ሚኒስቴሩ ወደውጭ ለሥራ የምልከው ሰው እያጠረኝ ነው አለ‼️የሥራ እና ክህሎት ሚኒስቴር በዘረጋው የውጪ ሀገር የሥራ ስምሪት ገበያ ላይ ሂዶ ለመስራት ከሀገራት ከሚቀርበው ጥያቄ አንፃር፤ በከፍተኛ ሁኔታ የሚላኩ ዜጎች እጥረት መኖሩ ተገልጿል፡፡
ከመዳረሻ ሀገራት በኩል በርካታ የሰለጠነ የሰው ሀይል ጥያቄን ለኢትዮጵያ እንደሚቀርብ ለአሐዱ የገለጹት፤ በሚኒስቴሩ የሥራ ገበያ መረጃ ስርዓት ፕሮጀክት ፅ/ቤት ኃላፊ ብርሀኑ አለቃ ናቸው፡፡
በብዛት የሰው ሀይል ጥያቄ ያለባቸው ሀገራት በሙሉ ከኢትዮጵያ ሰው ለመውሰድ ፍላጎት እንዳላቸው አንስተው፤ ከመካከለኛው ምስራቅ ኳታር፣ ሳውዲ አረቢያ፣ የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ፣ ኩዌት፣ ሊባኖስ እና ጆርዳን እንዲሁም ከአውሮፓ ሀገራት ደግሞ ጀርመን፣ ስዊድን፣ ኖርዌይ እና ፖላንድ በከፍተኛ ሁኔታ ከኢትዮጵያ የሰው ሀይል የሚፈልጉ ሀገራት መሆናቸውን አስታውቀዋል።
እነዚህ ሀገራትም በጥቅሉ በሚሊዮን የሚቆጠር የሰው ሀይል ጥያቄን እንደሚያቀርቡ ተናግረዋል።
ከዚህ ቀደም በዓመት ከ50 ሺሕ ያልበለጠ የሰው ሀይል ወደ ውጪ ሀገራት ይላክ እንደነበር ያነሱት ኃላፊው፤ "አሁን ላይ ቴክኖሎጂን በመጠቀም በመጣው ለውጥ አማካኝነት በትንሹ እስከ 400 ሺሕ ሰው ይላካል" ብለዋል።
ይሁን እንጂ አሁን ላይ ሀገራት ከሚያቀርቡት ቁጥር አንፃር ከፍተኛ የሰው ሀይል እጥረት ስለመኖሩ ተናግረዋል።
በዚህም ሰዎችን ለሥራ ከማሰማራት አኳያ ብቻም ሳይሆን፤ ኢትዮጵያም ከዘርፉ ማግኘት የሚገባትን ጥቅም እንዳላገኘች ኃላፊው ተናግረዋል፡፡
ስለዚህም ማንኛውም ሰው በየሙያው ሰልጥኖ ተገቢውን የምዘና ፈተና በመውሰድ፣ የሥራና ክህሎት በሚያዘጋጀው የሥራ ገበያ አሰራር ላይ በመመዝገብ እና በየቀበሌው ባሉት የመረጃ መቀበያ ጣቢያዎች አስፈላጊ መረጃዎችን በመሙላት የእድሉ ተጠቃሚ እንዲሆን ጥሪ አቅርበዋል።
አሐዱ
====================
💎⬇️⬇️⬇️👇👇👇👇👇👇
የቴሌግራም ቻናላችንን join በማድረግ ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ይከታተሉ፣ሊንክ👇
https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2shttps://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s