AddisWalta - AW


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: Новости и СМИ


This is Walta Media and Communication Corporate’s official Telegram channel.
For more updates please visit https://shorturl.at/ehosX https://www.youtube.com/c/WaltaTV/featured

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
Новости и СМИ
Статистика
Фильтр публикаций


በ#ፍትሕ ዘርፍ ባለፉት ስድስት ዓመታት የተመዘገቡ ውጤቶች፡-

⚖️ዳኞች ሥራቸውን በነፃነት መስራት ችለዋል

⚖️ውዝፍ መዝገብ እንዲቀንስ ተደርጓል

⚖️ለእያንዳንዱ ጉዳይ የጊዜ ገደብ ተቀምጧል

⚖️የአንድ መስኮት አገልግሎት እንዲተዋወቅ ተደርጓል

⚖️የጉዳዮች መዘግየት ሙሉ በሙሉ ባይጠፋም ቀንሷል

⚖️ለጉዳዮች አጫጭር ቀጠሮ መስጠት ተጀምሯል

⚖️የዳኞችን ብቃት ከማሳደግ ጋር በተያያዘ በተለያዩ ርዕሶች ላይ ስልጠና መስጠት ተችሏል

⚖️የጉዳዮች ፍሰትን በተመለከተ የማስተግበሪያ ማኑዋል ወጥቷል፤ በህግ ማሻሻያው ሁለት አዋጆች ፀድቀው ወደ ስራ ገብተዋል

⚖️በብዙ ቢሊዮን የሚቆጠር የህዝብና የሀገር ሀብት የመዘበሩ አካላትን ለህግ የማቅረብ ስራዎች ተሠርተዋል

#የሪፎርም_ቀን


በቴክኖሎጂ ዘርፍ ባለፉት ስድስት ዓመታት የተመዘገቡ ውጤቶች፡-

💻የሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ፖሊሲ ፀድቆ ወደ ስራ ተገብቷል

💻የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ ተነድፎ በስራ ላይ ውሏል

💻የኢ-ትራንዛክሽን አዋጅ ወጥቶ በስራ ላይ ነው

💻የግል ዳታ ጥበቃ አዋጅ ለፓርላማ ቀርቦ ፀድቋል

💻የቴሌኮም ዘርፍን ሪፎርም በማድረጉ ተጨማሪ ኦፕሬተር (ሳፋሪኮም) ወደ ሴክተሩ እንዲገባ ተደርጓል

💻የዲጂታል መሠረተ ልማትን ለመጠበቅ እና በዲጂታል ኢኮኖሚ ላይ ለማጎልበት የሳይበር ደህንነትን ለማሻሻል ያለሙ የህግ ማዕቀፎች ወጥተው ስራ ላይ ውለዋል

#የሪፎርም_ቀን


ባለፉት ስድስት ዓመታት በትምህርት ዘርፍ የተመዘገቡ ውጤቶች፡-

🎓ዩኒቨርሲቲዎችን ከማንነትና ከአካባቢያዊነት በመነጠል የዕውቀትና የእውነት ማደሪያ ለማድረግ ተሰርቷል

🎓ተማሪዎችን፣ መምህራንን፣ የትምህርት ክፍሎችን፣ ኮሌጆችና ዩኒቨርሲቲዎችን በመመዘን የትምህርት ጥራትን ለማስጠበቅ የምዘና ስርዓት ተዘጋጅቶ ወደ ስራ ተገብቷል

🎓በትምህርት ግብዓት በተለይም የመማሪያ መፃሕፍትን ለሁሉም ለማዳረስ፤ የሀገራችንን የቋንቋ ፖሊሲ መሠረት አድርጎ ልጆች በአፍ መፍቻ ቋንቋቸው እንዲማሩ ለማስቻል ተሰርቷል

🎓የትምህርት ቤት ምገባ መርኃ ግብር የሚተገብሩ ሀገር በቀል መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች በአዲስ አበባና በሌሎች አካባቢዎች ተግባራዊ ተደርገዋል

🎓በከፍተኛ ትምህርት የፕሮግራሞች መዋቅር በስርዓተ ትምህርትና በፕሮግራሞች የጊዜ ርዝማኔ ላይ ለውጥ ተደርጓል

🎓በሁሉም የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚሰጡ የቅድመ ምረቃ ፕሮግራሞች ላይ የመውጫ ፈተና ለመተግበር የሚያስችል መመሪያ ተዘጋጅቶ ወደ ስራ ተገብቷል

🎓የከፍተኛ ትምህርት ተቋማዊ ነፃነትን ለማረጋገጥ የራስ ገዝ ዩኒቨርሲቲዎች ረቂቅ አዋጅ ፀድቋል

#የሪፎርም_ቀን


ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው በአዋሬ መንደር የተገነቡ 275 ቤቶችን ቁልፍ ለነዋሪዎቹ አስረከቡ

ጳጉሜን 2/2016 (አዲስ ዋልታ) ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው በአዋሬ መንደር የተገነቡ 275 ቤቶችን ቁልፍ ለነዋሪዎቹ አስረክበዋል::


ባለፉት ስድስት ዓመታት በኢኮኖሚ ዘርፍ በተደረገው የሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ የተመዘገቡ ውጤቶች፡-

• በአማካይ የሀገር ውስጥ ምርት ዕድገት 71 በመቶ ደርሷል
• ከ60 በላይ ዘርፎች ለውጭና ሀገር ውስጥ ኢንቨስትመንት ክፍት ሆነዋል
• የቴሌኮም ዘርፉ በከፊል ወደ ግል ይዞታ መዞሩን ተከትሎ የመንግሥት ገቢ 1 ቢሊዮን የአሜሪካን ዶላር ጨምሯል
• የባንኮች ቁጥር ከ18 ወደ 32 ደርሷል
• የባንክ ቅርንጫፎች ቁጥር ከእጥፍ በላይ ጨምሯል
• የባንኮች አጠቃላይ ሀብት 2 ትሪሊዮን ብር ደርሷል
• የመንግሥት ዕዳ ከጠቅላላ የሀገር ውስጥ ምርት ያለው ድርሻ ወደ 35 በመቶ ዝቅ እንደሚልና የገቢና ወጭ ንግድ ዋጋም ወደ 20 ቢሊዮን ዶላር እንደሚያድግ ትንበያ ተቀምጧል
• በ2015 በጀት ዓመት ከምርትና አገልግሎት ወጭ ንግድ ከ10 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ ተገኝቷል
• በ2015 የበጀት ዓመት ከሐዋላ አገልግሎት ከ6 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ ተገኝቷል
• በ2016 የበጀት ዓመት የ3 ነጥብ 8 ቢሊዮን ዶላር የውጭ ቀጥተኛ ኢንቨስትመንት ፍሰት ተመዝግቧል
• ስንዴን ጨምሮ በተኪ ምርቶች ከፍተኛ ለውጥ የተመዘገበ ሲሆን በ2015 የበጀት ዓመት 10 ወራት 2 ቢሊዮን ዶላር የሚያወጡ ምርቶችን በአገር ውስጥ ምርት መተካት ተችሏል
• የታክስ ምህዳሩን በማስፋትና ዘመናዊ የታክስ አሰባሰብ ሥርዓት በመተግበር በ2015 የበጀት ዓመት ከ529 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰብ ተችሏል

#የሪፎርም_ቀን


“ሪፎርም ኮርነር” የተሰኘ መጽሐፍ እና የቴሌቪዥን ዝግጅት ይፋ ተደረገ

ጳጉሜን 2/2016 (አዲስ ዋልታ) ባለፉት ስድስት ዓመታት በኢትዮጵያ የተከናወኑ ሪፎርሞችን የተመለከቱ ጉዳዮች የተዳሰሰበት “ሪፎርም ኮርነር” የተሰኘ መጽሐፍ እንዲሁም ሪፎርሙን የተመለከቱ ጉዳዮችን የሚዳስስ ሳምንታዊ የቴሌቪዥን ዝግጅት በዋልታ ሚዲያና ኮሙዩኒኬሽን ኮርፖሬት ዛሬ ይፋ ተደርጓል።

ለንባብ በበቃው መጽሐፍ በኢትዮጵያ በፍትሕ፣ በትምህርት፣ በኢኮኖሚ፣ በኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ እንዲሁም በሲቪል ሰርቪስ ዘርፎች የተገኙ ስኬቶች እና የተደረጉ ማሻሻያዎች ተዳሰዋል።

በተጨማሪም በዛሬው ዕለት “ሪፎርም ኮርነር” የተሰኘ ሳምንታዊ የቴሌቪዥን ዝግጅት በአዲስ ዋልታ ቴሌቪዥን ለተመልካቾች መቅርብ ይጀምራል።

የቴሌቪዥን ዝግጅቱ እና መጽሐፉ ለበርካታ ወራት ከፍተኛ ዝግጅት እና ጥናት በማድረግ የተሰራ ነው።

ዝግጅቱን ዋልታ ሚዲያና ኮሙዩኒኬሽን ኮርፖሬት ከገንዘብ ሚኒስቴር ጋር በመሆን አከናውኗል።


“አዋሬን ለሰው ልጅ ክብር ምቹ አድርጎ ወደ ህያውነት የመለወጥ ትልማችን እና ጥረታችን እውን ሆኗል።” - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)


ኢትዮጵያ በተግዳሮት ውስጥ በማለፍ ከፍተኛ ስኬት ማስመዝገብ ችላለች - አደም ፋራህ

ጳጉሜን 2/2016 (አዲስ ዋልታ) ኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት ባካሄደችው ዘርፈ ብዙ የሪፎርም ሥራዎች በከባድ ተግዳሮት ውስጥ በማለፍ ከፍተኛ ስኬት ማስመዝገብ ችላለች ሲሉ በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊና የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አደም ፋራህ ገለጹ።

ባለፉት ስድስት ዓመታት የተከናወኑ የሪፎርም ሥራዎችን በማስመልከት "ሪፎርም ለላቀ አገልግሎት" በሚል መሪ ቃል በሳይንስ ሙዚየም እየተከበረ ነው።

በመርኃ ግብሩ ላይ የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አደም ፋራህ ኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት ባካሄደችው ዘርፈ ብዙ የሪፎርም ሥራዎች በከባድ ተግዳሮት ውስጥ በማለፍ ከፍተኛ ስኬት ማስመዝገብ ችላለች ሲሉ ተናግረዋል።

ቀኑን አስመልክቶ በተዘጋጀው የፓናል ውይይት መድረክ ባለፉት ዓመታት በተለያዩ ዘርፎች በተካሄዱት የሪፎርም ሥራ መነሻዎች፣ ሂደቶች፣ የተገኙ ስኬቶች እንዲሁም ያጋጠሙ ተግዳሮቶች እና ቀጣይ አቅጣጫዎች ላይ ውይይት ይካሄዳል።

በውይይቱ ላይ የገንዘብ ሚኒስቴር፣ የትምህርት ሚኒስቴር፣ የፍትህ ሚኒስቴር፣ የኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር እንዲሁም የሲቪል ሰርቪስ ከሚሽን እየተሳተፉ ይገኛል።

በሔለን ታደስ


ሪፎርም ለላቀ አገልግሎት

#አዲስ_ዋልታ


"አብዮት በጎውን ከክፉው አጃምሎ ጠርጎብናል። ተሻጋሪ ተቋሞች ለመገንባት አላስቻለንም። ለዚህ ነው ሪፎርምን የመረጥነው። እየመዘንን፣ እያነጠርን፣ እየመረመርን የሚበጀንን እንወስዳለን፤ የማይበጀንን እንጥላለን።

በዚህ ዕሳቤ ታላላቅ ስኬቶችን እያስመዘገብን ነው። የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚ፣ የጸጥታ ዘርፍ፣ የሕግ፣ የግብርና፣ የትምህርት፣ የሲቪል ሰርቪስ ሪፎርሞችን እያሳካን በመጓዝ ላይ ነን።   በትብብር ከሠራን የማናሳካው ሪፎርም፤ የማይደረስበት ብልጽግና አይኖርም።"

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)


በሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውር ወንጀል የተሰማሩ የ49 ኤጀንሲዎች ባለቤቶች በቁጥጥር ስር ዋሉ

ጳጉሜን 1/2016 (አዲስ ዋልታ) በሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውር ወንጀል የተሰማሩ የ49 ኤጀንሲዎች ባለቤቶች በቁጥጥር ስር እንዲውሉ መደረጉን የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት አስታወቀ።

የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ለአዲስ ዋልታ በላከው መረጃ እንዳስታወቀው ሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውርን አስመልክቶ በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገራት ወንጀሉን በመፈፀም ላይ የሚገኙ አካላትንና የትስስር ሰንሰለታቸውን ለመለየት ሰፊ ጥናትና ክትትልና ሲያደርግ ቆይቷል፡፡

ጥናቱንና ክትትሉን መነሻ በማድረግ ከኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ጋር በመቀናጀት በተከናወነው ስምሪት በድርጊቱ ሲሳተፉ ተደርሶባቸው የተጠረጠሩ የ49 ኤጀንሲዎች ባለቤቶች በቁጥጥር ስር ውለዋል፡፡

እንደ አገልግሎት መሥሪያ ቤቱ መረጃ፤ መንግሥት ሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውርን ለማስቀረት ከተለያዩ ሀገራት ጋር ስምምነቶችን በመፈራረም ዜጎች ጥቅማቸው ሳይጓደልና ክብራቸው ተጠብቆ ወደ ውጭ ለሥራ እንዲሰማሩ የሚያስችል ሕጋዊ አሠራር ዘርግቷል፡፡

ይህን የሥራ ስምሪት የሚመራ የሚኒስቴር መሥሪያ ቤት ከማቋቋም በተጨማሪ ሕጋዊ ስርዓትን የሚያሳልጥ ቴክኖሎጂ ተግባራዊ በማድረግ ከ1ሺ ሁለት መቶ ለሚበልጡ ኤጀንሲዎች ፈቃድ ሰጥቷል፡፡
👇👇
https://www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate/posts/pfbid0ZJGNHbFP2zjEp5Cc7eWMdU7EV7LiyTaNaoww4ncJzj9rxHbRQRNTrj6NG5Xeq2b6l


"ሀገር የምትሻገረው ከትንሽ ተነስተው ወደ ትልቅ ኩባንያዎች በሚያድጉ ስራ ፈጣሪ ወጣቶች ነው። ዛሬ ወጣቶች በሰመር ካምፕ የሰሯቸውን የፈጠራ ቴክኖሎጂዎችን የተመለከትን ሲሆን፣ የፈጠራ ስረዎቹም ለኢትዮጵያ ብልጽግና መሰረት የሚጥሉ ናቸው።" - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)


በይፋዊ ጨዋታዎች የዓለማችን አራት ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪዎች

#አዲስ_ዋልታ
#እግር_ኳስ


የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ውጤት በመጪው ሰኞ ይፋ ይሆናል

ጳጉሜን 1/2016 (አዲስ ዋልታ) የ2016 የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ውጤት በመጪው ሰኞ ጳጉሜን 4/2016 ዓ.ም ይፋ እንደሚሆን የትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ።

በዘንድሮው የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና 684 ሺሕ 372 ተማሪዎች መውሰዳቸው ይታወሳል።

Показано 14 последних публикаций.