Фильтр публикаций


ህዝባዊ አደረጃጀት'ና........!

የአማራ ፋኖ በጎጃም ጎጃም አገዉ ምድር (3ኛ) ክ/ጦር በፋ/ለ/ወ ፲/አ ኤፍሬም አጥናፉ ብርጌድ በሚያስተዳድራቸው 28 ቀበሌዎች ዉስጥ ባለፉት 3 ወራት  የተሰሩ የህዝብ አደረጃጀቶች'ና የተደረጉ የህዝብ መድረኮች በሚል ዛሬ መጋቢት 01/2017 ዓ/ም የብርጌዷ ስራ አስፈፃሚ አመራሮች ጥልቅ የሆነ የስራ ግምገማ አድርገናል።

በዛሬዉ የስራ ግምገማው ወቅት ከቀረቡ አስተያየቶች መካከል የብርጌዷ አደረጃጀት ዘርፍ ሀላፊ ፋኖ አንድነት ፀጋ እንደገለፀዉ
"ህዝባዊ አደረጃጀትን ከሌሎች ስራዎች ሁሉ አስቀድመን ከምንሰራበት ምክኒያቶች አንዱ
የፋኖን ስራ ለማቅለል'ና  ቀጥተኛ የትግሉ ባለቤት በመሆን ትግሉን በተገቢዉ  መጠን ለመደገፍ ህዝባዊ አደረጃጀት የግድ እንደሆነ ህዝባችን በአግባቡ ተረድቶ አደረጃጀቱ ፈጥኖ እንዲሰራለት ቀን ከሌት አበክሮ በመጠየቁ ምክኒያት ሲሆን
በሁለተኛ ደረጃም ድርጅታችን የአማራ ፋኖ በጎጃም እያስተዳደረዉ ካለዉ  ህዝብ ጋር በመተሳሰር'ና በቀላሉ ተደራሽ በመሆን ለህዝብ ጠቃሚ የሆኑ የልማት ጥያቄዎችን ጨምሮ የትኛውንም አይነት ኩነቶች በፍጥነት ለመተግበር ህዝባዊ አደረጃጀቶች ግድ በመሆናቸዉ ነዉ!  ሲል አብራርቷል።

በሌላ በኩልም
"ከፖለቲካ ክንፍ ተቀዳሚ ግዴታዎች አንዱ:-
  ወቅት'ና ሁኔታዎችን እየመዘነ ለአማራ ህዝብ የህልዉና ታጋዮች (ፋኖ ሰራዊት) ከሚሰጠዉ ወቅቱን የጠበቀ ትምህርት እኩል ህዝባዊ መድረኮችን በመፍጠር ሁለቱ ዋና የትግሉ ባለቤቶች ማለትም የአማራ ህዝብ'ና የአማራ ፋኖ በተመሳሳይ የትግል አረዳድ በአንድ ድርጅታዊ መስመር የሚጓዙበትን መንገድ ጠርጎ በማዘጋጀት  ትግሉ ወደ  ሚሄድበት የድል መንደር እኩል በሆነ ሁኔታ ማድረስ ነዉ።  ያለዉ  የ፲/አ  ኤፍሬም አጥናፉ ብርጌድ ፖለቲካ ክንፍ ሀላፊ ፋኖ ነፃነት ከበደ ባደረጋቸዉ ህዝባዊ መድረኮች ሁሉ የገጠመዉን ሁኔታ ሲገልፅ
  የህዝባችንን ፖለቲካዊ አረዳድ ከአታጋያችን የአማራ ፋኖ በጎጃም ድርጅታዊ መርህና አሰራር አንፃር ስናየዉ ህዝባችን የትግሉን መነሻ'ና መድረሻ  በአግባቡ የተረዳ'ና ጠላቱን በአግባቡ በማወቁ   ነፍጥ አንስተን እየተፋለምነ  ካለነዉ የአማራ ፋኖ አደረጃጀቶች ባልተናነሰ ሁኔታ የብልጽግናን ስርዐት ሲፋለም የቆየ'ና እየተፋለመ የሚገኝ ቀጣይም ለዚህ የህልዉና ትግል ሁሉ ነገሩን ለመስጠት የተዘጋጀ ሁኖ አጊንተነዋል ብሏል።"

እንዲሁም ከማህበራዊ ፀፅታ አኳያ አስተያየቷን ያስቀመጠችዉ የ፲/አ ኤፍሬም አጥናፉ ብርጌድ ማህበራዊ ፀፅታ ዘርፍ ሀላፊ ፋኒት ወጋየሁ ጥላሁን እንደነገረችን:-

"ይህ የአማራ ህልዉና ትግል  ከጨርሶ መጥፋት አደጋ ለመትረፍ ሲል ነፍጥ አንስቶ መታገል ከጀመረበት ስዓት ጀምሮ ለአለፉት አንድ አመት ከሰባት ወር ገደማ ማህበራዊ ቀዉሶች'ና ግለሰባዊ ግጭቶች በከፍተኛ ሁኔታ መቀነሳቸዉን ማረጋገጥ ችለናል። ይህ የሆነበትን ገፊ ምክኒያት ለማወቅ በአደረግነዉ ዳታ የማሰባሰብ ሂደት ያገኘነዉ ዉጤት የሚነግረንም
ህዝባችን ለትግሉ እንቅፋት የሚሆኑ ነገሮችን ከማስወገድ አኳያ ሰፊ ስራዎችን በመስራት ጤናማ የሆነ ማህበራዊ ግንኙነት መፍጠር መዉደዱ እንደሆነ'ና
ይህ ዉጤት የተገኘዉም እንደዚህ አይነት መስተጋብር  እንዲመጣ ትግላችን በወሰደዉ ወንጀልን የማጥፋት ቁርጠኝነት  ወንጀልን ተፀያፊ ማህበረሰብ  መፍጠር መቻሉ  ሁኖ አጊንተነዋል ብላለች።"

አዲስ ትዉልድ! አዲስ አስተሳሰብ! አዲስ ተስፋ!!!
ድል ለአማራ ፋኖ!!!

ትግሉ በፍጥነት ወደ መዳረሻው እየተምዘገዘገ ነዉ!!!

ፋኖ ተሻገር አደመ ከ፲/አ ኤፍሬም አጥናፉ ብርጌድ ህ/ግንኙነት
መጋቢት 1/2017 ዓ/ም


ተቋማችንን ከጠላት ሰርጎ ገብ እጆች የማፅዳቱ ስራ ተጠናክሮ ቀጥሏል ።

ከአማራ ፋኖ በጎጃም 3ተኛ ጎጃም አገው ምድር ክ/ጦር ቢትወደድ መንገሻ ጀምበሬ ብርጌድ ለተከበረው ህዝባችን በወቅታዊ ጉዳይ ላይ የተሰጠ  ማብራሪያ ።

ትግላችን በርካታ የትግል የእድገት ደረጃዎችን አልፎ አሁን የመታደስ ምእራፍ ላይ ደርሷል ። አስካሁን የመነሳት የማደግ አታጋይ መሪ እና ድርጅት የመፍጠሩን ሒደት በብቃት ተወጠነዋል በዚህ ሁሉ ውስጥ አለምን ያስደመሙ ጠላትን እራሱ እስኪገርመው ድረስ ሰብረናቸዋል ባሉ ማግስት አማራ ራሱን አደራድቶ የጠላቱን አከርካሪ ሰብርሮ ጨፍጫፊው ሀይል ተመልሶ መንግስት መሆን ወደማይችልበት ደረጃ ላይ አድርሰነዋል ።

አሁን ትግላችን የመታደስ ምእራፍ ላይ ደርሷል  በዚህ ምእራፍ ውስጠ ድርጅት አንድነታችንን እየፈተሽን ጠላት ወደ ውስጣችን አስርጎ ያስገባቸውን አንደኛ በፋኖ ስም ተደራጅተው በውስጣችን ገብተው የሚሰርቁ (የሚዘርፉ) ሁለተኛ ለጠላት መረጃ በመስጠት የወገንን ሀይል ለማዳከም የሚያሴሩ ባንዳዎችን ህጋዊ እርምዳ የመውሰድ ስራ እየሰራን እንገኛለን ።  በዚህም የጥናታችን ኢላማዎች (የውስጥ ባንዳዎች) ወደ ላካቸው (አገዛዙ ) እየሔዱ እንደሚቀላቀሉ ቀድሞም ወደዚህ ስራ ስንገባ የገመትነው ነበር እየሆነም ነው ።

ይህ ሲሆን ፋኖ እጅ ሰጠ የሚል ፕሮፖጋንዳ በመንዛት ማዲያዎቻቸውን እያስጮሁ ይገኛሉ ። ለዚህም ማሳያ ዛሬ በማለትም መጋቢት 2/2017ዓ.ም አንድ ትዝዙ ስሜነህ(ወገቤ) የተባለ የቢትወደድ መንገሻ ጀምበሬ ብርጌድ አባል አገዛዙን ተቀላቀለ የሚል ተራ የፕሮፖጋንዳ ሲያስተጋባ ሰምተናል ግለሰቡ ከአንድ አሁን በፋኖ ጥናት ለጠላት መረጃ ሲያቃብል እጅ ከፈንጅ ከተያዘ ግብራበሩ ጋር በመሆን የጠላት የውስጥ ክንፍ በመሆን ሲሰራ ስለተደረሰት ወደ ላኪዎቹ እና ከፋዮቹ የብልፅግና ሰወች ጋር ተቀላቅሏል  በቅፅል ስሙ "ወገቤ"(ትዛዙ ስሜነህ) በግዳጅ ወቅት ፈሪ ሁሌም ወገቤን አመመኝ እራሴን አመመኝ በማለት ራሱን ከግዳጅ ስለሚያርቅ ጦሩ ወገቤ እያለ የሚጠራው እዚህ ግባ የማይባል ሆዳም ስለሆነ ጦራችንን መልቀቁ አንድም ትልቅ አረፍታችን ነው ሌላም የጀመርነውን የማጥራት እና የመታደስ ምእራፍ ስኬታማነት የሚያሳይ እንጅ በፍፁም የህዝባችንን እና የደጋፊዎቻችንን ሞራል የሚነካ እንዳይሆን ለትግላችን ደጋፊዎች ማስገንዘብ እንወዳለን ።
በቅርቡ በታደሰ እና በተጠናከረ መንፈስ በለመደው እና በምንታወቅበት  ጠላትን የማንበርከክ እና የመቅጣት እስከመጨረሻው የመሸኘት አዳዲስ ዘመቻች እንገናኛለን
ድል ለህዝባችን
ዘላለማዊ ክብር ለትግሉ ሰማእታት

አዲስ ትውልድ
አዲስ አስተሳሰብ
አዲስ ተስፋ
  አማራ ፋኖ በጎጃም 3ተኛ ጎጃም አገው ምድር ክ/ጦር ቢትወደድ መንገሻ ጀምበሬ ብርጌድ ህዝብ ግንኙነት ፋኖ ምስጌ ዘድንግል




የልዩ ኮማንዶ ስልጠና ጥሪ ለአማራ ወጣቶች
መጋቢት 02 ቀን 2017 ዓ.ም

ወሎ ቤተ አማራ

እነሆ የልዩ ኮማንዶ 4ተኛ ዙር ስልጠና ለመጀመር ዝግጅታችን አጠናቀናል፤ ይህን ወርቃማ እድል መላው የአማራ ወጣት እንድጠቀምበት ስለምንፈልግ ይፋዊ ጥሪ ለማስተላለፍ ወስነናል።

ወንዝ ሳይገድብህ ጎራ ሳይከልልህ ከያለህበት ወደ ወሎ በመትመም በዘመናት አንድ ጊዜ የሚገኘውን ይህን ታሪካዊ እድል እንድትጠቀምበት ይፋዊ ጥሪ የምናስተላልፍልህ የቀድሞው የአማራ ልዩ ኃይል ኮማንዶ ዩኒት አደራጅ እና አሰልጣኝ የነበርን የጄኔራል አሳምነው ጽጌ ልጆች ነን።

የአማራ ህዝብ የተጋረጠበትን የህልውና አደጋ ቀልብሰን ህዝባችን የሰላም አየር ይተነፍስ ዘንድ የበኩላችንን ድርሻ በመወጣት የወል ማንነታችን ተከብሮ እና ነጻነትን ተጎናፅፈን ማህበራዊ እረፍትም አግኝተን በኢትዮጵያ ምድር መኖር እንድንችል ሁሉም የአማራ ልጅ የሞት ሽረት ትግሉ አካል ሊሆን እንደሚገባ ይታመናል። ነጻነት በነጻ አይገኝምና የነጻነትን ዋጋ ለመክፈል ሁላችንም መዘጋጀት ስላለብን ስልጠናውን መውሰድ ለነገ የማይባል ስራ ነው።

በተለይ ወጣቱን በስፋት ማደራጀት፣ በብቃት ማሰልጠን፣ በጥራት እና በአይነት ማስታጠቅ እና በፅናት ማታገል አስፈላጊ ስለሆነ በሁሉም ዘርፍ መነቃቃት የታየበት ስራ በመስራት ላይ እንገኛለን።

የዚሁ እንቅስቃሴያችን አካል የሆነው የምልመላ እና ስልጠና ስራን ለመከወን እድሜያቸው እና የጤና ሁኔታቸው የሚፈቅድላቸው በየትኛውም የሀገሪቱ ክፍል የሚገኙ የአማራ ልጆችን መልምለን ለማሰልጠን ስለምንፈልግ ከመጋቢት 3 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ እስከ መጋቢት 15 ቀን 2017 ዓ. ም ባለው ጊዜ ወደ አማራ ፋኖ በወሎ (ቤተ- አማራ) የጦር ሰፈር በመምጣት የስልጠና ማዕከላችን ሊሰጥ ያሰበውን የልዩ ኮማንዶ ስልጠና ወስዳችሁ ለህዝባችሁ እንባ አባሽ እና የህልውናው ዘብ የምትሆኑበትን እድል ትጠቀሙበት ዘንድ ይህን የስልጠና እና የትግል ጥሪ አቅርበንላችኋል።

ወደ ስልጠና ማዕከላችን የሚመጣ እጩ ሰልጣኝ ሊያሟላቸው የሚገቡ ቅድመ ሁኔታዎች እንደሚከተለው ተዘርዝረዋል።

1ኛ፦ የትምህርት ደረጃ (ማንበብ እና መጻፍ የሚችል/የምትችል))፣

2ኛ፦ ሙሉ ጤነኛ የሆነ እና ቁመት ከ1ሜትር ከ65 ሴንቲ ሜትር በላይ የሆነ/የሆነች፣

3ኛ፦ ከተለያዩ ደባል ሱሶች ነፃ የሆነ/የሆነች፣

4ኛ፦ የየትኛውም የፖለታካ ድርጅት አባል ያልሆነ/ያልሆነች፣

5ኛ፦ ከጎጥ አስተሳሰብ ፍፁም የፀዳ/የፀዳች፣

6ኛ፦ በተመደበበት ቦታ ለመታገል ዝግጁ የሆነ/የሆነች፣

7ኛ፦ የህልውና ትግሉ እስከሚጠናቀቅ ድረስ ለመታገል ፈቃደኛ የሆነ/የሆነች፣

8ኛ፦ ምንም አይነት የወንጀል ሪከርድ የሌለበት እና የስነ ምግባር ጉድለት እንደሌለበት ማረጋገጥ የሚችል/የምትችል፣

9ኛ፦ የትዳር ሁኔታ:- ያላገባ/ያላገባች፣

10ኛ፦ እድሜ ከ18 ዓመት በላይ፣

11ኛ፦ በፋኖ መተዳደሪያ ደንብ ለመመራት ሙሉ ፍቃደኛ የሆነ/የሆነች፣

12ኛ፦ የቀበሌ መታወቂያ ማቅረብ የሚችል/የምትችል፣

እነዚህን መስፈርቶች የምታሟሉ በአማራ ክልልም ይሁን ከአማራ ክልል ውጭ የምትኖሩ የአማራ ወጣቶች ይህ የስልጠና ማስታወቂያ ከወጣበት ዕለት ጀምሮ ከላይ እስከተጠቀሰው ቀን ድረስ ወደ ማዕከላችን መግባት እንደምትችሉ እየገለፅን የዚህ ታሪካዊ ተጋድሎ አካል እንዲትሆኑ በድጋሜ ለማስታወስ እንወዳለን።

የአማራ ፋኖ በወሎ (ቤተ አማራ) ወታደራዊ ስልጠና መምሪያ ኃላፊ መቶ አለቃ ዮሴፍ አስማረ እና የመምሪያው ም/ኃላፊ ሀምሳ አለቃ ጌታቸው ሲሳይ




ፀረ አማራዉ ተስፋ ቆርጧል!!!

ክብር ለአማራ ፋኖ በጎጃም የጎጃም አገው ምድር (3ኛ) ሶስት እረመጥ ብርጌዶች ፲/አ ኤፍሬም አጥናፉ ብርጌድ ቢትወደድ መንገሻ ጀምበሬ ብርጌድ'ና ቀኛዝማች ስሜነህ ደስታ ብርጌድ ይሁን'ና በቀን 30/06/2017 ዓ/ም ገዘኸራ ቀበሌ ላይ በ፲/አ ኤፍሬም አጥናፉ ብርጌድ ፊት አዉራሪነት በተደረገ ኦፕሬሽን ሁለት ስዓት ባልሞላ የተኩስ ልዉዉጥ 73 ግትልትል ሰራዊቱን ገና በጥዋቱ የገበረዉ እና 29 ክላሽንኮፍ መሳሪያ ከተወሰነ አጥቦ አይለብስ ጋር በለሊቱ የተማረከዉ ቀበቶ አልባዉ የፈሪወች ስብስብ ስልቡ የብልፅግና ታጣቂ ቡድን የእለት ከለት ግብሩ የሆነዉን ፀረ አማራነት ተግባር በመፈፀም በንፁሃን ወገኖቻችን ላይ ጉዳት ማድረሱን ቀጥሎበታል።

ይህ ምድር ላይ ያሉ የበቀል አይነቶችን ሁሉ በንፁሀን አማራዎች ላይ ሰርቶ የጨረሰዉ ሆድ አደሩ ባንዳ የአማራ ብልፅግና ስብስብ ለፋግታ ለኮማ ወረዳ በሰየመዉ ተወካዩ ባንዳ የእናት ጡት ነካሽ ታገል እጅጉ እየታዘዘ'ና ህሌና ቢስ የአድማ ብተና ሚሊሻና ፖሊስ አመራሮች የህልም ጉዞ ስምሪት እየተነዳ ከአዲስ ቅዳም ከፅሪጊ'ና ከጫራ በመነሳት በቀን 30/06/2017 ዓ/ም የተደመሰሰ ጓዱን ለመለቃቀም ወደ ገዘኸራ የገባዉ ቡድን በቀን 01/07/2017 ዓ/ም ከአዲስ ቅዳም 1 ሻለቃ የብርሀኑ ጁላ ተጨማሪ ጦር በማስመጣት ተጠረቃቅሞ በቀን 01/07/2017 ዓ/ም ወደ ድማማ ቀበሌ በመግባት በድማማ ማህበረሰባችን ላይ ከፍ ያለ የቁስና የስነልቦና ጥቃት ፈፅሟል።

ይህንን የሰሙት የአማራ ፋኖ በጎጃም የጎጃም አገዉ ምድር (3ኛ) ክ/ጦር በፋ/ለ/ወ ፲/አ ኤፍሬም አጥናፉ ብርጌድ ሻለቃ ፪ ተርቦች እንደ ልማዱ ሊመክሩት ቦታዉ ላይ ደርሰዉ የነበረ ሲሆን የተርቦችን መድረስ የተረዳው ጠላትም የይካቲት 30/2017 ዓ/ም የተርቦች አመካከር ዘዴ ምን ይመስል እንደነበረ አስታውሶ ቀደም ሲል ገና በጥዋቱ ከአቃጠለዉ የ9 ግለሰቦች ሙሉ የቤት እቃ በተጨማሪ 3 ግለሰቦች ቤት ዉስጥ የነበረ ለአመታዊ ክብረ በአል ድግስ የተዘጋጀ የጠላ ድፍድፍን ከእርጎ ጋር በመቀላቀል እግሬ አዉጭኝ ብሎ ወደ መጣበት ፈርጥጧል።

አዲስ ትዉልድ! አዲስ አስተሳሰብ! አዲስ ተስፋ!!!
ድል ለአማራ ፋኖ!!!

ትግሉ በአዲስ ፍጥነት ወደ መዳረሻው እየተምዘገዘገ ነዉ!!!

ሲል ፋኖ ተሻገር አደመ ከ፲/አ ኤፍሬም አጥናፉ ብርጌድ ህ/ግንኙነት ገልፆል

ፋኖ ይበልጣል የዉነቱ የጎጃም አገዉ ምድር ክ/ጦር የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ




የአማራ ፋኖ በጎጃም የ24 ስዓት አበይት ሁነቶች፦

ሀ. የአብይ አሕመድ አሸባሪ አገዛዝ ንፁሃንን ጨፈጨፈ

የዐቢይ አሕመድ ጨፍጫፊ ሠራዊት መንገድ ሥራ ላይ የነበረውን አንድ የማሽን ኦፕሬተር ገሏል።
ከጅጋ_ገበዘማርያም_ዓርብ ገበያ_ግብ ዓባይ_ቲሊሊ የአስፓልት መንገድ ፕሮጀክት ሥራ ላይ የነበረውን የከባድ ማሽን ኦፕሬተር በዛሬው ዕለት ገድለውታል።
ይህ ስርዓት አማራው መሰረተ ልማት አንዳይኖረው በተገኘው አጋጣሚ ሁሉ እያወደመ ይገኛል፤ በደረሰበት ሁሉ ትምህርት ቤቶችን እያፈረሰ ከዚያም ሲዘል እንደካምፕ አየተጠቀመ ይገኛል። ይህ ስርዓት ፋኖ በተቆጣጠራቸው አካባቢ ያሉ ጤና ጣቢያዎቸ መድሃኒት በመከልከል ህዝብን በበሽታ የመጨረስ አላማ ነው ያለው።
በመሆኑም በዚህ ሳምንት ብቻ በምዕራብ ጎጃም ዞን ገነት አቦ የሚገኘውን ማህበረሰብ ቡቲክስሶች ፣ጫማ ቤቶችን፣ ሆቴሎችን ፣ ሞባይል ቤቶችን፣ኤሌክትሮኒክስ ቤቶችን ፣ ሞተር ሳይክሎችን ዘርፏል፣ አቃጥሏል።በአጠቃላይ ከ20 በላይ ሱቆችንንና ሆቴሎችን በመዝረፋ አሳፋሪ ስራ ሰርቷል።

በተመሳሳይ ሁኔታ በትናንትናው ዕለት በደጋዳሞት ወረዳ ዝቋላ ወገም ቀበሌ ወገም ጊወርጊስ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ የተለመደውን ሀይማኖታዊ ክዋኔ በመፈፀም ላይ ያሉ ከ20 በላይ አርሶአደሮችን የአገዛዙ ዙፋን ጠባቂ ሰራዊት በማፈስ ወደ ፈረስ ቤት ከተማ የወሰዷቸው ሲሆን ለከተማው ማህበረሰብም የፋኖ ታጣቂዎችን ማርከን መጣን የሚል ተራ ፕሮፓጋንዳ እየነዛ ይገኛል።

ለ. አውደ ውጊያ

1. ራስ ቢትወደድ መንገሻ አቲከም 5 ኛ ክፍለጦር ገረመው ወንዳውክ ብርጌድ ጠላትን ደመሰሰ።
ገረመው ወንዳውክ ብርጌድ የካቲት 29 እና 30/2017 ዓ.ም ምሽት ድረስ በወሰደው ድንገተኛ እርምጃ ከ20 በላይ የአገዛዙ ሠራዊት አባላት ሲሸኙ በርካቶቹ ቁስለኛ ሁነዋል።
ሦስት ሚሊሻዎች በጦርነቱ እስከ ወዲያኛው የተሸኙ ሲሆን፤ በከባድ ሁኔታ መቁሰሉ የተረጋገጠው አንድ ሚሊሻ ደግሞ መሞቱ ተሰምቷል።
ቋሪትን ለመውረር ግዳጅ ተሰጥቶት ጉዞ ከጀመረ አራት ቀናት ያሳለፈው ጨፍጫፊው ሠራዊት ገነት አቦን አልፎ የነበረ ቢሆንም ጀግኖቹ ወደ መጣበት እያስፈረጠጡት ይገኛሉ።

2. ጎጃም አገውምድር 3ኛ ክፍለጦር ፲ አለቃ ኤፍሬም አጥናፉ ብርጌድ የተሳካ የደፈጣ ጥቃት ፈፀመ።

ኤፍሬም አጥናፉ ብርጌድ ደፈጣ በመያዝ የአገዛዙ ሎሌዎችን አመድ አድርጋለች ከአዲስቅዳም ወደ አሸዋ ጉዞ ሲያደረግ የነበረ ዲሽቃ የጫነ 1 ፓትሮል በኤፍሬም አጥናፉ ብርጌድ ልጆች አሸዋ ላይ በደፈጣ ሲመታ መኪናዋ ተገልብጣ 6 ሰዎች ወደ ላይኛዉ ሲላኩ ዲሽቃዉን ከጥቅም ዉጭ ማድረግ ተችሏል።

ፎቶ2:- ከቤተክርስቲያን ታፍነው የተወሰዱ አርሶ አደሮች ናቸው።

አዲስ ትውልድ፣ አዲስ አስተሳሰብ፣ አዲስ ተስፋ!

[የአማራ ፋኖ በጎጃም]
መጋቢት 1/ 2017 ዓ.ም


ፀረ አማራዉ  ተስፋ ቆርጧል!!!

ክብር ለአማራ ፋኖ  በጎጃም የጎጃም አገው ምድር (3ኛ)  ሶስት እረመጥ ብርጌዶች  ፲/አ ኤፍሬም አጥናፉ ብርጌድ ቢትወደድ መንገሻ ጀምበሬ ብርጌድ'ና ቀኛዝማች ስሜነህ ደስታ ብርጌድ ይሁን'ና በቀን 30/06/2017 ዓ/ም ገዘኸራ ቀበሌ ላይ በ፲/አ ኤፍሬም አጥናፉ ብርጌድ ፊት አዉራሪነት በተደረገ ኦፕሬሽን ሁለት ስዓት ባልሞላ የተኩስ ልዉዉጥ  73 ግትልትል ሰራዊቱን ገና በጥዋቱ የገበረዉ እና 29 ክላሽንኮፍ መሳሪያ ከተወሰነ አጥቦ አይለብስ ጋር በለሊቱ የተማረከዉ   ቀበቶ አልባዉ የፈሪወች ስብስብ ስልቡ  የብልፅግና ታጣቂ ቡድን የእለት ከለት ግብሩ የሆነዉን ፀረ አማራነት ተግባር በመፈፀም በንፁሃን ወገኖቻችን ላይ ጉዳት ማድረሱን ቀጥሎበታል።

ይህ ምድር ላይ ያሉ የበቀል አይነቶችን ሁሉ በንፁሀን አማራዎች ላይ ሰርቶ የጨረሰዉ ሆድ አደሩ ባንዳ የአማራ ብልፅግና ስብስብ ለፋግታ ለኮማ ወረዳ  በሰየመዉ ተወካዩ ባንዳ የእናት ጡት ነካሽ ታገል እጅጉ እየታዘዘ'ና ህሌና ቢስ የአድማ ብተና ሚሊሻና ፖሊስ አመራሮች የህልም ጉዞ ስምሪት እየተነዳ  ከአዲስ ቅዳም ከፅሪጊ'ና ከጫራ በመነሳት በቀን 30/06/2017 ዓ/ም የተደመሰሰ ጓዱን ለመለቃቀም ወደ ገዘኸራ የገባዉ ቡድን በቀን 01/07/2017 ዓ/ም ከአዲስ ቅዳም 1 ሻለቃ  የብርሀኑ ጁላ ተጨማሪ ጦር በማስመጣት ተጠረቃቅሞ  በቀን 01/07/2017 ዓ/ም ወደ ድማማ ቀበሌ በመግባት  በድማማ ማህበረሰባችን ላይ ከፍ ያለ የቁስና የስነልቦና ጥቃት ፈፅሟል።

ይህንን የሰሙት የአማራ ፋኖ በጎጃም የጎጃም አገዉ ምድር (3ኛ) ክ/ጦር በፋ/ለ/ወ ፲/አ ኤፍሬም አጥናፉ ብርጌድ ሻለቃ ፪ ተርቦች እንደ ልማዱ ሊመክሩት ቦታዉ ላይ ደርሰዉ የነበረ ሲሆን  የተርቦችን መድረስ የተረዳው ጠላትም የይካቲት 30/2017 ዓ/ም የተርቦች አመካከር ዘዴ ምን ይመስል እንደነበረ  አስታውሶ ቀደም ሲል ገና በጥዋቱ ከአቃጠለዉ የ9 ግለሰቦች ሙሉ የቤት እቃ በተጨማሪ  3 ግለሰቦች ቤት ዉስጥ የነበረ ለአመታዊ  ክብረ በአል ድግስ የተዘጋጀ የጠላ ድፍድፍን  ከእርጎ ጋር በመቀላቀል እግሬ አዉጭኝ ብሎ ወደ መጣበት ፈርጥጧል።

አዲስ ትዉልድ! አዲስ አስተሳሰብ! አዲስ ተስፋ!!!
ድል ለአማራ ፋኖ!!!

ትግሉ በአዲስ ፍጥነት ወደ መዳረሻው እየተምዘገዘገ ነዉ!!!

ፋኖ ተሻገር አደመ ከ፲/አ ኤፍሬም አጥናፉ ብርጌድ ህ/ግንኙነት




ሰበር ዜና!

የመረሐቤቴ ወረዳ አገሪት ቁማባ ቀበሌ ሊቀመንበር አቶ ገለታው ደለለኝ ተሸኘ!

አለባብሰው ቢያርሱ በአረም ይመለሱ ይላሉ አበው፣ በአንድ ድንጋይ ሁለት ወፍ የጥቁር ናዚው የአብይ አህመድ ስልጣን አስጠባቂ ጋሻጃግሬው ሰራዊት  የገምሹ በየነን መንገድ ስራ ማህበር በመረሐቤቴ አውራጃ እና አካባቢው ከመንገዶች ባለስልጣን ለመስራት ውል መፈፀሙ ይታወቃል።

ስለሆነም መንገድ መስራቱን አቆርጦ ከአገዛዙ ተደራድሮ  ንብረቱን በአገዛዙ ሰራዊት አስጠብቆ ከመርሐቤቴ ወደ ለሚ  ጀማን አቋርጦ በሄደበት ሰአት ልዩ ጥናት ክትትል በማድረግ ኮኮብመስክ የተባለ ቀበሌ ላይ ድንገት የናደው ክፍለጦር ተወርዋሪ ሃይል እሳተገሞራ ሻለቃ ከአገዛዙ ሰራዊት አንድ  ፓትሮል እና አንድ ገምሹ በየነ መንገድ ስራ ላይ በኮንትራት የሚሰራ የግል መኪና ተማርኮ የግል መኪናው ከነሹፌሩ ሲለቀቅ በድርጊቱ የማይመስል ቁጭት እና እልህ  ውስጥ የገባው የአገዛዙ ሰራዊት እሳተገሞራ ሻለቃን ተከታትሎ ጀማ በረሀ በመውረድ በርሲና አንባገነን ወንዝ ላይ እልህ አስጨራሽ ውጊያ ሲያደረግ ሞት አይፈሬው የናደው ክፍለጦር ተወርዋሪ ሃይል እሳተ ገሞራ ሻለቃና ከናደው ክፍለ ጦር  መቅደላ ብርጌድ ለልዩ ኦፕሬሽን የተውጣጣ ሰራዊት በጋራ  ከወንዙ የገባውን ሰራዊት በርካቶችን እስከወዲያኛው የተሸኙ ሲሆን የቆጡን አውርድ ብላ የብብቷን ጣለች የሚለውን አነጋገር እየተናገሩ ሞት አይፈሬዎቹ ከፍተኛ ድል ተቀዳጅተዋል።

      በሌላ ዜና  የአማራ ህዝብ የሞት  አዋጅ ከታወጀበት ዕለት ጀምሮ ጦርነቱን በመመከት የስርአቱን መዋቅር በማፈራረስ  ከአማራ ህዝብ አብራክ የወጣው ፋኖ በተቆጣጠረበቸው ቦታ ሁሉ ጠንካራ ስርአት እየዘረጋ መሆኑ ይታወቃል ይሁን እንጅ  የትሮይ ፈረሶቹ የመረሐቤቴ ወረዳ የብልፅግና አጋፋሪዎች ፋኖ በሚያስተዳድረው አገሪት ቁማባ ቀበሌ ከከተማው 4 ኪ/ሜ  ቅርብ እርቀት ላይ በከባድ መሳርያም ቢሆን ሽፋን እየሰጠን እናስተዳድረዋለን ብለው ከዚህ በፊት በመረጃ አገዛዙን ሲያገለግለው የነበረውን ገለታው ደለለኝ የተባለውን ግለሰብ ቀበሌ አስተዳዳሪ አድርጎ በመሾም ተሿሚውን በተሾመ ማግስት ላይመለስ በናደው ክፍለጦር አናብስቶች እስከወዲያኛው ተሸኝቷል።

   ይህ በእንዲህ እንዳለ ቀጣይም በአማራ የህዝብ ህልውና ጦርነት ላይ የሚሳለቅ እንዲሁም የአማራን ህዝብ ከምድረ ገፅ  መጥፋት አለብህ ብሎ ካወጀ ፋሽስታዊ ስርአት ጋር ተሰልፎ በማገልገል ላይም ይሁን ለማገል ገል በቋመጠ የትኛውም ሃይል ላይ ክፍለ ጦራችን የማያዳግም እርምጃ እንደሚወስድ እናሳስባለን።
                                   
ክብር ለተሰው ሰማዕታት
                           
ድላችን በተባበረ ክንዳችን

ሸዋ አማራ ኢትዮጵያ
መጋቢት02/2017ዓ.ም
ከአማራ ፋኖ በሸዋ የናደው ክፍለ ጦር የሚዲያና ኮምንኬሽን ክፍል




የባንዳ ጥቆማ‼

ምስጋናው አብተው ይባላል  በደብረ ማርቆስ ከተማ ገቢወች ቢሮ ውስጥ ነው የሚሰራው ህዝቡን በማስለቅስ ማንነቱን በሆዱ የሸጠ  የአረመኔ ብልጽግና  ቀንደኛ ተላላኪ ነው ቤተሰብ ካለው መክራችሁ ከዚህ ስራው እንዲታቀብ አድርጉት  ካልሆነ ግን ልክ እንደሌሎቹ የማያዳግም እርምጃ    እንወስዳለን ይላሉ አካባቢው ላይ የሚንቀሳቀሱት የባንዳ መዳኒት ያልታወቁ ሀይሎች ለግዜ ከመከላከያ ካምብ ብታድርም ከስራህ ካልታቀብክ ቃላችን ነው አታመልጠን ተብለሃል።
የባንዳው የእጅ ስልክ
0913322049

መጋቢት 02/2017ዓ.ም
 




#ይበቃል‼️

"አፋህድ" የአማራ ፋኖ ወደ መናገሻ ከተማው አዲስ አበባ ለመግባት ይጠቀምባቸዋል የሚባሉ (በሸዋ ቀጠና የሚገኙ) ቁልፍ ቀጠናዎችን ለመያዝና በአካባቢ የሚገኙ ፋኖዎችን  ከማጥፋት ባለፈ የፋኖን የቤተመንግስት ጉዞ ለመግታት እየሰራ ይገኛል::

ከብልግናው አገዛዝ ጋር የተናበበ በሚመስል መልኩ ቦታውን ቀድሞ ለመያዝና የአማራ ፋኖን ጉዞ ለመግታት በእስክንድር ነጋ የሚዘወረውና በመከታው ማሞ የሚመራው ሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ በገዛ ወንድሞቹ ላይ የከፈተውን ጦርነት የማያቆም ከሆነ እንደአማራ ህዝብ ሊወገዝ ይገባል::

አርበኛ መከታው ማሞ ራምቦ ክፍለጦርን በመላክ በሚዳ የሚገኙ የቀስተ ንህብ ብርጌድ ፋኖዎች የመበተን ስራ እየሰራ እንደሆነ የተረጋገጠ ሲሆን በቀጣይ የዕዙ ቅልብ ጦር የሚሰኘውና ብዙ መዓዕለ ንዋይ እንደፈሰሰበት የሚነገረው የተሰማ እርገጤ ክፍለጦርን ወደ ቀወት ቀጠና በመላክ የ7ለ70 ብርጌድን ለማጥፋት በዝግጅት ላይ እንደሚገኝና ከዚያ በመቀጠልም በሸዋ ግዛት ስመጥር የሆነውና ከአገዛዙ ወታደሮች ጋር በርካታ ትንቅንቆችን በማድረግ የሚታወቀውን ከሰም ክፍለጦርን ለማጥቃት እንዳቀዱም መረጃዎች ወጥተዋል::

እናም የህዝባችን ስቃይ ለማራዘም ሌት ከቀን የሚሰሩ አካላቶች በቃችሁ ሊባሉ ይገባል::

ወንድም በወንድሙ ላይ ቃታ መሳብና ጦር ማዝመት ይበቃል!!




ሰበር ዜና❗️❗️

👉👉 አናብስቶች ስናን አባጅሜ ብርጌድ ጠላትን ሲያርበደብዱት ዉለዋል!!

##የነ!ሞት አይፈሬ ሃ/ማክቤል ዳኜና አ/አለቃ ባለዉ ጊዜ ወንዴ ጦር ስናን አባጅሜ ብርጌድ የብርሃኑ ጁላን ጦር በከበባ ቆርጠዉ ሲረፈርፉት ዉለዋል!!

በቀን 02/07/2017 ዓ.ም የአገዛዙ ጦር በማን አለብኝነት የማ/ሰቡን ዛፍ ለመመንጠር በከተማ ጫፍ ሲንቀሳቀስ ጀግኖች በቆረጣ ገብተዉ አይቀጡ ቅጣት ቀጥተዉታል!!

በተለምዶ "ደበደቦ" ተብሎ በሚጠራዉ አካባቢ በነበረዉ ቀጠና በማዕበል ቁጥር ሁለትናአበረ ልየዉሻለቃ የአገዛዙ ሰራዊት ከባድ ክስረት የደረሰበት ሲሆን በታችኛዉ ቀጠና የደማን በማዕበል ቁጥር አንድናፋሲካዉ ሻለቃ አገዛዙ ከባድ ሽንፈት ደርሶበታል!!

በሽንፈቱ የተበሳጨዉ የአገዛዙ ጦር ፍጩ ለማስፈጨት ከገጠር ወደ ከተማ የገቡትን ንፁሃን መንገድ ላይ በማቆም ሲደባደብ ዉሏል!!

በዉጊያዉም 4 የጠላት ሐይል ሙቷል!!

ይህ በእንዲህ እንዳለ

1:-ይመኑ ደሴ
2:-ስናማዉ እንዳለዉና
3:-ልጥገበዉ ቢያብል የተባሉ ሶስት የአገዛዙ የመረጃ ደህንነቶች በዉጊያዉ የፋኖን መዉጫ መግቢያ ለማጥናት ሲንቀሳቀሱ በስናን አባጅሜ ብርጌድ ቁጥጥር ስር ዉለዋል!!

©ፋኖ መ/ር ስሜ ፈንታ


ቀን 02/07/2017 ዓ.ም
ሰበር አውደ ውጊያ ዜና‼️
የአማራ ፋኖ በጎጃም ፩ኛ ክፍለ ጦር የኮለኔል ታደሰ ሙሉነህ ብርጌድ ሁለት ቦታዎች ላይ በሰራው ኦፕሬሽን ህዝብን ከዘረፋ ታድጓል።
የመጀመሪያው ሜጫ ወረዳ ብራቃት አካባቢ አጣሪ የሚባል ተራራ ላይ ሰፍሮ የሚገኘው የብርሀኑ ጁላ ዘራፊ ቡድን ወደ ባርኳ ማሪያም ሚባል ቀጠና የጤና መድን እና የቀይ መሥቀል ብለው በሰጡት የዳቦ ስም ህዝባችን ለመመዝረፍ ሲንቀሳቀስ የብርጌዱ አካል የሆነችው አበራ ሙጨ ሻለቃ መብረቃዊ ጥቃት በማድረስ 4ቱ እስከወዲያኛው ያሸለበና 6 ቁስለኛ አሸክማ እያስሮጠች ወደተለመደው የቀበሮ ጉድጓዱ አስገብታዋለች።

በሌላ በኩል ኮሎኔል ባህሩ በሚባል የዘራፊ ቡድን የሚመራው የ76ኛ ክፍለ ጦር ከገርጨጭ በመነሳት ዘመነ ብርሀን (አጉጋ) ወደተባለ ቦታ ለዘረፋ ሲንቀሳቀስ ሌላኛዋ የኮለኔል ታደሰ ሙሉነህ ብርጌድ ነበልባሏ አለማየሁ ከቤ ሻለቃ ወደ ተለመደው የኮንኩሪት ምሽጉ ገረጨጭ ከተማ እያሮሯጠች ሰደዋለች።

ፋኖ ሙሉሰው የኔአባት የአማራ ፋኖ በጎጃም ፩ኛ ክፍለ ጦር ህዝብ ግንኙነት


የእነ ሽመልስ ቤት ፈረሳ
ዜና 3
እነ ሽመልስ አብዲሳ በሸገርና በሞጆ ከተሞች ህጋዊ ቤቶችን ጭምር ማፍረሳቸውን እንደቀጠሉ ነው

የሸገር ከተማ አስተዳደር በባለፈዉ ጊዜ “ሁሉም የማይመጥኑ ቤቶች ይፈርሳሉ”  ባለዉ መሰረት የደሃ ቤቶችን ማፍረስ ጀምሯል።
ደሃን የሚጸየፈውና ከተሜን የሚያሳድደው የብልጽግናው አገዛዝ በየአቅጣጫው የዜጎችን ቤት ማፍረስ ዋነኛ ስራው አድርጎታል፡፡
ከዚህ ቀደም ቤታቸውን ያፈረሰባቸውን ሰዎች ህጋዊ ደሃ አድርገናቸዋል ያለው የሸገር ከተማ አስተዳደር ለገጣፎ ከ አባ ኪሮስ 3ኪሜ አካባቢ  ወረገኑ ገዋሳ የሚባል ሰፈር በ መደዳዉ ለማፍረስ ቄሮዎችን አሰማርቶ ቀለም እየቀባ ነው።
ነዋሪዎችም ከከተማ ሸሽተን ኪራይ ይቀንሳል በሚል ነበር የገባነው ፣ የቤት ባለቤቶችም ጥሪታችንን አራግፈን ነበር የገዛነው ከዚህ በሁዋላ ከሀገራችን የት እንሂድ? ሲሉ ይጠይቃሉ፡፡
በተመሳሳይ በሞጆ ከተማ ጨረቃ ቤት በማለት በአንድ ቀበሌ ብቻ ከ አራት መቶ በላይ የሚሆኑ ቤትችን ለማፍረስ የቀበሌ አመራሮች ቀይ ቀለም እየቀቡ እንደሚገኙ እየተገለጸ ነው፡፡
ነገር ግን እነዚህ ቤቶች ከ አዋጅ በፊት የተሰሩ ማለትም 2004 እና ከዛ በኋላ ሲሆኑ ካርታ ወጥቶላቸው ህጋዊ ይሁኑ የተባሉ ነበሩ፡፡
ሂደቱም ተጀምሮ ነበር የሚሉት አስተያየት ሰጪዎች ይሁን እንጂ ከ2005 ወዲህ ያሉ ቤቶችን ለኢንቨስትመንት ተፈልገዋል ፣ሞጆ ደረቅ ወደብ ለወጣቶች መዝናኛ ሊሰራበት ነው እንዲወሰዱ ተደርጓል፡፡ ህዝቡንም ምትክ እንሰጣለን ተደራጁ በማለት አፍርሰው ቦታውን ግን በሙስና ለግለሰብ መርተውታል።
ሕዝቡም ያለ አቅሙ ተከራይቶ በችግር እየኖረ ነው የሚሉት ነዋሪዎች አሁንም እነዚህን ለማፍረስ እየተዘጋጁ ይገኛሉ ብለዋል፡፡
“ይሄም ህዝብ ችግርተኛ ህዝብ ነው በዚህ ኑሮ ውድነት ብዙ የለፋበት መኖሪያ ቤቱንም ቢያጣ ምን ሊሆን እንደሚችል ግልጽ ነው"ሲሉ አብራርተዋል።

ሮሃ ቲቪ

መጋቢት 02 /07/2017 ዓ.ም
  አሻራ ሚዲያ

# አዲሱን የአሻራ ፌስቡክ ገፅ ይወዳጁ 👇👇

https://www.facebook.com/profile.php?id=61554383356900

የተከበራችሁ የአሻራ ሚዲያ ቤተሰቦች ነባሩ የአሻራ ዩትዩብ ቻነል ስለተዘጋ አዲሱን ቻነል

ሰብስክራይብ በማድረግ መረጃዎችን ይከታተላሉ ‼
👇👇👇

የአሻራ ሚዲያ ዩትዩብ ቻነል ለ50ኛ ጊዜ በአገዛዙ ተዘግቷል።
አዲሱን ቻነል Subscribe,share,like በማድረግ ይወዳጁን‼

https://youtu.be/RMy0eA0psEA
👇👇👇👇

አዲሱ ቻናላችን ነው ቤተሰብ ይሁኑ
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇


https://youtu.be/BBY7d2wkuKI


#AddisAbaba

ዛሬ አዲስአበባ ሳርቤት ብስራተ ገብርኤል አካባቢ ሁለት የንግድ ባንክ ጥበቃዎች ተገድለው ንግድ ባንክ መዘረፉ ተሰምቷል።

Показано 20 последних публикаций.