በትረማርያም አበባው Betremariam Abebaw


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: Религия


አቀድም አእኵቶቶ ለእግዚአብሔር

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
Религия
Статистика
Фильтр публикаций


ነገረ ክርስቶስ ክፍል ፪፻፴፰
"ከእነርሱም (ከአባቶችም) ክርስቶስ በሥጋ መጣ፥ እርሱም ከሁሉ በላይ ኾኖ ለዘለዓለም የተባረከ አምላክ ነው አሜን" (ሮሜ ፱፣፭)።

ቅዱስ ጳውሎስ የኢየሱስ ክርስቶስን አምላክነት በግልጽ ከተናገረበት አንቀጽ አንዱ ይህ ነው። ቅድመ ዓለም የነበረ ዓለምን የፈጠረ ወልደ እግዚአብሔር አዳምን ለማዳን ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም ተወለደ። ከአባቶች ተወለደ ብሎ የተናገረው አያቶቹን ለመጥቀስ ነው። ይኽውም ከኢያቄም ጀምሮ እነ ዳዊትን እነአብርሃምን እና ሌሎችንም ታላላቅ ቅዱሳን ለመጥቀስ ነው። ኢየሱስ ክርስቶስ በባሕርይው አምላክ ነው። ቅዱሳን አምላክ ቢባሉ የጸጋ አምላክ ሆነው ነው። እርሱ ግን አምላክነቱ የባሕርይ አምላክ ነው። ለዘለዓለም የተባረከ አምላክ ተብሎ የተገለጸውም ለዚህ ነው።

© በትረማርያም አበባው

የፌስቡክ ገጼ:- Betremariam Abebaw
https://www.facebook.com/profile.php?id=100075547015721 ነው።

የዩቲይብ ቻናሌ:- ንሕነ ዘክርስቶስ
@edenawizechristos?si=6V4y-73OM3LTzhAf' rel='nofollow'>https://youtube.com/@edenawizechristos?si=6V4y-73OM3LTzhAf ነው።

ክፍል ፪፻፴፱ ይቀጥላል


ነገረ ክርስቶስ ክፍል ፪፻፴፯
"የሞተው፥ ይልቁንም ከሙታን የተነሣው፥ በእግዚአብሔር ቀኝ ያለው፥ ደግሞ ስለ እኛ የሚፈርደው ክርስቶስ ኢየሱስ ነው" (ሮሜ ፰፣፴፬)።

ነገረ ክርስቶስ ክፍል ፪፻፴፮ ላይ እንደተመለከትነው መንፈስ ቅዱስም ይማልድልናል (ይከራከርልናል) እንደተባለና አብም ይከራከርልናል (ይትዋቀስ በእንቲኣነ) እንደተባለ አይተናል። በዚህኛው ክፍል ደግሞ ኢየሱስ ክርስቶስ የሚፈርደው ተብሏል። ይህም በግእዙ "ወይትዋቀስ በእንቲኣነ" ይላል። ይኽውም ይከራከርልናል (ይማልድልናል) ተብሎ ሊተረጎም ይችላል። ሁሉንም ቢል ትርጉሙ ተመሳሳይ ነው። ዋጋችንን ከአብ ከመንፈስ ቅዱስ ጋር ሆኖ ይሰጠናል ማለት ነው። በሥጋው በደሙ አማካኝነት እስከ ዕለተ ምጽአት ድረስ ጸጋውን እያደለ ሰይጣንን እንድንቃወም ይረዳናልና ይማልድልናል አለ እንጂ ከትንሣኤ በኋላ ኢየሱስ ክርስቶስ ሁልጊዜ እያማለደ ይኖራል ማለት አይደለም። ምድር ላይ በሠራልን የማዳን ሥራ አምነን ተጠምቀን ሥጋውን ደሙን ተቀብለን ብንኖር መንግሥተ ሰማያትን ሰጥቶ የሚፈርድልን እርሱ ነው።

© በትረማርያም አበባው

የፌስቡክ ገጼ:- Betremariam Abebaw
https://www.facebook.com/profile.php?id=100075547015721 ነው።

የዩቲይብ ቻናሌ:- ንሕነ ዘክርስቶስ
@edenawizechristos?si=6V4y-73OM3LTzhAf' rel='nofollow'>https://youtube.com/@edenawizechristos?si=6V4y-73OM3LTzhAf ነው።

ክፍል ፪፻፴፰ ይቀጥላል


ነገረ ክርስቶስ ክፍል ፪፻፴፮
"እንዲሁም ደግሞ መንፈስ ድካማችንን ያግዛል እንዴት እንድንጸልይ እንደሚገ፟ባ፟ን አናውቅምና፥ ነገር ግን፥ መንፈስ ራሱ በማይነገር መቃተት ይማልድልናል" (ሮሜ ፰፣፳፮)።

መንፈስ ቅዱስን ይማልድልናል እያለ ነው። ዋጋ መስጠትን መማለድ ብሎ የሚገልጽበት ወቅት አለ። ይኽውም ውጤቱን በመቅድሙ መጥራት ነው። መንፈስ ቅዱስ የተለያዩ መከራዎችን ስንቀበል ዋጋችንን ይሰጠናል። ከአብ ከወልድ ጋር አንድ ሆኖ ለምዕመናን ዋጋቸውን ይሰጣቸዋል። እግዚአብሔር ምእመናን እንዳይወድቁ ይማልድላቸዋል ማለት ጸጋውን ያድላቸዋል። ከእነርሱ ጋር በረድኤት ሆኖ የሚድኑበትን መንገድ ይገልጽላቸዋል ማለት ነው። ይማልድልናል የሚለው ቃል በግእዝ "ይትዋቀስ-ይከራከርልናል" ተብሏል። ይህ ከሆነ ደግሞ አብም እንደሚከራከርልን (እንደሚማልድልን) ተጽፏል። "ስለእርሳቸው ይከራከርላቸዋልና በጠላታቸምም እጅ አይጥላቸውምና ከሚጠሏቸው ከጠላቶቻቸው እጅ ያድናቸዋል" እንዲል (፩ኛ መቃ. ፳፣፫)። ትርጉሙ ዋጋን ይሰጠናል ማለት ነው።

© በትረማርያም አበባው

የፌስቡክ ገጼ:- Betremariam Abebaw
https://www.facebook.com/profile.php?id=100075547015721 ነው።

የዩቲይብ ቻናሌ:- ንሕነ ዘክርስቶስ
@edenawizechristos?si=6V4y-73OM3LTzhAf' rel='nofollow'>https://youtube.com/@edenawizechristos?si=6V4y-73OM3LTzhAf ነው።

ክፍል ፪፻፴፯ ይቀጥላል


ነገረ ክርስቶስ ክፍል ፪፻፴፭
"ወይስ ከክርስቶስ ኢየሱስ ጋራ አንድ እንኾን ዘንድ የተጠመቅን ዅላችን ከሞቱ ጋራ አንድ እንኾን ዘንድ እንደ ተጠመቅን አታውቁምን። ሞቱንም በሚመስል ሞት ከርሱ ጋራ ከተባበርን ትንሣኤውን በሚመስል ትንሣኤ ደግሞ ከርሱ ጋራ እንተባበራለን" (ሮሜ ፮፣፫_፭)።

በጥምቀት ከኢየሱስ ክርስቶስ ጋር አንድ እንሆናለን። ስንጠመቅ ራሳችን ኢየሱስ ክርስቶስ ይሆናል። እኛም ሕዋሳቶቹ እንሆናለን። ስንጠመቅ አካላችን የክርስቶስ ማደሪያ ይሆናል። ስለዚህ በእርሱ በክርስቶስ ክርስቲያን እንባላለን። ስንጠመቅ ሞቱን በሚመስል ሞት እንሞታለን። ሞቱን በሚመስል ሞት ስንሞት ትንሣኤውን በሚመስል ትንሣኤ እንተባበራለን። በጥምቀት ከእግዚአብሔር የጸጋ ልጅነትን እናገኛለን (ዮሐ. ፫፣፫)። በጥምቀት ሥርየተ ኃጢአትን እናገኛለን። ስንጠመቅ ከእርሱ ከጌታ ጋር አንድ እንሆናለን ማለት በጸጋ ተዋሕዶን ታላላቅ መንፈሳዊ ሥራዎችን እንድንሠራ ያደርገናል ማለታችን ነው።

© በትረማርያም አበባው

የፌስቡክ ገጼ:- Betremariam Abebaw
https://www.facebook.com/profile.php?id=100075547015721 ነው።

የዩቲይብ ቻናሌ:- ንሕነ ዘክርስቶስ
@edenawizechristos?si=6V4y-73OM3LTzhAf' rel='nofollow'>https://youtube.com/@edenawizechristos?si=6V4y-73OM3LTzhAf ነው።

ክፍል ፪፻፴፮ ይቀጥላል


ነገረ ክርስቶስ ክፍል ፪፻፴፬
"ጠላቶች ሳለን ከእግዚአብሔር ጋራ በልጁ ሞት ከታረቅን፥ ይልቁንም ከታረቅን በኋላ በሕይወቱ እንድናለን" (ሮሜ ፭፣፲)።

ኢየሱስ ክርስቶስን ሁለት አካል ሁለት ባሕርይ ነው ብለው የሚናገሩ ሰዎች በዚህ ኃይለ ቃል ይሸነፋሉ። "ወልደ እግዚአብሔር አይሞትም፣ አይራብም፣ አይጠማም፣ አይደክምም ወልደ ማርያም ይሞታል፣ ይራባል፣ ይጠማል፣ ይደክማል" እያሉ አንዱን ኢየሱስ ክርስቶስን ሁለት አድርገው የሚናገሩ ሰዎች አሉ። እኛ ግን አንዱን ኢየሱስ ክርስቶስን ወልደ አብም ወልደ ማርያምም እንለዋለን። ከተዋሕዶ በኋላ የሠራውን ሥራ በተዋሕዶ ሠራው እንላለን እንጂ እየነጣጠልን ይህ የሥጋ ሥራ ነው፣ ይህ የመለኮት ሥራ ነው እያልን አንናገርም።

ቅዱሳት መጻሕፍትም ኢየሱስ ክርስቶስን ወልድ ዋሕድ (አንድ ልጅ) ይሉታል እንጂ ሁለት አይሉትም። ይህንንም የሚያስረዳን ከላይ የጠቀስነው ኃይለ ቃል ነው። እግዚአብሔር በልጁ ሞት ታረቀን ብሎ ወልደ አብ በሥጋው እንደሞተ ነግሮናል። በምንታዌ (Dualism) የሚያምኑ ሰዎች የእግዚአብሔር ልጅ አይሞትም ካሉ እግዚአብሔር በልጁ ሞት ታረቀን ይልባቸዋልና ክሕደታቸው ከንቱ መሆኑን ይወቁ።

© በትረማርያም አበባው

የፌስቡክ ገጼ:- Betremariam Abebaw
https://www.facebook.com/profile.php?id=100075547015721 ነው።

የዩቲይብ ቻናሌ:- ንሕነ ዘክርስቶስ
@edenawizechristos?si=6V4y-73OM3LTzhAf' rel='nofollow'>https://youtube.com/@edenawizechristos?si=6V4y-73OM3LTzhAf ነው።

ክፍል ፪፻፴፭ ይቀጥላል


ነገረ ክርስቶስ ክፍል ፪፻፴፫
"በኢየሱስ ክርስቶስም በሆነው ቤዛነት በኩል እንዲያው በጸጋው ይጸድቃሉ" (ሮሜ ፫፣፳፬)።

ቤዛነት ማለት ምትክነት ማለት ነው። ይኽውም ለአዳም ስለአዳም እንደ አዳም ሆኖ የወደቀውን አዳምን ለማንሣት ያደረገው የቸርነት ሥራ ነው። ባጠፋው ጥፋት ምክንያት መሰቀል ይገባው የነበረ አዳም ነው። ነገር ግን በአዳም ምትክ (ህየንተ አዳም) ጌታ ተሰቅሎ አዳምን ነጻ አውጥቶታል። አምላኬ አምላኬ ለምን ተውከኝ ብሎ ማልቀስና ወደ እግዚአብሔር ማመልከት የሚገባው አዳም ነበር። ነገር ግን አዳም በበደል ስለተያዘ በፊቱ ቆሞ እንዲህ ብሎ ለመጮህ አልቻለም። ስለዚህ በአዳም ምትክ የአዳምን ጩኸት ራሱ ኢየሱስ ክርስቶስ ጮኸለት። እንደ አምላክነቱም የአዳምን በደል በመስቀል ላይ ተሰቅሎ ይቅር አለው። ምእመናን በክርስቶስ ቤዛነት እንዲያው በጸጋው ይጸድቃሉ። ይህም ማለት ጌታ ያደረገውን የማዳን ሥራ አምነው፣ ተጠምቀው፣ ሥጋውን ደሙን ተቀብለው፣ መልካም ሥራን ሠርተው በእግዚአብሔር ቸርነት ይጸድቃሉ ማለት ነው። የእግዚአብሔር ቸርነት ካልተጨመረበት ሰው ምንም ያህል በጎ ሥራ ቢሠራ መጽድቅ እንደማይችል ለመግለጽ እንዲያው በጸጋው ይጸድቃሉ ብሎ ተናገረ።

© በትረማርያም አበባው


የፌስቡክ ገጼ:- Betremariam Abebaw
https://www.facebook.com/profile.php?id=100075547015721 ነው።

የዩቲይብ ቻናሌ:- ንሕነ ዘክርስቶስ
@edenawizechristos?si=6V4y-73OM3LTzhAf' rel='nofollow'>https://youtube.com/@edenawizechristos?si=6V4y-73OM3LTzhAf ነው።

ክፍል ፪፻፴፬ ይቀጥላል


ነገረ ክርስቶስ ክፍል ፪፻፴፪
"እምነታችኹ በዓለም ሁሉ ስለ ተሰማች አስቀድሜ ስለ ዅላችኹ አምላኬን በኢየሱስ ክርስቶስ አመሰግናለኹ" (ሮሜ ፩፣፰)።

በምስጋና መጀመር ለሐዋርያት ልማዳቸው ነው። እግዚአብሔር አብን አስቀድሜ አመሰግናለሁ አለ። አምላኬ ያለው አብን ነው። ወልድን ቀጥሎ የሚያመጣው ነውና። በኢየሱስ ክርስቶስ አመሰግናለሁ አለ። ኢየሱስ ክርስቶስን ማመስገን አብን ማመስገን ነው። አብን ማመስገን ኢየሱስ ክርስቶስን ማመስገን ነውና። አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ በምስጋና አንድ ናቸው። እነርሱን የምናመሰግነው ምስጋና የባሕርይ ምስጋና ነው። ይኽውም ይህን ዓለም ካለመኖር አምጥተው ስለፈጠሩ፣ ብንወድቅ ከሦስቱ አካላት አንዱ ወልድ ሥጋችንን ተዋሕዶ በመስቀል ተሰቅሎ ስላዳነን፣ ብንራብና ብንጠማ ዘለዓለማዊነትን የሚያጎናጽፍ ሥጋውን ቆርሶ ደሙን አፍስሶ ስለሰጠን እናመሰግነዋለን። እግዚአብሔር ምስጋና የባሕርይው ነው ማለታችን ባሕርይው ምስጉን ነው ማለታችን ነው። ይኽውም ቅዱሳን መላእክትና ሰዎች ቢያመሰግኑት የማይጨመርለት ባያመሰግኑት የሚቀነስበት አይደለም ማለታችን ነው።

© በትረማርያም አበባው


የፌስቡክ ገጼ:- Betremariam Abebaw
https://www.facebook.com/profile.php?id=100075547015721 ነው።

የዩቲይብ ቻናሌ:- ንሕነ ዘክርስቶስ
@edenawizechristos?si=6V4y-73OM3LTzhAf' rel='nofollow'>https://youtube.com/@edenawizechristos?si=6V4y-73OM3LTzhAf ነው።

ክፍል ፪፻፴፫ ይቀጥላል


ነገረ ክርስቶስ ክፍል ፪፻፴፩
"ራሱን ያለምስክር አልተወም" (የሐዋ. ሥራ ፲፬፣፲፯)።

የዚህች ዓለም ፈጣሪ፣ አስተዳዳሪ እንዳላትና ይኽውም እግዚአብሔር እንደሆነ በብዙ መንገድ ራሱ አሳውቆናል። የፈጣሪን መኖር ከሚያረጋግጡልን ምስክሮች መካከል የሚከተሉት ይጠቀሳሉ።
፩) ሥነ ፍጥረት
፪) መጽሐፍ ቅዱስ
፫) ሥጋዌ
ቤት ያለባለቤት እንደማይገኝ ሁሉ ፍጡርም ያለ ፈጣሪ አልተገኘም። ሁሉንም ፍጥረት ካለመኖር ወደመኖር ያመጣና የፈጠረ ለእርሱ ምንም ምክንያት የሌለው ልዑል እግዚአብሔር ነው። ለእርሱ መኖር ሌላ ምክንያት እንደሌለውም "እስመ አልቦ ውስተ ህላዌሁ አመክንዮ" ተብሎ ተገልጿል። በመጽሐፍ ቅዱስ የተጻፉ የነቢያት ትንቢቶች ተፈጻሚ ሆነው በመታየታቸው ያጻፈው እግዚአብሔር እውነተኛ እንደሆነ ይመሰክራሉ። ስለዓለም አፈጣጠር በእርግጠኝነት የሚናገር መጽሐፍ መጽሐፍ ቅዱስ ነው። የእግዚአብሔርን መኖር በጎላ በተረዳ ነገር የሚያሳውቀን ደግሞ ከሦስቱ አካላት አንዱ ወልድ ከድንግል ማርያም ተወልዶ የአምላክነት ሥራን እየሠራ በማሣየቱ ነው።

© በትረ ማርያም አበባው

የፌስቡክ ገጼ:- Betremariam Abebaw
https://www.facebook.com/profile.php?id=100075547015721 ነው።

የዩቲይብ ቻናሌ:- ንሕነ ዘክርስቶስ
@edenawizechristos?si=6V4y-73OM3LTzhAf' rel='nofollow'>https://youtube.com/@edenawizechristos?si=6V4y-73OM3LTzhAf ነው።

ክፍል ፪፻፴፪ ይቀጥላል


ነገረ ክርስቶስ ክፍል ፪፻፴
"በኢየሱስ ክርስቶስ ስምም ይጠመቁ ዘንድ አዘዛቸው" (የሐዋ. ሥራ ፲፣፵፰)።

በአብ ማመን በወልድ ማመን፣ በወልድ ማመን በአብ ማመን እንደሆነ ከዚህ ቀደም ተማምረናል። ስለዚህ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ተጠመቁ ብሎ ያዘዛቸው በእርሱ ስም መጠመቅ በአብ ስም መጠመቅ ስለሆነ ነው። በእርሱ ስም መጠመቅ በመንፈስ ቅዱስ ስም መጠመቅ ስለሆነ ነው። በባሕርያዊ ግብር ሦስቱ አንድ ስለሆኑ የአንዱ ስም ቢጠቀስም ሁለቱንም የሚመለከት ጉዳይ እንደሆነ ደጋግመን ደጋግመን ተማምረናል። ስለዚህ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ተጠመቁ ማለት በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ተጠመቁ ማለት ነው። በጥምቀት የእግዚአብሔር የጸጋ ልጆች እንሆናለን። ስንጠመቅ ከጥምቀት በፊት የሠራነው ኃጢአታችን ይሠረይልናል። በጥምቀት ድኅነትን እናገኛለን።

© በትረማርያም አበባው

የፌስቡክ ገጼ:- Betremariam Abebaw
https://www.facebook.com/profile.php?id=100075547015721 ነው።

የዩቲይብ ቻናሌ:- ንሕነ ዘክርስቶስ
@edenawizechristos?si=6V4y-73OM3LTzhAf' rel='nofollow'>https://youtube.com/@edenawizechristos?si=6V4y-73OM3LTzhAf ነው።

ክፍል ፪፻፴፩ ይቀጥላል


ነገረ ክርስቶስ ክፍል ፪፻፳፱
"ጴጥሮስ ይህን ነገር ገና ሲናገር ቃሉን በሰሙት ሁሉ ላይ መንፈስ ቅዱስ ወረደ" (የሐዋ. ሥራ ፲፣፵፬)።

"መንፈስ ቅዱስ ወረደ" ማለት ምን ማለት ነው? መንፈስ ቅዱስ የሌለበት ቦታ የለም። በሁሉ ቦታ ያለ ስለሆነ ወረደ ወጣ ሄደ የሚሉት ቃላት እንደ ቃላዊ ፍቻቸው አይተረጎሙም። አንድ ነገር ከሰማይ ወረደ ከተባለ ቀድሞ ከምድር አልነበረም ማለት ነው። ወደ ሰማይ ወጣ ከተባለ ደግሞ አስቀድሞ በምድር አልነበረም ማለት ነው። መንፈስ ቅዱስ ወረደ ማለት ግን ከሰማይ ታጣ ከምድር ተገኘ ማለት ሳይሆን ረድኤትን ሰጠ፣ ጸጋን አደለ ማለት ነው። የእግዚአብሔርን ቃል መስማት ጸጋን ያሰጣል። ስለሆነም ጴጥሮስ ሲያስተምር በሰሙት ሰዎች ላይ ጸጋ እግዚአብሔር እንዳደረባቸው ለመግለጽ መንፈስ ቅዱስ ወረደ ተብሎ ተገልጿል። ቅዱሳት መጻሕፍት ጸጋ መንፈስ ቅዱስን መንፈስ ቅዱስ እያሉ እንደሚጠሩት ከዚህ ቀደም ተመልክተናል።

© በትረማርያም አበባው

የፌስቡክ ገጼ:- Betremariam Abebaw
https://www.facebook.com/profile.php?id=100075547015721 ነው።

የዩቲይብ ቻናሌ:- ንሕነ ዘክርስቶስ
@edenawizechristos?si=6V4y-73OM3LTzhAf' rel='nofollow'>https://youtube.com/@edenawizechristos?si=6V4y-73OM3LTzhAf ነው።

ክፍል ፪፻፴ ይቀጥላል


ነገረ ክርስቶስ ክፍል ፪፻፳፰
"ከሙታንም ከተነሣ በኋላ ከርሱ ጋራ የበላን የጠጣንም እኛ ነን" (የሐዋ. ሥራ ፲፣፵፩)።

አንዳንዶች ኢየሱስ ክርስቶስን ከሙታን መካከል አልተነሣም እያሉ ይክዳሉ። በቅርብ በስድስተኛው መቶ ክፍለ ዘመን የተመሠረተው የእስልምና እምነትም ይህን ያስተምራል። ነገር ግን ከሙታን እንደተነሣ በዘመኑ ከእርሱ የተማሩ ሐዋርያት ከሙታን መካከል እንደተነሣ አይተውታል። ወንጌላዊው ሉቃስ "ከሙታን ከተነሣ በኋላ ከእርሱ ጋር የበላን የጠጣንም እኛ ነን" ብሎ የጻፈውም ለዚህ ነው። የክርስትና ሃይማኖትን ከሌሎች ቤተ እምነቶች ልዩ የሚያደርገው ይህ የትንሣኤ ጉዳይ ነው። ክርስቶስ ከሙታን ተነሥቶ ትንሣኤ እንዳለ አረጋግጦልናል። ሌሎች ቤተ እምነቶች ትንሣኤ እንዳለ ቢያምኑ እንኳ ምስክር ግን የላቸውም። የእኛ ግን ራሱ ክርስቶስ ምስክር አለን። መነሣቱ እውነት እንደሆነም በዘመኑ የነበሩ ሰዎች ምስክር ናቸው።

© በትረ ማርያም አበባው

የፌስቡክ ገጼ:- Betremariam Abebaw
https://www.facebook.com/profile.php?id=100075547015721 ነው።

የዩቲይብ ቻናሌ:- ንሕነ ዘክርስቶስ
@edenawizechristos?si=6V4y-73OM3LTzhAf' rel='nofollow'>https://youtube.com/@edenawizechristos?si=6V4y-73OM3LTzhAf ነው።

ክፍል ፪፻፳፱ ይቀጥላል


ነገረ ክርስቶስ ክፍል ፪፻፳፯
"እግዚአብሔር የናዝሬቱን ኢየሱስን በመንፈስ ቅዱስ በኀይልም ቀባው፥ ርሱም መልካም እያደረገ ለዲያብሎስም የተገዙትን ሁሉ እየፈወሰ ዞረ፥ እግዚአብሔር ከርሱ ጋራ ነበረና" (የሐዋ. ሥራ ፲፣፴፰)።

በመንፈስ ቅዱስ ቀባው የሚለው ትርጉሙ በግብረ መንፈስ ቅዱስ ቀባው ማለት ነው። ይኽውም ከመታሰብ በላይ የሆኑ አምላካዊ ሥራዎችን ቅዱሳት መጻሕፍት ለመንፈስ ቅዱስ አድለው ቢናገሩም መቀባት የሦስቱም የአንድነት ሥራ ነው። ሥጋ ከቃል ጋር ተዋሕዶ አምላክ እንዲሆን ማድረግም የሦስቱም የአንድነት ሥራ ነው። በሃይማኖተ አበውም ዘአንገሦ ለሥጋ አዳም በመንፈስ ቅዱስ ወረሰዮ ቅዱሰ ወማሕየዌ ሲል ይገኛል። በመንፈስ ቅዱስ አዋሐጅነት ሥጋን አምላክ አድርጎ ማሕየዊና ቅዱስ ያደረገው ተብሎ ተገልጿል። ከዚህም ላይ መንፈስ ቅዱስ ይጠቀስ እንጂ ማዋሐድ የሦስቱም አካላት የአንድነት ሥራ ስለሆነ አብም ወልድም ያሉበት ሥራ ነው። ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ እግዚአብሔር ከእርሱ ጋራ ነበረ ተብሎ መነገሩ በህልውና አብና መንፈስ ቅዱስ በእርሱ ህልው ሆነው ስለሚኖሩ ነው።

© በትረማርያም አበባው

የፌስቡክ ገጼ:- Betremariam Abebaw
https://www.facebook.com/profile.php?id=100075547015721 ነው።

የዩቲይብ ቻናሌ:- ንሕነ ዘክርስቶስ
@edenawizechristos?si=6V4y-73OM3LTzhAf' rel='nofollow'>https://youtube.com/@edenawizechristos?si=6V4y-73OM3LTzhAf ነው።

ክፍል ፪፻፳፰ ይቀጥላል


ነገረ ክርስቶስ ክፍል ፪፻፳፮
"ጌታ ሆይ፥ ማን ነህ አለው። እርሱም፦ አንተ የምታሳድደኝ እኔ ኢየሱስ ነኝ የመውጊያውን ብረት ብትቃወም ለአንተ ይብስብኻል አለው" (የሐዋ. ሥራ ፱፣፭)።

ከትንሣኤ በኋላ በኢየሱስ ክርስቶስ መሳደድ የለበትም። ነገር ግን የምእመናን ራስ፣ የቤተ ክርስቲያን አካል ስለሆነ ምእመናን መከራ ሲደርስባቸው የምእመናንን ስደትና መከራ የራሱ ስደትና መከራ እንደሆነ አስቦ ሳውልን ለምን ታሳድደኛለህ? ብሎታል። ሳውልም ተጸጽቶና እርሱን ኢየሱስ ክርስቶስን አምኖ ክርስቲያን ሆነ። ወንጌልን በየሀገሩ በማስተማሩም ብርሃነ ዓለም ቅዱስ ጳውሎስ ለመባል በቃ። ክርስቶስ የወይን ግንድ ነው። እኛ ምእመናን ደግሞ ቅርንጫፎቹ ነን። ቅርንጫፍ ከግንዱ ካልተለየ ለምልሞ፣ አብቦ ጥሩ ፍሬን ያፈራል። እኛም ከኢየሱስ ክርስቶስ ካልተለየን በመልካም ሥራ አሸብርቀን ገነት መንግሥተ ሰማያት እንገባለን።

© በትረማርያም አበባው

የፌስቡክ ገጼ:- Betremariam Abebaw
https://www.facebook.com/profile.php?id=100075547015721 ነው።

የዩቲይብ ቻናሌ:- ንሕነ ዘክርስቶስ
@edenawizechristos?si=6V4y-73OM3LTzhAf' rel='nofollow'>https://youtube.com/@edenawizechristos?si=6V4y-73OM3LTzhAf ነው።

ክፍል ፪፻፳፯ ይቀጥላል


ነገረ ክርስቶስ ክፍል ፪፻፳፭
"እንሆ፥ ሰማያት ተከፍተው የሰው ልጅም በእግዚአብሔር ቀኝ ቆሞ አያለኹ አለ" (የሐዋ. ሥራ ፯፣፶፮)።

ቅዱስ እስጢፋኖስ ስለኢየሱስ ክርስቶስ እንዲህ ብሎ መሰከረ። የሰው ልጅ የእግዚአብሔር ልጅ ኢየሱስ ክርስቶስን በእግዚአብሔር ቀኝ ቆሞ አየ። እግዚአብሔር በሁሉ ቦታ ያለ ስለሆነ ይህ ቀኙ ነው ይህ ግራው ነው ተብሎ ተወስኖ የሚነገርለት አይደለም። ብዙ ጊዜ ሥልጣኑን ቀኝ ብሎ ይገልጸዋል። ስለዚህ ኢየሱስ ክርስቶስን በእግዚአብሔር ቀኝ ቆሞ አየሁት ማለቱ በእግዚአብሔርነት ሥልጣኑ አየሁት ማለቱ ነው። ከትንሣኤ በኋላ መራብ መጠማት መታመም ሳይኖርበት በአምላካዊ ግብር ጸንቶ ይኖራልና። ሰማያት ተከፈቱ ማለቱ ሰማይ የሚከፈት የሚዘጋ ሆኖ አይደለም። የተዘጋ ቤት ሲከፈት የቤቱ ምሥጢር እንደሚታወቅ ሁሉ ሰማያዊ ምሥጢር ተገለጠልኝ ሲል ሰማይ ተከፈተ አለ።

© በትረማርያም አበባው

የፌስቡክ ገጼ:- Betremariam Abebaw
https://www.facebook.com/profile.php?id=100075547015721 ነው።

የዩቲይብ ቻናሌ:- ንሕነ ዘክርስቶስ
@edenawizechristos?si=6V4y-73OM3LTzhAf' rel='nofollow'>https://youtube.com/@edenawizechristos?si=6V4y-73OM3LTzhAf ነው።

ክፍል ፪፻፳፮ ይቀጥላል


ነገረ ክርስቶስ ክፍል ፪፻፳፬
"ዕለት ዕለትም በመቅደስና በቤታቸው ስለ ኢየሱስ እርሱ ክርስቶስ እንደ ሆነ ማስተማርንና መስበክን አይተዉም ነበር" (የሐዋ. ሥራ ፭፣፵፪)።

የክርስትና አስተምህሮ ዋና ማዕከሉ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። ስለዚህ የሐዋርያት ቀዳሚ ትምህርት ስለእርሱ ማስተማር ነበር። ስለእርሱ ማስተማርን አይተውም ነበር። አይሁድ በኢየሱስ ክርስቶስ ስላላመኑ ሌላ መሲሕን ይፈልጉ ነበር። ስለዚህ ኢየሱስ እርሱ ክርስቶስ መሆኑን ሐዋርያት አብራርተው ነግረዋቸዋል። ጌታ ራሱም ብዙ ጊዜ መሲሑ እርሱ መሆኑ በቃልም፣ በተአምራትም ነግሯቸው አሳይቷቸውም ነበር። ነገር ግን እነርሱ የጠበቁት ከሮም ቅኝ ግዛት ነጻ የሚያወጣ ሥጋዊ ንጉሥን (መሲሕን) ነበር። ቅዱሳት መጻሕፍት ስለመሲሑ የተናገሩትን ትተው የራሳቸው ኅሊና የፈጠረውን መሲሕ ስለጠበቁ በኢየሱስ ክርስቶስ አላመኑም።

© በትረማርያም አበባው

የፌስቡክ ገጼ:- Betremariam Abebaw
https://www.facebook.com/profile.php?id=100075547015721 ነው።

የዩቲይብ ቻናሌ:- ንሕነ ዘክርስቶስ
@edenawizechristos?si=6V4y-73OM3LTzhAf' rel='nofollow'>https://youtube.com/@edenawizechristos?si=6V4y-73OM3LTzhAf ነው።

ክፍል ፪፻፳፭ ይቀጥላል


ነገረ ክርስቶስ ክፍል ፪፻፳፫
"በቀባኸው በቅዱሱ ብላቴናኽ በኢየሱስ ላይ___" (የሐዋ. ሥራ ፬፣፳፯)።

ኢየሱስ ክርስቶስ የተቀባ እየተባለ ይጠራል። ክርስቶስ ማለት ትርጉሙ ቅቡዕ (የተቀባ) ማለት ነው። የተቀባ ማለትም በአምላክነት የከበረ ማለት ነው። አፍቀርከ ጽድቀ ወዐመፃ ጸላዕከ በእንተዝ ቀብዐከ እግዚአብሔር ቅብዐ ትፍሥሕት እምእለ ከማከ እንዲል። እለከማከ ከተበሉት ከነቢያት የበለጠ የደስታ ዘይትን (አምላካዊ ክብርን) ቀባህ (አከበረህ) ተብሎ እንደተገለጸው ክርስቶስ ስለሰውነቱ ቅቡዕ ይባላል። ስለሰውነቱ ራሱን የሰው ልጅ እያለ ይገልጽ እንደነበረው ሁሉ በዚህ አግባብ ቅቡዕ እየተባለ ይጠራል። በቀባኽው በቅዱሱ ብላቴናህ የሚለውም ስለሰውነቱ የተነገረ መሆኑን ልብ ማድረግ ይገባል። በመቅባት (በማክበር) ሦስቱ አካላት አንድ ናቸው። ተለይቶ አንዱ ቢጠራ እንኳ ሁለቱንም የሚገልጽ አነጋገር መሆኑን ደጋግመን ተመልክተናል።

© በትረማርያም አበባው

የፌስቡክ ገጼ:- Betremariam Abebaw
https://www.facebook.com/profile.php?id=100075547015721 ነው።

የዩቲይብ ቻናሌ:- ንሕነ ዘክርስቶስ
@edenawizechristos?si=6V4y-73OM3LTzhAf' rel='nofollow'>https://youtube.com/@edenawizechristos?si=6V4y-73OM3LTzhAf ነው።

ክፍል ፪፻፳፬ ይቀጥላል


ነገረ ክርስቶስ ክፍል ፪፻፳፪
"መዳንም በሌላ በማንም የለም እንድንበት ዘንድ የሚገ፟ባ፟ን ለሰዎች የተሰጠ ስም ከሰማይ በታች ሌላ የለምና" (የሐዋ. ሥራ ፬፣፲፪)።

መዳን ያለው በእግዚአብሔር ነው። በትንቢተ ኢሳይያስ "እኔ እግዚአብሔር ነኝ፥ ከእኔ ሌላም የሚያድን የለም" ብሎ መዳን የሚገኝ ከእግዚአብሔር መሆኑን ገልጿል። ኢየሱስ ክርስቶስም እግዚአብሔር ስለሆነ መዳን በሌላ በማንም የለም በኢየሱስ ክርስቶስ እንጂ ተብሎ ተገልጿል። ይህ አነጋገር በባህርይው የሚያድን እግዚአብሔር ብቻ መሆኑን የሚያመለክት አነጋገር ነው።

ከእግዚአብሔር በተቀበሉት የማዳን ጸጋ የሚያድኑ ቅዱሳን ግን አሉ። እነርሱ በጸጋ ያድናሉ። "አገልጋይ የሆነ መልአክ ሩፋኤል ወደ ጦቢት ተላከ ጦብያንም በራጉኤል አገር ከሞት አዳነው" እንዲል (፩ኛ መቃ. ፭፣፲፱)። ሩፋኤል እንዳዳነ በዚህ ተገልጿል። ሩፋኤልም ሌሎች ቅዱሳንም ማዳናቸው የጸጋ ነው። የእግዚአብሔር ማዳን ግን የባሕርይው ስለሆነ ከሰማይ በታች ሌላ የሚያድን የለም አለ።

© በትረማርያም አበባው

የፌስቡክ ገጼ:- Betremariam Abebaw
https://www.facebook.com/profile.php?id=100075547015721 ነው።

የዩቲይብ ቻናሌ:- ንሕነ ዘክርስቶስ
@edenawizechristos?si=6V4y-73OM3LTzhAf' rel='nofollow'>https://youtube.com/@edenawizechristos?si=6V4y-73OM3LTzhAf ነው።

ክፍል ፪፻፳፫ ይቀጥላል


ነገረ ክርስቶስ ክፍል ፪፻፳፩
"የአብርሃምና የይሥሐቅ የያዕቆብም አምላክ፥ የአባቶቻችን አምላክ፥ እናንተ አሳልፋችኹ የሰጣችኹትንና ሊፈታው ቈርጦ ሳለ በጲላጦስ ፊት የካዳችኹትን ብላቴናውን ኢየሱስን አከበረው" (የሐዋ. ሥራ. ፫፣፲፫)

ብላቴናውን ኢየሱስን አከበረው ማለት አምላክነቱን በደመና ሁኖ የምወደው ልጄ ይህ ነው ብሎ አብ ገለጠው ማለት ነው። የአብርሃምና የይስሐቅ የያዕቆብም አምላክ ተብሎ ስለአብ የተነገረ ቢሆንም "አምላክ" መባል ሦስቱ አካላት በአንድነት የሚጠሩበት ስለሆነ ወልድም አምላክ ነው። መንፈስ ቅዱስም አምላክ ነው። ጌታ የአብርሃም የይስሐቅ የያዕቆብ አምላክ እየተባለ ተጠርቷል። በዚህም የደጋጎች አምላክ እንደሆነና በደጋጎች ቅዱሳን መጠራት እንደሚፈልግ እንረዳለን።

© በትረማርያም አበባው

የፌስቡክ ገጼ:- Betremariam Abebaw
https://www.facebook.com/profile.php?id=100075547015721 ነው።

የዩቲይብ ቻናሌ:- ንሕነ ዘክርስቶስ
@edenawizechristos?si=6V4y-73OM3LTzhAf' rel='nofollow'>https://youtube.com/@edenawizechristos?si=6V4y-73OM3LTzhAf ነው።

ክፍል ፪፻፳፪ ይቀጥላል


ነገረ ክርስቶስ ክፍል ፪፻፳
"ጴጥሮስ ግን፦ ብርና ወርቅ የለኝም ይህን ያለኝን ግን እሰጥኻለኹ በናዝሬቱ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ተነሣና ተመላለስ አለው" (የሐዋ. ሥራ ፫፣፮)።

"ኵሉ ብነ እንዘ አልብነ ኵሉ" ሁሉ ሳይኖረን ሁሉ አለን እንዲሉ። ሐዋርያት የገንዘብ ድኻዎች የጸጋ እግዚአብሔር ሀብታሞች ነበሩ። በዘመናችን በሐዋርያት እግር የተተኩት አንዳንድ ጳጳሳትን ስንመለከት ደግሞ የገንዘብ ሀብታሞች የጸጋ እግዚአብሔር ድኻዎች ሆነው እናገኛቸዋለን። ሐዋርያት ሰውን የሚያድኑት ከፈጣሪያቸው ከኢየሱስ ክርስቶስ ባገኙት የመፈወስ ጸጋ ነው።

እነ ቅዱስ ጴጥሮስ ድውያንን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ይፈውሱ ነበር። የእርሱ ስም ከኃያላን ሁሉ የበለጠ ታላቅ ኃያል ነውና። ስለሆነም በከበረ ቦታ፣ በከበረ ጊዜ ይነገራል እንጂ በቀልዱም በዋዛ ፈዛዛውም ኢየሱስ ኢየሱስ እያሉ መጥራት ተገቢ አይደለም። ክቡር ስም መጠራት ያለበት በክቡር ቦታና በከበረ ነገር ነው። በጸሎት ጊዜ ኢየሱስ ኢየሱስ ኢየሱስ ዘሠረፀ እም ቤተ ሌዊ ኮሬባዊ መለኮታዊ እምድንግል ተወልደ እያልን እናመሰግነዋለን።

© በትረማርያም አበባው

የፌስቡክ ገጼ:- Betremariam Abebaw
https://www.facebook.com/profile.php?id=100075547015721 ነው።

የዩቲይብ ቻናሌ:- ንሕነ ዘክርስቶስ
@edenawizechristos?si=6V4y-73OM3LTzhAf' rel='nofollow'>https://youtube.com/@edenawizechristos?si=6V4y-73OM3LTzhAf ነው።

ክፍል ፪፻፳፩ ይቀጥላል


ነገረ ክርስቶስ ክፍል ፪፻፲፱
"እግዚአብሔርንም እያመሰገኑ በሕዝብ ሁሉ ፊት ሞገስ ነበራቸው። ጌታም የሚድኑትን ዕለት ዕለት በእነርሱ ላይ ይጨምር ነበር" (የሐዋ.ሥራ ፪፣፵፯)።

ጌታ አንድ ጊዜ ተሰቅሎ ዓለምን አድኖታል። እግዚአብሔር አድኖኛል እያሉ ለክፉ ሥራቸው ማስተባበያ የሚሰጡ አንዳንድ አሳዛኝ ሰዎች አሉ። እግዚአብሔር የእርሱን የማዳን ድርሻ በመስቀል ላይ ፈጽሟል። የሰው ድርሻ ግን ይቀራል። ሰው እግዚአብሔር ያደረገለትን የማዳን ሥራ አምኖ መጠመቅና መልካም ሥራ መሥራት ይጠበቅበታል። ይህን ሳያደርግ ድኛለሁ ማለት ግን ራስን ማታለል ነው። "ጌታም ዕለት ዕለት የሚድኑትን በእነርሱ ላይ ይጨምር ነበር" ተብሎ የተገለጸው ድኅነት የሰውን ልጅ ነጻ ፈቃድ መሠረት አድርጎ ለሰው የሚፈጸም እንደሆነ የሚያስረዳ ኃይለ ቃል ነው። ምእመናን እያመኑ እየተጠመቁ መልካም ሥራን እየሠሩ ከክርስቶስ የማዳን ሥራ ይሳተፋሉ እንጂ ሳያምኑ፣ ሳይጠመቁና መልካም ሥራን ሳይሠሩ ዝም ብሎ ድኛለሁ በማለት ከክርስቶስ የማዳን ሥራ መሳተፍ አይቻልም።

© በትረማርያም አበባው

የፌስቡክ ገጼ:- Betremariam Abebaw
https://www.facebook.com/profile.php?id=100075547015721 ነው።

የዩቲይብ ቻናሌ:- ንሕነ ዘክርስቶስ
@edenawizechristos?si=6V4y-73OM3LTzhAf' rel='nofollow'>https://youtube.com/@edenawizechristos?si=6V4y-73OM3LTzhAf ነው።

ክፍል ፪፻፳ ይቀጥላል

Показано 20 последних публикаций.