ነገረ ክርስቶስ ክፍል ፪፻፴፬
"ጠላቶች ሳለን ከእግዚአብሔር ጋራ በልጁ ሞት ከታረቅን፥ ይልቁንም ከታረቅን በኋላ በሕይወቱ እንድናለን" (ሮሜ ፭፣፲)።
ኢየሱስ ክርስቶስን ሁለት አካል ሁለት ባሕርይ ነው ብለው የሚናገሩ ሰዎች በዚህ ኃይለ ቃል ይሸነፋሉ። "ወልደ እግዚአብሔር አይሞትም፣ አይራብም፣ አይጠማም፣ አይደክምም ወልደ ማርያም ይሞታል፣ ይራባል፣ ይጠማል፣ ይደክማል" እያሉ አንዱን ኢየሱስ ክርስቶስን ሁለት አድርገው የሚናገሩ ሰዎች አሉ። እኛ ግን አንዱን ኢየሱስ ክርስቶስን ወልደ አብም ወልደ ማርያምም እንለዋለን። ከተዋሕዶ በኋላ የሠራውን ሥራ በተዋሕዶ ሠራው እንላለን እንጂ እየነጣጠልን ይህ የሥጋ ሥራ ነው፣ ይህ የመለኮት ሥራ ነው እያልን አንናገርም።
ቅዱሳት መጻሕፍትም ኢየሱስ ክርስቶስን ወልድ ዋሕድ (አንድ ልጅ) ይሉታል እንጂ ሁለት አይሉትም። ይህንንም የሚያስረዳን ከላይ የጠቀስነው ኃይለ ቃል ነው። እግዚአብሔር በልጁ ሞት ታረቀን ብሎ ወልደ አብ በሥጋው እንደሞተ ነግሮናል። በምንታዌ (Dualism) የሚያምኑ ሰዎች የእግዚአብሔር ልጅ አይሞትም ካሉ እግዚአብሔር በልጁ ሞት ታረቀን ይልባቸዋልና ክሕደታቸው ከንቱ መሆኑን ይወቁ።
© በትረማርያም አበባው
የፌስቡክ ገጼ:- Betremariam Abebaw
https://www.facebook.com/profile.php?id=100075547015721 ነው።
የዩቲይብ ቻናሌ:- ንሕነ ዘክርስቶስ
@edenawizechristos?si=6V4y-73OM3LTzhAf' rel='nofollow'>
https://youtube.com/@edenawizechristos?si=6V4y-73OM3LTzhAf ነው።
ክፍል ፪፻፴፭ ይቀጥላል