Фильтр публикаций


የPLC እና የአክሲዮን ድርጅት ልዩነት! አዋጭ የቢዝነስ ማህበራት አመሰራረት!

በኢትዮጵያ የቢዝነስ ህግ ኋላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር (PLC) እና የአክሲዮን ድርጅት በማቋቋም መካከል ያለውን ልዩነት እንመልከት!

ድርጅት በማህበራት ሂደት ለማቋቋም ለምታስቡ በሙሉ PLC በማድረግ እና ድርጅትን በአክሲዮን በመመስረት መካከል ያለውን አንድነት እና ልዩነት እንመልከት!

በግል ይሰራ የነበረ ቢዝነስ እንዴት ወደ PLC ወይም አክሲዮን ድርጅትነት መለወጥ እንደሚችል እንመልከት!https://youtu.be/Uo7Dz49quaU


#ለመረጃ፦ የአሜሪካ መንግስት ከ6 ሳምንት ግምገማ በኋላ 5,200 የUSAID ኮንትራቶች ሰርዟል! ይህም ማለት የUSAID 83% ፕሮማራሞቹ ተሰርዘዋል።

"ቀሪው 18% ማለትም 1,000 የድርጅቱ ፕሮግራሞች በስቴት ዲፓርትመንቱ በአግባቡ እየተመሩ ይቀጥላሉ" ሲሊ የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ አስታውቀዋል።


የኢትዮጵያ ብር ጉልበት የሚያገኘው መቼ ነው? ምን ያህል ዶላር ቢከማች ብር የመግዛት አቅሙ ያድጋል?

የኢትዮጵያ ብር የመግዛት አቅም በፍጥነት እየተዳከመ ነው!

በገበያው ምክንያት በዋናነት ከሃምሌ 2016 ጀምሮ ብር መዳከም በያዘበት ፍጥነት ከቀጠለ ጠቅላላ ኢኮኖሚው አደጋ ውስጥ መሆኑ ይቀጥላል!

የብር የመግዛት አቅም እንዲያድግ የሚጠበቅ የዶላር ክምችት መጠን እና የሚወስድበት ጊዜ ከምንገምተው ውጪ ነው!

የሚከተለውን ትንታኔ እንመልከት....https://youtu.be/M0ngKvGpxaI


#ለመረጃ፦ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ ባካሄደው የዶላር ጨረታ በጨረታው ተሳታፊ ከነበሩ 27 ባንኮች ውስጥ ዶላር ያገኙት #12_ባንኮች ብቻ ናቸው፡፡ እነዚህ 12 ባንኮች ለአንድ ዶላር ከ130 እስከ 141 ብር ዋጋ ሰጥተዋል።

ምንጭ፦ ሪፖርተር ጋዜጣ!


ባንኮች ካሽ የሚገዙበት ዋጋ #ውድ በመሆኑ #በጣም_ውድ በሆነ ዋጋ እየሸጡት ነው!

የብድር ወለድ ከፍተኛ መሆን እዳው የተበዳሪ ነው!

የባንኮች የስራ ማስኬጃ ወጪ መጨመሩ ከቀጠለ የወለድ መጠን መጨመሩ ይቀጥላል!

ብሄራዊ ባንክ የካሽ እጥረትን እንዴት ሊፈታ ይችላል?

የቁጠባ ወለድ መጠንን መጨመሪያ ትክክለኛ ጊዜ መቼ ነው?

በዝርዝር እንመልከታቸው....https://youtu.be/_H_uBCHgVBE


#ለመረጃ፦ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የብድር ወለድ መጠኖች ላይ ጭማሪ ተደረገ።

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከየካቲት 28 ቀን 2017 ዓ.ም. ጀምሮ ተግባራዊ የሚደረግ በተለያዩ የብድር ዓይነቶች ላይ ጭማሪ ማድረጉን አስታዉቋል።

ይህ ጭማሪ የመጣው መንግስት የፋይናንስ ዘርፉን ተወዳዳሪ ለማድረግ እያደረገ ያለው ጥረት አካል እንደሆነ ባንኩ ገልጿል።

በተደረገው ማስተካከያ መሰረት፦

የግብርና ብድሮች እስከ 15.5%፣

የንግድ ብድሮች እስከ 18%፣

የወጪ ንግድ ብድሮች እስከ 14%፣

የግል ብድሮች ደግሞ እስከ 15% ጭማሪ አሳይተዋል።

ይሁን እንጂ ለኮንዶሚኒየም መኖሪያ ቤቶች ብድሮች የወለድ ምጣኔ በ12 በመቶ እንደነበረው ይቀጥላል ተብሏል።

የውጭ ምንዛሬ የሚያቀርቡ ድርጅቶች ሰራተኞች የግል ብድሮች በስምምነቱ ውል ላይ በመመስረት ከ11 በመቶ እስከ 13 በመቶ የሚደርስ ሲሆን፣ ለየት ያለ ከፍተኛ ዋጋ ላላቸው ደንበኞች ሰራተኞች የግል ብድሮች በ12 በመቶ እንደነበረው እንደሚቀጥልም ታውቋል።

ምንጭ :- ካፒታል ጋዜጣ


ከኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ 4 ወሳኝ ወቅታዊ መረጃዎችን እንጠይቃለን!

ባንኩ ተገማች አለመሆኑ ለገበያው አደጋም አለው! https://youtu.be/7pvPOdSw5V4


የራሽያ ኢኮኖሚ 28,000 ማዕቀብ ተቋቁሞ እንዴት አደገ?

ኢኮኖሚው ለ3 ዓመት ጦርነት ውስጥ ሆኖ እጥፍ የGDP እና የፖለቲካ አጋርነት እድገት አስመዝግቧል!

የራሽያ ኢኮኖሚ ( ፑቲን) በጦርነት እና በማዕቀብ ውስጥ ሆኖ ኢኮኖሚን የማሳደግ ምሳሌ ሆነዋል!

ራሽያ ላለፉት 3 ዓመታት 28,000 ማዕቀብ ቢጣልባትም ኢኮኖሚዋ ማዕቀብ ከጣሉባት ሃገራት የተሻለ እድገት ማስመዝገቡን IMF እየመሰከረ ነው!

ጠለቅ አድርገን እንመልከተው.....https://youtu.be/wkH0Ln2QgVE


የኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ 27 ባንኮች በተሳተፉበት ጨረታ አንድ የአሜሪካ ዶላርን በ136 ብር ቢሸጥላቸውም ንግድ ባንኮቹ ከ3 ቀን በኋላ አብዛኞቹ የመሸጫ ዋጋ ለውጥ አላደረጉም!

የ10 ባንኮችን የተከታታይ 3 ቀናት የዶላር የመሸጫ ዋጋ ስንመለከት ያደረጉት ለውጥ የሚጠበቅ አይደለም!

ባንኮች ዶላር ከገዙበት በታች እየሸጡ ያሉበት ድራማ መነሻው ምንድን ነው?

ከጨረታው በኋላ እድል የተከፈተላቸው ባንኮች....

የኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ ዶላር የሸጠው ገበያው ውስጥ ወርቅ ለመግዛት የበተነውን ብር ለመሰብሰብ ነው ወይስ ለወርቅ ሸመታ ብር አጥሮት ብር ለማግኘት?

በዝርዝር እንመልከተው.....https://youtu.be/LDONqlkHZMs


ብሄራዊ ባንክ ገበያውን አረጋጋለሁ ብሎ ብርን ለምን ከ8-10 ብር ድረስ ለማዳከም ወሰነ?

ብሔራዊ ባንክ በዛሬው የዶላር ጨረታ አንድ የአሜሪካ ዶላር በአማካይ 135.61 ብር ዋጋ መሸጡን አስታወቋል!

ከዛሬው የመደበኛ ባንኮች የምንዛሬ ተመን አንፃር ብር ከ8-10 ብር ተዳክሟል!

የዚህ ጨረታ ዋጋ መጋነን ምክንያት ምንድን ነው?

የብር መዳከም ከነገ ጀምሮ በገበያው ላይ የሚፈጥረው ተፅዕኖ ምን ሊሆን ይችላል?

ብሄራዊ ባንክ የምንዛሬው ዋጋው መጋነኑን ከተመለከተ በኋላ ጨረታውን ለምን አልሰረዘም?

በፍፁም የጨረታው ዋጋ ብርን በጣም ያዳክማል ብዬ አላሰብኩም ነበር! በዝርዝር እንመልከተው....https://youtu.be/Q0LmEXlEMdU


#ለመረጃ፡ ብሔራዊ ባንክ በዛሬው የዶላር ጨረታ አንድ የአሜሪካ ዶላር በአማካይ 135.61 ብር ዋጋ መሸጡን አስታወቀ።

ጥያቄው ንግድ ባንኮቹ ለውጪ ምንዛሬ ፈላጊው በስንት ሊሸጡ ነው?


የኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ የ60 ሚሊየን ዶላር ጨረታ አወጣ! የዶላር ጨረታው የዶላር ዋጋን ይወስናል?

የመጀመሪያው የዶላር ጨረታ ከኢኮኖሚ ለውጡ 10 ቀን በኋላ (ነሃሴ 1/2016) ነበር አንድ ዶላር 107.9 ብር ዋጋ ወጥቶለት የነበረው!

ከ6 ወር በኋላ 60 ሚሊየን ዶላር ለጨረታ ቀርቧል! በገበያው ምን አይነት ለውጥ ሊያመጣ ይችላል?

የመጀመሪያው ጨረታ የሚገመት ውጤት አልነበረውም!

ከአሁኑ ጨረታ የውጪ ምንዛሬ ገበያው ለውጥ ሊኖረው ይችላል...https://youtu.be/FUqXEb_oM2c


#ለመረጃ፦ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ልዩ የውጭ ምንዛሪ ጨረታ ነገ የካቲት 18 ቀን 2017 ዓ.ም እንደሚያካሂድ አስታውቋል፡፡

ለጨረታ የሚቀርበው የውጭ ምንዛሪ መጠን 60 ሚሊየን የአሜሪካን ዶላር ሲሆን ጨረታው ለሁሉም ባንኮች ክፍት እንደሚሆን ታውቋል።


የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ አዲስ ህመም እየገጠመው ነው!

ኢኮኖሚው የውጪ ምንዛሬ ቢያከማችም! መልሶ የሚሸጥበት የኢትዮጵያ ብር አቅርቦት እጥረት ገጥሞታል!

ባንኮች የጥሬ ብር አከማችተዋል ብለው ለሚያስቡት ተቋም እና ግለሰብ የጊዜ ገደብ ቁጠባ ከ20 ከመቶ በላይ ወለድ እንደሚያስቡ እየተደራደሩ ነው!

በጊዜ ገደብ ገንዘብ መቆጠብ ያለውን እድል እና ስጋት እንመልከት....

በዝርዝር አዲሱን ህመም እንፈትሽ....https://youtu.be/y6Ug5H6zk2k


አሜሪካ ከተባበሩት መንግስታት ድርጅት (UN) ልትወጣ ስለማሰቧ እየገለፀች ነው!

ምክንያታቸው UN ባለ ትልቅ በጀት አዋጪዋን ሀገር አሜሪካንን ማስቀደም አልቻለም ነው!

አሜሪካ 28% (በ2022 ብቻ 18 ቢሊየን ዶላር ከፍላለች)፤ ቻይና 15%፤ ጃፓን (8.5%)፤ ጀርመን እና እንግሊዝ በተከታታይ ከፍተኛ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በጀት ድርሻ የያዙ ናቸው።

የድርጅቱ አባል ሆነው የሚጠበቅባቸውን የበጀት መዋጮ የማያደርጉ ሀገራት ጥቂት አይደሉም! ለምሳሌ ኢራን፤ ባርባዶስ፤ ኮሞሮስ፤ ኮንጎ፤ ጊኒ፤ ፓፓዋ ኒው ጊኒ፤ ቬንዙዌላ፤ ሱዳን እና ሳዎቶሜ ናቸው።

ኢትዮጵያ በ2022 (289 ሺ ዶላር)፤ በ2023 (292ሺ ዶላር)፤ በ2024 (315 ሺ ዶላር)፤ 2025 (340ሺ ዶላር) መዋጮ አድርጋለች!

የአሜሪካንን መውጣት እንደ አንድ ሃገር መውጣት ለመመልከት ከባድ ነው!

መግለጫውን ማንበብ ለምትፈልጉ https://www.whitehouse.gov/presidential-actions/2025/02/withdrawing-the-united-states-from-and-ending-funding-to-certain-united-nations-organizations-and-reviewing-united-states-support-to-all-international-organizations/


ዩክሬን ለጦርነት የተሰጣትን 500 ቢሊየን ዶላር ድጋፍ በተፈጥሮ ሃብት መክፈል አለባት! የማታሸንፉትን ጦርነት ማን ጀምሩ አላችሁ (ትራምፕ!) በራሽያ እና በዩክሬን መካከል የተጀመረው ጦርነት 3 ዓመት ሞላው!

ጦርነቱ እንዲያበቃ አሜሪካ እና ራሽያ ውይይት ቢጀምሩም ዋናዋ የሚመለከታት ሀገር ዩክሬን ለውይይቱ አልተጋበዘችም!

ዩክሬን ለጦርነት የተሰጣትን 500 ቢሊየን ዶላር ድጋፍ በተፈጥሮ ሃብት መክፈል አለባት! የማታሸንፉትን ጦርነት ማን ጀምሩ አላችሁ (ትራምፕ!) እየተባለ ነው!

የሁለቱን ሀገራት ኢኮኖሚ ከጦርነቱ 3 ዓመት በፊት እና ከጦርነቱ ጀምሮ ላለፊት 3 ዓመታት ከፋፍለን እንመልከተው....

ዩክሬን ለውድመት የዳረጋትን የ500 ቢሊየን ዶላር ድጋፍ እንዴት አድርጋ መክፈል እንደምትችል እንመልከት....https://youtu.be/cyR3sOAkZxM


#መልካም_ዜና: አሊባባ ከሚቀጥለው ሳምንት ጀምሮ #በኢትዮጵያ_ብር ክፍያ መቀበል እንደሚጀምር አስታወቀ!

አለም አቀፍ የኤሌክትሮኒክስ ግብይት ተቋም የሆነው አሊ ባባ እንደገለፀው ከሚቀጥለው ሳምንት ጀምሮ #በአሊ_ኤክስፕረስ የበርካታ አገራትን ገንዘብ ጥቅም ላይ ያውላል፡፡

ከእነዚህ አገራት መካከል ኢትዮጵያ፣ ናይጄሪያ፤ ግብፅ፣ ኬንያ እና ደቡብ አፍሪካ ይገኙበታል፡፡ የክፍያ መፈፀሚያ ገንዘቦችን ማስፋፋት ያስፈለገው ለአፍሪካ ተጠቃሚዎች በስፋት ተደራሽ ለመሆን በማሰብ እንደሆነ የጠቀሰው አሊ ባባ በተጨማሪም በአለም አቀፍ የክሬዲት ካርዶችና #የውጭ_ምንዛሬ ላይ ያለውን ጥገኝነት ለማስቀረት እንደሆነ አስረድቷል፡፡

የአፍሪካ አገራትን ገንዘብ በግብይቱ ውስጥ ጥቅም ላይ ማዋሉ በአለም አቀፍ የክፍያ ስርአት የተነሳ ለአፍሪካዊያን ትልቅ ማነቆ የሆነውን ችግር ለመቅረፍ ማቀዱንም አስታውቋል፡፡ በዚህም አዳዲስ የአገልግሎቱ ተጠቃሚዎችን እንደሚያገኝ ተስፋ ሰንቋል፡፡

ለዚህ እንዲረዳው በተጠቀሱት አገራት ከሚገኙ የዲጂታል ክፍያ አገልግሎት ሰጪዎች ጋር ጥምረት መፍጠሩን የገለፀው አሊ ባባ ከሚቀጥለው ሳምንት ማለትም #የካቲት_17 ጀምሮ ብርን ጨምሮ የተለያዩ ገንዘቦችን በግብይት ስርአቱ ውስጥ እንደሚያካትት አስታውቋል፡፡

#ለምሳሌ፦ አሊባባ ከቴሌ ብር ጋር ለመስራት ቢስማማ ከአሊ ኤክስፕረስ ላይ ኦንላይን/Online እቃ ለመግዛት ቴሌ ብር ተጠቅሞ መክፈል ይቻላል ማለት ነው!


የንግድ ጦርነት (Trade War)!

በዓለም ላይ ላለፉት 150 ዓመታት የንግድ ጦርነት ልምምዶች አሉ!

በንግድ ጦርነት ደጋፊዎች እና ተቺዎች መካከል ክርክር አለ!

የንግድ ጦርነት ምንነት፤ በዓለም ላይ የነበሩ ጦርነቶች፤ ጦርነት ውስጥ ያሉ እድሎች እና አደጋዎችን በምሳሌ እንመልከት.....https://youtu.be/ZcnRGR9oqpY


#ምን_ማለት_ነው?

"ኢትዮጵያ ለውጭ ባንኮች ፈቃድ የምትሰጠው #ለወዳጅ_አገራት መሆኑን የብሄራዊ ባንክ ገዥ ተናገሩ....

ጥሩ ስም ያላቸው አለም አቀፍ ባንኮች በኢትዮጵያ ውስጥ መሰማራታቸው ጠቃሚ ቢሆንም ፈቃድ ለማግኘት ባንኮቹ የሚገኙበት #አገር ከግምት ውስጥ እንደሚገባ....

የውጭ ባንኮቹ መነሻ አገራት ከኢትዮጵያ ጋር መልካም ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ያላቸውና ከኢትዮጵያ ጋር ለመተባበር ፈቃደኛ መሆን ይገባቸዋል" ብለዋል።

የፖለቲካ ዓለሙ ዘላቂ ወዳጅም ጠላትም በማያድልበት ምዕዳር ውስጥ የንግድ ግንኙነትን በሚገፋ የፖለቲካ መለኪያ ለመምራት መሞከር ደካማ ምክንያታዊነት ያለው ነው!

አቶ ማሞ ምህረቱ ከመንግስታዊው ዘመን ኢኮኖሚ መጽሔት ጋር ካደረጉት ቃለ ምልልስ!


📍 ፒያሳ አድዋ ሙዚየም ፊትለፊት
የንግድ ሱቆች በ 900 ሺ ብር ቅድመ ክፍያ ጀምሮ እንዲሁም ፒያሳ ሊሴ ገ/ማሪያም ት/ቤት አጠገብ የመኖርያ አፓርትመንት በምዝገባ ላይ እንገኛለን።

🎖ለልማት ተነሺዎች አና ለመርካቶ ነጋዴዎች።

🎖መረከቢያ ጊዜ 1 አመት ከ 6ወር

🎖በዶላር ሳይሆን በኢትዮጵያ ብር ይስተናገዳሉ !!!

🎖 የሱቆቹ ስፋታቸው ከ10--- 30ካሬ

📞0974981373

❗️ፒያሳ ሊሴ ገ/ማሪያም ት/ቤት አጠገብ
👉30%ሲከፍሉ 25% ቅናሽ ያገኛሉ
በ18 ዙር ምቹ አከፋፈል 10% ቅድመ ክፍያ  የቤት ባለቤት ይሁኑ።30%ሲከፍሉ 25% ቅናሽ ያገኛሉ
  ስቲዲዮ ,,,
    ♦️46 ካሬ
    ♦️48 ካሬ
ባለ1 መኝታ:
        ♦️64ካሬ
        ♦️66ካሬ
        ♦️71ካሬ
        ♦️75 ካሬዎች
ባለ2 መኝታ:
        ♦️ 71,ካሬ
         ♦️75,ካሬ
         ♦️78,ካሬ
         ♦️91, ካሬ
         ♦️92 እና 99 ካሬ
ባለ3 መኝታ:130 እና 142 ካሬ
NB:100% ለከፈለ 25% Discount.
Nb:ምንም አይነት ዶላር  ጭማሪ አያሳስብዎትም
📣📣📣📣📣
0974981373

Показано 20 последних публикаций.