🎙Zena Adis Ethiopia🎙


Гео и язык канала: Эфиопия, Английский
Категория: Новости и СМИ


ይህ ዜና አዲስ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።
#ኢትዮጵያ_ትቅደም!!

Связанные каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Английский
Категория
Новости и СМИ
Статистика
Фильтр публикаций


☄️በትግራይ ክልል በህወሓት አመራሮች መካከል ተፈጥሮ በነበረው ግጭት ምክንያት አሁንም  ወደ ክልሉ ነዳጅ እየገባ እንዳልሆነ ተገለፀ ።

ከጣቢያችን ጋር ቆይታ ያደረጉት የትግራይ ክልል ንግድና ኤክስፖርት ኤጀንሲ የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር አቶ ተኸልሽ ገ/ህይወት  የነዳጅ ዕጥረት ችግር በክልሉ ካጋጠመ አምስት ወር መሆኑን ገልፀዋል።

ከጦርነቱ በፊት ይገባ የነበረው ነዳጅ መጠን በቀን ከ8 እስከ 16 ቦቴ እንደነበር ገልጸው፤ አሁን ላይ ግን በቀን ከ2 እስከ 3 ቦቴ ብቻ እየገባ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

በዚህም ምክንያት በአሁን ሰዓት በትግራይ ክልል ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ እንቅስቃሴ ሰፊ ችግር እየገጠመዉ እንደሚገኝ አንስተዋል።

የነዳጅ ችግር እንዲፈታ አንድ ዳይሬክተር ወደ አዲስ አበባ በመላክ ከሶስት ሳምንት በላይ  ንግግር ቢደረግም የሚመለከተዉ አካል ምንም መፍትሄ እንዳልሰጣቸዉ ተናግረዋል።

የተወሰነ ነዳጅ  ቢመጣም ለሚያስፈልጋቸው ለጤና ተቋማት እየሰጡ መሆኑን ገልፀው፤ አንዳንድ ድርጅቶች በነዳጅ እጥረት ምክንያት መስራት አለመቻላቸውንም ገልፀዋል።


@zena_Adis_Ethiopia


ነገ  ብሔራዊ ባንክ የ70 ሚሊዮን ዶላር የውጭ ምንዛሬ ጨረታ እንደሚካሄድ ገለፀ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ቀጣዩን በየሁለት ሳምንቱ የሚካሄደውን የውጭ ምንዛሬ ጨረታ ነገ ሐሙስ ሚያዝያ 9 ቀን 2017 ዓ.ም.  እንደሚካሄድ ዛሬ አስታውቋል።

በዚህ ጨረታ የሚቀርበው ጠቅላላ የውጭ ምንዛሬ መጠን 70 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር መሆኑን ባንኩ አሳውቋል። ፍላጎት ያላቸው ባንኮች በተሰጠው መመሪያ መሰረት በጨረታው ላይ እንዲሳተፉ ጥሪ ቀርቧል።

@Zena_Adis_Ethiopia


አሜሪካ ወደ 30 የሚጠጉ በዓለም ዙሪያ የሚገኙ ኤምባሲዎቿንና ቆንስላዎቿን ልትዘጋ መሆኑ ተገለፀ፡፡

የዶናልድ ትራምፕ አስተዳደር፤ ኤምባሲዎችን እና ቆንስላ ፅህፈት ቤቶችን ለመዝጋት ማቀዱን ሲኤንኤን የሀገሪቱን የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት ሰነድ ጠቅሶ አስነብቧል፡፡

ሰነዱ 10 ኤምባሲዎችን እና 17 ቆንስላዎች እንዲዘጉ የሚመክር ሲሆን አብዛኛዎቹ በአውሮፓ እና በአፍሪካ ውስጥ ሲሆኑ የተቀሩት በእስያ እና በካሪቢያን የሚገኙ መሆናቸው ተጠቁሟል፡፡

ሰነዱ በኢራቅ እና በሞቃዲሾ ሶማሊያ የዲፕሎማቲክ አባላትን መጠን የመቀነስ ሐሳብም ማቅረቡም ተነግሯል፡፡ የአሜሪካ መንግሥት ለውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤቱ ከሚያወጣው ገንዘብ ወደ 30 ቢሊዮን ዶላር የሚጠጋውን ለመቀነስ ማቀዱም ተሰምቷል፡፡

ዶናልድ ትራምፕ ዳግም ወደ ስልጣን ከመጡ ወዲህ ከሀገሪቱ ፍላጎት ጋር አይጣጣሙም ያሏቸውን ተቋማት በመዝጋት እና እርዳታዎችን በማቋረጥ መሆናቸው ይታወቃል፡፡ ዘገባው የሲኤንኤን ነው፡፡

@Zena_Adis_Ethiopia


የአሜሪካው ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ ዛሬ የ 245% አዲስ የታክስ ታሪፍ  ቻይና ላይ ጥሏል።

@Zena_Adis_Ethiopia


❗️ ትራምፕ የአሜሪካን ኤምባሲዎች በሙሉ ለመዝጋት አቅደዋል - CNN

በፈረንሳይ፣ ጀርመን፣ እንግሊዝ፣ ደቡብ ኮሪያ ውስጥ ጨምሮ ወደ 30 የሚጠጉ ኤምባሲዎች እና ቆንስላዎች ሊዘጉ ይችላሉ።

@Zena_Adis_Ethiopia


"ፑቲን ሰላም ፈላጊ ናቸው" አሜሪካ
።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ባለፈው ሳምንት ከሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ጋር የተገናኙት የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ መልዕክተኛ ስትቭ ዊትኮፍ  ፑቲን ዘላቂ ሰላም ይፈልጋሉ ሲሉ ተናገሩ፡፡

ህጋዊ ማዕቀፍን በተከተለ መልኩ የዩክሬን ጦርነት እስከወዲያኛው እንዲያበቃ እና  ዘላቂ ሰላም እንዲፈጠር ፑቲን  መግለጻቸውንም ተናግረዋል፡፡   

ለአምስት ሰዓት ያህል በሴነት ፒተርስ በርግ ከፑቲን ጋር ቆይታ አድርገው የነበሩት ልዩ መልዕክተኛው የዩክሬንን ጦርነት ለማቆም ወሳኝ ደረጃ ላይ መድረሳቸውን ለመገናኛ ብዙሀን አብራርተዋል ፡፡

መልዕክተኛው ስትቭ ዊትኮፍ ፑቲን ሰላምን እንደሚመርጡ እና ከተኩስ አቁም ስምምነት የተሻገረ እንዲሆን  ይፈልጋሉም ብለዋል ፡፡ 

አር ቲ ኒውስ፣ አናዶሉ፣ ስካይ ኒውስ እና ዘ ሞስኮ ታይምስ ዘግበውታል፡፡ 

#ዜና_አዲስ_ኢትዮጵያ

@Zena_Adis_Ethiopia


መንገድ ላይ ሽንት በመሽናት ደንብ የተላለፉ ግለሰቦችን አንድ መቶ ሺህ ብር መቅጣቱን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን አስታወቀ፡፡

በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ በመርካቶ እና በመሳለሚያ አካባቢ በመንገድ ላይ ሽንት በመሽናት አካባቢ በማቆሸሽ ደንብ ቁጥር  167/2016 የተላለፉ 50 ግለሰቦች እያንዳንዳቸው  2000 ብር በድምሩ 100,000 ብር የገንዘብ ቅጣት  በመቅጣት  አስተዳደራዊ እርምጃ መውሰዱን ባለስልጣኑ አሳውቋል፡፡

የከተማ አስተዳደሩ አዲስ አበባን ውብና ፅዱ ለማድረግ ቀንና ማታ እየሰራ ባለበት ወቅት አንዳንድ ሀላፊነት የጎደላቸው ግለሰቦች የተማውን ፅዳት ሲያበላሹ ህብረተሰቡ አካባቢውን ሊጠብቅ እንደሚገባ ተገልጿል።

ባለስልጣኑ በደንብ ቁጥር 167/2016 ላይ ለህብረተሰቡ በተለያዩ አግባቦች ሰፊ የግንዛቤ ስራ መስራቱን የገለጸ ሲሆን፣ ደንብ በሚተላለፉ ግለሰቦች ላይ የሚወስደውን እርምጃ አጠናክሮ  አንደሚቀጥል አስታውቋል።
መረጃው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።(አራዳ ኤፍ ኤም)

#ዜና_አዲስ_ኢትዮጲያ

@Zena_Adis_Ethiopia


የኢትዮጵያ ታምርት  የ10 ኪ.ሜ የጎዳና ላይ ሩጫ  ሊካሄድ መሆኑ ተገለጸ

የኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖ 2017 አንዱ ማስፈጸሚያ የሆነው አለም አቀፍ አትሌቶች እና የተለያዩ ክለቦች የሚሳተፉበት የ10 ኪ.ሜ የጎዳና ላይ ሩጫ ሚያዚያ 19/2017 ዓ.ም እንደሚካሄድ ተገልጿል ።

ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር እንዳስታወቀው፤የኢትዮጵያ ታምርት 10ኪ.ሜ የጎዳና ላይ ሩጫ ዋና ዓላማ  የአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፉን ችግሮች ለመፍታት እና ለማሳደግ የተጀመረው የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄን ማስተዋወቅ መሆኑ ተነግሯል።

እንዲሁም ገቢ ምርትን በመተካት የተሰማሩ የሀገር ውስጥ አምራች ኢንዱስትሪዎችን የስፖርት አልባሳት ማስተዋወቅ እና የማምረት አቅማቸውን ማሳየት አንደሆነም ተገልጿል።

የሩጫው መነሻ መስቀል አደባባይ  ከ12፡30 ጀምሮ መሆኑ የተገለጸ ሲሆን፤ዉድድሩ ላይ ከ34 ክለቦች የተወጣጡ ከ 5መቶ65 በላይ አትሌቶች እና 80 ወንድ እና 35 ሴት የግል ተወዳዳሪ አትሌቶች ይሳተፋሉ ተብሏል።

ከክልል፣ ከከተማ አስተዳደር እና በግል የሚወዳደሩ አትሌቶች እንደሚገኙበትም ተገልጿል።

ውድድሩን ለየት የሚያደርገው አንዱ ወደ ውጭ ሄደው መወዳደር ላልቻሉ አትሌቶች በሀገር ውስጥ እድል መፍጠሩ መሆኑ ተጠቅሷል።

ለውድድሩ አሸናፊዎች 1ኛ ለሚወጡ 300ሺ ብር ፣2ኛ ለሚወጡ 200ሺ ብር እና  3ኛ ለሚወጡ ደግሞ የ100ሺ ብር ሽልማት አዘጋጅቷል ተብሏል።


#ዜና_አዲስ_ኢትዮጲያ
@Zena_Adis_Ethiopia


ቻይና የአሜሪካ ብሔራዊ ደህንነት ኤጀንሲ የበይነ መረብ ጥቃት ፈፅሞብኛል ስትል ከሰሰች

የቻይና መንግስት ሚድያ በድርጊቱ ላይ ተሳታፊ ናቸው ያላቸውን ሶስት የአሜሪካ ብሄራዊ ደህንነት ቢሮ ሰራተኞች ስም ዝርዝር ይፋ ያደረገ ሲሆን በጥቃቱም እንደ ህዋዌ የመሳሰሉ ግዙፍ የቻይና ኩባንያዎች ኢላማ ተደርጎባቸዋል። መገኛውን በሀርቢን ከተማ ያደረገው የቻይና ፖሊስ፤ የአሜሪካ ብሔራዊ ደህንነት ኤጀንሲ (ኤን ኤስ ኤ) ከፍተኛ የሆነ የበይነ መረብ ጥቃት ከፍቶብናል በማለት የከሰሰ ሲሆን ክስተቱ ያጋጠመው ደግሞ ባለፈው የካቲት ወር ላይ ነበር ብሏል።

ፖሊስ አክሎ እንደተናገረው ሶስት የኤስ ኤን ኤ ሰራተኞች ጥቃቱን በማቀናጀት ከሶ እየፈለጋቸው መሆኑ የገለፀ ሲሆን ከግለሰቦቹ በተጨማሪ የካሊፎርንያና የቨርጂንያ የቴክኖሎጂ ዩኒቨርስቲዎችን በጥቃቱ ላይ እጃቸው አለበት ማለቱን ዢንዋ ዘግቧል።የኤን እስ ኤ አባላት ተብለው የተለዩት ግለሰቦችም ካትሪን ዊልሰን፣ ሮበርት ስኔሊንግና ስቴፈን ጆንሰን የተባሉ ሲሆን ከዚህ ቀደምም በተመሳሳይ የበይነ መረብ ጥቃቶች ሲሳተፉ ነበር ሲል ዥንዋ ይዞት የወጣ ዘገባ ያሳያል። ነገር ግን ሁለቱ የአሜሪካ ዩኒቨርስቲዎች በምን መልኩና ደረጃ በጥቃቱ ላይ መሳተፋቸው አልተገለፀም። ክሱን በተመለከተ ሮይተርስ በቻይና የሚገኘውን የአሜሪካ ኤምባሲ ቢጠይቅም መልስ አለማግኘቱን አስነብቧል።

ምንም እንኳ የበይነ መረብ ጥቃቱ የካቲት ወር ላይ የተፈፀመ ነው ቢባልም፤ ከወራት በኃላ አሁን ይፋ ማድረግ የተፈለገበት ምክንያት ግልፅ ነው ምክንያቱ ደግሞ ሁለቱ ኃያላን ሀገራት በጦፈ የንግድ ጦርነት ውስጥ ገብተዋልና ሲሉ ተንታኞች ተናግረዋል።በጉዳዩ ላይ መግለጫ የሰጠው የሀርቢን ከተማ የፀጥታ ቢሮም የአሜሪካው ብሔራዊ ደህንነት ኤጀንሲ ወሳኝ በሚባሉ የቻይና የኃይል፣ የትራንስፖርት፣ የውሃና የኮሚኒኬሽን መሰረተ ልማት ላይ ብሎም በሀገራዊ የደህንነት ምርምር ተቋም ላይ ያነጣጠሩ ጥቃቶች ከፍቶብኛል ብሏል።

በሚሊዮን ሙሴ

@Zena_Adis_Ethiopia


አፕል አሜሪካ ከበርካታ ሀገራት ጋር ባላት የንግድ ጦርነት ምክንያት ከኮቪድ ወዲህ ከከፋ ቀውስ አፋፍ ላይ ነው - ብሉምበርምግ

@Zena_Adis_Ethiopia


❗️ዶ/ር ደብረጺዮን ስለ ፕሪቶሪያው ስምምነት ምን አሉ?

የሕወሓት ሊቀመንበር ደብረጺዮን ገብረሚካኤል፣ የአፍሪካ ኅብረት የፕሪቶሪያው የግጭት ማቆም ስምምነት ተከታታይ ከፍተኛ ቡድን በፍጥነት በፕሪቶሪያው የግጭት ማቆም ስምምነት አፈጻጸም ላይ እንዲወያይ መጠየቃቸውን የትግራይ ቴሌቪዥን ዘግቧል።

ደብረጺዮን ይህን የጠየቁት፣ የአፍሪካ ኅብረት የፕሪቶሪያው የግጭት ማቆም ስምምነት ተከታታይ፣ አረጋጋጭና ተቆጣጣሪ ኮሚቴ ከፍተኛ ሃላፊ ኾነው አዲስ ከተሾሙት ሜጀር ጀኔራል ሳማድ አላዴ አሶዴ ጋር ዛሬ መቀሌ ውስጥ በተወያዩበት ወቅት ነው።

ሕወሓት እና መንግሥት በግጭት ማቆም ስምምነቱ መሠረት እስካሁን የፖለቲካ ውይይት እንዳልጀመሩና የፓርቲው ሕጋዊ እውቅና እንዳልተመለሰለት ደብረጺዮን መግለጣቸውን ዘገባው ጠቅሷል። 

አፍሪካ ኅብረት ጀኔራል ሳማድን የሾመው፣ የሥራ ጊዜያቸውን ባጠናቀቁት ጀኔራል እስጢፋኖስ ራዲናን ምትክ ነው። ሕወሓት ከኮሚቴው ጋር በትብብር እንደሚሠራ ያረጋገጡት ደብረጺዮን፣ ኮሚቴው መሬት ላይ ያለውን ተጨባጭ ኹኔታ በግልጽ በመለየት ሪፖርት እንዲያቀርብ ጠይቀዋል ተብሏል።

#ዜና_አዲስ_ኢትዮጵያ
@Zena_Adis_Ethiopia


ግለሰቡ በቁጥጥር ስር ውሏል

ከኢትዮጵያውያን ባህል፣ ኃይማኖትና ወግ ተቃራኒ የሆነ በርካታ ድርጊቶችን በማህበራዊ ሚዲያ ላይ ያስረጨ ግለሰብን በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራ እያጣራ እንደሚገኝ የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታወቀ።

ግለሰቡ " ሚሊዮን ድሪባ "የሚባል ሲሆን በተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያዎች በሚለቃቸው ተንቀሳቃሽ ምስል በርካታ የህብረተሰብ ክፍሎች ቅሬታቸውን ያነሱበት ጉዳይ ሆኗል።

ፖሊስ እንዳስታወቀው ግለሰቦቹ ከሚያነሱት ቅሬታ ባሻገር በኢትዮጵያ የወንጀል ህግ ፀያፍ ወይም ለመልካም ጠባይ ተቃራኒ የሆነ ድርጊት መፈፀም ወንጀል መሆኑን ይደነግጋል።

የአዲስ አበባ ፖሊስ እንዳስታወቀው ግለሰቡ በጎዳናዎች ላይ የተለያዩ አፀያፊ በተለይም የሴቶችን ክብር የሚነካ ኢ-ሞራላዊ ድርጊቶች በመፈፀም የቀረፃቸውን ምስሎች በመልቀቅ በፈፀመው ህገ ወጥ ተግባርና በለቀቀው ተንቀሳቃሽ ምስል በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራ እያጣራ እንደሚገኝ ፖሊስ ገልጿል።

በአንዳድ ማህበራዊ ሚዲያዎች የሚለቀቁ አንዳንድ ምስሎች ተገቢነታቸውን የሳቱና ያፈነገጡ እየሆኑ መምጣታቸውን ፖሊስ ገልፆ ህገ ወጥ ተንቀሳቃሽ ምስሎችን በሚለቁ ግለሰቦች ላይ የሚወስደውን ህጋዊ እርምጃ አጠናክሮ እንደሚቀጥል የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል።   

ምንጭ:- አ.አ ፖሊስ
#ዜና_አዲስ_ኢትዮጵያ
@Zena_Adis_Ethiopia


Видео недоступно для предпросмотра
Смотреть в Telegram
የዕለቱ አጭር ታሪክ፡ በሰርቢያ ፖሊሶች አንድን ሰው ያዙና በፖሊስ መኪና ውስጥ አስገቡት፤ ያ ብልህ ሰው ግን ከሌላ በር ወጣ።


ፖሊሶቹ በተቆጡት እግረኞች ትኩረታቸው ተከፋፍሎ ነበር፣ ያ ሰውም ምንም እንዳልተፈጠረ ያህል በረጋ መንፈስ ወደ ቤቱ ሄደ።

@Zena_Adis_Ethiopia


የዕዳ ሽግሽግ ባይኖር ኖሮ ኢትዮጵያ በዚህ ዓመት 2.8 ቢሊዮን ዶላር ዕዳ ትከፍል ነበር ተባለ

የኢትዮጵያ መንግስት ለ2017 በጀት ዓመት የነበረውን ከፍተኛ የዕዳ ጫና በግልጽ አስቀምጧል። የፕላን እና ልማት ሚኒስትሯ ፍፁም አሰፋ እንደተናገሩት፣ ምቹ የዕዳ ማስተካከያ (ሽግሽግ) ባይኖር ኖሮ ሀገሪቱ በዚህ ዓመት ብቻ 2.8 ቢሊዮን ዶላር የሚገመት ከፍተኛ ዕዳ መክፈል በግድ ይላት ነበር።

ይሁን እንጂ መንግስት በ G20 የጋራ ማዕቀፍ ውስጥ ከአበዳሪ አገራት ኮሚቴዎች ጋር ባደረገው ውጤታማ ድርድር 1.9 ቢሊዮን ዶላር ብቻ ለመክፈል ተችሏል። ይህም የዕዳ ሽግሽጉ በግምት 1 ቢሊዮን ዶላር የሚሆን እፎይታ እንዳስገኘላቸው ሚኒስትሯ አመልክተዋል።

በተጨማሪም በ2016 በጀት ዓመት መገባደጃ ላይ የሀገሪቱ አጠቃላይ የውጭ ዕዳ ከሀገር ውስጥ አጠቃላይ ምርት (GDP) ጋር ሲነፃፀር 13.7 በመቶ እንደነበር ፍፁም አሰፋ ( ዶ/ር)  አብራርተዋል።

በአጠቃላይ የኢትዮጵያ መንግስት ከአበዳሪ ኮሚቴዎች ጋር ባካሄደው ገንቢ ውይይት በመርህ ደረጃ 3.5 ቢሊዮን ዶላር የሚሆን የዕዳ እፎይታ ስምምነት ላይ ደርሷል።

ይህ ስምምነት እንደተገለፀው በ2017 የ 1.5 ቢሊዮን ዶላር፣ በ2018 የ 400 ሚሊዮን ዶላር፣ በ2019 የ 500 ሚሊዮን ዶላር እንዲሁም በ2020 የ 1.5 ቢሊዮን ዶላር የዕዳ ሽግሽግን ያካተተ ነው እንደ ካፒታል ዘገባ።

@Zena_Adis_Ethiopia


ቡርኪናፋሶ የተለበሱ ልብሶች ከአሜሪካ ወደ ሃገሯ እንዳይገቡ ከልክላለች።

ቡርኪናፋሶ ውሳኔውን በዚህ ሳምንት የወሰነች ሲሆን የሃገር ውስጥ የጨርቃ ጨርቅ ምርቱን ለማበረታታት እና በባህል ለመኩራት ውሳኔው መወሰኑ ተገልጿል።

የቡርኪናፋሶ መንግስት ቃለ አቀባይ የአፍሪካውያንን ምርት ለመልበስ ለአፍሪካ ጊዜው አሁን ነው ብለዋል።

ቃለ አቀባዩ ሃገር በቀል የፋሽን ኢንዱስትሪያችንን የሚገሉትን በውጪ ሃገራት የተለበሱ ምርቶች ላይ ያለንን ጥገኝነት መቀነስ ይገባል ብለዋል።

በ2023 በመፈንቅለ መንግስት ስልጣን በያዘው የ37 አመቱ ወታደር ኢብራሂም ትራኦሬ የምትመራዋ ቡርኪናፋሶ የፖለቲካ እና የኢኮኖሚ ለውጦችን እያደረገች ስትገኝ ከፈረንሳይ ጋር ያላትን ግንኙነት በማሻከር ፊቷን ወደ ሩሲያ ማዞሯም ይታወሳል።

ትራኦሬ በቡርኪናፋሶ ለረጅም ዘመናት የቆዩ የፈረንሳይ ወታደሮችን ከሃገራቸው በማባረር በሩሲያ ወታደሮች ተክተዋል።

ትራኦሬ ወርቅ ሳናጣራ መላካችን ገቢያችንን ይቀንሳል በማለት በቀን 450 ኪሎ ግራም ወርቅ የሚያጣራ የወርቅ ማጣሪያ እንዲገነባም አድርገዋል።

የተለበሱ ልብሶች ወደ ሃገሪቱ እንዳይገቡ የተወሰነው ውሳኔም የኢኮኖሚ ለውጡ አካል ሲሆን ፕሬዚዳንቱ የሃገራቸው የባህል ልብስ እንዲለበስና የሃገር ውስጥ የልብስ አምራቾች እንዲነቃቁ እንደሚፈልጉ ተነግሯል።

@Zena_Adis_Ethiopia


⚡️የኮምቦልቻ ከተማ አስተዳደር ለነዋሪው የ100 ሚልዮን ብር አበድሩኝ ጥያቄ አቀረበ

ብድሩ 'ለኮሪደር ልማት እና ለገበያ ማረጋጊያ' ይውላል ተብሏል

የኮምቦልቻ ከተማ አስተዳደር ነዋሪው ለቤት መስሪያ በሚል ለበርካታ አመታት በማህበር ከቆጠበው ገንዘብ ውስጥ የ100 ሚልዮን ብር አበድሩኝ ጥያቄ ማቅረቡ ተሰምቷል።

መጋቢት 12/2017 ዓ/ም በከተማው የከንቲባ ፅህፈት ቤት ሀላፊ አቶ ሙሉጌታ ደርሴ የተፈረመ ደብዳቤ ለኮምቦልቻ ህብረት ስራ ማህበራት የተፃፈ ሲሆን የከተማ አስተዳደሩ 'ግዜያዊ የገንዘብ እጥረት' እንዳጋጠመው ይገልፃል

"የከተማ አስተዳደሩ ጊዜያዊ የበጀት እጥረት ስላጋጠመው የጋራ መኖርያ ቤት ህብረት ስራ ማህበራት ካላቸው ቁጠባ ላይ ለኮሪደር ልማትና ለገበያ ማረጋጊያ አገልግሎት የሚውል ከሁሉም ማህበራት ብር 100 ሚልዮን እስከ ሰኔ ወር 2017 ዓ/ም የሚቆይ ብድር እንድትሰጡን" የሚለው የከንቲባው ፅህፈት ቤት ደብዳቤ ገንዘቡ በአስቸኳይ ስለሚፈለግ ገቢ እንዲደረግ ይጠይቃል።

@Zena_Adis_Ethiopia


ቻይና የክብደት መጠናቸው ከ50 ኪሎ ግራም በታች የሆኑ ዜጎቿ ከመኖሪያቸው እንዳይወጡ አሳሰበች
*

በቻይና ሰሜናዊ ክፍል ዝናብ የቀላቀለ ከባድ ነፋስ መከሰቱን ተከትሎ የሰውነት ክብደት መጠናቸው ከ50ኪሎ ግራም በታች የሆኑ ዜጎቿ ከመኖሪያቸው እንዳይወጡ አሳስባለች።

ከሀገሪቱ ደቡባዊ አዋሳኝ ሞንጎሊያ መነሻውን ያደረገው ነፋስ በሰዓት 150 ኪሎ ሜትር በመሸፈን ቤጂንግ፣ ቲያንጂንን እና ሄበይን ጨምሮ የቻይናን ሰሜናዊ ክፍሎች እየመታ ይገኛል።

የነፋስ ጥንካሬ ከ1 እስከ 17 ባለ ደረጃ የሚለካ ሲሆን አሁን ላይ የተከሰተው ከባድ ንፋስ ባለፉት 10 ዓመታት ከተመዘገቡት የመጀመሪያው መሆኑ ተገልጿል።

የተከሰተው ከባድ ንፋስ ደረጃ 13 ሲሆን ዝናብ ፣ በረዶ እና ነጎድጓድ የቀላቀለ  መሆኑን የቻይና  የአየር ትንበያ ኤጀንሲ  ጠቁሟል።

በሁነቱ በሰው ህይወት ላይ የደረሰ ምንም ዓይነት ጉዳት እንደሌለ ያመላከተው ኤጀንሲው፤ ከ300 በላይ ግዙፍ ዛፎች ተገንድሰው መውደቃቸውን ጠቁሟል።

ይህን ተከትሎ  የሰውነት ክብደታቸው ከ50 ኪሎ ግራም በታች የሚመዝኑ ዜጎች በንፋሱ እንዳይወሰዱ በማሰብ ነው ከመኖሪያቸው እንዳይወጡ ማስጠንቀቂያው የተሰጠው።

እንዲሁም ንፋሱ የባሰ አደጋ እንዳያስከትል አስቸኳይ እርምጃዎች እየተወሰዱ ይገኛል። ዛፎች በቀላሉ እንዳይነቀሉ ማጠናከር ብሎም መቁረጥ፣ ፓርኮች እንዲዘጉ እንዲሁም ወሳኝ እና አስፈላጊ ያልሆኑ በረራዎች እንዲሰረዙም ተደርጓል። 

ክስተቱን ተከትሎ የቤጂንግ እና ሌሎች የቻይና ሰሜናዊ አካባቢ ጎዳናዎች ጭር ብለው መዋላቸውን አርቲ በዘገባው አመላክቷል።

@Zena_Adis_Ethiopia


🇪🇹ኢትዮጵያ በአህያ ቁጥር ብዛት ከአለም በአንደኝነት ተቀምጣለች!

ኢትዮጵያ በአሁኑ ሰዓትም በአጠቃላይ ወደ 8.8 ሚሊዮን የሚሆኑ አህዮች የሚኖሩባት ሀገር እንደሆነችም ይፋ ተደርጓል።

@Zena_Adis_Ethiopia


በህንድ የተከሰተው ምንድን ነው ?
::::::::::::::::

በህንድ እና ኔፓል  ከባለፈው ረቡዕ አንስቶ በጣለው ከባድ ዝናብ ከ100 በላይ ሰዎች ህይወታቸው ማለፉ  ተገለጸ::

በምስራቃዊ ህንድ  በምትገኘው ቢሀር  82 የሚደርሱ ሰዎች  ህይወታቸው ማለፉን  የሀገሪቱ አደጋ ጊዜ መስሪያ ቤት አስታውቋል፡፡
የህንድ ሚትሮሎጂ ተቋም በምዕራብ እና ምስራቅ ህንድ ያሉ ዜጎች ጥንቃቄ እንዲያደርጉም አሳስቧል፡፡

በተመሳሳይ በደቡብ እስያዋ ሀገር ኔፓል  በከባድ ዝናብ ምክንያት  8 ሰዎች ህይወታቸው ማለፉ ተዘግቧል፡፡

ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በዓለም ላይ የሚከሰቱ የመሬት መንቀጥቀጥ፤ አውሎ ነፋሳት፤ እና ከባድ ዝናብ ዓለማችን ፈታኝ የአየር ንብረት ለውጥ   እንዳጋጠማት አመላካች ነው ሲል  ኢስተርን አይ ዘግቦታል፡፡

@Zena_Adis_Ethiopia


#መቄዶንያ

በመቄዶንያ የአረጋውያንና የአእምሮ ህሙማን መርጃ ማዕከል ቀደምት ተገልጋይ የነበረው የጌዲዮን ሙላቱ ስርዓት ቀብር መቄዶንያ የአረጋውያንና የአእምሮ ህሙማን መርጃ ማዕከል ፊት ለፊት በሚገኘው አያት መድኃኒዓለም ቤተክርስቲያን ተፈፅሟል።

በስርዓት ቀብሩ ላይ የመቄዶንያ የአረጋውያንና የአእምሮ ህሙማን መርጃ ማዕከል መስራች እና ዋና ሥራ አስኪያጅ ቢኒያም በለጠን ጨምሮ የማዕከሉ አረጋውያን አንዲሁም ወዳጆቹ ተገኝተዋል።

ጌዲዮን በትልልቅ ሆስፒታሎች የልብ ሕክምና ሲደረግለት የነበረ ሲሆን፤ በጥቁር አንበሳ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል በድንገተኛ ሕክምና ክፍል ተኝቶ ልዩ ክትትል እየተደረገለት በትናትናው ዕለት ሚያዝያ 4 ቀን 2017 ዓ.ም በሕክምና ላይ እያለ በ37 ዓመቱ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል።

መረጃው የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ነው።

Показано 20 последних публикаций.