በትረማርያም አበባው Betremariam Abebaw


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: Религия


አቀድም አእኵቶቶ ለእግዚአብሔር

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
Религия
Статистика
Фильтр публикаций


🧡 መዝሙረ ዳዊት ክፍል 9 🧡

🧡መዝሙር ፹፩፡- እግዚአብሔር በአማልክት መካከል እንደቆመና በአማልክትም መካከል እንደሚፈርድ

🧡መዝሙር ፹፪፡- ዳዊት እግዚአብሔርን አንተ ብቻ ልዑል እንደሆንክ አሕዛብ ይረዱ ዘንድ በመቅሠፍት ምታቸው እንዳለ

🧡መዝሙር ፹፫፡- በእግዚአብሔር ቤት የሚኖሩ ሰዎች ብፁዓን እንደሆኑ
-የአማልክት አምላክ በጽዮን እንደሚታይ
-እግዚአብሔር ምጽዋትንና እውነትን እንደሚወድ

🧡መዝሙር ፹፬፡- እግዚአብሔር ምሕረቱን እንደሚሰጥ

🧡መዝሙር ፹፭፡- እግዚአብሔር መሓሪና ይቅር ባይ እንደሆነ
-እግዚአብሔር መዓቱ የራቀ ምሕረቱ የበዛ እውነተኛ አምላክ እንደሆነ

🧡መዝሙር ፹፮፡- እግዚአብሔር የጽዮንን ደጆች እንደሚወድ
-እግዚአብሔር ለሕዝቡ በመጽሐፍ እንደሚነግራቸው

🧡መዝሙር ፹፯፡- ዳዊት የድኅነቴ አምላክ እግዚአብሔር ሆይ ጸሎቴን ስማ ብሎ እንደጸለየ

🧡መዝሙር ፹፰፡- እግዚአብሔር ከመረጣቸው ጋር ቃል ኪዳንን እንዳደረገ
-እግዚአብሔር በቅዱሳን ምክር ክቡር እንደሆነ
-ሰማያትም ምድርም የእግዚአብሔር እንደሆነች
-የእግዚአብሔር የዙፋኑ መሠረት ፍትሕና ርትዕ እንደሆኑ
-እልልታን የሚያውቅ ሕዝብ ብፁዕ እንደሆነ

🧡መዝሙር ፹፱፡- እግዚአብሔር ከዓለም መፈጠር በፊት እንደነበረ
-የሰው ልጅ እድሜ ሰባ ቢበዛም ሰማንያ እንደሆነ

🧡መዝሙር ፺፡- እግዚአብሔር ከሚያስደነግጥ ነገር ሁሉ እንደሚያድን

🧡የዕለቱ ጥያቄ🧡
፩. እግዚአብሔር ከሚወዳቸው መካከል ያልሆነው የቱ ነው?
ሀ. ሽንገላ
ለ. ምጽዋት
ሐ. እውነት
መ. ቅንነት

https://youtu.be/MvC1bh6pX3U?si=sW0ZF1MIZXV8NmR3


✔️መልስ፦ መዝሙር 72 ስለትሩፋን የተጻፈ ነው። ስለዚህ ትሩፋን የባቢሎናውያንን ተድላ ደስታ አይተው ይቀኑ እንደነበረ ያመለክታል። ለሞታቸው መጣጣር የለውም ማለት ሰውን ለመግደል ዕረፍት የላቸውም ማለት ነው። ከሰው ጋር አልተገረፉም ማለት እነርሱ ሁሉን ፈጅተው ተረፉ ማለት ነው።

▶️፴፮. "በሰማይ ያለኝ ምንድን ነው? በምድርስ ውስጥ ከአንተ ዘንድ ምን እሻለሁ?" ይላል (መዝ.72፥25)። ምን ለማለት ነው?

✔️መልስ፦ እግዚአብሔር ትሩፋንን የወቀሰበት አነጋገር ነው። በሰማይ ምን አለኝ ማለቱ እናንተን ልጠብቅ ነው እንጂ በሰማይ መላእክትን እጠብቃለሁን ለማለት ነው። በምድርስ ከአንተ ዘንድ ምን እሻለሁ ማለት አንተን እሻለሁ እንጂ ማለት ነው።

▶️፴፯. "በምድርም መካከል መድኃኒትን አደረገ" ይላል (መዝ.73፥12)። ይህ ምን ተብሎ ይተረጎማል?

✔️መልስ፦ የምድር መካከል፣ የምድር እንብርት እየተባለች የምትጠራው ኢየሩሳሌም ናት። ስለዚህ በምድር መካከል መድኃኒትን አደረገ ማለት አዳምን ፈጥሮ ድኅነትን አደረገ ማለት ነው።

▶️፴፰. "ጊዜውን ስቀበል እኔ በቅን እፈርዳለሁ። ምድርና በእርሷ ውስጥ የሚኖሩት ሁሉ ቀለጡ እኔም ምሰሶችዋን አጠናሁ" ይላል (መዝ.74፥2-3)። እዚህ ላይ ተናጋሪው ማን ነው? ምን ማለትስ ነው?

✔️መልስ፦ ተናጋሪው ዳዊት ነው። ይህ የተነገረላቸው ደግሞ እነ ሕዝቅያስ ናቸው። ጊዜውን ስቀበል እኔ በቅን እፈርዳለሁ ማለት ጊዜውን ባገኘሁ ጊዜ እፈርዳለሁ ይላል። በእርሷ ውስጥ የሚኖሩ ሁሉ ቀለጡ ማለት በለኪሶን የሚኖሩ ሰዎች ጠፉ ማለት ነው። እኔ ምሰሶዎቿን አጸናሁ ሲል ኃያላኖቿን በሞት ለየሁ ማለት ነው። ከዚህ ላይ ተናጋሪው ልዑል እግዚአብሔር ነው።

▶️፴፱. "አቤቱ መንገድህ በመቅደስ ውስጥ ነው። አቤቱ ውኆች አዩህ ውኆችም አይተውህ ፈሩ። ጥልቆች ተነዋወጡ ውኆችም ጮኹ። ደመኖች ድምፅን ሰጡ ፍላጾችህም ወጡ። የነጎድጓድህ ድምፅ በዐውሎ ነበረ። መብረቆች ለዓለም አበሩ ምድር ተናወጠች ተንቀጠቀጠችም። መንገድህ በባሕር ውስጥ ነው። ፍለጋህም በብዙ ውኆች ነው አረማመድህም አልታወቀም" ይላል (መዝ.76፥13-19)። ትርጓሜው ምንድን ነው?

✔️መልስ፦ አቤቱ መንገድህ በመቅደስ ውስጥ ነው ማለት ሕግህ በቤተ መቅደስ ይነገራል ማለት ነው። ውሆች አዩህ ሲል ውሃ ዐይን ኖሮት የሚያይ ሆኖ አይደለም። ባሕረ ኤርትራ ፈለገ ዮርዳኖስ በአንተ አማካኝነት ተከፍለው እስራኤላውያን ተሻገሩ ለማለት ነው። ደመኖች ድሞፅን ሰጡ ማለት መዓትህ ሲደረግ ደመና እሳትን በረዶን አዘነበ ማለት ነው። መንገድህ በበሕር ውስጥ ነው ማለት ባሕርይህ አይታወቅም አይመረመርም ማለት ነው።

▶️፵. "የእግዚአብሔር ቍጣ በላያቸው መጣ ከእነርሱም ከፍ ያሉትን ገደለ። የእስራኤልንም ምርጦች አሰናከለ" ይላል (መዝ.77፥31)። የእስራኤልንም ምርጦች አሰናከለ ሲል ምን ማለት ነው?

✔️መልስ፦ የእስራኤል ምርጦች የተባሉ ለክህነት ለመንግሥት የተመረጡ እስራኤላውያን ናቸው። አሰናከለ ማለት በሞት ወሰዳቸው ማለት ነው።


© በትረ ማርያም አበባው


✝️የዩቲዩብ ቻናሌ:- ንሕነ ዘክርስቶስ https://youtube.com/@edenawizechristos?si=6V4y-73OM3LTzhAf ነው።

🌻የፌስቡክ ገጼ Betremariam Abebaw https://www.facebook.com/profile.php?id=100075547015721 ነው።


✔️መልስ፦ ከዚህ የተጠቀሱት ክፉዎች መላእክት የሚባሉት መደባቸው ከቅዱሳን መላእክት ሆኖ ነገር ግን ለአምላካቸው ከመቅናታቸው የተነሣ አጥፊዎችን ለመቅጣት የሚፋጠኑ ናቸው። ክፉ ያሰኛቸው ይህ ነው እንጂ በደል በድለው አይደለም። በነገደ ሚካኤል ሥር የሚመሩ ናቸው።

▶️፳. "አቤቱ የተገዳደሩህን መገዳደራቸዉን ለጎረቤቶቻችን ሰባት እጥፍ በብብታቸዉ ክፈላቸው" ይላል (መዝ.78፥12)። በብብታቸዉ ክፈላቸዉ ሲል ምን ማለት ነው?

✔️መልስ፦ በብብታቸው ክፈላቸው ማለት በጎረቤቶቻቸው አማካኝነት ፍዳቸውን አምጣባቸው ማለት ነው።

▶️፳፩. "የእንባችንን እንጀራ ትመግበናለህ። እንባችንንም በስፍር ታጠጣናለህ" ሲል ትርጉሙ ምን ማለት ነው (መዝ.79፥5)?

✔️መልስ፦ የእንባችንን እንጀራ ትመግበናለህ ማለት እንባችን የፈሰሰበትን እንጀራ ትመግበናለህ ማለት ነው። እንባችንንም በስፍር ታጠጣናለህ ማለት በኀዘን ሳሉ መጠጥ ሲያቀርቡላቸው እንባቸው በመጠጡ እየፈሰሰ ይጠጡታልና ነው። ይህ ስለ መቃብያን የተነገረ ነው።

▶️፳፪. መዝ.80፥6 ላይ "ጀርባውን ከመስገጃው መለሰ እጆቹም በቅርጫት ተገዙ" ሲል ትርጉሙ ምንድን ነው?

✔️መልስ፦ ይህ ስለዮሴፍ የተነገረ ነው። ዮሴፍ ጀርባውን ከመስገጃው መለሰ ማለት የግብፅን ጣዖት አለማምለኩን ያመለክታል። እጆቹም በቅርጫት ተገዙ ማለት ዮሴፍ በግብፅ ተሹሞ ሳለ መኳንንቱ ወደ ጣዖቱ እንሂድ ሲሉት እኔማ መች ያደርሰኛል እያለ ቅርጫት ሲያነሣ ሲጥል ይውል ነበርና ይህን ለመግለጽ ነው።

▶️፳፫. መዝ.77፥43 "በጣኔዎስ በረሃ ያደረገውን ድንቁን" ይላል። በጣኔዎስ በረሃ ያደረገው ተአምር ምንድን ነው? በረሃው የት ይገኛል?

✔️መልስ፦ የጣኔዎስ በረሃ በግብጽ ሀገር የሚገኝ በረሃ ነው። ጣኔዎስ የግብጽ አካል እንደመሆኗ እግዚአብሔር በግብጽ ዘጠኝ ተአምራትን አድርጓል።

▶️፳፬. "አፋቸውን በሰማይ አኖሩ። አንደበታቸውም በምድር ውስጥ ተመላለሰ" ይላል (መዝ.72፥9)። ምን ማለት እንደሆነ ቢያብራሩልን?

✔️መልስ፦ አፋቸውን በሰማይ አኖሩ ማለት በአንደበታቸው በሰማይ አምላክ የለም አሉ። አንደበታቸውም በምድር ተመላለሰ ማለት በምድርም አምላክ የለም ብለው ካዱ ማለት ነው። ስለከሓድያን ስለእነ ናቡከደነፆር የተነገረ ነው።

▶️፳፭. "ከሕልም እንደሚነቃ አቤቱ ስትነቃ ምልክታቸውን ታስነውራለኽ" ይላል (መዝ.72፥20)። ትርጓሜው ምንድን ነው?

✔️መልስ፦ ከሕልም የሚነቃ ሰው ፈጥኖ እንደሚነቃ ጌታ ሆይ ከእስራኤል ክፉዎችን አጥፋቸው ማለት ነው።

▶️፳፮. "የልቤ አምላክ ሆይ ልቤና ሥጋዬ አለቀ። እግዚአብሔር ግን ለዘለዓለም ዕድል ፈንታዬ ነው" ይላል (መዝ.72፥26)። ልቤና ሥጋዬ አለቀ ሲል ምን ማለት ነው?

✔️መልስ፦ ልቤና ሥጋዬ አለቀ ማለት በፈጣሪዬ አምኜ ነፍሴም ሥጋዬም በክብር ተፈጸመ ማለት ክብር በዛለት ማለት ነው።

▶️፳፯. "አንተ ባሕርን በኀይልኽ አጸናኻት። አንተ የእባቦችን ራስ በውሃ ውስጥ ሰበርኽ" ይላል (መዝ.73፥13)። የእባቦችን ራስ በውሃ ውስጥ ሰበርኽ ሲባል ምን ማለት ነው?

✔️መልስ፦ የእባብ ራስ ከተመታ መንቀሳቀስ እንደማይችል በናጌብና በአድማስ መካከል ባለው ውቅያኖስ የምትኖረዋ ሌዋታን የተባለች ፍጥረት ከዚያ ውጭ እንዳትንቀሳቀስ በእግዚአብሔር መወሰኗን ያመለክታል።

▶️፳፰. "ሰው በፈቃዱ ያመሰግንኻልና ከኅሊናቸው ትርፍም በዓልኽን ያደርጋሉ" ይላል (መዝ.75፥10)። ከኅሊናቸው ትርፍም በዓልኽን ያደርጋሉ ሲባል ምን ማለት ነው?

✔️መልስ፦ ከኅሊናቸው ትርፍ ማለት በልተው ጠጥተው ከተረፈ ገንዘባቸው ሰጥተው በዓልህን ያደርጋሉ ማለት ያከብራሉ ማለት ነው።

▶️፳፱. "ይህ ድካሜ ነው አልኹ። የልዑል ቀኝ እንደ ተለወጠ የእግዚአብሔርን ሥራ አስታወስኹ። የቀደመውን ተአምራትኽን አስታውሳለኹና በምግባርኽም ዅሉ እናገራለኹ። በሥራኽም እጫወታለኹ" ይላል (መዝ.76፥10-12)። የልዑል ቀኝ እንደ ተለወጠ እና በሥራኽም እጫወታለኹ ሲል ምን ማለት ነው?

✔️መልስ፦ የልዑል ቀኝ እንደተለወጠ ማለት እግዚአብሔር በሥልጣኑ ሳያጠፋን ማለት ቸርነቱ በዝቶልን ማለት ነው። በሥራህ እጫወታለሁ ማለት አድርግ ያልከኝን ተግባር አድርጌ እኖራለሁ ማለት ነው።

▶️፴. "ከግብጽ በወጣ ጊዜ ለዮሴፍ ምስክር አቆመው። ያላወቅኹትን ቋንቋ ሰማኹ። ጫንቃውን ከሸክም እጆቹንም በቅርጫት ከመገዛት አራቅኹ" ይላል (መዝ.80፥5-6)። ያላወቅኹትን ቋንቋ የተባለው ምን ዓይነት ቋንቋ ነው?

✔️መልስ፦ ይህ ስለዮሴፍ የተነገረ ነው። ዮሴፍ ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ ግብፅ ሲሄድ የግባፃውያንን ቋንቋ ባለማወቁ እንደተቸገረ የሚገልጽ ነው።

▶️፴፩. "ከግብጽ ምድር ያወጣኹኽ እኔ እግዚአብሔር አምላክኽ ነኝና አፍኽን አስፋ እሞላዋለኹም" ይላል (መዝ.80፥10)። አፍኽን አስፋ እሞላዋለኹም ማለት ምን ማለት ነው?

✔️መልስ፦ አፍህን አስፋ ማለት በጸሎት ለምነኝ ማለት ነው። እሞላዋለሁም ማለት የለመንከኝን አድርግልሀለሁ ማለት ነው።

▶️፴፪. "አቤቱ ፍርድህን ለንጉሥ ስጥ። ጽድቅህንም ለንጉሥ ልጅ። ሕዝብህን በጽድቅ ችግረኞችህንም በፍርድ ይዳኝ ዘንድ። ተራሮችና ኰረብቶች ለሕዝብህ ሰላምን ይቀበሉ" ይላል (መዝ.71፥1-3)። እዚህ ላይ ንጉሥና የንጉሥ ልጅ ያለው ራሱን ዳዊትንና ልጁን ነው?

✔️መልስ፦ አዎ። መዝሙር 71ን ዳዊት ስለልጁ ሰሎሞን ተናግሮታል። ስለዚህ ንጉሥ ያለው ዳዊትን የንጉሥ ልጅ ያለው ደግሞ ሰሎሞንን ነው። በምሥጢር ንጉሥ ያለው አብን የንጉሥ ልጅ ያለው ወልድን ተብሎ መተርጎም ይችላል። ወልድ የአብ የባሕርይ ልጅ ነውና።

▶️፴፫. "የተርሴስና የደሴቶች ነገሥታት ስጦታን ያመጣሉ። የዓረብና የሳባ ነገሥታት እጅ መንሻን ያቀርባሉ" ይላል (መዝ.71፥10)። ይህ በዋናነት ስለ ሰሎሞን ወይስ ስለክርስቶስ የተነገረ ነው? ቢያብራሩልኝ።

✔️መልስ፦ በዋናነት ስለሰሎሞን የተነገረ ቢሆንም ስለክርስቶስም ያስተረጉማል። የነቢያት ቃል አንዱ ብዙ ሐሳቦችን የሚያስተላልፍ ነውና። ለጊዜው ሰሎሞን ጠቢብ ንጉሥ ስለነበረ የተርሴስ፣ የደሴቶች ነገሥታት የተለያዩ ስጦታዎችን አመጡለት ማለት ነው። ስለክርስቶስ ሲነገር ደግሞ ሰብአ ሰገል እጅ መንሻ አመጡለት ማለት ነው።

▶️፴፬. "በምድር ውስጥ በተራሮች ላይ መጠጊያ ይሆናል። ፍሬውም ከሊባኖስ ይልቅ ከፍ ከፍ ይላል። እንደ ምድር ሣር በከተማ ይበቅላል። ስሙ ለዘላለም ቡሩክ ይሆናል። ከፀሐይም አስቀድሞ ስሙ ይኖራል። የምድር አሕዛብ ሁሉ በእርሱ ይባረካሉም አሕዛብ ሁሉ ያመሰግኑታል" ይላል (መዝ.72፥16-17)። የዚህ ንባብ ትርጓሜው ምንድን ነው?

✔️መልስ፦ የሰሎሞን መንግሥት ለተቸገሩት መጠጊያ እንደሆነ ያመለክታል። ፍሬውም ከሊባኖስ ይልቅ ከፍ ከፍ ይላል ማለት ፍሬ ነገሩ ጥበቡ ከዛፍ ፍሬ ይበዛል ማለት ነው። ሰሎሞን በኢየሩሳሌም ከተማ መኖሩን ለመግለጽ በከተማ ይበቅላል ተብሏል። ስሙ የከበረ ነው ተብሏል። ለክርስቶስ ሲነገር በባሕርይው የሚመሰገን መሆኑን መግለጽ ነው። አሕዛብ ሁሉ ያመሰግኑታል ማለት በእርሱ አምነው ያመሰግኑታል ማለት ነው።

▶️፴፭. "የኃጢአተኞችን ሰላም አይቼ በዐመፀኞች ቀንቼ ነበርና። ለሞታቸው መጣጣር የለውምና። ኃይላቸውም ጠንካራ ነውና። እንደ ሰው በድካም አልሆኑም። ከሰው ጋርም አልተገረፉም" ይላል (መዝ.72፥3-5)። ይህን ንባብ ግልጽ ቢያደርጉልኝ።


💙💙 የጥያቄዎች መልስ ክፍል 140 💙💙

▶️፩. መዝ.77፥25 ላይ "የመላእክትንም እንጀራ የሰው ልጆች በሉ" ሲል ምንን ለማመልከት ነው?

✔️መልስ፦ የመላእክት እንጀራ የሚባለው ምስጋና ነው። መላእክት ረቂቃን በመሆናቸው ሥጋዊ ምግብ አያስፈልጋቸውም። ምግባቸው ምስጋናቸው ነውና። ስለዚህ የመላእክትን እንጀራ የሰው ልጆች በሉ ማለት ሰዎች የመላእክትን ምስጋና አመሰገኑ ማለት ነው።

▶️፪. መዝ.73፥14 ላይ "አንተም የዘንዶውን ራሶች ቀጠቀጥህ። ለኢትዮጵያ ሰዎች ምግባቸውን ሰጠሃቸው" ይላል። ምን ማለት ነው?

✔️መልስ፦ የዘንዶውን ራስ ቀጠቀጥህ የተባለ ብሔሞት ነው። ብሔሞት ዓለም ላይ ካሉ ፍጥረታት እጅግ በጣም ግዙፉ ደማዊ ፍጥረት ነው። እና ብሔሞት የሚኖረው በናጌብና በአድማስ መካከል ተወስኖ ነው። ስለዚህ የዘንዶውን ራስ ቀጠቀጥክ ማለት ዘንዶ ራሱ ከተቀጠቀጠ እንደማይንቀሳቀስ ሁሉ ብሔሞትንም ከናጌብና ከአድማስ መካከል ውጭ እንዳይንቀሳቀስ አደረግኸው ማለት ነው። ለኢትዮጵያ ሰዎች ምግባቸውን ሰጠኻቸው ማለት እግዚአብሔር መጋቢ እንደመሆኑ ሰዎችን መገብካቸው ማለቱ ነው። ይኸውም በኢትዮጵያ የዓለሙን ሁሉ መናገር ነው።

▶️፫. መዝ.77፥65 ላይ "እግዚአብሔርም ከእንቅልፍ እንደሚነቃ ተነሣ። የወይን ስካር እንደ ተወው እንደ ኀያልም ሰው" ይላል። ይህ ክፍለ ንባብ ስለ ጌታችን አምላካችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ትንሣኤ እንደሆነ ይተረጎማል። ታዲያ "የወይን ስካር እንደተወው እንደ ኅያልም ሰው" ሲል ምን ማለቱ ነው?

✔️መልስ፦ የወይን ስካር ያለፈለት ኃያል ሰው ፈጥኖ እንደሚነሣ ሁሉ በወይን ስካር በተመሰለ ሞት የሞተ ክርስቶስ ፈጥኖ ከሙታን ተነሣ ማለት ነው። የወይን ስካር ያጋጠመው ኃያል ያንቀላፋል እንጂ አይሞትም። ክርስቶስንም በሥጋው ሞተ ብንለው በመለኮቱ ሕያው ነው እንለዋለንና በዚህ አንጻር የተነገረ ነው። ሐዋርያው ቅዱስ ጴጥሮስ ሞተ በሥጋ ወሐይወ በመንፈስ እንዳለ።

▶️፬. መዝ.71፥9 ላይ "በፊቱም ኢትዮጵያ ይሰግዳሉ። ጠላቶቹም ዐፈር ይልሳሉ" ይላል። ሐሳቡ ምን ለማለት ነው?

✔️መልስ፦ ይህ መዝሙር ስለሰሎሞን የተነገረ ነው። በፊቱ ኢትዮጵያ ይሰግዳሉ ማለትም የኢትዮጵያ ሰዎች እነ ማክዳ ለሰሎሞን እጅ መንሻ ይዘው ይቀርባሉ ማለት ነው። ጠላቶቹም አመድ ይመገባሉ ማለት የሰሎሞን ጠላቶች ይዋረዳሉ ማለት ነው።

▶️፭. "ከግብጽ የወይን ግንድ አመጣህ። አሕዛብን አባረርህ እርሷንም ተከልህ" ይላል (መዝ.79፥8)። የወይን ግንድ የተባለው ማን ነው?

✔️መልስ፦ ከዚህ የወይን ግንድ የተባሉ እስራኤላውያን ናቸው። ሙሉ ትርጉሙም እስራኤላውያንን ከግብጽ ባርነት ነጻ አውጥተህ ወደ ከነዓን አመጣሀቸው ማለት ነው።

▶️፮. "ሥጋን እንደ ዐፈር፣ የሚበሩትንም ወፎች እንደ ባሕር አሸዋ አዘነበላቸው" ይላል (መዝ.77፥27)። የሚበሩት ወፎች የተባሉ ምንድን ናቸው?

✔️መልስ፦ የሚበሩት ወፎች የተባሉት የሚበሉ የአዕዋፍ ዝርያዎችን ቆቅን፣ ዥግራን የመሳሰሉትን እግዚአብሔር ለእስራኤላውያን አብዝቶ አዘነመላቸው ማለት ነው።

▶️፯. "አንተ በዘለዓለም ተራራዎች ሆነህ በድንቅ ታበራለህ" ይላል (መዝ.75፥4)። ተራራዎች የተባሉት እነማን ናቸው?

✔️መልስ፦ የዘለዓለም ተራራዎች የተባሉ ቅዱሳን አበው ናቸው። በቅዱሳን አበው አድረህ እግዚአብሔር ሆይ በተአምራት ረድኤትህን ትሰጣለህ ማለት ነው።

▶️፰. "ተራራዎችና ኰረብታዎች ለሕዝብህ ሰላምን ይቀበሉ" ይላል (መዝ.71፥3)። ተራራዎችና ኮረብታዎች የተባሉት መልክአ ምድሩን ነው ወይስ ሌላ ምሥጢር አለው?

✔️መልስ፦ ከዚህ ላይ ተራራ ኮረብታ እያለ የተናገረው ስለመሬት መልክአ ምድር አይደለም። በተራራ የተመሰሉ ነገሥታት ሲሆኑ በኮረብታ የተመሰሉት ደግሞ መኳንንት ናቸው።

▶️፱. መዝ.77፥54 ላይ "ወደ መቅደሱ ተራራ ወሰዳቸው። ቀኙ ወደ ፈጠረችው ተራራ" ይላል። ቀኙ ወደ ፈጠረችው ሲል ምን ለማለት ነው?

✔️መልስ፦ ለእግዚአብሔር ቀኝ ሲነገር ሥልጣን ተብሎ ይተረጎማል። ስለዚህ በሥልጣኑ ወደ ፈጠረው ተራራ ማለት ነው።

▶️፲. መዝ.71፥5 ላይ "ፀሐይ በሚኖርበት ዘመን ሁሉ በጨረቃም ፊት ለልጅ ይኑር" ሲል ምን ማለት ነው?

✔️መልስ፦ ይህ ስለሰሎሞን ንግሥና የተነገረ ምረቃ ነው። ብዙ ዘመን ያኑርህ ለማለት ፀሐይ ሳታልፍ ወይም ጨረቃ ሳታልፍ አትለፍ ብሎታል። ንጉሥ ሆይ ሺ ዓመት ያንግሥህ እንደሚለው ነው።

▶️፲፩. "በፊቱም ኢትዮጵያ ይሰግዳሉ ጠላቶቹም ዐፈር ይልሳሉ" ይላል (መዝ.71፥9)። ኢትዮጵያ ተብላ የተጠራችው የአሁኗን ግዛት ብቻ የሚያጠቃልል ነው ወይስ ሌሎችም ካሉ ቢነግሩን።

✔️መልስ፦ በዚያ ዘመን የኢትዮጵያ ግዛት ከምን እስከምን እንደነበረ መጽሐፍ ቅዱሱ ወሰኑን አላስቀመጠልንም። ስለዚህ አለማወቅ ይገድበናል። በታሪክ ግን የኢትዮጵያ ግዛት ሰፊ እንደነበር ይነገራል።

▶️፲፪. "ዐይናቸው ስብ ስለ ሆነ ወጣ። ልባቸውም ከምኞታቸው ይልቅ አገኘ" ይላል (መዝ.72፥7)። ምን ማለት ነው?

✔️መልስ፦ ከዐይን ጉድፍ እንደሚወጣ ሁሉ ክፉ ሐሳብን ከልቡናቸው አወጡ ማለት ነው። ልባቸውም ከምኞታቸው ይልቅ አገኘ ማለት ከትዕቢት ወደ ትዕቢት ተሽጋገሩ ማለት ነው።

▶️፲፫. "ጽዋ በእግዚአብሔር እጅ ነውና ያልተቀላቀለ የወይን ጠጅ ሞላበት ከዚህ ወደዚያ አገላበጠው ነገር ግን አተላው አልፈሰሰም የምድር ኀጢአተኛዎች ሁሉ ይጠጡታል" ይላል (መዝ.74፥8)። ትርጉሙ ይብራራልን።

✔️መልስ፦ ጽዋዕ በእግዚአብሔር እጅ ነው ማለት በእግዚአብሔር እጅ መዓት አለ ማለት ነው። ያልተቀላቀለ የወይን ጠጅ ሞላበት ማለት ምሕረት የሌለው መዓትን አመጣ ማለት ነው። አተላው አልፈሰሰም ማለት ሁሉም መከራውን ተቀበሉ ከመከራው ያመለጠ የለም ማለት ነው። ይህ ስለእነ ሰናክሬም የተነገረ ነው።

▶️፲፬. "ስፍራው በሳሌም ማደሪያውም በጽዮን ነው" ይላል (መዝ.75፥2)። ይብራራልን።

✔️መልስ፦ ሳሌም ማለት ሰላም ፍቅር ማለት ነው። ስለዚህ ስፍራው በሳሌም ነው ማለት ሀገሪቱ በሰላም በፍቅር ኖረች ማለት ነው። ማደሪያውም በጽዮን ነው ማለት እግዚአብሔር ረድኤቱን በኢየሩሳሌም አደረገ ማለት ነው።

▶️፲፭. "ዝንቦችንም በላያቸው ሰደደባቸው በሏቸውም በጓጕንቸርም አጠፋቸው" ይላል (መዝ.77፥45)። ጓጒንቸር የሚባለው ምንድን ነው?

✔️መልስ፦ ጓጉንቸር የሚባለው እንቁራሪት ወይም ጉርጥ በመባል የሚታወቀው ነው። በውሃ ውስጥም በየብስም መኖር የሚችል ፍጥረት ነው።

▶️፲፮. "ፍሬያቸውን ለኵብኵባ ሥራቸውንም ለአንበጣ ሰጠ" ይላል (መዝ.77፥46)። ኲብኲባና አንበጣ ልዩነቱ ምንድን ነው?

✔️መልስ፦ ኩብኩባ የሚባለው ትንሹ ሲሆን አንበጣ የሚባለው ደግሞ ትልቁ ነው። ፌንጣ የመሰለ እህልን የሚያወድም ክንፋማ ፍጥረት ነው። የአንበጣ ትንሹ ኩብኩባ ይባላል።

▶️፲፯. "ወይናቸውን በበረዶ በለሳቸውንም በዐመዳይ አጠፋ" ይላል (መዝ.77፥47)። ዐመዳይ የሚባለው ምንድን ነው?

✔️መልስ፦ አመዳይ አመድ የመሰለ ከደመና የሚወርድ በረዷማ ነገር ነው።

▶️፲፰. "ቀንዳችሁን እስከ አርያም አታንሡ" ሲል ምን ማለቱ ነው (መዝ.74፥5)?

✔️መልስ፦ በሥልጣናችሁ በአርያም ያለ እግዚአብሔርን አታሳዝኑ ማለት ነው።

▶️፲፱. መዝ.77፥49 "መዓትህን መከራንም በክፉዎች መላእክት ሰደደ" ይላል። በክፉዎች መላእክት ሲል ምን ለማለት ነው?


....ጉባኤ ቤት vs መንፈሳዊ ኮሌጅ....
በሁለቱም የሚሰጠው ትምህርት ነገረ መለኮት ነው። በሁለቱም የሚሰበከው ነገረ ክርስቶስ፣ ነገረ ማርያም፣ ነገረ ቅዳሳን...ወዘተ ነው። ነገር ግን ጥንተ ጠላታችን ሰይጣን በሰዎች እያደረ በሁለቱ የተለያየ ትምህርት እንደሚሰጥና አንደኛው የአጽራረ ቤተክርስቲያን መፈልፈያ ሌላኛው የቤተክርስቲያን ተቆርቋሪ የሚወጣበት በማስመሰል እያስወራ የአንድ እናት ቤተክርስቲያን ልጆችን ሲከፋፍል ኖሯል። እውነታው ምንድን ነው? የሚለውን ግን ማወቅ ያስፈልጋል። እውነታው በጉባኤ ቤት እና በመንፈሳዊ ኮሌጆች መካከል የትምህርት አሰጣጥ ልዩነት እንጂ የትምህርት ልዩነት የለም። በደንብ ለማስረዳት ልሞክር። የጉባኤ ቤት/ መንፈሳዊ ኮሌጅ መሥራች ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። 12 ሐዋርያትን አስተምሮ በዕለተ ጰራቅሊጦስ መርቆ ወደ ዓለም እንዲያስተምሩ ልኳቸዋል።ሑሩ ወመሀሩ ውስተ ኩሉ አጽናፈ ዓለም ብሏቸዋል። በብሉይ ኪዳን በነቢዩ ኤርምያስ የተመሠረተ ጉባኤ ቤት እንደነበር ይነገራል። በኋላም ታዋቂው የእስክንድያ ትምህርት ቤት እና የአንጾኪያ ትምህርት ቤት እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ ሁለቱም ታላላቅ ቅዱሳን ሊቃውንት የወጡባቸው ጉባኤ ቤቶች ናቸው። የትምህርት አሰጣጣቸው ሁለቱም የተለያየ ነበር። ትምህርታቸው ግን አንድ ነው። ከሁለቱም ግን የወጡ አጽራረ ቤተክርስቲያን ግን ነበሩ።

በጉባኤ ቤት እያንዳንዷ የመጽሐፍ ቅዱስ ቃል ትተነተናለች። ለምሳሌ አንድ ማሳያ ላንሳ። "ክርስቶስ ተጠመቀ" የሚል ዓረፍተ ነገር ቢኖር መጀመሪያ መጠመቅ ምንድን ነው? ይባልና። መጠመቅ ማለት በውሃ መነከር በውሃ መዘፈቅ ተብሎ ይተረጎማል። [አንድን ቃል ለሰሚው በሚቀርብ ቋንቋ መተርጎም ነው]። ከዚያ በማን ተጠመቀ ቢሉ በዮሐንስ ተጠመቀ። የት ተጠመቀ ቢሉ በዮርዳኖስ ተጠመቀ። መቼ ተጠመቀ ቢሉ ጥር 11 በ30 ዓመቱ ተጠመቀ። ይላል በዚህ አያቆምም ነገሩን በምክንያት እያጎለመሰ ይሄዳል። በዮሐንስ ለምን ተጠመቀ ቢሉ ትሕትናን ለማስተማር። ንጉሥ ከካህን እንዲጠመቅ ለማስተማር እያለ ይተረጎማል። በምን ተጠመቀ ቢሉ በውሃ። በውሃ ለምን ተጠመቀ ውሃ እድፍን ያስለቅቃል። እሱም በጥምቀት ኃጢአታችንን ያስተሠርይልናልና። ውሃ ርካሽ ነው። ድሃውም ሀብታሙም ያገኘዋል። ድኅነት ለሁሉ እንደተሰበከ ለማጠየቅ ይባላል። በዮርዳኖስ ለምን ተጠመቀ ቢሉ ሰይጣን አዳም ገብሩ ለዲያብሎስ ሔዋን አመቱ ለዲያብሎስ ብሎ በእብነ ሩካም ጽፎ አስቀምጦበት ነበርና እንደሰውነቱ ተረግጦ እንደ አምላክነቱ አቅልጦ ለማጥፋት ይላል። በ30 ዓመቱ ለምን ተጠመቀ ቢሉ አዳም የ30 ዓመት ጎልማሳ የያዘውን ቁመና ይዞ ተፈጥሮ ስለበደለ ያንን ለመካስ። ጌታችን ራሱ ለምን ተጠመቀ? ቢሉ እጠቀም ብሎ ክብርን ሽቶ የተጠመቀ አይደለም። ለእኛ አርአያ ሊሆን ነው እንጂ። አንድም ማያትን ይቀድስ ዘንድ እየተባለ ይተረጎማል። ያው አንባቢን ላለማሰልቸት እዚህ ላቁም እንጂ እፎ ተጠምቀ ለምን እየተባለ በምሥጢር እየዋኘህ ብትውል ብታድር አያልቅም። ለእነዚህ ነገሮች ደግሞ ጉሥዐተ ልብ እንዳይሆን እንዲል እንዲል እየተባለ ማስረጃ ከሌላ መጻሕፍት እየተጠቀሰ ይቀርባል።

የመሠረተ እምነት (Doctrine) ሳይሆን የእይታ (Speculation) ልዩነቶች ግን በጉባኤ ቤትና በመንፈሳዊ ኮሌጆች ብቻ ሳይሆን ከጉባኤ ቤት ጉባኤ ቤትም ልዩነት አለ። ይህንም በደንብ ከመረመርነው ተለጥጦ የሚያበጣብጥ ሳይሆን ተቀራርበን ብናየው የንባብ ልዩነት እንጂ የምሥጢር ልዩነት የለውም። ለምሳሌ አንዷን ዕፀ ሕይወት ቅዱስ ማር ይሥሐቅ ዕፀ ሕይወት የተባለ ፍቅር ነው ብሎ ተርጉሞታል። ሌላኛው ሊቅ ቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ ደግሞ ሥጋሁ ወደሙ ብሎ ተርጉሞታል። እነዚህ ልዩነቶች አይደሉም።እነዚህን የመሳሰሉ ቃላትን እየመዘዙ ጉባኤ ቤትና መንፈሳዊ ኮሌጆችን ዓይንና አፈር ለማድረግ መጣር ግን አይገባም። ሁለቱም የቤተክርስቲያናችን አካላት ናቸው። ወደፊት በሁለቱም በኩል የሚወጡ ሊቃውንት ተቀራርበው የሚሠሩበት ጊዜ እንደሚኖር ተስፋ አደርጋለሁ። ጥሩ ጅምሮችንም እያየሁ ነው። የቀድሞ አባቶቻችን እነ ቅዱስ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ በዘመኑ የነበረውን አለማቀፋዊ ቋንቋ ያውቁ ነበር። ይህንንም ተጠቅመው ብዙ ቅዱሳት መጻሕፍትን ከግሪክ ከአረብኛ እየተረጎሙ አምጥተውልናል። አሁን ላይም የመንፈሳዊ ኮሌጅ ተማሪዎች ሀገር በቀሉን የትርጓሜ መንገድ አስቀድመው ቢያውቁ የኦርየንታል አብያተ ክርስቲያናትን ታሪክም የትምህርት ዘዴም በትክክል አዋሕደው ለማወቅ ይረዳቸዋል። የጉባኤ ቤት ደቀመዛሙርትም እንግሊዘኛና ሌሎች ቋንቋዎችን በመልመድ የውጩን ትምህርት በያዝነው ትርጓሜ እየመዘንን ደንበኛውን ለመያዝ ልክ ያልሆነውን ለመተው ይረዳናል። ስለዚህ በሁለቱ መካከል ምንም ዓይነት የትምህርት (Doctrine) ልዩነት ስለሌለ ልዩነት እንዳለ አስመስለው የሚያወሩ ሰዎችን ልንቀበላቸው አይገባም። ከጉባኤ ቤትም ከመንፈሳዊ ኮሌጅም ብዙ አጽራረ ቤተክርስቲያን ወጥተዋል። ከጌታ ተማሪዎችስ አንዱ ይሁዳ ክዶ የለምን። ይህ አይገርመንም። ሁለቱንም ከቀሣጥያን ልንጠብቃቸው ይገባናል እላለሁ።

© በትረማርያም አበባው


✝️የዩቲዩብ ቻናሌ:- ንሕነ ዘክርስቶስ https://youtube.com/@edenawizechristos?si=6V4y-73OM3LTzhAf ነው።

🌻የፌስቡክ ገጼ Betremariam Abebaw https://www.facebook.com/profile.php?id=100075547015721 ነው።




💗 መዝሙረ ዳዊት ክፍል 8 💗

💗መዝሙር ፸፩፡- ልዑል እግዚአብሔር ብቻውን ተአምራትን እንደሚያደርግ

💗መዝሙር ፸፪፡- እግዚአብሔር ቸር እንደሆነ
-እግዚአብሔርን መከተል እንደሚሻል

💗መዝሙር ፸፫፡- እግዚአብሔር ከዓለም አስቀድሞ ንጉሥ እንደሆነና በምድርም መካከል መድኃኒትን እንዳደረገ
-በጋንና ክረምትን የሚያፈራርቅ እግዚአብሔር እንደሆነ

💗መዝሙር ፸፬፡- በእግዚአብሔር ላይ ዐመፃን መናገር እንደማይገባ

💗መዝሙር ፸፭፡- እግዚአብሔር ግሩም እንደሆነ

💗መዝሙር ፸፮፡- ዳዊት እግዚአብሔርን አሰብኩት ደስ አለኝም እንዳለ
-የእግዚአብሔር ፍለጋው እንደማይታወቅ

💗መዝሙር ፸፯፡- የእግዚአብሔርን ምስጋና፣ ኃይሉንና ያደረገውን ተአምራት መናገር እንደሚገባ
-እግዚአብሔር መሓሪ እንደሆነ

💗መዝሙር ፸፰፡- ዳዊት ስለስምህ ክብር አቤቱ ታደገን፣ ስለስምህም ኃጢአታችንን አስተሥርይልን እንዳለ

💗መዝሙር ፸፱፡- እግዚአብሔር ፊቱን ካበራልን እንደምንድን

💗መዝሙር ፹፡- ከእግዚአብሔር ውጭ ሌላ አምላክ ማምለክ እንደማይገባ

💗የዕለቱ ጥያቄ💗
፩. ስለ ልዑል እግዚአብሔር ትክክል የሆነው የቱ ነው?
ሀ. ብቻውን ተአምራትን ያደርጋል
ለ. ቸር ነው
ሐ. ሀ እና ለ
መ. መልስ የለም

https://youtu.be/Gzf4fQdXzvM?si=AwO4nm9rIh0Bgeol


ማለት በልምላሜ ተሸፍነው ደስ ያሰኛሉ ማለት ነው። በምሥጢር ስለክርስቶስና ስለትሩፋን የሚተረጎምበት መንገድም አለ። (የበለጠ አንድምታ ዳዊትን ይመልከቱ)።

▶️፴፫. "ሰማያዊ ንጉሥ በላይዋ ባዘዘ ጊዜ በሰልሞን ላይ በረዶ ዘነበ። የእግዚአብሔር ተራራ የለመለመ ተራራ ነው። የጸና ተራራና የለመለመ ተራራ ነው። የጸኑ ተራራዎች ለምን ይነሣሉ? እግዚአብሔር ይህን ተራራ ያድርበት ዘንድ ወደደው። በእውነት እግዚአብሔር ለዘላለም ያድርበታል" ይላል (መዝ.68፥14-17)። የዚህ ንባብ ትርጓሜው ምን ይሆን?

✔️መልስ፦ ይህ ማለት እግዚአብሔር ሰልሞን በሚባል ሀገር ላይ በረዶን አዘነበ ማለት ነው። የእግዚአብሔር ተራራ፣ የጸና ተራራ፣ የለመለመ ተራራ የተባሉ ትሩፋን ናቸው። በሌላ አተረጓጎም ምእመናን ናቸው። እግዚአብሔር በትሩፋን እስራኤላውያን በረድኤት እንዳደረ ለምእመናን ደግሞ ልጅነትን ሰጠ ማለት ነው።

▶️፴፬. "ወጣቱ ብንያም በጕልበቱ በዚያ አለ። ገዦቻቸው የይሁዳ አለቆች የዛብሎን አለቆችና የንፍታሌምም አለቆች። አቤቱ ኃይልህን እዘዝ። አቤቱ ይህንም ለእኛ የሠራኸውን አጽናው" ይላል (መዝ.68:27-28)። ይህ መቼና ሰለምን የተዘመረ ነው?

✔️መልስ፦ ከብንያም ነገድ የሚወለዱትን ሁሉ ብንያም ብሎ መጥራት በመጽሐፍ ቅዱስ የተለመደ ነው። የይሁዳ አለቆች፣ የዛብሎን አለቆች፣ የንፍታሌም አለቆች ያላቸውም በዳዊት ዘመን የነበሩ ከእነርሱ ተወልደው ነገዱን በአለቅነት የሚመሩትን ሰዎች የሚያመለክት ነው። የተዘመረው በዳዊት ነው። ለምን ተዘመረ ለሚለው በእርሱ ዘመን ለነበሩ ለእነዚህ ነገድ ተወላጅ ሰዎች ነው።

▶️፴፭. "አቤቱ  ውኃ እስከ ነፍሴ ደርሶብኛልና አድነኝ። በጥልቅ ረግረግ ጠለቅሁ መቋሚያም የለኝም። ወደ ጥልቅ ባሕር ገባሁ ማዕበልም አሰጠመኝ። በጩኸት ደከምሁ ጕሮሮዬም ሰለለ። አምላኬን ስጠብቅ ዓይኖቼ ፈዘዙ" ይላል (መዝ.69፥1-3)። ትርጓሜው ምንድን ነው?

✔️መልስ፦ ይህ ስለመቃብያን የተነገረ ነው። ከላይ የተጠቀሱት ሁሉ ከባድ መከራ ደረሰብኝ ለማለት የተገለጹ ናቸው። አምላኬን ስጠብቅ ዓይኖቼ ፈዘዙ ማለት ረድኤቱን ስጠባበቅ ቆየሁ ማለት ነው።

▶️፴፮. "በከንቱ የሚጠሉኝ ከራሴ ጠጕር በዙ። በዓመፅ የሚያሳድዱኝ ጠላቶቼ በረቱ። በዚያን ጊዜ ያልቀማሁትን መለስሁ" ይላል (መዝ.69፥4)። በዚያን ጊዜ ያልቀማሁትን መለስሁ ሲል ምን ማለት ነው?

✔️መልስ፦ ያልተበደርኩትን ተበድረሀል እያሉ አስከፈሉኝ ማለት ነው። ወይም ያልቀማሁትን ቀምተሀል ብለው አስከፈሉኝ ማለት ነው።

▶️፴፯. "ስለ አንተ ስድብን ታግሻለሁና እፍረትም ፊቴን ሸፍናለችና። ለወንድሞቼ እንደ ሌላ ለእናቴ ልጆችም እንደ እንግዳ ሆንሁባቸው። የቤትህ ቅንዓት በልታኛለችና የሚሰድቡህም ስድብ በላዬ ወድቋልና። ነፍሴን በጾም አስመረርኋት ለስድብም ሆነብኝ። ማቅ ለበስሁ ምሳሌም ሆንሁላቸው። በደጅ የሚቀመጡ በእኔ ይጫወታሉ ወይን የሚጠጡ እኔን ይዘፍናሉ" ይላል (መዝ.69፥7-12)። ይህን ንባብ ቢያብራሩልኝ።

✔️መልስ፦ ይህ ስለመቃብያን የተነገረ ነው። መቃብያን ስለእግዚአብሔር ስም ስድብን እንደታገሡ፣ እፍረትን እንደተቀበሉ ያስረዳል። እንዲሁም በሦስቱ ከሓድያን ካህናት መከራ መቀበላቸውን ለመግለጽ ለወንድሞቼ እንግዳ ሆንኩባቸው ብለዋል። መቃብያን አንጥያኮስ በቤተ መቅደስ የጣዖት መሥዋዕት ሲሠዋ አይተው ለእግዚአብሔር ሕግ መቅናታቸውን ለመግለጽ የቤትህ ቅንዐት በላኝ አሉ። በደጅ የሚቀመጡ በእኔ ይጫወታሉ ወይን የሚጠጡ እኔን ይዘፍናሉ ማለት የአንጥያኮስ ወገኖች ወይን እየጠጡ ሲጫወቱ በመቃብያን ይተርቱ ነበርና ነው።

▶️፴፰. "እንዳይውጠኝ ከረግረግ አውጣኝ፤ ከሚጠሉኝና ከጥልቅ ውኃ አስጥለኝ። የውኃው ማዕበል አያስጥመኝ። ጥልቁም አይዋጠኝ። ጕድጓድም አፉን በእኔ ላይ አይዝጋ" ይላል (መዝ.69፥14-15)። ትርጓሜው ምንድን ነው?

✔️መልስ፦ ይህ ስለ መቃብያን የተነገረ ነው። ረግረግ፣ ጉድጓድ፣ ጥልቅ የተባሉ አንጥያኮስና ሠራዊቱ ናቸው። እነዚህ ከሚያመጡት መከራ አድነን እያሉ መቃብያን ይጸልያሉ ማለት ነው።

▶️፴፱. "ለመብሌ ሐሞት ሰጡኝ። ለጥማቴም ሆምጣጤ አጠጡኝ። ማዕዳቸው በፊታቸው ለወጥመድ ለፍዳ ለዕንቅፋት ትሁንባቸው። ዓይኖቻቸው እንዳያዩ ይጨልሙ። ጀርባቸውም ዘወትር ይጕበጥ። መዓትህን በላያቸው አፍስስ። የቍጣህ መቅሠፍትም ያግኛቸው። ማደሪያቸው በረሃ ትሁን በድንኳኖቻቸውም የሚቀመጥ አይገኝ" ይላል (መዝ.69፥21-25)። ይህን ንባብ ቢያብራሩልኝ።

✔️መልስ፦ ይህ ስለክርስቶስ የተነገረ ነው። ክርስቶስ ሰውን ለማዳን በመስቀል በተሰቀለ ጊዜ አይሁድ ሐሞት እንዳጠጡት ያመለክታል። ከዚያ ቀጥሎ ያለው እርግማን በክፉዎች አይሁድ ይድረስባቸው ማለት ነው። ይህም ብዙው በ70 ዓመተ ምሕረት በጥጦስ ደርሶባቸዋል።

▶️፵. "ነገር ግን ክብሬን ይሽሩ ዘንድ መከሩ በጥሜም ሮጥሁ" ይላል (መዝ.61፥4)። በጥሜም ሮጥሁ ይልና ዕብራይስጡ ሐሰትን ይወድዳሉ ይላል የትርጉም ለውጥ አያመጣም?

✔️መልስ፦ በጥሜም ሮጥኩ ማለት በደል ሳልሠራ ወደ ጽርዕ ተማረክሁ ማለቱ ነው። ማየ ኃጢአትን አለመጠጣቱን በጽምእ መስሎ ተናገረ። ዕብራይስጡ ሐሰትንም ይወዳሉ ያለው በምሥጢር ክብሬን ይሽሩ ዘንድ መከሩ ካለው ጋር አንድ ስለሆነ የትርጉም ለውጥ አያመጣም።

▶️፵፩. "አቤቱ ፈትነኸናልና ብርንም እንደሚያነጥሩት አንጥረኸናልና። ወደ ወጥመድ አገባኸን። በጀርባችንም መከራን አኖርህ። በራሳችን ላይ ሰውን አስረገጥኸን። በእሳትና በውኃ መካከል አለፍን ወደ ዕረፍትም አወጣኸን" ይላል (መዝ.65፥10-12)። የዚህ ንባብ ትርጓሜ ምንድን ነው?

✔️መልስ፦ ዳዊት ስለእስራኤላውያን ከቀድሞ ጀምሮ የነበረውን እያወሳ ይናገራል። ስለዚህ ብርን እንደሚያነጥሩት አንጥረኸናል ማለት በመከራ ፈትነኸናል ማለት ነው። ወደ ወጥመድ አገባህን ማለት ወደ ግብፅ ወሰድከን ማለት ነው። በጀርባችን መከራን አኖርክ ማለት በዚያ መከራን እንድንቀበል አደረግከን ማለት ነው። በእሳትና በውሃ መካከል አለፍን ወደ እረፍትም አወጣህን ማለት ባሕረ ኤርትራን አሻግረህ ወደ ከነዓን አገባህን ማለት ነው።

▶️፵፪. "ከዕጣንና ከወጠጤዎች ጋራ ለሚቃጠል መሥዋዕት ፍሪዳን አቀርባለኹ። ላሞችንና ፍየሎችን እሠዋልኻለኹ" ይላል (መዝ.65፥15 )። ወጠጤ ምን ማለት ነው?

✔️መልስ፦ ወጠጤ የሚባለው ከግልገልነት ከፍ ያለ ከአውራነት ያነሠ መካከለኛው ወንድ ፍየል ነው።

▶️፵፫. "እግዚአብሔር ይማረን ይባርከንም ፊቱንም በላያችን ያብራ" ይላል (መዝ.66፥1)። ፊቱንም በላያችን ያብራ ሲባል ምን ማለት ነው?

✔️መልስ፦ ፊቱን በላያችን ያብራ ማለት ረድኤቱን ይግለጽልን ረድኤቱን ይስጠን ማለት ነው።

▶️፵፬. "እግዚአብሔርን በጉባኤ ጌታችንንም በእስራኤል ምንጭ አመስግኑት" ይላል (መዝ.67፥26)። በእስራኤል ምንጭ ሲባል ምን ማለት ነው?

✔️መልስ፦ ከዚህ የእስራኤል ምንጭ ያለው የኤርትራ ባሕርን ነው። ስለዚህ ባሕረ ኤርትራን ከፍሎ ያሻገረ እግዚአብሔርን በጉባኤ አመስግኑት ማለት ነው።


© በትረ ማርያም አበባው

✝️የዩቲዩብ ቻናሌ:- ንሕነ ዘክርስቶስ https://youtube.com/@edenawizechristos?si=6V4y-73OM3LTzhAf ነው።

🌻የፌስቡክ ገጼ Betremariam Abebaw https://www.facebook.com/profile.php?id=100075547015721 ነው።


✔️መልስ፦ በርስቶች መካከል ብታድሩ ማለት የከነዓን ሰዎች ወደ ወረሷት ወደሴም ዕፃ ብትደርሱ እንደ ርግብ ክንፎች በቅጠልያ ወርቅም እንደተለበጡ ላባዎቿ ትሆናላችሁ። ይህም ማለት ወርቅ ጽሩይ እንደሆነ ልብን የምታጠራ ሕግን ታገኛላችሁ ማለት ነው።

▶️፲፭. መዝ.67፥17 ላይ የእግዚአብሔር ሠረገላዎች የተባሉ እነማን ናቸው?

✔️መልስ፦ የእግዚአብሔር ሠረገላዎች የሚባሉት በእግዚአብሔር ሕግ የሚመሩ እስራኤላውያን ናቸው።

▶️፲፮. መዝ.67፥18 "ምርኮን ማርከኽ ወደ ሰማይ ወጣኽ። ስጦታኽንም ለሰዎች ሰጠኽ። ያድሩ ዘንድ ይክዱ ነበርና'' የሚለውን ቢያብራሩልኝ።

✔️መልስ፦ ምርኮን ማርከህ ወደ ሰማይ ወጣህ ማለት ለጊዜው እስራኤላውያንን ከባቢሎን ምርኮኝነት አውጥተህ በዘሩባቤል አማካኝነት ወደ ኢየሩሳሌም መለስካቸው ማለት ነው። በሌላ አገላለጽ (ኦ ክርስቶስ) ነፍሳትን ከሲኦል አውጥተህ ወደ ገነት አገባሀቸው ማለት ነው። ስጦታህንም ለሰዎች ሰጠህ ማለት ሚጠተ ሥጋን ለእስራኤል ሰጠህ፣ ሚጠተ ነፍስን ደግሞ ለነፍሳት ሰጠህ ማለት ነው። ሚጠትን ባትሰጥ ኖሮ ይክዱ ነበር ማለት ከመከራው ጽናት የተነሣ ከአምልኮተ እግዚአብሔር ይወጡ ነበር ማለት ነው።

▶️፲፯. መዝ.67፥20 ላይ "የሞት መንገድ የእግዚአብሔር ነው'' ሲል ምን ለማለት ነው?

✔️መልስ፦ የሞት መንገድ የእግዚአብሔር ነው ማለት የሰውን ነፍሱን ከሥጋው የመለየት ሥልጣን የእግዚአብሔር ነው ማለት ነው።

▶️፲፰. መዝ.67፥21 ላይ ''በጠጉራቸው ጫፍም በደላቸው ይኼዳል'' ሲል ምን ማለቱ ነው?

✔️መልስ፦ ይህ ማለት ማዕበል ሞገዱ በራሳቸው ላይ ይሔዳል ማለት ነው። ይኸውም ለበደሉ እስራኤላውያን ታላቅ መከራ ይመጣባቸዋል ማለት ነው። በሌላ አገላለጽ የምእመናን ኃጢአታቸው በክርስቶስ ይቅር ይባላል ማለት ነው።

▶️፲፱. መዝ.67፥22 ላይ ''ወጥቼ እመለሳለኹ'' ይላል። ቢብራራ።

✔️መልስ፦ ይህ ስለክርስቶስም ያስተረጉማል። (ይቤ ክርስቶስ) ወደ ሰማይ ዐርጌ እመለሳለሁ ይላል። ይህም ማለት በምጽአት መጥቶ ፍርድ እንደሚሰጥ ያመለክታል።

▶️፳. መዝ.67፥23 ላይ ''እግሮችኽ በደም ይነከሩ ዘንድ የውሻዎችኽ ምላስ በጠላቶች ላይ ነው'' ማለቱ ምንድን ነው?

✔️መልስ፦ እግሮችህ በደም ይነከሩ ዘንድ የተባለ ክርስቶስ በመስቀል እግሮቹ ተቸንክረው በደም እንደሚነከሩ ያመለክታል። ሰላም ለአጽፋረ እግርከ በደመ ቅንዋት እለ ተጠምዓ እንዳለ ደራሲ። የውሾችህ ምላስ በጠላቶች ላይ ነው ማለት ውሻ ለጌታው ታማኝ እንደሆነ በአንተ የሚያምኑ ምእመናን አንደበት በአጋንንት ላይ ነው ማለት ነው።

▶️፳፩. "ቀንድና ጥፍር ካበቀለ ከእንቦሳ ይልቅ እግዚአብሔርን ደስ ያሠኘዋል" ይላል (መዝ.68፥31)። ምን ማለት እንደሆነ ቢያብራሩልን?

✔️መልስ፦ ቀንድና ጥፍር ያበቀለ እንቦሳ የተባለው ለቤተ መቅደስ የሚሠዋውን መሥዋዕት ነው። ከዚህ መሥዋዕት ይልቅ እግዚአብሔርን ደስ ያሰኘዋል የተባለ ግን ከፍ ብሎ እንደተገለጠው ምስጋና መሆኑን ያመለክታል።

▶️፳፪. ''በምሥራቅ በኩል ወደ ሰማየ ሰማያት ለወጣ ለእግዚአብሔር ዘምሩ" ሲል ምን ማለት ነው? ቢብራራልኝ (መዝ.67፥33)።

✔️መልስ፦ በምሥራቅ በኩል ወደ ሰማየ ሰማያት ለወጣ ለእግዚአብሔር ዘምሩ ማለት ትሩፋንን ይዞ ከፋርስ ባቢሎን ወደ ኢየሩሳሌም ለወጣ ለእግዚአብሔር ምስጋና አቅርቡ ማለት ነው። በሌላ አገላለጽ ነፍሳትን ከሲኦል ወደ ገነት ለመለሰ ለእግዚአብሔር ምስጋና አቅርቡ ማለት ነው።

▶️፳፫. መዝ.68፥6 ''የእስራኤል አምላክ ሆይ የሚሹኽ በእኔ አይነወሩ'' ሲል ምን ማለት ነው?

✔️መልስ፦ ይህ ማለት እግዚአብሔር ሆይ አንተን በሕግ በአምልኮ የሚሹህ ነቢያት ካህናት የእኔ መከራ አይድረስባቸው ይላል ዳዊት።

▶️፳፬. መዝ.70፥6 ''በማሕፀን ውስጥም አንተ ሸሸግኸኝ'' ሲል ምን ማለት ነው?

✔️መልስ፦ በማሕፀን ውስጥ ሸሸግኸኝ ማለት በጽንስነቴ እንዳልሞት አንተ ጠበቅኸኝ ማለት ነው።

▶️፳፭. መዝ.70፥7 ''እንደ ጥንግ ኾንኹ" ሲል ጥንግ ምንድን ነው?

✔️መልስ፦ ጥንግ የሚባለው እንደ ኳስ ክብ የሆነች በጣም ትንሽ ነገር ስትሆን በገና ጨዋታ ተጫዋቾች የሚጫወቱባት የሚለጓት ነገር ናት።

▶️፳፮. መዝ.62፥8 ላይ "ነፍሴ በዃላኽ ተከታተለች እኔንም ቀኝኽ ተቀበለችኝ" ይላል። ቢብራራልኝ።

✔️መልስ፦ ነፍሴ በኋላህ ተከታተለች ማለት በአምልኮ አንተን ተከተለች ማለት ነው። ስለዚህም ቀኝህ ተቀበለችኝ ማለት ረድኤትህን ሰጠኸኝ ማለት ነው።

▶️፳፯. መዝ.64፥2 "ሥጋ ዅሉ ጸሎትን ወደምትሰማ ወደ አንተ ይመጣል" ይላል። ሥጋ ሲል ምን ማለት ነው?

✔️መልስ፦ ሥጋ ብሎ የጠቀሰው ሰውን ነው። ሰውን አንዳንድ ጊዜ ሥጋ አንዳንድ ጊዜ ነፍስ ብሎ ይጠራዋልና ነው። ስለዚህ ሰው ሁሉ፣ ሥጋዊ ደማዊ ፍጥረት ሁሉ ወደ አንተ ይመጣል ማለት ጸሎቱን ያቀርባል ማለት ነው።

▶️፳፰. መዝ.65፥18 "በልቤስ በደልን አይቼ ብኾን ጌታ አይሰማኝም ነበር" ይላል። ይህ ምን ማለት ነው?

✔️መልስ፦ ዳዊት ይህንን የተናገረው ስለትሩፋን ነው። ከትሩፋንም ስለአስቴርና ስለመርዶክዮስ ነው። መርዶክዮስ በልቡናዬ ቂም በቀል፣ በቃሌ መበደል፣ በእጄ መግደል ቢኖር እግዚአብሔር ልመናዬን ባልሰማኝም ነበር ይላል።

▶️፳፱. "እስከ መቼ በሰው ላይ ትቆማላችሁ? እናንተ ሁላችሁ እንዳዘነበለ ግድግዳ እንደ ፈረሰም ቅጥር ትገድላላችሁ" ይላል (መዝ.61፥3)። እንዳዘነበለ ግድግዳ እንደ ፈረሰም ቅጥር ትገድላላችሁ ሲል ምን ማለት ነው?

✔️መልስ፦ ያዘነበለን ግድግዳና የፈረሰን አጥር ሌላ ሰው እንዳይጎዳ እንደምታፈርሱት ሁሉ መቃብያንን ለምን ትገድሏቸዋላችሁ ብሎ ዳዊት ይናገራል። ደግ ሆነው ሳለ መግደል አይገባችሁም ነበር ማለቱ ነው።

▶️፴. "ነገር ግን የሰው ልጆች ከንቱ ናቸው። የሰው ልጆችም ሐሰተኞች ናቸው። በሚዛንም ይበድላሉ። እነርሱስ በፍጹም ከንቱ ናቸው" ይላል (መዝ.61፥9)። በሚዛንም ይበድላሉ ሲል ምን ማለት ነው?

✔️መልስ፦ በሚዛን ይበድላሉ ማለት በሚዛን ያታልላሉ ማለት ነው። ይኸውም በታናሽ ሚዛን ሰጥተው በታላቅ ሚዛን ይቀበላሉ ወይም በታላቅ ተቀብለው በታናሽ ይሰጣሉ ማለት ነው። ምሥጢሩ ሕግን ያሳብላሉ ማለት ያፈርሳሉ ማለት ነው።

▶️፴፩. "የባሕሩን ጥልቀት የሞገድንም ጩኸት ታናውጣለህ" ይላል (መዝ.64፥7)። ምን ማለት ነው?

✔️መልስ፦ የባሕርን ጥልቀት የሞገድንም ጩኸት ታናውጣለህ ማለት በጥልቅ ባሕር ሞገድ ፈርዖንን አሰጠምክ ማለት ነው።

▶️፴፪. "ትልሟን ታረካለህ። ቦይዋንም ታስተካክላለህ። በነጠብጣብ ታለሰልሳታለህ። ቡቃያዋንም ትባርካለህ። በቸርነትህ ዓመትን ታቀዳጃለህ። ምድረ በዳውም ስብን ይጠግባል። የምድረ በዳ ተራሮች ይረካሉ። ኮረብቶችም በደስታ ይታጠቃሉ። ማሰማርያዎች መንጎችን ለበሱ። ሸለቆችም በእህል ተሸፈኑ። በደስታ ይጮኻሉ ይዘምራሉም" ይላል (መዝ.65፥10-12)። የዚህ ትርጓሜው ምንድን ነው?

✔️መልስ፦ ከላይ ያለው ስለዚህች ዓለም የተነገረ ነው። እግዚአብሔር ትልሟን በዝናም አርክቶ፣ ወንዞቿን አስተካክሎ ምድር ቡቃያን እንደምታወጣ ያመለክታል። በቸርነትህ ዓመትን ታቀዳጃለህ ማለት በቸርነትህ ዘመን የተገኘውን ዓመት ትባርካለህ በዘመኑ የሚገኘውን እህሉንም ታበዛለህ ማለት ነው። ተራሮች ይረካሉ፣ ኮረብቶች በደስታ ይታጠቃሉ ማለት አብበው ለምልመው ያሸበርቃሉ ማለት ነው። ማሰማሪያዎች መንጎችን ለበሱ ማለት አውራ በጎች ሴት በጎችን ይንጠላጠሏቸዋል ማለት ነው። ሸለቆዎች በእህል ተሸፈኑ፣ በደስታ ይጮኻሉ ይዘምራሉ


💙💙 የጥያቄዎች መልስ ክፍል 139 💙💙

▶️፩. መዝ.67፥31 ላይ "መኳንንት ከግብጽ ይመጣሉ ኢትዮጵያ እጆቿን ወደ እግዚአብሔር ትዘረጋለች" ይላል። መኳንንት ከግብጽ ይመጣሉ ሲል ምን ማለት ነው? ከሌሎች ሀገሮች ተለይታ ኢትዮጵያ እጆቿን ወደ እግዚአብሔር ትዘርጋለች ለምን ተባለ?

✔️መልስ፦ መኳንንተ ግብጽ እጅ መንሻቸውን ይዘው ወደ ኢየሩሳሌም ይሄዳሉ ማለት ነው። ኢትዮጵያ እጆቿን ወደ እግዚአብሔር ትዘረጋለች ማለትም በንግሥት ሳባ አማካኝነት እጅ መንሻን ይዛ ወደ ኢየሩሳሌም ትሄዳለች ማለት ነው። በሀገሪቱ ሰዎችን መናገር ነው።

▶️፪. መዝ.69፥2 "ጠላቶቼ ይታመሙ ከፊትህም ይጥፉ" ይላል። መዝ.62፥9-10 ላይ ደግሞ "እነርሱ ግን ነፍሴን ለከንቱ ፈለጓት ወደ ምድር ጥልቅ ይግቡ" ይላል። መዝ.67፥1-2 ላይ እና መዝ.68፥22-23 ላይ ስናነብም ቅዱስ ዳዊት ጠላቶቼ እንዲህ ይሁኑ የሚላቸው ያኔ ሲያሳድዱት የነበሩትን ነው ወይስ አጋንንትን ነው? ይህስ ጠላቶቻችሁን ውደዱ ካለን ጋራ አይጋጭም ወይ?

✔️መልስ፦ አይጋጭም። በብሉይ ኪዳን የጠሏቸውን መጥላት በደል አልነበረም። ስለዚህ ዳዊት ጠላቶቼ ይጥፉ እያለ ጸልዩዋል። በሐዲስ ኪዳን ግን አፍቅሩ ጸላእተክሙ (ጠላቶቻችሁን ውደዱ) የሚል ሕግ አለና ከሰው ወገን ማንንም እንድንጠላ አልተፈቀደም። በሐዲስ ኪዳን ይህንን የመዝሙረ ዳዊት ክፍል ስንደግም አጥፋቸው የምንላቸው አጋንንትንና እግዚአብሔር በሚያውቀው ከክፋታቸው የማይመለሱትን ነው። ይህ ለሁለቱም ይጠቅማልና። ክፉ ሰው ቶሎ ቢሞት ይጠቀማል። በክፋቱ ቆይቶ ፍዳው ከሚጸና ፍዳው ይቀልለት ዘንድ ቶሎ ቢያርፍ ይሻለዋልና።

▶️፫. "ረዳቴ ሆነኸኛልና በክንፎችህም ጥላ ደስ ይለኛልና" ይላል (መዝ.62፥7)። በክንፎችህ ጥላ ሲል የእግዚአብሔር ክንፎች አሉት ማለት ነው?

✔️መልስ፦ ለእግዚአብሔር ክንፍ ኖሮት አይደለም። ክንፎችህ እያለ የሚገልጸው ረድኤቱን ነው። ደራሲ ከመ ዖፍ አፍኅርቲሃ ትሴውር በክንፋ እንዳለ ወፍ ልጆቿን በክንፎቿ እንደምትሠውር ሁሉ እግዚአብሔርም በቸርነቱ በረድኤቱ ከመከራ ሁሉ ያድነናልና ይህን ለመግለጽ በወፍ ግሥ የተነገረ ነው።

▶️፬. "ንጉሥ ግን በእግዚአብሔር ደስ ይለዋል። በእርሱ የሚምል ሁሉ ይከብራል ሐሰትን የሚናገር አፍ ይዘጋልና" ይላል (መዝ.62፥11)። በእግዚአብሔር የሚምል ይከብራል የሚለው ሐሳብ በሌላ የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል ደግሞ ሰው በራሱ እንኳን መማል እንደማይችል የሚናገር እናገኛለንና አይጋጭም ወይ?

✔️መልስ፦ አይጋጭም። በብሉይ ኪዳን በሐሰት መማል እንደማይገባ ተገልጿል (ዘፀ.20)። በእውነት መማል ግን የሚቻል እንጂ ኃጢአት አልነበረምና ዳዊት በእርሱ የሚምል ይከብራል አለ። በሐዲስ ኪዳን ግን በእውነትም በሐሰትም መማል ስለማይገባ ፈጽማችሁ አትማሉ ስለተባለ አሁን ላይ ዳኛ ሳያዝዘን በእውነትም ቢሆን መማል ፈጽሞ አይገባም።

▶️፭. መዝ.63፥3 "ምሕረትህ ከሕይወት ይሻላልና ከንፈሮቼ ያመሰግኑሃል" ይላል። ሕይወት ብሎ ከምሕረቱ ጋር ያወዳደራት የእርሱን ሕይወት ነው ወይስ ምን ለማለት ተፈልጎ ነው?

✔️መልስ፦ ይህ ስለትሩፋን የተነገረ እንደመሆኑ ሕይወት ያላት በባቢሎን ተማርከው የሚኖሩ ሰዎችን ሕይወት ነው። ስለዚህ ምሕረትህ ከሕይወት ይሻላልና ማለት በባቢሎን ብዙ ዘመን ከመኖር በይቅርታህ ኢየሩሳሌም ገብቶ አንድ ቀን አድሮ መሞት ይሻላል ማለቱ ነው።

▶️፮. መዝ.67፥16 ላይ "እግዚአብሔር ያድርበት ዘንድ የወደደው ተራራ ይኽ ነው" ይላል። ያ የተወደደ ተራራ የተባለ ምንድን ነው? እዚሁ ምዕራፍ ቁጥር 18 ላይ "ያድሩ ዘንድ ይክዱ ነበርና" ያለው እነማንን ነው?

✔️መልስ፦ በዚህ አግባብ እግዚአብሔር ያድርበት ዘንድ የወደደው ተራራ የተባለ ትሩፍ እስራኤላዊ ነው። እግዚአብሔር ብዙ ጊዜ በረድኤት ከእስራኤል ጋር ነበርና። ያድሩ ዘንድ ይክዱ ነበር የተባሉ እስራኤላውያን ናቸው። ተስፋ ሚጠት፣ ሚጠት ባይኖርላቸው ኖሮ እስራኤላውያን እግዚአብሔርን ክደው ጣዖትን ያመልኩ እንደነበረ የሚያሳውቅ ነው።

▶️፯. መዝ.68፥15 ላይ "የውኃ ማዕበል አያስጥመኝ ጥልቁም አይዋጠኝ። ጒድጓዶችም አፋቸውን በእኔ ላይ አይክፈቱ" ያለው ጒድጓዶችም የተባሉ እነማን ናቸው?

✔️መልስ፦ መዝሙር 68 ስለመቃብያን የተነገረ ትንቢት ነው። ከላይ ያለው ዓረፍተ ነገር ለመቃብያን ሲነገር ጣዖት አምላኪው አንጥያኮስ ፈጽሞ እንዳያጠፋኝ አድርገኝ ተብሎ ይተረጎማል። ጉድጓዶች የተባሉ እነ አንጥያኮስ ናቸው።

▶️፰. "ለሰይፍ እጅ ዐልፈው ይሰጣሉ የቀበሮም ዕድል ፈንታ ይሆናሉ" ይላል (መዝ.62፥10)። የቀበሮ ዕድል ምን ዓይነት ነው?

✔️መልስ፦ የቀበሮ ዕድል ፋንታ ይሆናሉ ማለት በሰይፍ አልቀው ተገድለው ሬሳቸውን የሚያነሣው ጠፍቶ ቀበሮ ይበላዋል ማለት ነው።

▶️፱. "በሸምበቆ ውስጥ ያሉትን አራዊት በአሕዛብ ውስጥ ያሉትን የበሬዎችንና የወይፈኖችን ጉባኤ ገሥጽ። እንደ ብር የተፈተኑት አሕዛብ እንዳይዘጉ ሰልፍን የሚወዱትን አሕዛብን በትናቸው" ይላል (መዝ.67፥30)። ከዚህ ላይ የበሬዎችንና የወይፈኖችን ጉባኤ ገሥጽ ሲል ምን ማለት ነው?

✔️መልስ፦ ከዚህ ላይ የበሬዎችና የወይፈኖች ጉባኤ የተባሉ እስራኤላውያን ናቸው። ገሥጻቸው ማለት በአሕዛብ ተማርከው እንዳይቀሩ አስተምራቸው ማለት ነው።

▶️፲. መዝ.62፥1 ላይ "እንጨትና ውኃ በሌለበት ምድረበዳ ሥጋየን ላንተ እንዴት ልዘርጋልህ?" ይላል። ቢብራራ።

✔️መልስ፦ ይህ ስለትሩፋን የተነገረ ነው። እንጨትና ውሃ በሌለበት ምድረበዳ ማለት ለቤተ መቅደስ አገልግሎት የሚውሉ ዕፀዋት በሌሉበት በባቢሎን መሥዋዕትን እንዴት ልሠዋልህ? ማለት መሠዋት አልቻልኩም ማለት ነው።

▶️፲፩. "ነፍሴ ለእግዚአብሔር የምትገዛ አይደለችምን? መድኀኒቴ ከእርሱ ዘንድ ናትና" ይላል (መዝ.61፥1)። እዚህ ላይ መድኃኒቴ ያላት እመቤታችንን ነው ብለን መናገር እንችላለን ወይስ አንችልም?

✔️መልስ፦ ነፍሴ ለእግዚአብሔር የምትገዛ አይደለችምን? የሚለው በአሉታ የተጠየቀ አዎንታዊ መልስ ያለው ነው። ይህ ማለት በአጭሩ ነፍሴ ለእግዚአብሔር ትገዛለች ማለት ነው። መድኃኒቴ ከእርሱ ዘንድ ናት ማለት ከእግዚአብሔር ዘንድ ናት ማለት ነው። ትርጓሜው ላይ ለድንግል ማርያም ሰጥቶ አልተረጎመውም ነገር ግን አክሊለ ምክሕነ ወቀዳሚተ መድኃኒትነ በሚለው አግባብ በጸጋ በምልጃዋ የምታድነን ስለሆነች ሌላ መተርጉም ተርጉሞት ቢገኝ መልካም ምሥጢር ነው።

▶️፲፪. መዝ.66፥3-5 አሕዛብ እግዚአብሔርን እንደሚያመሰግኑት እና በእርሱም ደስ እንደሚላቸው ይናገራል። ይህ ቢብራራልኝ።

✔️መልስ፦ ከዚህ ላይ አሕዛብ የሚላቸው እስራኤላውያንን ነው። ሕዝብ የሚለው ውስጠ ብዙ (ብዛትን አመልካች ቃል) የብዙ ብዙ ሲሆን አሕዛብ ይላልና ከዚህ አሕዛብ ያላቸው ራሳቸውን እስራኤላውያንን ነው።

▶️፲፫. መዝ.67፥4 "ወደ ምዕራብ ለወጣው መንገድን አብጁ" ይላል። ከዚህ ላይ ምዕራብ ሲል ምን ማለቱ ነው?

✔️መልስ፦ ከዚህ ላይ ምዕራብ ያለው ባቢሎንን ነው። እግዚአብሔር እስራኤላውያንን ከባቢሎን ወደ ኢየሩሳሌም እንደመለሳቸው ያመለክታል። በተጨማሪም በምሥጢር ሊቃውንት ምዕራብን ሲኦል ብለውታል። ከሲኦል እግዚአብሔር ነፍሳትን አውጥቶ ወደ ገነት እንደመለሳቸው ለመግለጽ ነው።

▶️፲፬. መዝ.67፥13 ላይ ''በርስቶች መካከል ብታድሩ ከብር እንደ ተሠሩ እንደ ርግብ ክንፎች በቅጠልያ ወርቅም እንደ ተለበጡ ላባዎቿ ትኾናላችኹ'' የሚለውን ቢያብራሩልኝ።


በቅዱሳት ገድላትና ድርሳናት ዙሪያ እንዲሁም በጥንተ አብሶ ዙሪያ

፩፦ እስካሁን በተመለከትኩት ገድላት አያስፈልጉም መወገድ አለባቸው የሚል ንግግርም ጽሑፍም ከኦርቶዶክሳውያን አልሰማሁም። ምክንያቱም ገድላትና ድርሳናት የወንጌል ትርጉሞች ናቸው። የቅዱሳን ሕይወት የሚታይ የሚዳሰስ የወንጌልን ቃል በተግባር የሚያሳይ ነውና።

፪፦ ነገር ግን በአንዳንድ ገድላትና ድርሳናት ውስጥ በተለያዩ ምክንያቶች ብዙ ስሕተቶች ሊገኝባቸው ይችላል። ይህ እንዳይፈጠር የሊቃውንት ጉባኤያችን ጠንክሮ ማዕከላዊ የቅዱሳት መጻሕፍት ኅትመት ቢኖረውና በዚያ ቢታተሙ መልካም ነው። ብሔርን ከብሔር የሚያጣሉ፣ ጥላቻን የሚያስተላልፉ ሐሳቦች በግል በሚታተሙት ገድላት ይስተዋላል።

፫፦ ለምሳሌ ቡና ይጠጣል ወይስ አይጠጣም የሚለው ክርክር ምንጩ ገድልና ድርሳን ነው። ለምሳሌ እኔ ከአምስት የገድላትና የድርሳናት መጻሕፍት ቡና እንደማይጠጣ የሚገልጽ አግኝቻለሁ። በተማርኩባቸው ጉባኤ ቤቶችና በየትኛውም የመጻሕፍት ትርጓሜ ጉባኤ ቤት ቡና አይጠጣም የሚለው ሐሳብ ተቀባይነት የለውም። ታዲያ ጉባኤ ቤቶች ይህንን ሐሳብ ቀጥታ የመቀበል ግዴታ አለባቸውን?

፬፦ ባለፈው መጋቤ ሐዲስ ኃይለ እግዚእ አሰፋ (የጠቅላይ ቤተክህነት የትምህርትና ሥልጠና ክፍል ኃላፊ) ማዕከላዊ ጎንደር ሀገረ ስብከት በነበረው ሥልጠና እንደማሳያ ብለው ብዙ የተአምረ ማርያም ቅጅዎችን እንዳዩ ገልጸውልን ነበር። እና በአንዱ የብራና ተአምረ ማርያም ቅጂ አጼ ቴዎድሮስን እጅግ በጣም አክፋፍቶ የሚገልጽ እንዳገኙ ገልጸውልን ነበር። አስተውሉ በአንዱ ቅጂ ነው የተገኘ እንጂ በሁሉ አይደለም። ትክክልነቱ ምን ያህል ነው? የሚለው ጥናት ይጠይቃል።

፭፦ ገድለ ዮሐንስ መጥምቅ ላይ ዮሐንስ አሥር ጊዜ ከተለያዩ እናቶችና አባቶች እንደተወለደ የሚገልጽ አግኝቻለሁ። ዮሐንስ መጀመሪያ የተወለደ ከአዳምና ከሔዋን ሲሆን ስሙም ያን ጊዜ "ሔና" ነበረ ይላል። ከዚያ በየዘመናቱ እየተወለደና መጨረሻ ላይ ከዘካርያስና ከኤልሳቤጥ ተወለደ ይላል። ይህ በአንድ ወቅት ደብረ ሊባኖስ ገዳም ግጭት ፈጥሮ ነበር። በወቅቱ በገዳሙ የነበሩት የንታ ብሩክ ይህ መስተካከል አለበት ሲሉ አንዳንድ ከመጻሕፍት ሩቅ የነበሩ ሰዎች ለእግዚአብሔር የሚሳነው ነገር ስለሌለ እንዳለ እንቀበላለን አሉ። ነገሩ ግን ከቤተክርስቲያን አስተምህሮ አንጻር መመርመር አለበት። ይህ በአንዳንድ የገድለ ዮሐንስ መጥምቅ ቅጂዎች አይገኝም።

፮፦ ገድለ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ላይ እስከ ዕለተ ምጽአት የጎጃም ሕዝብ ይቅር እንደማይባል ይገልጻል። በሌሎች ገድሎችና ድርሳኖች ለምሳሌ በገድለ አቡነ ሰላማ፣ በድርሳነ ኡራኤል፣ በገድለ ተከሥተ ብርሃን፣ በገድለ አቡነ ዜና ማርቆስ ደግሞ እስከ ዕለተ ምጽአት ወልድ ዋሕድ በተዋሕዶ ከበረ ብለው እግዚአብሔርን የሚያመልኩና እግዚአብሔርም የሚወዳቸው በሃይማኖታቸውና በምግባራቸው የተመሰከረላቸው የጎጃም ሰዎች ናቸው ይላል። እና የትኛውን እንቀበለው? መመርመር አለበት። ራእየ ማርያም ላይ ሻን*ቅላ ለዘለዓለም እንደማይጸድቅ የሚናገር አለ። በእውነት ይህን እናታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ናት የተናገረችው? ከክርስቶስ የማዳን ሥራ ጋር አይጋጭም?

፯፦ እንደዚህ እርስ በእርሱ የሚጋጩ ጉዳዮች ገድላት ላይና ድርሳናት ላይ ይስተዋላሉ። ይህ በተለያየ ምክንያት ነው። አንዳንድ መምህራን ሚሲዮናውያን ኢትዮጵያውያንን ለማለያየት ያስገቧቸው ናቸው ይላሉ። ይህ ሁሉ ቢሆንም ገድላትና ድርሳናት የሚታረሙት እየታረሙ በማዕከላዊነት በጠቅላይ ቤተክህነት ቢታተሙ እነዚህን ችግሮች መቅረፍ ይቻላል።

፰፦ በጥንተ አብሶ ዙሪያ ለምሳሌ ማኅበረ ቅዱሳን ባሳተመው ሊቀ ጉባኤ አባ አበራ በጻፉት መጽሐፍ የሰው ልጅ ከጥንተ አብሶ የሚላቀቅ ሲጠመቅ ነው ይላሉ። ሌሎች ደግሞ ጥንተ አብሶ በክርስቶስ መሰቀል ተወግዷል። ከዚህ በኋላ ሰው ቢኮነን እንኳ ራሱ በሠራው ኃጢአት እንጂ በጥንተ አብሶ አይደለም ይላሉ። (በጉባኤ ቤቶች ያለው አስተምህሮ ይህኛው ነው። በክርስቶስ መስቀል የውርስ ኃጢአት ጠፍቷል የሚል ነው። የእኔም አቋም ይህ ነው)። ጥንተ አብሶ የሚለው የግእዝ ቃል ሲሆን የበደል መጀመሪያ ማለት ነው። ይኸውም አዳምና ሔዋን የሠሩት በደል ነው። ይህ በደል ለአዳምና ለሔዋን ብቻ ይነገራል። የእነርሱ የበደል ውጤት (መርገም) ከእነርሱ ወደሚወለዱት ልጆች ተላልፏል። ይህን ውጤቱን የውርስ ኃጢአት እንለዋለን። ቅድስት ድንግል ማርያም የውርስ ኃጢአት የለባትም። ቀደሰ ማኅደሮ ልዑል እንዲል ከማኅፀን ጀምሮ ራሱ እግዚአብሔር ጠብቋታልና።

፱፦ በሚዲያ ዞር ዞር ስል ሕዝቤ ለሁለት ተቧድኖ ይቧቀሳል። በሁለቱም ወገን ያለው በእመቤታችን ንጽሕናና ቅድስና ይስማማል። ጠቡ በቃላት ያለመግባባት ሆኖ አግኝቼዋለሁ። ሁሉም ጽንፍ ይዞ የአንዱ ደጋፊና የአንዱ ነቃፊ ሆኖ በየራሱ ትርጉም ክፉ ስም ይሰጣጣል እንጂ ቆም ብሎ አንዱ አንዱን ለማዳመጥ ጊዜ ቢሰጣጡ ተመሳሳይ አረዳድ ላይ ይደርሱ ነበር። አንዳንዱ ደግሞ ስለጉዳዩ የሚያውቀው ነገር የለም። ነገር ግን በደጋፊነትና በነቃፊነት ጎራ ይተራመሳል። የዚህ መፍትሔው ከፍ ያሉ ጉዳዮች ላይ ዝም ብሎ ማዳመጥ የተሻለ ነው።

፲፦ ወቅት እየጠበቁ የሚያከራክሩ ጉዳዮች አሁንም ብዙ አሉ። ለምሳሌ የልደት ጾም በዘመነ ዮሐንስ ህዳር 15 ይጀመራል ወይስ 14? ጥምቀት ሰኞ ሲውል ቅዳሜና እሑድ ይጾማል ወይስ እሑድ ብቻ የመሳሰሉ ጉዳዮች ይነሳሉ። (እነዚህን የጠቀስኳቸው ታዋቂ ስለሆኑ እንጂ ሌላም ቀኖናዊ ያልሆኑ ከፍ ያሉ ብዙ ጉዳዮች አሉ። ለጊዜው ከዚህ አልጠቅሳቸውም)። አሁን ዘመኑ የሚዲያ ስለሆነ ሁሉም የየራሱን አብነት እየያዘ ከሚወጋገዝ በማዕከላዊነት ሊቃውንት ተሰብስበው ወጥ የሆነ እይታ እንዲኖር ማድረግ ግድ ይላል። የሊቃውንት ጉባኤ ከዘመኑ መቅደም አለበት። EOTC Tv ከአሉባልታና ከጳጳሳት ውዳሴ ወጥቶ ዘመኑን የሚመጥንና ጥያቄዎችን ቀድሞ የመመለስ ሥራ ሊሠራ ይገባል።

ኦርቶዶክሳዊው መንገድ ጉዳይ ተኮር ነው። ክርስቶስ ኃጢአትን እንጂ ኃጢአተኛን አልጠላም ብሏል። ይህ ጉዳይን በጉዳይነቱ መሞገት እንደሚገባ ያስረዳናል። ሁሉም ሰው የቤተክርስቲያንን አስተምህሮ ከውስጥም ከውጭም ጠላቶች መጠበቅ አለበት። ሲጠብቅ ግን እውነትን መሠረት አድርጎ እንጂ በተሳሳተ ፍረጃ፣ ስምን በማጥፋት፣ በስድብ ሊሆን አይገባም።

© በትረ ማርያም አበባው




💓 መዝሙረ ዳዊት ክፍል 7 💓

💓መዝሙር ፷፩፡- እግዚአብሔር አምላካችን ረዳታችንም መድኃኒታችንም እንደሆነ
-ዳዊት ክብሬ በእግዚአብሔር ነው እንዳለ
-ይቅርታ የእግዚአብሔር እንደሆነ
-እግዚአብሔር ለሁሉ እንደ ሥራው እንደሚከፍለው

💓መዝሙር ፷፪፡- ንጉሥ በእግዚአብሔር ደስ እንደሚለው

💓መዝሙር ፷፫፡- ጻድቅ በእግዚአብሔር ደስ እንደሚለው ልባቸውም የቀና እንደሚከብሩ

💓መዝሙር ፷፬፡- የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ቅዱስ እንደሆነ

💓መዝሙር ፷፭፡- እግዚአብሔርን ማመስገን እንደሚገባ
-ለእግዚአብሔር ነውር የሌለበትን ንጹሕ መሥዋዕትን መሠዋት እንደሚገባ

💓መዝሙር ፷፮፡- እግዚአብሔር በቅን እንደሚፈርድ

💓መዝሙር ፷፯፡- የእግዚአብሔር ተራራ የለመለመ ተራራ ነው መባሉና እግዚአብሔር ያድርበት ዘንድ የወደደው ተራራ ይህ ነው መባሉ
-እግዚአብሔር አምላክ ቡሩክ እንደሆነና የማዳን አምላክ እንደሆነ
-ኢትዮጵያ እጆቿን እንደምትዘረጋ መነገሩ

💓መዝሙር ፷፰፡- ሰውነትን በጾም ማድከም እንደሚገባ
-የእግዚአብሔር ይቅርታው በጊዜው እንደሚሆን

💓መዝሙር ፷፱፡- ዳዊት እኔን ለማዳን ተመልከት ብሎ እንደጸለየ

💓መዝሙር ፸፡- እግዚአብሔርን የታመነ እንደማያፍር
-የእግዚአብሔርን ጽድቅና ማዳኑን መናገር እንደሚገባ

💓የዕለቱ ጥያቄ💓
፩. ከሚከተሉት ውስጥ ትክክል ያልሆነው የቱ ነው
ሀ. እግዚአብሔር ለሁሉ እንደ ሥራው ይከፍለዋል
ለ. ይቅርታ የእግዚአብሔር ገንዘብ ነው
ሐ. የጻድቃን ክብራቸው በእግዚአብሔር ነው
መ. ሁሉም

https://youtu.be/CkLLLI35xzw?si=LiCaoW2TYeso3NED


Tiktok
ልክፈተው እንጂ ተጠቅሜበት አላውቅም

፩ኛ፦ ቅድሚያ የጀመርነውን የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት መጨረስ ስለሚገባ ነው። መጽሐፍ ቅዱሱን ከግማሽ በላይ አጥንተናል። ለ2300 አካባቢ ጥያቄዎች ምላሽ ተሰጥቷል። አሁንም ተሳታፊው ጨምሮ ትምህርቱ እንደቀጠለ ነው።

፪ኛ፦ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናቱ እስኪያልቅ ከዕለቱ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት ውጭ የሆኑ ጥያቄዎችን አልመልስም። ጊዜ ስለሚያጥረኝ ነው እንጂ የሁሉን ጥያቄ ብመልስ ደስ ይለኝ ነበር።

፫ኛ፦ ለሐሰተኛ ክሶች፣ ለስድቦች፣ ለስም ማጥፋቶች ብዙ ጊዜ መልስ መስጠት አይገባም። ቢያንስ ይህን የሚያደርጉ ሰዎች እውነታውን ልባቸው ያውቀዋል። በረከት ስለሚገኝበት በዝምታ ማለፍ ጥሩ ነው።

፬ኛ፦ ለምሁራን (በዘመናዊው በኩል ላሉ ምሁራንም፣ በአብነቱ በኩል ላሉ ምሁራንም) ታላቅ ክብር አለኝ። ብዙ ጊዜ ጉዳይ ተኮር ናቸው። የሚሞግቱ ጉዳዩን ነው። ለሰው ስሜት ያላቸው ጥንቃቄ ያስቀናኛል። ክብር ለአዋቂዎቻችን።

፭ኛ፦ እግዚአብሔር ልብንና ኩላሊትን የሚመረምር ስለሆነ ከእያንዳንዱ ጉዳይ ጀርባ ያለውን ስሜታችንን እንመርምር። እግዚአብሔር የሚወደው ሥራ ላይ እናተኩር።

© በትረ ማርያም አበባው


Dr. Samuel Seifu
Dr. Mule Dereje
Dr. Samuel Gebretsadik
እንኳን ደስ አላችሁ። እናንተን የመሳሰሉ ዶክተሮች ስላሉን እንደ ሀገር ደስተኞች ነን።

ሐመረ ኖህ ስፔሻሊቲ የጥርስ ህክምና ክሊኒክ በአዲስ አበባ ተከፈተ

ሐመረ ኖህ ስፔሻሊቲ የጥርስ ህክምና ክሊኒክጨ ትናንት የካቲት 9 ቀን 2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ መገናኛ ማራቶን የገበያ ማዕከል ጀርባ በሚገኘው ራሄም ህንፃ ላይ በይፋ ተመርቆ ስራውን መጀመሩን አሳወቀ።

በህክምና ሙያተኞች አማካኝነት የተመሠረተው ክሊኒኩ የሙያ ስነምግባር የተሞላ አገልግሎትን መርሁ አድርጎ፡በተጓዳኝ አቅም ለሌላቸውን ዜጎች በጎ ፈቃድ አገልጎሎት ለመስጠት የተቋቋመ መሆኑን በምረቃው መርሐግብር ላይ ተገልጿል።

ዶክተር ሳሙኤል ሰይፉ የሐመረ ኖህ ስፔሻሊቲ የጥርስ ህክምና ክሊኒክ መስራች እና የአፍ ውስጥ ፣ የፊት እና የመንጋጋ ቀዶ ህክምና ስፔሻሊስት ፤እንደገለፁት ክሊኒኩ ዘመናዊ የህክምና መሳሪያዎችን ያሟላ ሲሆን ለህብረተሰቡም ተደራሽ የሆነ አገልግሎት ለመስጠት ዝግጁ መሆኑን እና በቀጣይም በዘርፉ የልህቀት ማዕከል ለማድረግ እንደሚሰራ ገልጸዋል።

በሌላ በኩል የክሊኒኩ መስራች ከሆኑት መካከል አንዱ የሆኑት ዶክተር መለሰ ብዙአየሁ ደግሞ እንደገለፁት ክሊኒኩ በዘመናዊ መሳሪያዎች መደራጀቱንና በየወሩ በ16ኛው ቀን ነጻ የህክምና አገልግሎት እንደሚደረግ ገልጸዋል። በተጨማሪም የክሊኒኩ መከፈትን አስመልክቶ ከዛሬ የካቲት 10 እስከ የካቲት 16 ቀን 2017 ዓ.ም ድረስ ወደክሊኒኩ ለሚመጡ ታካሚዎች አስቀድሞ 0976 16 00 16 ላይ በመደወል የ50 በመቶ ቅናሽ እንደሚደረግ ጨምረው ገልጸዋል።

በመክፈቻው መርሐግብሩ ላይ ፣ በዘርፉ ዕውቅ የሆኑ ባለሙያዎች፣ ታዋቂ ግለሰቦች እና የመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች ተገኝተዋል።


▶️፳፱. "ቍጣቸው እንደ እባብ መርዝ ነው እንደ ምድር አውሬም ጆሮዋ የተደፈነ ነው" ይላል (መዝ.57፥4)። ጆሮው የተደፈነ የምድር አውሬ ምንድን ነው?

✔️መልስ፦ ጆሮው የተደፈነ የምድር አውሬ የተባለ እባብ ነው። ይህም ለእባብ ተፈጥሯዊ ጆሮ የለውም ለማለት ሳይሆን እባብ ከሰይጣን ጋር ተባብሮ አዳምና ሔዋንን ስላሳተ ከስብሐተ እግዚአብሔር መከልከሉን ለመግለጽ ነው። የሰይጣንን ቃል መስማት ስብሐተ እግዚአብሔርን አለመስማት ነውና።

▶️፴. "ለንጉሥ ከቀን በላይ ቀን ትጨምራለህ ዓመታቱም ከትውልድ ወደ ትውልድ ይሆናሉ" ይላል (መዝ.60፥6)። ለንጉሥ ቀንን ትጨምራለህ ሲል ምን ማለት ነው? የሚጨመርስ ለንጉሥ ብቻ ነው?

✔️መልስ፦ ይህ ስለዘሩባቤል የተነገረ ትንቢት ነው። የዘሩባቤልን የንግሥና ዘመን ታበዛለህ ማለቱ ነው። 49 ዓመት ገዝቷልና። ዳዊት ሲናገር የመጣው ስለትሩፋን ስለሆነ ከዚህ ላይ ዘሩባቤልን አነሣ እንጂ እርሱ እግዚአብሔር ባወቀ እድሜያቸውን የሚጨምርላቸው ከነገሥታት ውጭም ብዙ ሰዎች አሉ።

▶️፴፩. "ገለዓድ የእኔ ነው ምናሴም የእኔ ነው ኤፍሬም የራሴ መጠጊያ ነው። ይሁዳ ንጉሤ ነው።
ሞዓብ መታጠቢያዬ ነው። በኤዶምያስ ላይ ጫማዬን እዘረጋለሁ። ፍልስጥኤም ይገዙልኛል" ይላል (መዝ.59፥7-8)። ምሥጢሩን ቢያብራሩልን።

✔️መልስ፦ የገለዓድ ነገድ፣ የምናሴ ነገድ፣ የኤፍሬም ወገን፣ የይሁዳ ወገን ሁሉ ንጉሥ ስለሆንኩ ገንዘቤ ነው ይላል ዳዊት። ሞዓብ መታጠቢያዬ ነው ማለት አገልጋዬ ነው ማለት ነው። በኤዶምያስ ላይ ጫማዬን እዘረጋለሁ ማለት ኤዶምያስ የድካም ማረፊያዬ ናት ማለቱ ነው። ቀጥሎም ፍልስጥኤምም ይገዙልኝ ነበር ይላል ዳዊት።


© በትረ ማርያም አበባው


✝️የዩቲዩብ ቻናሌ:- ንሕነ ዘክርስቶስ https://youtube.com/@edenawizechristos?si=6V4y-73OM3LTzhAf ነው።

🌻የፌስቡክ ገጼ Betremariam Abebaw https://www.facebook.com/profile.php?id=100075547015721 ነው


▶️፲፭. "ነፍሴን ከሞት እግሮቼን ከመውደቅ አድነሃልና በሕያዋን ብርሃን እግዚአብሔርን ደስ አሰኘው ዘንድ" ይላል (መዝ.55፥13)። በሕያዋን ብርሃን እግዚአብሔርን ደስ አሰኘው ዘንድ ሲል ምን ለማለት ይሆን?

✔️መልስ፦ ይህም ስለመቃብያን የተነገረ ነው። የመቃቢስ ልጆች ሰማዕትነትን ቢቀበሉም ወደ እግዚአብሔር መንግሥት ገብተው እንደ መላእክት እያመሰገኑት እንደሚኖሩ የሚያሳውቅ ነው። የሕያዋን ብርሃን የተባለች መንግሥተ ሰማያት ናት።

▶️፲፮. "ቍጣቸው እንደ እባብ መርዝ ነው። እንደ ምድር አውሬም ጆሮዋ የተደፈነ ነው። አዋቂ ሲደግምባት የአስማተኛውን ቃል እንደማትሰማ። እግዚአብሔር ጥርሳቸውን በአፋቸው ውስጥ ይሰብራል። እግዚአብሔር የአንበሶቹን መንጋጋቸውን ያደቅቃል። እሳት ወደቀች። ፀሐይንም አላዩአትም። እሾኻችሁ ሳይታወቅ በትር ሆነ። ሕያዋን ሳላችሁ በመዓቱ ይነጥቃችኋል" ይላል (መዝ.57፥4-9)። የዚህ ንባብ ትርጓሜው ምንድን ነው?

✔️መልስ፦ የእባብ መርዝ እንደሚጎዳ የኃጥኣን ቁጣቸው ይጎዳል ማለት ነው። እባብ የሰይጣን ተባባሪ እንደሆነች ኃጥእ ሰውም የሰይጣን ተባባሪ እንደሆነ ያመለክታል። ጆሮዋ ተደፈነ ማለት ጆሮው የተደፈነ እንደማይሰማ ኃጥኣንም ስብሐተ እግዚአብሔርን አይሰሙም ማለት ነው። እግዚአብሔር የአናብስቶችን መንጋጋቸውን ይሰብራል ማለት የነገሥታትን ሥልጣን ያጠፋል ማለት ነው። እሳት ወደቀች ማለት መከራ ረኃብ መጣች ማለት ነው። ፀሐይንም አላዩአትም ማለት የራበው ሰው ስልት ይዞት ቀና ብሎ እንደማያይ ለመግለጽ የተነገረ አነጋገር ነው። እሾኻችሁ ሳይታወቅ በትር ሆነ ማለት በደላችሁ በዛ ማለት ነው።

▶️፲፯. "እነሆ በአፋቸው አሰምተው ይናገራሉ። ሰይፍም በከንፈሮቻቸው አለ ማን ይሰማል? ይላሉ" ይላል (መዝ.58፥6-7)። ምን ለማለት ነው? ቢብራራልኝ።

✔️መልስ፦ በአፋቸው አሰምተው ይናገራሉ ማለት በአንደበታቸው የማይገባ ነገር ይናገራሉ ማለት ነው። ሰይፍ በከንፈሮቻቸው አለ ማለት የሚጎዳ ነገርን ይናገራሉ ማለት ነው።

▶️፲፰. "ማታ ይመለሱ እንደ ውሾችም ይራቡ በከተማም ይዙሩ። እነርሱም መብል ለመፈለግ ይበተኑ። ያልጠገቡ እንደ ሆነም ያንጎረጕራሉ" ይላል (መዝ.58፥14-15)። ትርጓሜው ምንድን ነው?

✔️መልስ፦ በከተማ ዞረው ዞረው የሚበሉት አጥተው ይደሩ ማለት ነው። እርግማን ነው። ሳይጠግቡ አድረው እንደሚያንጎራጉሩ የሚገልጽ ነው።

▶️፲፱. "አቤቱ ጣልኸን አፈረስኸንም። ተቈጣኸን ይቅርም አልኸን። ምድርን አናወጥሃት አወክሃትም። ተናውጣለችና ቍስሏን ፈውስ። ለሕዝብህ ጭንቅን አሳየሃቸው። አስደንጋጩንም ወይን አጠጣኸን" ይላል (መዝ.59፥1-3)። አፈረስኸን፣ ምድርን አናወጥሃት አወክሃትም፣ አስደንጋጩንም ወይን አጠጣኸን ሲል ምን ማለት ነው? ስለምን የተነገረ ቃል ነው?

✔️መልስ፦ አፈረስኸን፣ ምድርን አናወጥሃት አወክሃትም፣ አስደንጋጩንም ወይን አጠጣኸን ማለት እስራኤላውያን ሀገራቸው ፈርሳ ተማርከው ወደ ባቢሎን መሄዳቸውን የሚያመለክት ነው። አስደንጋጩንም ወይን አጠጣህን ማለት ተማርከን መከራን እንድንቀበል አደረግከን ማለት ነው። ስለመቃብያንም ስለትሩፋንም የተነገረ ቃል ነው።

▶️፳. "ወደ ጽኑ ከተማ ማን ይወስደኛል? ማንስ እስከ ኤዶምያስ ይመራኛል?" ይላል (መዝ.59፥9)። ጽኑ ከተማ ያለው ምንድን ነው?

✔️መልስ፦ ቀድሞ ጽኑ ከተሞችን እነኢያሪኮን አሳልፈህ ወደ ሀገራችን እንድንገባ አደረግከን። አሁን ግን በመከራ ላይ ነው ያለን ለማለት ትሩፍ የተናገረው የኀዘን ንግግር ነው።

▶️፳፩. በዳዊት ዘመን ቅኔ ነበረ ወይ?

✔️መልስ፦ ቅኔ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ውስጥ ያለ የኢትዮጵያ ሀብት ብቻ እንደሆነ ታላቁ ሊቅ መልአከ ብርሃን አድማሱ ጀንበሬ ገልጸዋል። እንደቅኔ ሰምና ወርቅ ያለው አነጋገር በመጽሐፍ ቅዱስ ያለ ቢሆንም የቅኔን ዜማ ልክ ያልጠበቀ ስለሆነ ቅኔ ለመባል ይጎድለዋል። ስለዚህ በዳዊት ጊዜ ቅኔ መኖሩን የሚያሳይ ምንም ማስረጃ አላገኘሁም። በሀገራችንም ቅኔ ተጀመረ የሚባለው ዋሸራ በእነዘሱቱኤል እንደሆነና በኋላ ደግሞ ዮሐንስ ገብላዊና ተዋነይ እንዳስፋፉት ነው የሚነገር። ይህ ታሪክ እውነት ከሆነ ዘሱቱኤል በሐዲስ ኪዳን የነበረ ሊቅ እንደሆነ ስለሚነገር ቅኔ በዳዊት አልነበረም ወደሚል ድምዳሜ ያደርሰናል። የሆነ ሆኖ ግን ይህ ታሪክ ስለሆነ በየጊዜው በተገኙና በሚገኙ ማስረጃዎች (Evidences) ሊከለስ ይችላል።

▶️፳፪. መዝ.58፥5 ላይ "አሕዛብን ሁሉ ጎብኛቸው ይቅርም በላቸው። ዐመፅ የሚያደርጉትን ሁሉ ግን አትማራቸው" ይላል። ሁለቱ ዓረፍተ ነገር አይጋጭም ወይ? ሙሉ ቃሉ ቢብራራ?

✔️መልስ፦ አሕዛብን ጎብኛቸው ያለው እስራኤልን ጎብኛቸው ለማለት ነው። ሕዝብ ሲበዛ አሕዛብ ይሆናልና (የብዙ ብዙ)። ስለዚህ እስራኤላውያንን በረድኤት ጎብኛቸው ዐመፅን የሚያደርጉ ሌሎችን ግን ይቅር አትበላቸው ማለት ነው።

▶️፳፫. "ኃያል ሆይ በክፋት ለምን ትኮራለህ ሁልጊዜስ በመተላለፍ" ይላል (መዝ.51፥1)። ኃያል ሆይ ተብሎ የተጠራው ማን ነው?

✔️መልስ፦ ኃያል ሆይ ለምን ትኮራለህ የተባለ በሕዝቅያስ ላይ የተዘባበተ ሰናክሬም ነው።

▶️፳፬. "ጻድቃን አይተው ይፈራሉ በእርሱም ይሥቃሉ እንዲህም ይላሉ" ይላል (መዝ.51፥6)። ጻድቃን አይተው ይፈራሉ ካለ በኋላ እንደገና ደግሞ ይሥቃሉ ሲል አይጋጭም ወይ? የሚስቁትስ ከምን አንጻር ነው?

✔️መልስ፦ ጻድቃን አይተው ይፈራሉ የተባሉት ሕዝቅያስ የሚመራቸው ሁለቱ ነገድ የሰናክሬምን መጥፋት አይተው በፍርሀት ለእግዚአብሔር ይገዛሉ ማለት ነው። በእርሱም ይስቃሉ ማለት ከእጄ የሚያድናችሁ ማን ነው ብሎ በተናገረ ሰናክሬም ይዘባበታሉ ማለት ነው። ስለዚህ በተለያዩ ጉዳዮች ዙሪያ የተነገሩ ስለሆኑ አይጋጩም። የሚስቁት በእግዚአብሔር ላይ በተገዳደረ በሰናክሬም ትዕቢት ነው።

▶️፳፭. "እንግዳዎች ቁመውብኛልና ኃያላንም ነፍሴን ሽተዋታልና። እግዚአብሔርን በፊታቸው አላደረጉትም" ይላል (መዝ.53፥3)። እንግዳዎች እና ኃያላን የተባሉት እነማን ናቸው?

✔️መልስ፦ ይህም ስለሕዝቀያስ የተነገረ ነው። እንግዳዎች እና ኃያላን የተባሉትን ሕዝቅያስንና ኢየሩሳሌምን ለማጥፋት የመጡ ሰናክሬምና ሠራዊቱ ናቸው።

▶️፳፮. "በርሬ ዐርፍ ዘንድ እንደ ርግብ ክንፍን ማን በሰጠኝ" ይላል (መዝ.54፥6)። የዚህን ምስጢር ቢያብራሩልን።

✔️መልስ፦ ርግብ ከአንድ አስቸጋሪ ቦታ ተነሥታ ወደ መልካም ቦታ እንደምትሄድ እኔም ከመከራው አርፍ ዘንድ እንደ ርግብ ክንፍ የሚያሻግር ረድኤት ማን በሰጠኝ ይላል መቃቢስ። የናፍቆት አነጋገር።

▶️፳፯. "በሕይወት ሳሉም ወደ ሲኦል ይውረዱ" ይላል (መዝ.54፥15)። በሕይወት ሳሉ ወደ ሲኦል ይውረዱ ሲባል ምን ማለት ነው?

✔️መልስ፦ ከዚህ ላይ ሲኦል ያለው መቃብርን ነው። በሕይወት ሳሉ እንደ ዳታንና እንደ አቤሮን ወደ መቃብር ይውረዱ ማለት ነው።

▶️፳፰. "ኃጥኣን ከማሕፀን ጀምረው ተለዩ ከሆድም ጀምረው ሳቱ ሐሰትንም ተናገሩ" ይላል (መዝ.57፥3)። ከማሕፀን ጀምረው ሐሰትን ተናገሩ ሲል ምን ማለት ነው? እንዴት ከማሕፀን መናገርና ስሕተት መሥራት ይችላሉ?

✔️መልስ፦ ማንኛውም ሕፃን በማሕፀን ሳለ ክፋትን ስለማያውቅ ሳተ አይባልም። ለነቢያት ግን የክፉ ሰዎች የኋላ ሥራቸው ተገልጾላቸው የኋላውን ለጽንስ አድርገው ይናገራሉ። ኋላ ክፉ የሚሠራበት ተሥዕሎተ መልክእ የሚፈጸም በማኅፀን ሳለ ነውና።


💙💙 የጥያቄዎች መልስ ክፍል 138 💙💙

▶️፩. "ጻድቅ በቀልን ባየ ጊዜ ደስ ይለዋል በኀጢአተኛው ደምም እጁን ይታጠባል" ይላል (መዝ.57፥10)። ምን ማለት ነው?

✔️መልስ፦ ጻድቅ ንጉሥ ጠላቶቹን ባጠፋ ጊዜ ደስ ይለዋል ማለት ነው። በፍትሕ ሥጋዊ ንጉሥ በትክክለኛ ምክንያት ጠላቶቹን ቢቀጣና ቢያጠፋ በደል አይሆንበትምና። ከዚህ መተርጉማን በተለየ የጠቀሱት ይሁዳ መቅብዩ የሚባልን ሰው ታሪክ ነው። ጠላቶቹን ሲገድል ውሎ በሰይፉ የገደላቸው የጠላቶቹ ደም በእጁ ተዘፍቆ እጁም ከሰይፉ ጋር ተጣብቆ ነበር። በኋላ በውሃ ታጥቦ እጁን ከሰይፉ አስለቅቆታልና ይህን ለመግለጽ ነው። ይህ ይሁዳ ለመቃብያን የተበቀለ ሰው ነው።

▶️፪. "ከፊትህ አትጣለኝ። ቅዱስ መንፈስህንም ከእኔ ላይ አትውሰድብኝ" ይላል (መዝ.51፥11)። ቅዱስ መንፈስህንም ከእኔ ላይ አትውሰድብኝ ሲል ምን ተብሎ ይተረጎማል?

✔️መልስ፦ መንፈስ የሚለው በብዙ ይተረጎማል። ከዚህ ላይ ከብዙ ትርጉሙ በአንዱ ማለትም በረድኤቱ በጸጋው ይተረጎማል። ቅዱስ መንፈስህን ከእኔ ላይ አትውሰድብኝ ማለት ረድኤትህን ከእኔ አትለየው ማለት ነው።

▶️፫. መዝ.59፥4 ላይ "ለሚፈሩህ ምልክትን ሰጠሃቸው" ይላል። ንባቡን ቢያስረዱን።

✔️መልስ፦ ይህ በብዙ ይተረጎማል። አንደኛው ለሚያመልኩህ ሰዎች ከመከራ ይድኑ ዘንድ ልዩ ረድኤትን፣ ተአምራትን ሰጠሀቸው ማለት ነው። ይህ ለመስቀልም ይተረጎማል። ጌታ ሆይ ለሚያመልኩህ ለምእመናን አጋንንትን የሚያሸንፉበትን መስቀልን ምልክት አድርገህ ሰጠሀቸው ማለት ነው።

▶️፬. "ከፈቃዴ እሠዋልሃለሁ። አቤቱ መልካም ነውና ስምህን አመሰግናለሁ" ይላል (መዝ.53፥6)። ከፈቃዴ እሠዋልሃለሁ ሲል ምን ለማለት ነው?

✔️መልስ፦ የምንወደውን ነገር ለእግዚአብሔር ብሎ መሠዋት የጽድቅ መንገድ እንደሆነ የሚገልጽ መንገድ ነው።

▶️፭. መዝ.50፥7 ላይ "በሂሶጵ እርጨኝ እነጻማለሁ። እጠበኝ ከበረዶም ይልቅ ነጭ እሆናለሁ" ይላል። ሂሶጵ ምንድን ነው?

✔️መልስ፦ ሂሶጵ በብሉይ ኪዳን የመንጻት ሥርዓት ወቅት ደም ወይም ውሃ ለመርጨት ያገለግል የነበረ ቀጫጭን ቅርንጫፎችና ቅጠሎች ያሉት ተክል ነው።

▶️፮. "እኔ ግን ፈራሁ በአንተም ታመንሁ" ይላል (መዝ.54፥3-4)። ሌላ ቦታ ላይ ደግሞ በእግዚአብሔር ታመንሁ አልፈራም ይላል (መዝ.26፥1)። እኔ ግን ፈራሁ ካለ በኋላ አልፈራም ሰው ምን ያደርገኛል ይላልና አይጋጭም?

✔️መልስ፦ አይጋጭም። ዳዊት መጀመሪያ ፈርቶ ነበር። በኋላ ግን በእግዚአብሔር ታምኖ ፍርሀትን አስወግዷል። ሥጋዊ ፍርሀቶች ሁሉ እግዚአብሔርን በመፍራት ይርቃሉና።

▶️፯. "እነሆ እውነትን ወደድህ። የማይታይ ስውር ጥበብን አስታወቅኸኝ። በሂሶጵ እርጨኝ እነጻማለሁ። እጠበኝ ከበረዶም ይልቅ ነጭ እሆናለሁ" ይላል (መዝ.50፥6-7)። የማይታይ ስውር ጥበብን አስታወቅኸኝ ሲል ይህ ስውር ጥበብ ምንድን ነው? እርጨኝና አጠበኝ ሲልስ ምን ለማለት ነው?

✔️መልስ፦ የማይታይ ስውር ጥበብ የተባሉ የእግዚአብሔር ትእዛዛት ናቸው። ኅቡዕ ጥበብ መባሉ በገቢር ለአሕዛብ የተሰወረ ለምእመናን የተገለጠ ስለሆነ ነው።

▶️፰. "ልቤ ጨካኝ ነው። አቤቱ ልቤ ጨካኝ ነው። እቀኛለሁ እዘምራለሁ። ክብሬ ይነሣ። በገናና መሰንቆም ይነሡ። እኔም ማልጄ እነሣለሁ" ይላል (መዝ.56፥7-8)። ልቤ ጨካኝ ነው፣ ክብሬ ይነሣ፥ እኔም ማልጄ እነሣለሁ ሲል ምን ለማለት ነው?

✔️መልስ፦ ልቤ ጨካኝ ነው ማለት ሕግህን ለመጠበቅ ትጉሕ ነው የታመነ ቆራጥ ነው ማለት ነው። ክብሬ ይነሣ ማለት ደግሞ ክብሬ ይመለስልኝ ማለት ነው። ማልጄ እነሣለሁ ማለት ዘወትር ለምስጋና እነሣለሁ ማለት ነው።

▶️፱. "ሕግህን እንዳይረሱ አትግደላቸው። አቤቱ ጋሻዬ በኃይልህ በትናቸው አውርዳቸውም" ይላል (መዝ.59፥11)። ቁጥር 13 ላይ ደግሞ "በቍጣ አጥፋቸው። እንዳይኖሩም አጥፋቸው" ይላል። አይጋጭም? ሕግህን እንዳይረሱ አትግደላቸው ሲልስ ምን ለማለት ነው?

✔️መልስ፦ ሕግህን እንዳይረሱ አትግደላቸው ማለት ምናልባት መመለስ ቢችሉ አታጥፋቸው ማለቱ ነው። ከላይ አጥፋቸው ማለቱ የማይመለሱ ከሆነ አጥፋቸው ማለቱ ነው። ስለዚህ የተነገረበት ዐውድ የተለያየ ስለሆነ አይጋጭም።

▶️፲. "አቤቱ በውዴታህ ጽዮንን አሰማምራት። የኢየሩሳሌምንም ቅጽሮች ሥራ" ይላል (መዝ.50፥18)። ምን ማለት ነው?

✔️መልስ፦ ጽዮንን አሰማምራት ማለት በጽዮን ሕዝቡን መናገር ነው። በባቢሎን የሚኖሩ ትሩፋንን ወደ ሀገራቸው ወደ ጽዮን መልሰህ አከናውናቸው ማለት ነው። የኢየሩሳሌምንም ቅጽሮች ሥራ ያለው እነ ነህምያ የሚያደርጉትን እንዲያከናውንላቸው በትንቢት መናገሩ ነው። መተርጉማን ለምእመናንም ተርጉመውታል። እግዚአብሔር ሆይ ምእመናንን ከሲኦል መልሰህ ልጅነትን ሰጥተህ ወደ ገነት አግባቸው ማለት ነው።

▶️፲፩. "መድኃኒትን ከጽዮን ለእስራኤል ማን በሰጠ! እግዚአብሔር የሕዝቡን ምርኮ በመለሰ ጊዜ ያዕቆብ ደስ ይለዋል እስራኤልም ሐሤት ያደርጋል" ይላል (መዝ.53፥6)። ስለምን የተነገረ ቃል ነው? ቢብራራልኝ።

✔️መልስ፦ በዚሁ ኃይለ ቃል ተገልጿል። በባቢሎን ተማርከው ስለሚመለሱ እስራኤላውያን የተነገረ ነው። ቀጥሎም ከምርኮ ሲመለሱ ደስ እንደሚላቸው ነው የተገለጠው።

▶️፲፪. "ጠላትስ ቢሰድበኝ በታገሥሁ ነበር። የሚጠላኝም ራሱን በላዬ ከፍ ከፍ ቢያደርግ ከእርሱ በተሸሸግሁ ነበር" ይላል (መዝ.55፥12)። ይህ ግልጽ ስላልሆነልኝ ቢያስረዱኝ።

✔️መልስ፦ የሚወዱትን ሰው ይናገሩታል እንጂ ጠላት ምንም ቢናገር መታገሥ ወይም መሸሽ እንደሚገባ የሚያመለክት ነው። ዳዊት ሌላ ጠላት ቢነሣብኝ በታገሥኩት ነበር ነገር ግን ሳኦል ቢነሣብኝ ወገኔ ስለሆነ የምነቅፍበትን ጉዳይ ቀጥታ እነግረዋለሁ ማለቱ ነው። ይህም ያላሳደጉትን ውሻ ጆሮ መቆንጠጥ እንደማይቻል ሁሉ ያላስተማሩትንና ያልቀረቡትን ሰው መገሠጽ ተገቢ አለመሆኑን ያስረዳናል።

▶️፲፫. "አንተ ግን እኩያዬ ሰው ባልንጀራዬና የልቤ ወዳጅ መብልን ከእኔ ጋር በአንድነት ያጣፈጥህ በአንድ ልብ በእግዚአብሔር ቤት ተራመድን" ይላል (መዝ.54፥14)። ዳዊት ማንን ነው እንደዚህ ያለው? መብልን ከእኔ ጋር በአንድነት ያጣፈጥህ፣ በአንድ ልብ በእግዚአብሔር ቤት ተራመድን ሲልስ ምን ማለት ነው?

✔️መልስ፦ ዳዊት እንዲህ ያለው ሳኦልን ነው። ሳኦል በዳዊት ከመቅናቱ በፊት ወዳጅ እንደነበሩና ከላይ የተጠቀሱትን ተግባራት በአንድነት ያድርጉ እንደነበር ያመለክታል።

▶️፲፬. "ከእርሱ ጋር ሰላም በነበሩት ላይ እጁን ዘረጋ። ኪዳኑንም አረከሱ። አፉ ከቅቤ ይልቅ ለዘበ። በልቡ ግን ሰልፍ ነበረ። ቃሎቹም ከዘይት ይልቅ ለሰለሱ። እነርሱ ግን እንደ ተመዘዘ ሰይፍ ናቸው" ይላል (መዝ.55፥20-21)። እዚህ ላይ ኪዳኑንም አረከሱ ያላቸው እነማንን ነው? የትኛውን ኪዳን ነው? እነርሱ ግን እንደ ተመዘዘ ሰይፍ ናቸው ያላቸውስ ምንድን ናቸው?

✔️መልስ፦ ዳዊት ስለመቃብያን የተናገረው ነው። አንጥያኮስ ለእግዚአብሔር እሰግዳለሁ ብሎ ቢገባም በኋላ ጣዖትን በማምለክ ቃል ኪዳኑን እንዳፈረሰ የሚገልጽ ነው። መጀመሪያውንም በአፉ ለእግዚአብሔር እሰግዳለሁ አለ እንጂ በልቡ አለማመኑን ያስረዳል። ቃሉን ቢያለሰልስም ሽንገላ ስለነበር ምላሶቹ እንደ ተመዘዘ ሰይፍ ናቸው አለ። ያ እንዲጎዳ በሽንገላ መቃብያንን ማጥፋቱን ለመግለጽ የተነገረ ቃል ነው።




✔️መልስ፦ ይህን የተናገረው ዳዊት ሲሆን የተናገረው ትንቢት በእንተ ክርስቶስ ነው።

▶️፵፩. "በልብሶችኽ ዅሉ ከርቤና ሽቱ ዝባድም አሉ። ከዝኆን ጥርሶች አዳራሽ ደስ ያሠኙኻል" ይላል (መዝ.44፥8)። ይህ የተነገረው ለማን ነው? ከርቤና ሽቱ፣ ዝባድ፣ የዝኆን ጥርሶች አዳራሽ ምንድን ናቸው?

✔️መልስ፦ ይህ የተነገረ ስለክርስቶስ ነው። ከርቤ፣ ሽቱ፣ ዝባድ፣ የዝሆን ጥርስ የተባሉና በእነዚህ የተመሰሉ ምእመናን ናቸው። ምእመናን ምግባር ትሩፋት ሠርተው ክርስቶስን ደስ ያሰኙታል ማለት ነው።

▶️፵፪. "ምስጋና የሚሠዋ ያከብረኛል። የእግዚአብሔርን ማዳን ለእርሱ የማሳይበት መንገድ ከዚያ አለ" ይላል (መዝ.49፥23)። እንዲህ ብሎ የተናገረው ማን ለማን ነው?

✔️መልስ፦ ይህ ለካህናትና ለምእመናን የተነገረ ነው። የተናገረው ተናጋሪው ደግሞ ዳዊት ነው።

▶️፵፫. "ብልኀተኛዎች እንዲሞቱ ሰነፎችና ደን*ቈ//ሮዎች በአንድነት እንዲጠፉ ገንዘባቸውንም ለሌላዎች እንዲተዉ አይቷል" ይላል (መዝ.48፥10)። ብልኀተኛዎች እንዲሞቱ ሲባል ምን ማለት ነው?

✔️መልስ፦ ብልኀተኞች የተባሉ ጻድቃንም በሞተ ሥጋ ይሞታሉ ማለት ነው። እነርሱ እንደሚሞቱ ሁሉ ኃጥኣንም ይሞታሉ የኃጥኣን ሞት ግን የከፋ ሞት ነው ለማለት ነው።


© በትረ ማርያም አበባው


✝️የዩቲዩብ ቻናሌ:- ንሕነ ዘክርስቶስ https://youtube.com/@edenawizechristos?si=6V4y-73OM3LTzhAf ነው።

Показано 20 последних публикаций.