አልፋና ዖሜጋ ዘተዋሕዶ


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: не указана


የዮሐንስ ራዕይ 22፥11-14
«ዐመፀኛው ወደ ፊት ያምፅ፥ ርኩሱም ወደ ፊት ይርከስ፥ ጻድቁም ወደ ፊት ጽድቅ ያድርግ፥ ቅዱሱም ወደ ፊት ይቀደስ አለ። እንሆ፥ በቶሎ እመጣለኹ፥ለያንዳንዱም እንደ ሥራው መጠን እከፍል ዘንድ ዋጋዬ ከእኔ ጋራ አለ። አልፋና ዖሜጋ፥ፊተኛውና ዃለኛው፥ መዠመሪያውና መጨረሻው እኔ ነኝ።
➘➘➘
@christian930
ግሩፕ፦ @AlphaOmega930
📩☞ @Kyrieelesion

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
не указана
Статистика
Фильтр публикаций






💚💛❤️ ልዩ ማሳሰቢያ ከራዕይ ዮሐንስ 20

የካቲት - 28 - 2017 ዓ.ም




Репост из: ዓለም ከመልእክታቱ አንፃር...
የእህታችን ወለተ ሥላሴ እጅግ ድንቅ ምስክርነት
ከቅድስት ሀገር ኢትዮጵያ = አሰላ
24/6/2017 ዓ.ም

👉 ወገኖቼ የእግዚአብሔር ቤተሰቦች! አዎን የእግዚአብሔር ቤተሰቦች! የኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን ቤተሰቦች!
እንዲሁም ይህን መልእክትም ሆነ የቀደሙትን ሰባት መልእክታት ለመስማት ዕድሉ የገጠማችሁ፥ ይህን
ታላቅ ምሥጢር የእግዚአብሔርን እውነት ለመገንዘብ የሚያስችል ልቡና ይስጣችሁ! መቼም እግዚአብሔር
ልቡናችሁን ካላበራው የቀደመው እባብ ሐሰተኛው ነቢይ ዘንዶው ያላደነቆረው፣ ወደራሱም ያላካተተው
የአዳም ዘር የለምና! ጥቂቶቹ በእግዚአብሔር የተወደዳችሁ የተመረጣችሁ የከበራችሁ ታላቁን መከራ
የታገሳችሁ ልትፅናኑ ይገባችኋል። ዛሬ ቀናችሁ ሊሆን ነውና! ብርሃናችሁ ሊበራ ድካማችሁ ሊታይ ሸክማችሁ
ሊራገፍ መድኃኔዓለም ሊክሳችሁ ነውና! አመስግኑ!

👉 ከኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልዕክት ዘጠኝ ገጽ 9 የተወሰደ።
ተጻፈ ታህሳስ 21 ቀን 2013 ዓ.ም.




Репост из: ዓለም ከመልእክታቱ አንፃር...
🟢 🟡 🔴
የካቲት 23 | በዚህች ቀን #ቅዱስ_ጊዮርጊስ ሊቀ ሰማዕታት አባቶቻችንን አድዋ ላይ የረዳበት ነው።

በ1854 ዓ.ም ጀግናው ገበየሁ ጣልያንን ካሸነፉ በኋላ እንደገና ቅኝ ለመግዛት፣ ሃይማኖት ለማጥፋት የጣልያን ሰዎች መጡ።

በ1888 ዓ.ም መስከረም 7 ቀን፥ ሣህለ ማርያም (አጤ ምኒልክ) አዋጅ አስነገሩ። በኋላም ወደ አድዋ ተጓዙ።

በዚያም የሣህለ ማርያም ሚስት ወለተ ሚካኤል (እቴጌ ጣይቱ) በንጉሥ ትእዛዝ ታቦተ #ቅዱስ_ጊዮርጊስን አስይዘው ከካህናቱ ጋር ሔዱ።

በዚያም ጊዜ የአክሱም ጽዮን መነኰሳትና ካህናት የእመቤታችንን ሥዕል ይዘው ወደ ንጉሡ ወደ ምኒልክ መጥተው ከሊቀ ጳጳሱ ከነአቡነ ማቴዎስ ጋር ተቀላቀሉ ከዚያም ሌሊቱን ሙሉ ጸሎት ምሕላ ሲያደርሱ አደሩ።

ቅዳሜ ማታ ለእሑድ አጥቢያ የካቲት 22 ቀን፥ ንጉሡ ሣህለ ማርያም (ምኒልክ) የጦር ልብሱን ለብሰው ከሠራዊቱ ጋር ወደ ጦር ግንባር ሄዱ። ከዚያም ከሮማውያን የጠላት ጦር ጋር ተገናኝቶ ከሌሊቱ ዐሥራ አንድ ሰዓት ጦርነቱን ጀመረ።

በዚያም ጊዜ ንጉሡ ሣህለ ማርያም (ምኒልክ) በጦርነቱ መካከል ሳለ ሊቀ ጳጳሱ አባ ማቴዎስ እንዲሁም የአክሱም መነኰሳትና ሌሎቹ ካህናት በሙሉ ታቦተ ጊዮርጊስንና ሥዕለ ማርያምን ይዘው ከንጉሡ በስተኋላ በደጀንነት ቆመው ጸሎተ ምህላ ያደርሱ ነበር።

ንግሥቲቱ ወለተ ሚካኤል (እቴጌ ጣይቱም) በጸሎት ጊዜ በመዓልትም በሌሊትም ከእነርሱ አትለይም ነበር። የጽዮን አገልጋዮችም በእግዚአብሔር የሕጉ ታቦት ፊት መለከት ይነፉ ነበር።

በየካቲት 23 ቀን በሮማውያንና በኢትዮጵያውያን መካከል ከፍተኛ ጦርነት ሆነ። በዚህም ጊዜ በሰማይ ታላቅ ተአምር ተደረገ። የቀስተ ደመና ምልክት ታየ። ከዚያም ከቀስተ ደመናው ውስጥ መልኩ አረንጓዴ የመሰለ ጢስ ይወጣ ነበር። ከዚህም ጢስ ውስጥ እንደ ክረምት ነጎድጓድ ያለ ድምጽ ተሰማ።

ከዚህም የነጎድጓድ ድምጽ የተነሣ በሮማውያን ወታደሮች ዘንድ ከፍተኛ ድንጋጤና ሽብር ሆነ ለመዋጋት አልቻሉም። ይልቁኑ ኃያሉ ገባሬ ተአምር ማር ቅዱስ ጊዮርጊስ በአምባ ላይ ፈረሱ ተቀምጦ ከነፋስ ሩጫ ይልቅ እየተፋጠነ በአየር ላይ በተገለጸ ጊዜ በግንባራቸው ፍግም እያሉ ወደቁ።

"የኢትዮጵያ ሕዝብ አምላካቸው ሊረዳቸው መጣ እንግዲህ ማን ያድነናል" አሉ፤ ምድርም ጠበበቻቸው።

በዚህን ጊዜ የኢትዮጵያ ሠራዊት የሮምን የጦር ሠራዊት ፈጁዋቸው የተረፉትንም ማረኳቸው ፈጽመውም እስኪያጠፏቸው ድረስ በሮማውያን ላይ በእግዚአብሔር ሥልጣን የኢትዮጵያውያን እጅ እየበረታ ሄደ።

ከዚህም በኋላ የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት ሣህለ ማርያም (ምኒልክ) በእግዚአብሔር ኃይልና በተአምራት አድራጊው በቅዱስ ጊዮርጊስ ተራዳኢነት የሮማውያንን የጦር ሠራዊት ድል አድርገው የድል አክሊል ተቀዳጅተው ተመለሱ።

ምንጭ፦ ተአምረ ቅዱስ ጊዮርጊስ
T.me/Ewnet1Nat


Репост из: ዓለም ከመልእክታቱ አንፃር...
#የካቲት_23


Репост из: ራዕይ ዮሐንስ 20 የንፅፅር ቻናል
የእህታችን ወለተ መድህን እጅግ ድንቅ ምስክርነት
ከባህሬን
19/6/2017 ዓ.ም

👉 ንጉሡና  ሌሎችም  አባቶች  እዚሁ  ኢትዮጵያ  ውስጥ  ነው  ያሉት።  ከዋናው  ከተማ  ጀምሮ  በሁሉም  የአገሪቱ ክልል  በተለያየ  ጉዳይ  እየተንቀሳቀሱ  ሁሉንም  ድርጊት  ይከታተላሉ።  በመገለጡ  ሰዓት  በቀዳማይ  ምክትልነትና በምክትልነት  በግራና  በቀኝ  የሚሆኑ  በንጉሥ  ማእረግ  ያሉ  ዛሬም  አብረውት  በሥራው  ሁሉ  እያገዙትና አብረውም  እየሠሩ  ነው።  ሌሎች  37  የሚሆኑ  በንጉሥ  ማእረግ  ያሉ  በየባእታቸው  ሆነው፤  በእግዚአብሔር መንፈስ  ቅዱስ  ሕብረትና  አንድነት  በሁሉም  እያገዙ  የሚገኙ  ናቸው።  ሁሉም  ሊያውቀው  የሚገባው  ቢኖር ዘመናዊ  መገናኛ  እስካለ  ድረስ፤  በቴሌግራም  የዮሐንስ  ራእይ  20  ቻናል  ላይ  ስለሁሉም  ሁኔታ  በቀጥታ የሚገለጽበት  ይሆናል።  የንጉሠ  ነገሥቱም፣  የንጉሦቹም  ድምፅ  የምትሰሙበት  የሚገለጥበት  ነው።  ከዚህ በተረፈ  በኢትዮጵያ  የዓለም  ብርሃን  መልእክታት  በግልጽ  የምታገኙት  ነው።  ቴሌግራሙም  እስካለ  ድረስ  ነው የሚያገለግለው።  ከዚህ  ውጪ  የሚመጣ  ነገር  የለም።  ተስፋ  የምታደርጉት  የኢትዮጵያ  ትንሣኤም  ሆነ  የንጉሠ ነገሥት  ቴዎድሮስና  አብረውት  የሚገለጡት  ንጉሦች  እንዲሁም  የኢትዮጵያ  ኦርቶዶክስ  ታላላቅ  አባቶች መላውን  ዓለም  በተዋሕዶ  እምነት  የሚመሩት  በይፋ  የሚገለጽበት  የሚታወቅበት  ይኸው  መንገድ  ብቻ  ነው። ከዚህ  በዘለለ  ሌላ  እውነት  አለን  ካላችሁ  በርቱ  ቀጥሉበት  እንላለን።  ዳኛው  በሰማይ  በመንበሩ  ሆኖ  ሁሉንም ስለሚመለከት  እንደየታመንበት  ፍርዱም  ትእዛዙም  አብረው  ይገለጣሉ።  በሌላ  በኩል  እንደ  እውነቱ  ከሆነ እኔን  ለምትቃወሙ  ቅሬታም  የለብኝ  እኔ  ዛሬም  ነገም  የምለው  የማምነው  የምረዳው  አምላኬም  ያስተማረኝ እውነትና  እውነትን  ብቻ  መግለጽ  ነው።  ስለዚህ  እኔ  ከሁሉ  የማንስ  ነኝ።  በሁሉም  ገጽታ  ከኔ  ትበልጣላችሁ ብዬ  አስባለሁ።  ግን  በምን  መስፈርት  እኔን  እንደመረጠ  እኔም  ስለማልረዳ  እናንተ  ቅር  የተሰኛችሁ  ሁሉ መድኃኔዓለምን  ድንግልን  ጠይቁ  መልስን  ታገኛላችሁ።  ይህን  ያልኩት  በዚህ  ምክንያት  እንዳትሰናከሉ  በማሰብ ነው።

👉 ከኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልዕክት ገጽ 55 የተወሰደ።
ተጻፈ ታህሳስ 21 ቀን 2013 ዓ.ም.


Репост из: ራዕይ ዮሐንስ 20 የንፅፅር ቻናል
የእህታችን ወለተ መድህን እጅግ ድንቅ ምስክርነት
ከባህሬን
19/6/2017 ዓ.ም
👇👇👇


📌 የሊቀ መዘምራን ኪነጥበብ ወልደቂርቆስ ሁሉም መዝሙሮች ስብስብ
🎬 ብዛት ከ90 በላይ ይሆናሉ
✅ አጠቃላይ የሰዓት ቆይታ 9 ሰዓት 53 ደቂቃ
🔑 መጠን 104 MB
👑 በአልፋና ዖሜጋ የንጽጽርና ትምህርት መገኛ ገጽ የቀረበ !

t.me/Ewnet1Nat




Репост из: ዓለም ከመልእክታቱ አንፃር...
🟩 🟨 🟥
ኢትዮጵያ
የሥላሴ የክብራቸው መገለጫና መመስገኛ ምድር!
ኢትዮጵያ ርስተ ድንግል ማርያም!
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን!
ኢትዮጵያ የዓለሙ ገዢ!

🍀 ዓቢይ ጾም [ ጾመ እግዚእ | ጾመ ሁዳድ ]
🍀

ዓቢይ ማለት «ዐብየ - ከፍ አለ» ከሚለው ግሥ የተገኘ ሲሆን
#ዐቢይ ማለት ከፍ ያለ ትልቅ ማለት ነው፡፡ ዐቢይ ጾም የተባለበት ምክንያት፦

[ሀ] ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የጾመው ጾም ስለሆነ፣
[ለ] በቀኑ ቁጥር ከሌሎች አጽዋማት የሚበልጥ ስለሆነ፣
[ሐ] ሦስቱ ታላላቅ የሰይጣን ፈተናዎች ማለትም ➻
#ትዕቢት#ስስት#ፍቅረ_ንዋይ ድል የተመቱበት ስለሆነ የሚሉት ይጠቀሳሉ።

❗️ “በዐቢይ ጾም መጀመሪያ ሱባኤ ፀሐይ እስኪገባ (እስከ 12 ሰዓት) ይጹሙ! ሌሎቹን ሳምንታት እስከ 11 ሰዓት ይጹሙ! በሰሙነ ሕማማት ግን ኮከብ እስኪወጣ (ምሽት 1 ሰዓት ድረስ) ይጹሙ!” ይላል (ፍት.ነገ.አን 15፥595)❗️

በቤተክርስቲያን ስያሜ መሠረት በዐቢይ ጾም ውስጥ የሚውሉ ሰንበታት እያንዳንዳቸው መጠሪያ ስም ሲኖራቸው እነርሱም፦
1. ዘወረደ
2. ቅድስት
3. ምኩራብ
4. መጻጉዕ
5. ደብረ ዘይት
6. ገብርኄር
7. ኒቆዲሞስ
8. ሆሳዕና ይባላሉ።

#እንኳን_አደረሳችሁ#እንኳን_አደረሰን !

ልዑል እግዚአብሔር አምላክ ጾሙን ንስሐ ገብተን፣ በእውነት ጾመን ከፈቃዱ ጋር የምንታረቅበት፥ የኢትዮጵያና የተዋሕዶን ትንሣኤ የሚረጋገጥበት ያድርግልን። ፍርዱን አጽንቶ በሰላም አስጀምሮ በሰላም ያስፈጽመን፤ ጾመን ለማበርከት ያብቃን አሜን።

[ይጹም ልሳን ፤ ይጹም ዓይን ፤ ይጹም እዝን]

አልፋና ዖሜጋ ዘተዋሕዶ
t.me/AlphaOmega930
http://t.me/Ewnet1Nat


👑 “አመድ ፡ ከዘነመ ፡ ከአራት ፡ ዓመት ፡ በኋላ ፡ የጌታችን ፡ የኢየሱስ ፡ ክርስቶስ ፡ ሰማዕት ፡ የሆነ ፡ በፊቅጦር ፡ በገድሉ ፡ መጽሐፍ ፡ እንደተነገረው፡ የስሙ ፡ ምልክት ፡ ተብሎ ፡ የተመለከተው ፡ ይነግሳል ፡፡”
👉🏿ድርሳነ ዑራኤል ዘጥቅምት ምእራፍ 2፥44

👑“...፲፤ በዚያን ጊዜ ወገኖቼ ምዕመናንን የሚጠላ ከዚህ ትውልድ ወገን ንጉሥ ይነሣል ፤ በሱ ዘመን ሃዘንና ትካዜ ይበዛባቸዋል፤ ልዩ ልዩ ችግር ያደርስባቸዋልና ልብሱንና ባሕሉን ይለውጣል ። ባሕላቸውን ለውጠው የአሕዛብን ባሕል እንዲይዙ ያስገድዷቸዋል ሕዝቦቼም ልክ እንደ ምድረ በዳ አህያ (እርኩም) ይሆናሉ።

፲፩ ዕወቁ ተጠንቀቁ በዚህ ትውልድ የመጨረሻ ጊዜ መከራ በመከራ ላይ ይደራረብባችኋል። ከምድረ ገጽ ነቅለው ጠራርገው ሊያጠፏችሁ ይፈልጋሉና ።

፲፪ ፤ ከዚያን በኋላ ግን ጽኑዕ መንፈሴን እልክና ከወገኖቼ መካከል መርጬ ንጉሥ አነግሣለሁ ፤ ከሱ በፊት ማንም ያልተቀመጠውን ፈረስ ይቀመጣል ፤ የፈረሱም ልጓም ከአዳም በለበስኩት ሥጋ የተቸነከርኩበት የብረት ችንካር ነው ።

፲፫ ይህም ንጉሥ የወገኖቼን በቀል ይወጣል፤ አሕዛብንም ሁሉ ተዋግቶ ያሸንፋቸዋል፤ እናንተም እነሱ ያለዋጋ እንደገዟችሁ፥ እንዲሁ ዓሥር እጅ ያለዋጋ ትገዟቸዋላችሁ ፤ እንደባሪያም ትሸጧቸዋላችሁ።

፲፬ ፤ በዚያም ጊዜ የሚነግሠው ንጉሥ ሃይማኖቱ የቀና በሥራው ሁሉ ዕውነተኛ የሆነ ነው ፤ ከዚህም በኋላ በምሥራቅ በኩል ያለውን ሀገር በር እከፍትና በዚያ የታሠሩትን እሥረኞች እፈታቸዋለሁ ። ከዚያም በከሐዲዎቹ ሰዎች ላይ ይፈርዱና እኔ ከአነገሥሁት ንጉሥ በስተቀር ያጠፏቸዋል ።

፲፭፤ ጥፋታቸውም በባሕርና በየተራራው ይሆናል ። ክብር ምስጋና ለሱ ይሁንና ጌታ ለደቀ መዛሙርቱ ይህን ተናገረ።”
🫴🏿ተአምረ እየሱስ፡ 65ኛ ተአምር ።

#ቴ!
#ኢትዮጵያ_የዓለም_ብርሃን!


Репост из: ዓለም ከመልእክታቱ አንፃር...
https://t.me/Amharic_messages/12

☝️☝️☝️ ይኸው በቅደም ተከተል☝️☝️


Репост из: ዓለም ከመልእክታቱ አንፃር...
✥ 🇨🇬 ✥ 🇨🇬 ✥

#_ተግሣጽ-፰ (ለኢ.ዓ.ብ ቤተሰብ ብቻ)
#_አጥፊዎች_ስለ_ቅድስና_የሚያውቁት_ነገር_የለም።

🇨🇬 የኢ.ዓ.ብ የሐዋርያት ሥራ ትምህርት ፭
| 🕛 | ከ ፱:፶፭ - ፲: ፵፬

አጥፊዎች ስለ ቅድስና የሚያውቁት ነገር የለም። ትላንት ቤተ ክርስቲያንን በልምድ ኖሩባት፤ ለጥፋቷ ተመልካች ኾነው አሳለፉ፤ ዛሬ ለደረሰችበት ጥፋት አስተዋጽኦ አደረጉ።

ዛሬም #_በጽዋ_ማኅበር_መሳተፍ_ብቻ_በቂ_ነው የሚል ስሜት ያደረባቸው ኾነው ንስሐ የማይገቡ፣ በእውነት መለወጥ፥ በእምነት ሳይጸኑ፣ በእውነትና በመንፈስ ጸንተው ሳይቆሙ፣ ጉድለታቸውን ሳያርሙ፣ በሌሎች ወንድም እኅቶቻቸው ላይ ነቀፋን፥ ትችትን፥ ሐሜትን የሚያስፋፉ ላይ #_እግዚአብሔር_ይገሥጻል_እርምጃም_ይወስዳል።

t.me/Ewnet1Nat 🇨🇬◉
http://t.me/AlphaOmega930 🇨🇬◉


Репост из: ዓለም ከመልእክታቱ አንፃር...
#ጾመ_ነነዌ
ጾመን ለማበርከት ያብቃን!
#እንኳን_አደረሳችሁ







Показано 20 последних публикаций.