግራት ከተማ ከመዲናችን አዲስ አበባ በስተሰሜን አቅጣጫ 1ሺሕ 38 ኪ.ሜ ርቀት ላይ ትገኛለች፡፡

የአመለሸጋ ሕዝብ መገኛ፣ የአብሮነት ማሳያና በእንግዳ አክባሪነቷ ተምሳሌት የሆነች ከተማ ናት፡፡

ከተማዋ ከባሕር ጠለል በላይ 2 ሺሕ 457 ሜትር ከፍታ ላይ የምትገኝ ሲሆን ደጋማ የአየር ፀባይ አላት፡፡

ለከተማዋ ስያሜ የሆነውና "አዲግራት" የሚለው ቃል ትግርኛ ሲሆን ትርጓሜውም "የእርሻ መሬት ሀገር" እንደ ማለት ነው።

በ6ኛው መቶ ክፍለ ዘመን እንደተገነባ የሚነገርለት "ደብረ ዳሞ" እና የ"ጉንዳ ጉንዶ" ገዳማት በአዲግራት አካባቢ የሚገኙ የቱሪስት መዳረሻዎች ናቸው፡፡

የከተማዋ ተወላጆች ከየአሉበት ተሰባስበው ከወላጆቻቸው ጋር የመስቀል እና የአረፋ በዓላትን በድምቀት የሚያከበሩባት ከተማ ነች።

ሙሉውን ለማንበብ ተከታዩን ማስፈንጠሪያ ይጫኑ👇👇
https://www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate/posts/pfbid0AJQXDKAqaHh6RecyrUZ85bL8CvqapPPVVEJrhjcTUR4XzYDDCKNa1SBB5HEkEGQgl


#አጀንዳ+
👉አሸባሪ መረጃዎች፣ ከፋፋይ ዜናዎች፣ አፍራሽ ፕሮፓጋንዳ በኢትዮጵያ እና ሌሎች ተያያዥ መረጃዎችን ይዳስሳል

ዛሬ ምሽት 3:00 ሰዓት ይጠብቁን!
https://www.youtube.com/watch?v=Brdybxke900


አትሌት ዘርፌ ወንድማገኝ ለአምስት ዓመታት ከአትሌቲክስ ውድድር ታገደች

ሚያዝያ 14/2016 (አዲስ ዋልታ) ኢትዮጵያዊቷ አትሌት ዘርፌ ወንድማገኝ የተከለከለ አበረታች መድኃኒት በመጠቀሟ ለአምስት ዓመታት ከአትሌቲክስ ውድድር ታገደች፡፡

አትሌቲክስ ኢንቴግሪቲ ዩኒት ይፋ ባደረገው መረጃ የ21 ዓመቷ የመካከለኛ ርቀት አትሌት ሁለት የተከለከሉ ንጥረ-ነገሮች መውሰዷን አምናለች ብሏል።

አትሌቷ ሦስት ጊዜ ምርመራ የተደረገላት ሲሆን በሁለቱ የተከለከለ አበረታች መድኃኒት መጠቀሟ ተረጋግጧል፡፡

የዓለም አትሌቲክስ አካል የሆነው አትሌቲክስ ኢንቴግሪቲ ዩኒት ባወጣው መግለጫ አትሌቷ ቴስቶስቴሮን የተባለውን እና ኢፒኦ የተሰኘውን አትሌቶች በደማቸው ውስጥ የበለጠ ኃይል እንዲያገኙ የሚያደርገውን ንጥረ ነገር መውሰዷን አምናለች ብሏል፡፡

ዋዳ የተሰኘው ዓለም አቀፉ የፀረ-አበረታች መድኃኒት ተቋም በ2023 ባወጣው ዝርዝር መሠረት አትሌቷ የወሰደችው ንጥረ-ነገር ሕግን የሚጥስ መሆኑ ተዘግቧል።

ከባለፈው ዓመት ኅዳር ወር ጀምሮ እገዳ ተጥሎባት ምርመራ ላይ የቆየች ሲሆን ዛሬ በይፋ መቀጣቷን አትሌቲክስ ኢንቴግሪቲ ዩኒት አስታውቋል፡፡

አትሌቷ ውሳኔውን በመቃወም ይግባኝ መጠየቅ እንደምትችልም በመግለጫው ላይ ተጠቁሟል፡፡

በሐብታሙ ገደቤ


ስለፕላስቲክ ብክለት መረጃዎች ምን ይላሉ?

#አዲስ_ዋልታ


60 ሺሕ ቻይናዊያንን ያፈናቀለው ከባድ ጎርፍ

ከሰሞኑ በተለያዩ ሀገራት የሚከሰቱ ኃይለኛ የጎርፍ አደጋዎች ሕይወት የሚቀጥፉ፣ ሃብትና ንብረት የሚያወድሙ በአጠቃላይ ከባድ ተጽዕኖ የሚያሳድሩ ሆነዋል። አውራ ጎዳናዎችና መኖሪያ ቤቶች በጎርፍ ተጥለቀለቁ የሚሉ ዜናዎች በተደጋጋሚ እየተሰሙ ነው። ይህን መሰል የጎርፍ አደጋ ዛሬ በቻይና ተከስቶ ዜጎችን ከቀያቸው አፈናቅሏል።

በቻይና ከፍተኛ የሕዝብ ብዛት በሚስተዋልበት የጓንግዶንግ የባህር ዳርቻ ግዛት ለቀናት የጣለውን ከባድ ዝናብ ተከትሎ በተከሰተው ጎርፍ ወደ 60 ሺሕ የሚጠጉ ዜጎች ከመኖሪያ ቤታቸው መፈናቀላቸው ተሰምቷል። 11 ሰዎች የጠፉ ሲሆን እስካሁን በሰው ሕይወት ላይ ጉዳት አለመድረሱ ተገልጿል።

በመንግስት ሚዲያዎች እና በበይነ መረብ ላይ የተሰራጩ ተንቀሳቃሽ ምስሎች በጎርፍ የተጥለቀለቀ ሰፊ መሬት ላይ የነፍስ አድን ሰራተኞች በጀልባዎች በጥልቅ እና ሰፊ ውሃ ላይ ሲንሳፈፉ ያሳያሉ።

ትላልቅ ወንዞች ሞልተው በዳርቻቸው ጎረፍ ይፈሳል። የሀገሪቱ የሚቲዎሮሎጂ ባለስልጣናት አደገኛውን ሁኔታ እና ከፍተኛውን የውሃ መጠን በቅርበት እየተከታተሉ መፍትሄ የሚሉትን ሁሉንም እየሞከሩ ናቸው ተብሏል።
ሙሉውን ለማንበብ ተከታዩን ማስፈንጠሪያ ይጫኑ👇👇
https://shorturl.at/bsDNX


ከአበባ የተሰራው የመጀመሪያው አልማዝ

ቻይና በዓለም የመጀመሪያ የሆነውን ከአበባ የተሰራ አልማዝ አበረከተች።

አልማዝ በተፈጥሮ ከሚገኙ እጅግ ውድ ማዕድናት መካከል አንዱ ነው፡፡ በተፈጥሮ ከሚገኙ ነገሮችም እጅግ ጠንካራው ነው፡፡ ይሁን እንጂ የቻይና ሳይንቲስቶች ፔኦኒ ከተሰኘ ቀይ አበባ ለመጀመሪያ ጊዜ በላብራቶሪ ውሰጥ ይህን በተፈጥሮ የሚገኝ ውድ ማዕድን መስራት መቻላቸውን ገልጸዋል፡፡

ይህ አልማዝ ሎያንግ ታይም ፕሮሚስ የተሰኘ በቻይና ሎያንግ ከተማ ውሰጥ የሚገኝ ድርጅት የሰራው ሲሆን አልማዙን ከአበባው በሚገኝ የካርቦን ንጥረነገሮች በመጠቀም እንደተሰራ ገልጸዋል፡፡

አልማዙ ከከተማው የፔኦኒ አባባ ማእከል በተገኙ አበቦች የተሰራ ሲሆን ድርጅቱ የተሰራውን 3 ካራት አልማዝ መልሶ ለአበባ ማእከሉ አበርክቷል፡፡

የአምራች ድርጅቱ ሥራ አስኪያጅ አልማዙ 41 ሺሕ ዶላር የሚጠጋ ዋጋ እንዳለው ጠቅሰው አልማዙን ለማምረት ባዮ ጄኒክ ካርቦን ኤክስትራክሽን የተሰኘ ከፍተኛ ሙቀትና ግፊት የሚጠቀም ቴክኖሎጂ እንደሚጠቀሙ ገልጸዋል፡፡

ይህ በቴክኖሎጂ በመታገዝ የሚሰራ አልማዝ በተፈጥሮ ከሚገኘው አልማዝ ጋር በአካልና በኬሚካል ስሪታቸው አንድ አይነት ሲሆኑ የሚለዩትም በዋጋቸውና ለመሰራት በሚፈጁበት ጊዜ ነው ተብሏል፡፡

ሰው ሰራሽ አልማዞቹ በወራት የሚፈጠሩ ሲሆን በተፈጥሮ የሚገኝ አልማዝ ግን ለመፈጠር በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዓመታትን ይፈጃሉ፡፡ በተጨማሪም በላብራቶሪ ውስጥ የሚሰሩት አልማዞች ዋጋቸው በተፈጥሮ ከሚገኙት አነስ ያለ ነው መባሉን ከብሪዚ ስክሮል ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡


ጀጎል የምስራቅ አፍሪካው አውራ ግንብ
#ሀገሬ

ሀገራችን ድንቅና ውብ የተፈጥሮና ሰው ሠራሽ መስህቦች እንዲሁም ታሪካዊ ቅርሶችና ባህላዊ እሴቶች ባለቤት ናት። እነዚህ የሚዳሰሱና የማይዳሰሱ ቅርሶች የውስጥና የውጭ ጎብኚዎችን ቀልብ በመግዛት ይታወቃሉ። ምርጥ የቱሪዝም መዳረሻ ከመሆን ባሻገርም የዓለም ቅርስ ሆነው የተመዘገቡ ብዙ ናቸው፡፡

ከእነዚህ የሀገራችን ውብ ቅርሶች በምሥራቁ የሀገራችን ክፍል የሚገኘው የጀጎል ግንብ አንዱ ሲሆን የግንባታው መሀንዲሶች በወቅቱ የነበሩ አባቶች ናቸው። የጀጎል ግንብ የሀረሪ ህዝብ የኪነ ህንፃ ችሎታውን የሚያስመሰክር የታሪክ እና የጥበብ ውጤትም ነው፡፡

የሀረር ከተማ መለያና የዓለም ቅርስ የሆነው የጀጎል ግንብ የተገነባው በ16ኛው ክፍለ ዘመን በአሚር ኑር ቢን ሙጃሂድ መሆኑን ታሪክ ያስረዳል።

ጀጎል በሀገር በቀል ዕውቅ የፈጠራ ባለቤቶች የተገነባ የሀገረሰብ ጥበብ ውጤት መሆኑ የሚታወቅ ሲሆን በዘመኑ አባቶች ያለምንም ቴክኖሎጂ እገዛ ነበር ግንቡን ያበጃጁት። ከፋብሪካ ውጤቶች ነፃ የሆነና በአካባቢያቸው የሚገኘውን ጥሬ ዕቃ በመጠቀም የገነቡት የዚህ ግንብ ቆይታው ደግሞ የአባቶችን የጥበብ ከፍታን ያሳየ ነው። በዘመኑ በምስራቅ አፍሪካ በግንብ የታጠረች የመጀመሪያዋ ድንቅ ከተማ ሀረር እንደሆነች መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡ የግንባታው ዓላማም ከተማዋን ከጠላት ለመከላከል እንደሆነ ይነገራል፡፡
👇👇
https://www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate/posts/pfbid02VCyxBNeQPPKMBqs55dzGPXpj5j7YSUapF4h1uHe9Hjcdh2yQMPZx7PMT4KiFvtH8l

Показано 20 последних публикаций.