Фильтр публикаций


ሰበር የድል ዜና

በቀን 09/5/2017 ዓ.ም ከአማራ ፋኖ በጎጃም ጃዊ መተከል (4ኛ) ክ/ጦር በነበልባሎች ኤፍሬም እልምነህ ብርገድ የተሰራ ደማቅ ታሪክ፦

ተወርዋሪ ኮከቦቹ ኤፍሬም ብርጌድ ከጥዋቱ 12:00 ሰዓት አካባቢ ወደ ጠላት ኬላ በመንቀሳቀስ በጠላት ላይ ከፍተኛ ኪሳራን አድርሰዋል።

ጃዊ ከተማ በመግባት 7 የሚሊሻ ፣ የፖሊስ፣ የአድማ ብተና አባላትን እንዲሁም 2 የመከላከያ ሰራዊት አባላትን እስከ ወዲያኛዉ ሸኝተዋቸዋል። በርካታ ከባድ እና ቀላል ቁስለኛ በማድረግ ወደ ፓዊ ሆስፒታል በ2 አምቡላንስ የተወሰዱ መሆናቸዉን የውስጥ መረጃዎች ይጠቁማሉ።

ከፍተኛ ማዕረግ ያለዉ አንድ የፖሊስ አዛዥን ጨምሮ ወደ 9 የሚደርሱ የጠላት ሃይልን መግደል ተችሏል። በትንሽ ሃይሎች ማለትም ከ8 ባልበለጡ ተወረዋሪዎች እና በሻለቃ 2 አስገራሚ ጥምረት ደማቅ ድልን መጎናፀፍ ተችሏል።

በዚህም የተበሳጨዉ የጠላት ሃይል አንድ ንፁህ ዜጋ አረሶ አደር በመግደል በአደባባይ በአስፓልቱ በመኪና በመጎተት የጭካኔ ጥጋቸዉን አሳይተዋል።

ከአማራ ፋኖ በጎጃም ጃዊ መተከል (4ኛ) ክ/ጦር ህዝብ ግንኙነት ሃላፊ ፋኖ ያዕቆብ ጌታሁን።


#ያ ሰዉ #ኢንጅነር_ፋኖ_እስቲበል_አለሙ ነዉ‼


የዛሬ 3 አመት አካባቢ ነዉ ይካቲት 23/2014 ዓ/ም #ከዳንግላ #ከዱርቤቴ #ግሩሜን ጨምሮ #ከቲሊሊ #ከኮሶበር #ከደብረማርቆስ እና ሌሎች አካባቢዎች የምንገኝ የፋኖ አባላት አዲስ ቅዳም ከተማ ቅዱስ ገብርኤል ሜዳ ተገናኝተን ተሰባሰብን።

የመገናኘታችን ምክኒያትም:_
የአድዋ ድልን ምክኒያት በማድረግ የአማራ የብረት በር የነበረዉን #የራስ_አርበኛ_ዘመነ_ካሴ ቀኝ እጅ  ከአማራ ፋኖ ጠንሳሾች አንዱ የሆነዉን የአማራ የቁርጥ ቀን ልጅ  ፋኖ ፲/አ #ኤፍሬም_አጥናፉን ለመዘከር እና አዲስ ቅዳም ከተማ ዉስጥ መልምለን በጀግናዉ ኮማንዶ ፋኖ ፲/አ #ሰማኸኝ_በቀለ አሰልጣኝነት ለ33 ቀን ስልጠና ያሰጠናቸዉን 28 ምልምል ፋኖዎች ጨምሮ ሌሎች ከአገዉ ምድር ከተሞች ተመልምለዉ ስልጠና ወስደዉ ያጠናቀቁ ፋኖዎችን ለማስመረቅ በማሰብ ነበር።


በወቅቱ የተያዙትን ሁለቱንም እቅዶቻችንን በጥሩ ሁኔታ ፈፅመን ለፕሮግራም የመጡ ጓዶቻችንን ለመሸኘት ወደ ከተማ በምንመለስበት ስዓት ግን አንድ ቀድመን የምንጠብቀዉ ችግር ገጠመን።

ከቀኑ 8:00 አካባቢ የአዲስ ቅዳም ከተማ ከንቲባውን ጨምሮ ሁሉም የአዲስ ቅዳም እና የወረዳ ካድሬ ከፀጥታ ሀይል (ፖሊስ) ጋር በመሆን መንገድ ዘግቶ አስቆመን። 

አስቁሞንም ከነበርነዉ አጠቃላይ ፋኖዎች እኔን (#ተሻገርን)  #ሀብታሙን  እና #አንሙት_ፀጋን ነጥለዉ ወደ እስር ቤት አስገቡን።

ከቆይታ በኋላ #መዝገብም ተቀላቀለን። አራታችንም እስር ቤት ገብተን እንጨነቅ የነበረዉ ለፕሮግራም መጥተዉ በፈሪ ሆድ አደር ካድሬ ኢ_ምክኒያታዊ ውሳኔ  የተነሳ እየተጉላሉ ለነበሩ እንግዶቻችን ነበር።

ሰዓቱ እየሄደ ነዉ። ቀኑም እየመሸ  ምሽት 1:30 አካባቢ ከእንግዶች ዉስጥ  የአንድ ጓዳችንን ድምፅ ሰማነዉ መስማት ብቻ አይደለም። የነበርንበት እስር ቤት ተከፎቶ በአይን ተያየነ። "ግባ!" ተባለ  እኛ አራታችንም በጣም ተደናገጥነ።

እነዚያ ሆድ አደር እርካሽ ካድሬዎች በዚህ ልክ መዳፈራቸዉ የምር አንገበገበን።

ይሁንም እንጂ አቅፈን በመሳም ወደ ጨለማዋ እስር ቤታችን  እየመራነ አስገባነዉ።

ዉስጥ ከገባነ በኋላ ጉዳዩን ስንጠይቀዉ  "ከእኛ መታሰር ጋር በተያያዘ ምድረ ሆድ አደር ባዶ ጭንቅላት ካድሬን  "#ለምን?"  ብሎ ሰቅዞ ስለያዛቸዉ መሆኑን ተረዳነ።

ያ ሰዉ #ኢንጂነር_ፋኖ_እስቲበል_አለሙ ነዉ!!

በዚህ አጋጣሚ ቆሎ እና ዉሀ በማዘጋጀት ከካድሬ አይን ደብቀን  ያስመረቅናቸዉን የአማራ ፋኖ በአገዉ ምድር የመጀመሪያ ዙር ፋኖዎች እዉቅና ሰጥቶ  ፋኖነታቸዉን ያበሰረልን የወቅቱ






Видео недоступно для предпросмотра
Смотреть в Telegram

3.7k 0 13 12 52

እናት እና አባትን አስቀምጦ ልጃቸውን ፊት ለፊታቸው መረሸን የመንግስትን ስልጣን ያፀናል ብለው ያምናሉ፤ አምነውም ይፈፅሙታል።ሲፈፅሙም ጀብዷቸውን በቪዲዮ ቀርፀው እንፈራቸው ዘንድ ያሰራጩታል። ሀቁ ግን ይህ ድርጊት ቢያንስ 100 ሰዎችን ከወደቁበት ጥልቅ አዚም ያነቃል። አስቀድመው ለነቁት ደግሞ የአረመኔዎችን እድሜ ለማሳጠር የበለጠ ያተጋቸዋል።

ሞት ለገዳይ አረመኔ የአብይ ወታደሮች!
ለወላጆቹ ፈጣሪ ብርታቱን ይስጣቸው!

Misganaw Belete


ከምደባ ጋር በተያያዘ፣

ከዚህ ቀደም የድርጅቱ ፋይናንስ መምሪያ ኃላፊ በመሆን ያገለግል የነበረው ፋኖ ማንችሎት እሱባለው/ Manchilot Esun - የአማራ ፋኖ በጎጃም ወታደራዊ አማካሪ በመሆን እንዲያገለግል ተመድቧል።

አዲስ ትውልድ!
አዲስ አስተሳሰብ!
አዲስ ተስፋ!

[አማራ ፋኖ በጎጃም]

7.8k 0 4 10 111

።።።።።።።ለአማራ ህዝብ ቀን ከሌት እንሰራለን!!
የአማራ ፋኖ በጎጃም ቀጠና ትስስር መምሪያ
........................ 9/5/2017 ዓ ም
አረንዛው ጎንቻ አንድነቱን ከፈጠረ በሗላ አመራሩን መረጠ። ብርጌዱ ከአሁን በሗላ ከፋፋይ አጀንዳ ይዞ የሚመጣውን አካል ላይቀበል ተማምሎ ተነስቷል።
ጎጃም ቤቱን ዘግቶ መመካከር ያውቅበታል።
አንድነት ለሁሉም ያስፈልጋል።
የአማራ አንድነት፣ የኢትዮጵያ አንድነት፣የአፈሪካ አንድነት እና የአለም አንድነት ሁሉ ለሰው ልጅ ያስፈልጋል።
ጎጃም የአማራ ጎጆ ለመስራት በቀናህነት እየጣርነ እንገኛለን።
አማራ የአማረ ቤት ለመስራት ተቃርቧል።
ይህን ቤት ስንሰራ የግል ፍላጎታችንን ገተን የህዝብ ፍላጎትን አስቀድመን እንደሆነ ሊታወቅ ይገባል።
ጎንቻ፣ጎንቻ ፣ጎንቻ ወደ ፊት ብቻ!!!
የበላይ ዘለቀን ታሪክ የሚደግም ትውልድ ፈጥረናል።
የምስራቅ ጎጃም ታሪክ ከፋ የሚያድር ሰራ ተሰርቷል።
ከዚህ በሗላ የአማራ አንድነት ዜና ለመስማት የምትጓጉ የትግላችን ደጋፊወች በቅርብ ቀን ጠብቁን!!
የፃፍሁት በደስታ ስለሆነ እንኳን ደስ አላችሁ።
መሪወቻችንም ጭምር እንኳን ደስ አላችሁ፣
እንኳን ደስ አለን!!

© አርበኛ የቆየ ሞላ




ሰበር ዜና

በወሎ ቤተ-አምሐራ ተጋድሎ እያደረጉ ያሉ የፋኖ አደረጃጀቶች የምስራቅ አማራ ኮር 1 ባለሽርጡ ክፍለጦር ልጅ እያሱ ኮር ራምቦ ክፍለጦር እና በኮማንዶ ዮሴፍ አስማረ የሚመራው ልዩ ዘመቻ ክፍለጦር በጋራ በሰሜን ወሎ ሀብሩ ወረዳ  ታላቅ ድል ተጎናፀፉ።

ዛሬ ጥር 9/2017 ዓ.ም በተደረገው ተጋድሎ  የባለሽርጡ ክ/ር 3ኛ ሻለቃ ሀብሩ ወረዳ ፋጅ መነዮ ላይ የፋሽስቱን ስርአት ወንበር ጠባቂ  ሰራዊትና ሆድ አደር ሚሊሻ 3ኛ ሻለቃን ከበባ አድርጎ ለማፈን የሞከረው ሀይል ሙትና ቁስለኛ ማድረግ ተችሏል፡፡ በዚህም 12 የሚሆኑ የዙፋን ጠባቂው ሰራዊት እና የሆድ አደሩ ሚኒሻ መሪ ደምሌ አራጋዉ አጃቢዎች እስከ ወዲያኛው ሲሸኙ ብዛት ያለዉ ሀይሉ ቆስለዉበታል:: የተደመሰሱ ሆድ አደር ሚሊሻዎች ስርዐተ ቀብር ላይ ለባንዳ ቀብር ሶላት አንሰግድም በማለት ህዝበ-ሙስሊሙ ወደ የቤታቸዉ ገብተዋል።


በተመሳሳይ  ሀብሩ ወረዳ የምትገኘዉን  መርጦ ከተማን ለመቆጣጠር ከስሪንቃ በአንዳይ መትር፣ በመቻሬ አማየ ሚጫ፣በጉባራ ቆሰሮ በሶስት አቅጣጫ የመጣዉን ወራሪ ሀይል ልጅ እያሱ ኮር ራምቦ ክፍለጦር 1ኛ እና 3ኛ ሻለቃ ልዩ ዘመቻ ክፍለጦር ሰርዶ ሻለቃ እና ምስራቅ አማራ ኮር1 ባለሽርጡ ክፍለጦር 1ኛ እና 2ኛ ሻለቃ በከፍተኛ መናበብ ከንጋቱ 2:00 ሰአት ጀምሮ እስከ 9:00 ሰአት ከባድ ዉጊያ የተደረገ ሲሆን በዉጊያዉም እስከ ሞርተር ድረስ በመጠቀም በጠላት ስብስብ ላይ ብዛት ያለዉ ሀይል ሙትና ቁስለኛ ሲሆን የተረፈዉ ወደ መጣበት ተመልሷል ።


በተጋድሎዉ
~ልጅ እያሱ ኮር ራምቦ ክ/ር 1ኛ እና 3ኛ ሻለቃ
~ምስራቅ አማራ ኮር 1 ባለሽርጡ ክ/ር  1ኛ ፣ 2ኛ ሻለቃ እና መካናይዝድ ክፋል
~በኮማንዶ ዮሴፍ አስማረ የሚመራዉ የልዩ ዘመቻ ክ/ር ሰርዶ ሻለቃ በጥምረት የተሰራ ግዳጅ ነዉ።

ጠላት የተለመደ የዉርደቱ መካሻ ብሎ የሚያስበዉን የንፁሀን ሀብት ንብረት ማቃጠል እና ንፁሃንን ኢላማ ያደረገ የከባድ መሳሪያ ድብደባ ድርጊቱን በፋጅ መነዮ የሰይድ ይማም ቤት ሲያቃጥል ወልድያ ጀነቶ በተተኮሰ ጀነራል መድፍ ስሪንቃ አንዳይ መትር የሁለት ግለሰቦች ቤት ሙሉ ለሙሉ ወድሟል ሲወድም 3 ንፁሀን ከፋተኛ ቁስለኛ ሁነዋል። ከዚህ በተጨማሪም አንድ አካባቢ ላይ ብቻ ከ28 በላይ የመድፍ ቅምቡላ የተጣለ ሲሆን የኮሰሮ ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን በከባድ መሳሪያ ጉዳት ደርሶበታል::

"ህልዉናችን በተባበረ ክንዳችን።"
ወሎ ቤተ-አምሐራ
ጥር 9/2017 ዓ.ም




ቀን09/05/2017 ዓ.ም
የድል ዜና
የአማራ ፋኖ በጎጃም ፩ኛ ክፍለጦር ኮሎኔል ታደሰ ሙሉነህ ብርጌድ አለማየሁ ከቤ ሻለቃ በአንድ ሻንበል ጦር ከገርጨጭ ከዳጊ በመውጣት ወደ አጉጋ የተንቀሳቀሰውን የዘራፊ ስብስብ ሙትና ቁስለኛ አድርጋ መልሳዋለች። በውጊውም ያለምንም መስዋትነት 3 አስክሬንና 7 ቁስለኛ በማድረግ መልሳዋለች። በሌላ በኩል ከጥር 1/2017 ዓ.ም እስከ ጥር 8/2017 ዓ.ም ድረስ 30 የጠላት ሀይል ለአማራ ፋኖ በጎጃም ፩ኛ ክፍለ ጦር ውስጥ ላሉ ሻለቃዎች እጃቸውን ሰጥተዋል ሲለሸ ሙሉሰው የኔአባት የአማራ ፋኖ በጎጃም ፩ኛ ክፍለ ጦር ህዝብ ግንኙነት ለአሻራ ሚዲያ ገልጿል።


የ3ቀን የተጠቃለለ መረጃ
ከቀን 07/05/2017-09/05/2017 ዓ.ም ለተከታታይ ሦስት ቀናት በኤፍራታና ግድም ወረዳ አፄ-ይኩኑአምላክ ክ/ጦር እና 7ለ70 ክፍለጦር በጋራ በሰሩት ልዩ ኦፕሬሽን 7ለ70 ክ/ጦር ወደ አላላ ለመግባት የሞከረውን የጠላት ሀይል ለ2ቀን ሲፋለም ቆይቶ ጠላት ሽንፈቱን ተቀብሎ ወደ ሰንበቴ እና ወደ ጅሌ ጥሙጋ ከነቁስለኛውና ከነ እሬሳው እዲፈረጥጥ ተደርጓል ።
በሌላ በኩል በዚሁ እለት በአጣዬ በኩል ወደ በርግቢና ይሙሎ ቀጠና በመጓዝ ኣላላ ለመግባት የሞከረውን የሚኒሻ፣የአድማበታኝና የመከላከያን ሀይል አፄ ይኩኑ አምላክ ክ/ጦር ሻለቃ 5 (አምስት) በቆረጣ በመግባት የመጣውን ጠላት በሙሉ አጣዬ ከተማ በማስገባት በምሽጉ አስገብቶ የሀይል ማዛባት ስራ በመስራት ና ከጠላት ግብዓት ለማግኘት ተችሏል።
በዚሁ ዕለት የመሀል ሜዳው የጠላት ሀይል ወደ በርግቢ ለመገስገስ ሞክሮ የአፄ ይኩኑ አምላክ ክ/ጦር ሻለቃ 4(አራት) በአርብ ገበያ በኩል ዲጃ ቀጠና አስፍቶ ደፈጣ በመውጣት የጠላትን ሀይል ወደ መጣበት እዲመለስ በማድረግ ሁለቱ ክ/ጦሮች የጋራ ድላቸውን አጣጥመዋል።
ሆኖም ይህ የጋራ ኦፕሬሽን እና መልካም ድላቸው ያበሳጨው የጠላት ሀይል በቀን 09/05/2017 ዓ.ም ከጠዋቱ 2:00 ሰዓት ጀምሮ በላይኛው አጣዬ አደሮ ጉባ ልዩ ስሙ ከርካሜ በተባለ ቦታ ሚኒሻን፣አድማ በታኝንና መከላከያን በማቀናጀት የመንግስት ሰራተኞችን እንዲመሩ በማድረግ ሀይሉን አጠናክሮ አስፍቶ ቢመጣም ከአፄ ይኩኑ አምላክ ክ/ጦር 5ኛ ሻለቃ እና ከ7ለ70 ክ/ጦር ከስበር ሻለቃ አንድ ሻምበል በመሆን ድባቅ እየመቱት ይገኛል።
በሌላ ዜና ከቀን 08-9/05/2017 ዓ.ም የነጎድጓዱ ክ/ጦር ጋተው ብርጌድ በባሶና ወረና ወረዳ ከደ/ብርሀን በቅርብ ርቀት ላይ በሚገኙት ድቡትና ፅጌረዳ ቀበሌዎች ጠላት ሀይሉን አጠናክሮ ና አስፍቶ በመምጣት ከባድ መሳሪያዎችን በመጠቀም ውጊያ የጀመረ ቢሆንም የወገን ጦር በቆረጣ በመግባት ወደ መጣበት አንገቱን ደፍቶ እዲመለስ አድርጎታልል። በዚህ የተነሳ የጠላት ሀይል ተስፋ በመቁሰጡ እየከዳ ወደ ወገን ሀይል ከነ
ሙሉ ትጥቁ ሲቀላቀል ውሏል።
በተያያዘ መረጃ ከአሳግርት ወረዳ ጊናገር ከተማ ተነስቶ ወደ አሳግርት ከተማ ሊገሰግስ የነበረ የጠላት ኃይል የከሠም ክ/ጦር ፊትአውራሪ አስማረ ብርጌድ አናብስቶች ምንም አይነት ተኩስ ሳይጀምር እዲመለስ አድርጎታል።
በሌላኛው የጠላት እንቅስቃሴ ሙከራ ከመራቤቴ በኩል ተንቀሳቅሶ ወደ ኮላሽ ቀበሌ ያቀና ቢሆንም የናደው ክ/ጦር ዝግጁነትን መረጃ ሲደርሰው ያለምንም የተኩስ ሙከራ ወደ መጣበት ሊመለስ ችሏል።
ክብር ለተሰውት
"ድላችን በክንዳችን"
የአማራ ፋኖ በሸዋ የህዝብ ግንኙነት ክፍል


ጥር 09/2017 ዓ.ም
በወቅታዊ ጉዳይ ከጉና ክ/ጦር የተሰጠ መግለጫ///
የኅልውና ትግላችንን ከጠንጋራ አስተሳሰብ አራማጆች የመጠበቅ ታሪካዊ ኃላፊነት አለብን!!!
አማራን በማንነቱ ምክንያት በጠላትነት ፈርጆ የተነሳው የብልጽግና ሥርዓት የሥልጣን መደላድሉን፣ የሃገረ መንግሥት ሥሪቱን ያደላደለው በጸረ አማራነት አስተሳሰብ ላይ የተዋቀረ ሕዝብን በጠላትነት ፈርጆ የዘር ማጥፋት ግብሩን በመንግሥታዊ መዋቅር እያስፈጸመ የሚገኝ ሥርዓት ነው። የክፉም የመልካምም ሥራ መቅድሙ አስተሳሰብ ነው። አማራን እንደሕዝብ የዘር ማጥፋት ድርጊት እየፈጸመ የሚገኘው ሥርዓት አስተሳሰቡ ትናንት በነጻ አውጭነት ስም ጫካ ውስጥ የተጸነሰ አጋጣሚውን ሲያገኝ በሥልጣን የተወለደ፣ በመንግሥት መዋቅር አድጎ ስሁት አስተሳሰቡን ጠላት በሚለው የአማራ ሕዝብ ላይ በገሐድ እየፈጸመ ያለ ስለመሆኑ የአደባባይ ሐቅ ነው።
አማራው ኅልውናው እንዳይጠፋ፣ ሰብዓዊ ክብሩ እንዲረጋገጥ፣ ነጻነትና እኩልነቱ እንዲረጋገጥ ታላሚ ባደረገ ሐቀኛ የኅልውና ትግላችን ውስጥ የበቀሉ የትግላችን ሾተላይ አስተሳሰቦች ከመጸነስ አልፈው ከትግል ዓላማችን በተጻራሪ መንገድ በገቢርም ጭምር እያየናቸው እንገኛለን። ከሕዝባችን ፍላጎት በተቃራኒ፣ ከግብና ዓላማችን ባፈነገጠ መልኩ ይልቁንም የሥርዓቱ መጠቀሚያ በሚሆን መልኩ ፍላጎቱን፣ ደስታውን፣ ሕይወቱን ለአማራ ሕዝብ ገብሮ ጫካ የሚገኘውን የኅልውና ታጋይ አንድነትና መስተጋብር የሚንዱ ተግባራት እጅ እግር አውጥተው ክፍለ ጦራችንን እና ትግላችንን ከትናንት እስከ ዛሬ እየፈተኑ ይገኛሉ። በትግል ሜዳ የግል ፍላጎት ቦታ የለውም፤ በትግል ሜዳ መለያዬት የግጭትና የመጠፋፋት መንገድ መሆን የለበትም፤ በትግል ሜዳ አደረጃጀቶችን በተሳሳተ መንገድ ለግል የፖለቲካ ፍጆታ መጠቀሚያነት ማፍረስ ጸረ አማራነት እንጅ የኅልውና ትግላችን ካንሰር ነው።
እንዲህ ያሉ አስተሳሰቦች የወለዷቸው ችግሮችን ለመግራትና ለማረም ጊዜ ወስደን መክረናል፤ ትግላችን ላይ ብቻ እንድናተኩርም አቅጣጫዎችን ሰጥተናል። በተለይ ደግሞ የጉና ክፍለ ጦር በሚንቀሳቀስባቸው ቀጠናዎች የፋይናንስ ተቋማትን የመዝረፍ፣ ግብራቸው የጠላት ግን የፋኖን ጭንብል በለበሱ የኅልውና ትግላችን ነቀርሳዎች ማኅበረሰብን በማሳቀቅ ፋኖን ከሕዝብ የመነጠል ልዩ ልዩ እንቅስቃሴዎች የተከናወኑ ሲሆን በክፍለ ጦራችን ልዩ ኦፕሬሽን እየተሠራ መፍትሄ ስናበጅ መቆየታችንም ይታወቃል።
ጉና ክፍለ ጦር የተቋማችን የአማራ ፋኖ በጎንደርን ተቋማዊ አሠራር አክብሮ የሚንቀሳቀስ በቀጠናው ከሚገኙ አደረጃጀቶች ጋር ተቀናጅቶ ጠላትን ቅስም የሚሰብር የጽኑ ጀግኖች አደረጃጀት፣ ከምንም በላይ ትግላችን በጀግንነት የተሰውትን አደራ ለደቂቃም ሳይዘነጋ በየእለቱ አደረጃጀቱን እያሰፋ የጠላት መጋኛ መሆኑ በውል እየታወቀ አደረጃጀታችንን ለማፍረስ እንቅልፍ አልባ ሰይጣናዊ ቀናተኞች አሁንም አርፈው አልተቀመጡልንም። እነዚህ አካላት ባለማወቅ ቢሆን ትናንት ተመክረው እንዲመለሱ ሲደረጉ እንዲህ ባለ እኩይ ግብራቸው ባልቀጠሉ ነበር፤ ከቀጠናችን አንድም ከአደረጃጀታችን ከምንም በላይ ከትግል ሐቀኛ እሳቤያችን አፈንግጠው ከላይ የዘረዘርናቸውን አስነዋሪ ድርጊቶችን በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ መልኩ ሲፈጽሙና ሲያስፈጽሙ የነበሩ ባለዲግሪ ደናቁርት ተልዕኮ ሰጭነት በብርቱ እየፈተኑን ቢገኙም ከተቋማችን ከፍተኛ አመራሮች ጋር በወጉ መክረን ነገሮችን ለማስተካከል ሌት ተቀን በመድከም ላይ እንገኛለን። እነዚህ አካላት የጉና ክፍለ ጦር የብርጌድ አደረጃጀት ውስጥ የሚገኙ ሁለት ሻለቃዎችን ወስደው የክፍለ ጦር ስያሜ ሰጥተው ጉና ክፍለጦርን ለማፍረስ የሄዱበት የጥፋት መንገድ ሙሉ በሙሉ በጀግኖቹ ከሽፏል። ድርጊቱ የትናንቱ ፋሕፍዴን፣ ሕዝባዊ ግንባር ጥምረት ወለዱ ሕዝባዊ ድርጅት የሚባል አደረጃጀት አመራሮች ስምሪት የሰጡበት ነውረኛ ተግባር ነው።
ስለሆነም የጉና ክፍለ ጦር አመራሮችን ትናንት ጠላት ሲያሳድዳቸው የኖሩ የጠላት ማርከሻዎችን ዛሬ ደግሞ ራስ ጋይንት፣ ገብርዬ፣ ጄኔራል ነጋ በሚል የክ/ጦር ስያሜ የሚንቀሳቀሱ ወንድም ያልናቸው አካላት በጉና ክ/ጦር ቀጠና አስነዋሪውን የጥፋት ተግባር እየፈጸሙ ይገኛሉ። የድርጊቱ መሪዎችም ከፍያለው ደሴ፣ አዲሱ ደባልቄ፣ ጸዳሉ ደሴ፣ እያሱ አባተ እና ጌታ አስራደ ዋነኞቹ ናቸው። ስለሆነም ይህንን አስነዋሪ ድርጊት የሚዲያ አካላት እንድታወግዙልን እና ለሕዝብ እንድትገልጹልን አደራ እንላለን፤ ከምንም በላይ የክፍለ ጦራችንን የአሥተዳደር ቀጠናም በአስቸኳይ ለቀው እንዲወጡ ጥብቅ መልእክታችንን ለማስተላለፍ እንወዳለን።.
ኅልውናችን በተባበረ አንድነታችን!!!
ጉና ክፍለ ጦር


ሰበር ዜና!

ካላኮርማ ክፍለጦር በቅሎ ማነቂያ እና ድልብ ላይ ታላቅ ድል ተጎናፀፈ::

የአማራ ፋኖ በወሎ ምስራቅ አማራ ኮር 2 ካላኮርማ ክፍለጦር 3ኛ ሻለቃ ትናትና ጥር 8/2017 ዓ.ም ማለዳ ድልብ ያለው ጠላት ከሳንቃ ስድስት ኦራል እና አንድ ፓትሮል ሰራዊት ተጨምሮት ወሳኝ ወታደራዊ ቦታ የሆነዉን  በቅሎ ማነቂያን ለመቆጣጠር የመጣን ጠላት አይቀጡ ቅጣት ቀጥተው ወደ መጣበት መልሰው ይዞታቸዉን አስከብረዋል::

በዚህ ውጊያ የአገዛዙን ወታደር 10 ሙትና 15 ቁስለኛ ማድረግ መቻሉን ለማወቅ ተችሏል።

ንጋት ጀምሮ እስከ ምሽት በዋለው ተጋድሎ በርካታ ዙፋን ጠባቂ ሰራዊት ሙትና ቁስለኛ ሆኖ ድልብ የነበረበትን በከፊል የለቀቀ ሲሆን ገሚሱ ወደ ሳንቃ ሙትና ቁስለኛዉን ይዞ ተመልሷል ሲል የካላኮርማ ክፍለጦር ህዝብ ግንኙነት ፋኖ አታሎ ፈንታ ገልፇል::

መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልዉና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!

ድል ለአማራ ህዝብ
የአማራ ፋኖ በወሎ
ወሎ ቤተ-አምሐራ
ጥር 9/2017 ዓ.ም


ለሚመለከተው ሁሉ!

የአማራ ትግል ያሸንፋል!!
[ተቋማዊ አሰራራችን ተጠናክሮ ይቀጥላል]

©ማርሸት ፀሐዩ
የአማራ ፋኖ በጎጃም
ህዝብ ግንኙነት ኃላፊ

12k 0 12 3 94

እናት ፓርቲ የጣሪያ ግድግዳ ግብር ላይ የመሠረተው ክስ ተቀባይነት ማግኘቱን አስታወቀ‼️

እናት ፓርቲ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የጣሪያ ግድግዳ (የንብረት ግብር) ብሎ ከከተማዋ ነዋሪ እየሰበበሰበ ባለው ግብር ላይ መስርቶ የነበረው ክስ ተቀባይነት ማግኘቱን ዛሬ ባወጣው መግለጫው አስታውቋል።

ፓርቲው ግብሩ "ሕገ ወጥ" መኾኑን በመግለጽ ክስ መስርቶ ነበር።

ክሱን የተመለከተው የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ አስተዳደር ችሎት በዛሬ እለት ባስቻለው ችሎት የንብረት ግብር ማሻሻያ ጥናት ተብሎ በሚያዝያ ወር 2015 ዓ/ም የወጣውና ለግብሩ መሰብሰብ መሠረት የሆነው መመሪያ "ተፈጻሚነት ሊኖረው አይገባም" ተብሎ መመሪያው እንዲሻር በሙሉ ድምጽ መወሰኑን እናት ፓርቲ አስታውቋል።

የፍርድ ሂደቱ ተፈፃሚነቱ ምን ያህል ይሆናል የሚለው ካሁኑ ብዙዎችን እያነጋገረ ቢሆንም የግድግዳ ግብር ላይ በርካታ የከተማው ነዋሪዎች ቅሬታቸውን ሲያቀርቡ ቆይተዋል።

via @MeseretMedia


ጄኔራሉ ማዕቀብ ተጣለባቸው‼️

ዩናይትድ ስቴትስ በሱዳን ጦር መሪው አብደል ፋታህ አል ቡርሃን ላይ ማዕቀብ መጣሏን በግምጃ ቤት ሚኒስቴር በኩል አስታውቃለች።

በአል-ቡርሃን ባለቤትነት የሚተዳደሩ ማንኛዉንም በአሜሪካ የሚገኝ ንብረት እንዳይንቀሳቀስ የሚያግድ እና አሜሪካውያንም ከጄነራሉ ጋር እንዳይገናኙና ንግድ እንዳይፈፅሙም ይከለክላል።

ማዕቀቡ በዚህ ወር መጀመሪያ ላይ ሄሜቲ በመባል በሚታወቁት የፈጣን ድጋፍ ሰጪ ሃይሎች (አርኤስኤፍ) መሪ መሀመድ ሃምዳን ዳጋሎ ላይ የተወሰዱ ተመሳሳይ እርምጃዎችን ተከትሎ የመጣ ነዉ፡፡


ባንዳዉ በቁጥጥር ስር ዉሏል !

በህልዉና ትግላችን ላይ ያሴረና ደባ የዋለ የትም አይደርስ

የአማራ ፋኖ በጎጃም ጎጃም አገዉ ምድር ክ/ጦር የቢትወደድ አያሌዉ አያሌዉ መኮነንን ብርጌድ እንደ አዲስ ሪፎርም ከሰራ በሆላ የዉስጥም የዉጭም አረሞችን እየነቀለ ይገኛኛል ብርጌዳችን በዉስጡ ያሉ የትግል ሶንኮፎችና ዳብል ኤጄንቶችን እየለቀመ ይገኛል በዚህም በሰረት የብርጌዱ ዘመቻ ሃላፊ የነበረዉ በማጭበርበሪያ ስሙ #ቅጣዉ በትክክለኛ ስሙ #ላቀ የተባለዉ ዳብል ኤጀንት ብርጌዱ በአደረገዉ ከፍተኛ ክትትል ከተለያዩ የመንግስት አካላትና ህገ ወጥ ቡድኖች ጋር ግንኙነት እንዳለዉ በማረጋገጥ ከዚህ ድርጊቱ እንዲቆጠብ ቢነገረዉም የአማራ ንትግል በምስር ወጥ አሳልፎ በመሸጥ በብርጌዱ ዋና #ገንዘብ ያዥ ላይ #ቦንብ በመጣል ከግብረ አበሮቹ ጋር የብርጌዱን ሃብት ዘርፎ ሊሰወር ሲል ወዲያዉኑ በስታፍ አባሎች በቁጥጥር ስር ዉሏል ከዚህ በተጨማሪ የብርጌዱን የቡድን መሳሪያና የተለያዩ ንብረቶችን የዘረፈና ትግሉ ወደ ፊት እንዳይራመድ ከጠላት ጋር ሲሰራም ተገኝቷል የወገንን አሰላለፍና ቁመና ለጠላት አሳልፎ ሲሰጥም መቆየቱ ተረጋግጧል ይህ ግለሰብ በተደጋጋሚ ከብልፅግና ሰዎች ጋር በተለያዩ የመገናኛ ዘዴዎች ከፍተኛ ግንኙነት ያለዉ መሆኑ በተጨባጭ ማስረጃ ተረጋግጧ በተደጋጋሚም በከፍተኛ የብርጌዱ አመራሮች ላይ የግድያ ሙከራ ለማድረግ ሞክሮል የተለያዩ ዘራፊ ቡድኖችን በማቋቋም አካባቢዉ ሰላም እንዳይሆን ሲሰራም ተገኝቷል ይህንን ዳብል ኤጀንት ብርጌዱ በቁጥጥር ስር ካዋለዉ በሆላ የብርጌዱ የሻለቃ መሪዎች እንዲሁም የብርጌዱ መሪዎች በመሰባሰብ ዉሳኔ አስተላልፈዋል በዚህም መሰረት ይንን ባለ ሁለት ካራ ባንዳ (ከሀዲ)
1_ከሃላፊነት ተነስቷል
2_ ከአባልነት ተሰናብቷል ከዚህ በተጨማሪ ባንዳዉ #ላቀ (ቅጣዉ) ከብርጌዱ የዘረፋቸዉን ንብረቶች እንዲመልስ ዉሳኔ ተላልፎል ባንዳዉም በእስር ላይም ይገኛል ............

በመጨረሻም ይህ ትግል ብዙ መስዓዉትነት እየተከፈለበት ያለ የህልዉና ትግል ነዉ ስለሆነም በዚህ ትግል ላይ በባንዳነት፣በከሀዲነት እና በተለያዩ ወንጀሎች ዉስጥ ተሰማርቶ የተገኘ ማንኛዉም አካል ለትግሉ መስዓዉትነት በከፈሉ ጎዶቻችን ላይ እንደመቀለድ አርገን እንወስደዋለን ስለዚህ ማንኛዉም በእንደዚህ አይነት ድርጊት ዉስጥ ተሰማርቶ የተገኘ አካል ላይ ጨከን ያለ ርምጃ ብርጌዳችን እንደሚወስድ እናረጋግጣለን

የዉስጥም የዉጭም ባንዳ ምንጠራ ይቀጥላል ......

አማራነት አሸናፊነት



Показано 20 последних публикаций.