ዳግማዊ ቄርሎስ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: Религия


የኢትዮጵያዊው ቄርሎስ የአባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ ሕይወትና ትምህርት ይቀርብበታል።
https://t.me/abagiyorgismnale
ለሌሎች በማጋራት መንፈሳዊ ግዴታችንን እንወጣ
ለጥያቄዎችና ለአስተያየት
@Dnmikii @feke17

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
Религия
Статистика
Фильтр публикаций




Репост из: ሐመረ ብርሃን የብራና መጻሕፍት ሥራ ድርጅት
የ6ወር የሥዕል ስልጠና


ማክሰኞ፣ ሐሙስ፣ ቅዳሜ
ከጠዋት 3:00 - 6:00 እና ከሰዓት 8:00 - 11:00
በሁለት ፈረቃ

ምዝገባ ፦ እስከ ሚያዝያ 26

በኦንላይን ጎግል ፎርም


የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ
    ትውፊታዊ አሣሣል ዘይቤ

የእርሳስ ሥዕል (drawing)
ቀለም ቅብ (painting)

ይህን ሊንክ ተጠቅመው ይመዝገቡ!


👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇

https://docs.google.com/forms/d/1iTjWvv9UWJUDr69ySsfVUQiSMIwVTGKl4mPa6mQv1I0


Видео недоступно для предпросмотра
Смотреть в Telegram
Does God abandon us in difficult times?

In some of our most difficult times, we are often tempted to think that God is not present with us. We feel like he is absent and has maybe even forsaken us. But is this true? Can we really believe what is said to us in Scripture and also believe that God has abandoned us? Stick around and lets investigate this together.


THE CRUCIFIXION OF THE KING OF GLORY
By:- Dr Eugenia Scarvelis Constantinou


Видео недоступно для предпросмотра
Смотреть в Telegram


Видео недоступно для предпросмотра
Смотреть в Telegram


Репост из: 𝕠𝕣𝕥𝕙𝕠𝕕𝕠𝕩 𝕡𝕒𝕥𝕣𝕚𝕤𝕚𝕥𝕚𝕔 𝕔𝕠𝕞𝕞𝕖𝕟𝕥𝕒𝕣𝕪,𝕒𝕡𝕠𝕝𝕠𝕘𝕖𝕥𝕚𝕔,𝕥𝕙𝕖𝕠𝕝𝕠𝕘𝕪,𝕓𝕠𝕠𝕜,𝕒𝕣𝕥𝕚𝕔𝕝𝕖 𝕝𝕚𝕓.
ለእግዚአብሔር የገባሁት ቃል ኪዳን የመረጋጋት እና የዝምታ ሕይወት ነበር ::እንደ ቃሌ ይህንን ሕይወት እየተለማመድኩ ሕሊናየ ከፍ ያለውን ነገር በሚመለከትበትና የሕይወት ፍልስፍናዬ ትክክል እንደሆነ እያመንኩ በመጣሁበት በዚህ ወራት ባልጠበቅኩት ጊዜና አጋጣሚ የተጫነብኝን ቀንበር ልሸከምበት የምችለውትከሻ አልነበረኝም :: ለእኔ አስፈላጊ የነበረው ነገር የስሜት ሕዋሳቶቼን በር ዘግቼ ከሥጋዊ እና ዓለማዊ ነገር ሁሉ ሸሽቼ ከራሴ ጋር ብቻ መሆንን ነው ::  ከራስ ጋ ከመነጋገር የበለጠ ደስታን የሚሰጥ ምን ነገር አለና ከማውቀው ከራሴ ጋር መወሰንን ወደድኩ :: ለራሴ እና ለእግዚአብሔር ነገርን እየተናገርኩ ከሚታይ እና ከሚዳሰሱ ነገሮች ሁሉ በላይ ትልቅ የሆነ ሕይወትን መኖርን ወደድኩ በልቡናዬ ውስጥ የምጫረውን ሰማያዊ ነገር ::

ከምድራዊ ሐሳብ ጋር ሳልቀላቅል መንፈሳዊ የሆነ ነገር በውስጤ እንዲያድር ማድረግ የዘወትር ፍላጎቴ ነበር  ይህ ሐሳብ ንጹሕ መስታወት የሰውን መልክ እንዲያሳይ እግዚአብሔርን እንድንመለከት የሚያደርግ የልቡና መስታወት ነው ::በብርሃን ላይ ብርሃንን የሚጨምር በእውቀት ላይ እውቀትን የሚጨምር በተስፋ የሚጠብቁት የሚደሰቱበት ከቅዱሳን መላእክት ጋር ሆነው እግዚአብሔርን የሚያመሰግኑበት ስሜት ነው ::

"ከራስ ጋ ከመነጋገር የበለጠ ደስታን የሚሰጥ ምን ነገር አለና ከማውቀው ከራሴ ጋር መወሰንን ወደድኩ ::"

(ቅዱስ ጎርጎርዮስ ዘእንዚናዙ ትምህርቱ እና ሕይወቱ ከገጽ 43-44 )




ቤዛ

ቤዛ ማለት ቃሉ የግእዝ ሲሆን ትርጉሙም አዳነ ተቤዠ ብሎ ይፈታል። ስለዚህም በየመጻሕፍቶቻችን ማዳን፣መቤዠት ለሚሉ ትርጉሞች ቤዛ...ቤዛ ሲል ይገኛል ለምሳሌ ፦

....በቈጠርሃቸው ጊዜ ከእነርሱ ሰው ሁሉ እንደ ቍጥራቸው መጠን የነፍሱን ቤዛ ለእግዚአብሔር ይስጥ
                                     *ዘጸ 30:12

° እዚህ ጋር ቤዛ ገንዘብ ተብሎ ተፈቷል ሙሴ ሕዝቡን በሚቆጥርበት ጊዜ በሕዝቡ መቅሰፍት እንዳይታዘዝ ለነፍሱ ቤዛ እንዲሰጥ ታዟል።

° ለሰው ነፍስ ቤዛው ሀብቱ ነው
                                            ምሳ 13:8

እዚህ ጋር ቤዛ ሀብት ተብሎ ተተርጉሟል እርግጥ ነው አቅንቶ ተርጉሞ ለሌላ ማድረግ ይቻላል ነገር ግን ቀጥታ ንባቡ ቤዛን ሀብት አድርጎታል።

እኔ የእስራኤል ቅዱስ አምላክህ እግዚአብሔር መድኃኒትህ ነኝ፤ ግብፅን ለአንተ ቤዛ አድርጌ፥ ኢትዮጵያንና ሳባንም ለአንተ ፋንታ ሰጥቻለሁ።
                                   
                                           ኢሳ 41:3

ሰው ዓለሙን ሁሉ ቢያተርፍ ነፍሱንም ቢያጐድል ምን ይጠቅመዋል?
ወይስ ሰው ስለ ነፍሱ ቤዛ ምን ይሰጣል?

                                        ማቴ 16:26

° እዚህ ጋር ቤዛ ፈንታ ተብሎ ተተርጉሟል


  ይህን ሙሴን በቍጥቋጦው በታየው በመልአኩ እጅ እግዚአብሔር ሹምና ቤዛ አድርጎ ላከው።
                                       የሐዋ 7:35

° እዚህ ጋር ቤዛ፣ሹም፣ዳኛፈራጅ ተብሎ ይፈታል።

የኢየሱስ ክርስቶስ ቤዛነት

የኢየሱስ ክርስቶስ ቤዛነት ደሙ በማፍሰስ ሥጋውን በመልዕልተ ቀራንዮ በመቁረስ ተከናውኗል።

ስለ አዳም እና ልጆቹ ሁሉ ኢየሱስ ክርስቶስ ቤዛ ሆኗል !

የእመቤታችን ቤዛነት

እነ ቅዱስ ያሬድ እነ ቅዱስ አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ በመጻሕፍታቸው ተባብረውበታል በጠቅላላ በሁሉም ዘመናት የተነሱ ቅዱሳን ሊቃውንት ተባብረውበታል።

የእመቤታችን ቤዛነት ክርስቶስን በመውለድ ፣ በኃጢአት ዓይኑ ለታወረበት ዓይን በመሆን ተገልጾል።

ሌላው ቢቀር ዕለት ዕለት ማኅሌት የሚቆም ሰው ይህንን ያውቃል !

ኪያኪ ሠናይተ ዘፈጠረ ለቤዛ ዓለሙ፤ እግዚአብሔር ይትባረክ ወይትአኮት ስሙ።

ሲጠቃለል

❤ ክርስቶስ ቤዛ ሆኖ አዳነን፥ እመቤታችን ቤዛዊተ ኩሉ መባሏ

1. ለዓለም ድኅነት ምክንያት ናትና
"አንቲ ውእቱ ተስፋሁ ለአዳም አመ ይሰደድ እም ገነት" አባ ሕርያቆስ
ክርስቶስ የባሕርይ ቤዛ ነው፥ እመቤታችን የጸጋ ናት (ተፈሥሒ ኦ ምልእተ ጸጋ እንዲል)

2. ምክንያተ ድምሳሴ ጥንተ አብሶ ናትና

= ጥንተ አብሶ
   - ሰዋሰዋዊ ትርጉሙ የመጀመሪያ በደል፥
   - መጽሐፋዊ ምሥጢራዊ ትርጉሙ መርገመ ሥጋ ወነፍስ - ከአዳም ጀምሮ የሚተላለፍ ኃጢአት አንድም እግዚአብሔርን ማጣት አንድም ከጸጋ እግዚአብሔር መራቆት (መሞት) ማለት ነው

ሉቃ 1:28 "ቡርክት አንቲ እምአንስት"፣
መሓ 4:7 "ወዳጄ ሆይ ሁለንተናሽ ውብ ነው፥ #ነውርም_የለብሽ"

3. በንጽሕና የተዋበች፣ ከምድር እስከ ሰማይ የደረሰች መሰላል ናትና
- (ምድር ያለው ውድቀቱን ያይደለ ሰማይ ያለ መነሣቱን ያየንብሽ)

4. መንበረ መለኮት ናትና
ዳን 7:9-13 "..."
አንድም "አንቲ ተዓብዪ እምኪሩቤል ወትፈደፍዲ እምሱራፌል" እንዲል

5. በጸጋ መድኃኒተ ዓለም ናትና
- የመዳን ምክንያት መሆን መቻል ነው፥
  - "ዘርን ባያስቀርልን" ኢሳ 9:1
  - "ምልክትን ይሰጣችኋል" ኢሳ 7:14

6. ከፈጣሪ በታች ከፍጡራን በላይ ናትና
   #ይህን መቧሏ ስለምንድን ነው ቢሉ
      - ጥንተ አብሶ የለባትምና
      - ድንግል ወእም ከእርሷ ውጪ የለምና
      - የመለኮት ማደርያ ናትና
      - አልቦ ኃጢአት ናትና
      - ከእርሷ በቀር ወላዲተ አምላክ የሚባልም ሆነ ሊባል የሚችል የለምና

ምክር ቢጤ ፦ ይህን ሳያውቁ ስለ ቤዛ ድምዳሜ መስጠት ነውር ነው ከትልቅ ሰው አይጠበቅም።

                                  መ/ር ነቢዩ ኤልያስ






ቤዛዊተ ኩሉ ዓለም ።

‘ሹምና ፈራጅ እንድትሆን የሾመህ ማን ነው?’ ብለው የካዱትን፥ ይህን ሙሴን በቍጥቋጦው በታየው በመልአኩ እጅ እግዚአብሔር ሹምና ቤዛ አድርጎ ላከው። የሐዋ ሥራ 7፥35


መቃብር ጾመኛ ሴትን መሰለ!

በጾም ቀን ወጥ የምትሠራ ሴት፥ ቀምሳ ጢቅ ትለዋለች፤ አትውጠውም፡፡እንደዚኹም ኹሉ፥ ጌታችን ክርስቶስን መቃብር ቀመሰው[ሞቶ ተቀበረ]፡፡

ያቺ ጾመኛ ሴት፥ ቀምሳ ጢቅ ትለዋለች እንጂ እንደማትውጠው፥መቃብርም ክርስቶስን ውጦ ያስቀረው ዘንድ አልቻለም፡፡

የክርስቶስ ሥጋ ዐለት ኾነበት፡፡ በዚኽ ዐለት ምክንያት የመቃብር ጥርስ ረገፈ! ይኽን ያየን እኛም 'ሞት ሆይ መውጊያ የት አለ?' እያልን ከነቢያትና ከሐዋርያት ጋር ዘመርን፡፡

ለአማኞች 'የሕይወት እንጀራ ነኝ' ያለ ጌታ፥ ለሞት ግን ሕያው ድንጋይ ኾነበት፡፡ አምስት ሺህ አምስት መቶ ዘመን የቆየ የሞት ሥልጣን፥ በሦስት ቀንና ሦስት ሌሊት ድል ተነሣ!

ጾመኛዋ ሴትና መቃብር የተገኙት "አኀዘ ይጥዐሞ ለሞት በፈቃዱ ዘእንበለ ግብር፤ ሞትን በፈቃዱ ቀመሰ" ከሚለው የአፈወርቅ ንባብ ነው፡፡

አገራችንም የደምና የጦርነት ጾመኛ ኾና፥እንደ አገር 'እምይዕዜሰ ኮነ ፍሥሓ ወሰላም' ለማለት ያብቃን፡፡

ሊቀ ሊቃውንት ስሙር አላምረው


የተጻፈው ቢነበብ
  የተነበበዉም ቢተረጒም
    በተተረጒመው ምግባር ቢሠራ
የዚህ ኹሉ የሃይማኖት ፍጻሜው  "#ትንሣኤ" ነው።

. ትንሣኤ ከሌለ፣ ሃይማኖት ኹሉ ከንቱ ነው፤

. የሃይማኖት የመጨረሻው ዋጋው፣
በትንሣኤ ማክበሩ ነው እንጂ፣
በምድር ማቀማጠሉ [መቀማጠሉ] አይደለም።

. ሰው የተፈጠረው #ለትንሣኤ ነው፤
የሚኖረዉም #ለትንሣኤ ነው፤
የሚጽናናዉም #በትንሣኤ ነው።

. ጌታችንም፦  
ሥጋውን የበላውን፣
ደሙን የጠጣውን ሰው፣  
ስለሚሰጠው ዋጋ ሲናገር
           'እሾመዋለኊ፤
            እሸልመዋለኊ፣
            ጤና እሰጠዋለኊ፤
             ሀብት አድለዋለኁ፤

                         ..." አላለም!!!


. ይልቁንም
"...ሥጋዬን የሚበላ፣ ደሜን የሚጠጣ፣
የዘለዓለም ሕይወት አለው፤
እኔም በመጨረሻ ቀን
#አነሣዋለኊ" ነው ያለው፤ 


. ሌሎች የማያስፈልጉን ኾነው ሳይኾን፣
እነዚያ [ሹመት፣ ጤና፣...] የፍጡርነት ዋጋ እንጂ፣
የሃይማኖት ዋጋ ስላልኾኑ ነው
የሃይማኖት ዋጋ #በክብር #መነሣት ነውና


. የሃይማኖት ዋጋው "ትንሣኤ" ነው፤

ሃይማኖት ለጤና፣
   ሃይማኖት ለፈውስ፣
      ሃይማኖት ለሹመት፣
        ሃይማኖት ለመብል ...
የሚል መርሕ ያላቸው፣ የእነ ሰዱቃውያን ዘመዶች ናቸው።


. ዓላማው 'ትንሣኤ' የኾነ ሰው፣ 
'ምንም የማይገታው ክርስትና' ይሉሃል ርሱ ነው፤



('ጸያሔ ፍኖት-መንገድ ጠራጊ፤ በአባ ገብረ ኪዳን፤ ገጽ ፻፶፰/፫፻፶፬/ 158/354፤ ፳፻፲፩/2011 ዓ.ም.)

እንኳን አደረሳችኊ


Репост из: ዲያቆን ሄኖክ ሃይሌ Henok Haile
Видео недоступно для предпросмотра
Смотреть в Telegram
በርባን

#share
@diyakonhenokhaile




Видео недоступно для предпросмотра
Смотреть в Telegram
#share #share
@diyakonhenokhaile




"ሁሉን የያዘውን ያዙት፤ ሁሉን የሚገዛውን አሠሩት፤ የህያውን አምላክ ልጅ አሠሩት፤ በቁጣ ጎተቱት፤ በፍቅር ተከተላቸው። በሚሸልተው ፊት እንደማይናገር እንደ የዋህ በግ በኋላቸው እየተከተለ ወሰዱት፤ ሊቃነ መላእክት በመፍራት እና በመንቀጥቀጥ ከፊቱ የሚቆሙለትን በአደባባይ አቆሙት፤

ኃጢአትን ይቅር የሚለውን ኃጥእ አሉት፥ በመኳንንት የሚፈርደውንም በእርሱ ፈረዱበት፤ ለሱራፌል ዘውድ የሚያቀዳጃቸውን የሾህ ዘውድ አቀዳጁት፤ ለኪሩቤል የገርማ ልብስ የሚያለብሳቸውን ለመዘበት ቀይ ግምጃ አለበሱት፤ ኪሩቤል በእሳት ክንፍ ተሸፍነው በፊቱ የሚሰወሩለትን እርሱን ክፉ ባሪያ አሥሮ ፊቱን ጸፋው፤ የመላእክት ሠራዊት በፍጹም መደንገጥ የሚሰግዱለት እየዘበቱበት በፊቱ ተንበረከኩ፡፡

ይህን ያህል ትህትና እንደምን ያለ ትህትና ነው? ይህን ያህል ትእግስት እንደምን ያለ ትእግስት ነው? ይህን ያህል ዝምታ እንደምን ያለ ዝምታ ነው? ይህን ያህል ቸርነት እንደምን ያለ ቸርነት ነው? ኃያል ወልድን ፍቅር ከዙፋኑ ሳበው እስከ ሞትም አደረሰው በደል የሌለበትን እንደበደለኛ ሰቀሉት፡፡ ህይወትን የሠራውን ከበደለኞች ጋር ቆጠሩት፤ አዳምን የሠሩ እጆች በመስቀል ቀኖዎት ተቸነከሩ፤  ወዮ በገነት የተመላለሱ እግሮች በመስቀል ተቸነከሩ፡፡

ወዮ በአዳም ፊት የህይወት እስትንፋስን እፍ ያለ አፍ ከሃሞት ጋር የተቀላቀለ የኮመጠጠ መፃፃን ጠጣ፤... ወዮ የወልድን መከራውን የሚናገር ምን አፍ ነው? ምን ከንፈር ነው? ምንስ አንደበት ነው? የፍቁሩ የጌታ ህማማት በተነገረ ጊዜ ልብ ይለያል፤ ህሊናም ይመታል፤ ነፍስም ትንቀጠቀጣለች፤ ሥጋም ይደክማል የማይሞተው ሞተ፤ ሞትን ይሽረው ዘንድ ሞተ፤ ሙታንን ያድናቸው ዘንድ ሞተ። የምትወዱት ሰዎች ፈጽሞ አልቅሱለት፡፡"

/ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ/



Показано 20 последних публикаций.