🎤✨ድምፀ ተዋህዶ✨🎤


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: Музыка


ድምጻችን ለተዋህዶ ሐይማኖታችን ለኢትትዮጲያ አገራችን

የእግዚአብሔር ሰላም የእናታች የቅድስት ድንግል ማርያም ምልጃና ፀሎት የመላእክት ጥበቃና የቅዱሳን በረከት ከናንተ
ጋር ይሁን አሜን!

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
Музыка
Статистика
Фильтр публикаций


ሌላውን ለጊዜው እንተውና እንዲህ ዓይነት መሠረታዊ ትምህርቶች ላይ ስሕተት ተፈጥሯል። እነዚህን ስሕተቶች ቢያርም መልካም ነው። እግዚአብሔር ወንድማችንን ከክፉ ነገር ኹሉ ይጠብቅልን። እንዲህ ዓይነት ስሕተቶችንም እንዲያርም እግዚአብሔር ኃይሉን ያድልልን። ምናልባትም አሁን ላይ እነዚህን ስሕተቶቹን አርሟቸውም ሊኾን ይችላል። ከኾነም እጅግ ደስ የሚያሰኝ ነው። እንዲህ አላልኩም ቢል እንኳን ደስታዬ ወደር የለውም። ዋናው ጉዳይ መስተካከሉ ነውና። አኹንም አቋም ኾኖ የተያዘ ከኾነ ግን ትልቅ ችግር ነው። ወንድም እኅቶቻችን ሆይ በአገልግሎት ተሠማርተን ላለነው ለኹላችንም ከወደዳችሁን ከልብ ጸልዩልን፤ ክፉ ሰይጣን ቀስ አድርጎ እንዳይጥለንና እንዳያጠፋን የእውነት የኾነ ልባዊ ጸሎት ያስፈልገናልና። ፍቅራችሁን እኛን ሊያድንና ሊጠቅመን በሚችል መንገድ ግለጹ እንጂ ሊጎዳን በሚችል መንገድ አታድርጉት።

                                     ቸር ሰንብቱ!
©ዲያቆን ዮሐንስ ጌታቸው

✨✨✨✨✨✨
✝️#ድምፀ_ተዋህዶ✝️
✨✨✨✨✨✨


#ስለ_ወንድማችን_አክሊል_አንዳንድ_ነገሮች!

#ወንድማችን_አክሊል_ጌታችን_ካረገ_በኋላ_አብን_ያመልካል_አላልኩም_የሚል_መልእክት_ስለላከልኝ_ዋናው_ጉዳይ_መስተካከሉ_ስለ_ኾነ_አንሥቼዋለሁኝ🙏

በመጀመሪያ አክሊልን ያወኩት በቲክቶክ ሲያስተምርና ለመ*ና*ፍ*ቃን መልስ ሲሰጥ ነው። በዚህ ረገድ በጣም የሚበረታታ ሥራን ሠርቷል፤ እየሠራም ይገኛል። በሚያቀርባቸው የሃይማኖት ትምህርቶች በቲክቶክ የሚከታተሉትን በውጭም በሀገር ውስጥም ያሉ ብዙ ምእመናንን አጽንቷል፤ የቤተ ክርስቲያንን ትምህርት እንዲረዱ ረድቷቸዋል። ይህም ብቻ ሳይኾን በኑ*ፋ*ቄ እሳት የነደዱትን መ*ና*ፍ*ቃንንም ወደ ቤተ ክርስቲያን እንዲመለሱ የበኩሉን አስተዋጽዖ አበርክቷል፤ አሁንም እያበረከተ ይገኛል። ይህን አገልግሎቱን የተረዳ ሰው ይጸልይለታል፤ እግዚአብሔር ከክፉ እንዲጠብቀው ያስበዋል።

እንደሚታወቀው አንድ ሰው አንድ መልካም ሥራ ሊሠራ ሲነሣ ብዙ ፈተናዎች ሊገጥሙት እንደሚችል ግልጽ ነው። ይህ ፈተና በመጀመሪያ ከራስ የሚመነጭ ነው። ይኸውም ስለ ራስ ያለ ቦታና ደረጃ ለወጥ እያለ የመሄድ ፈተና ቀዳሚው ነው። ይህ በእንዲህ ዓይነት ትጉህ አገልግሎት ላይ ባሉ ኹሉም ላይ ማለት እስኪቻል ድረስ የሚመጣ ፈተና ነው። ይህን ፈተና ተፈታኞቹ አንዳንዴ ላይረዱት ኹሉ ይችላሉ፤ አደገኛ የሚያደርገው ደግሞ ይህ ነው። በሌላ በኩል ደግሞ በምናቀርበው ነገር የተደሰቱ አካላት የሚያቀርቡልን ገነን ያለ ምስጋናና አክብሮት ሌላው የሕይወት ፈተና ይኾናል። ከእነዚህ ጋር ተያይዞ ደግሞ የበጎ ነገር ኹሉ ጠላት የኾነ ሰይጣን የሚያመጣብን ሰወር ያለ ወይም ግልጽ የኾነ ፈተና ይኖራል። ይህን መረዳት ተገቢ ነው። እንግዲህ ይህን በአጭሩም ቢኾንም ከግምት ውስጥ በማስገባት በአገልግሎት ላይ ላሉ ወንድሞቻችን ልንጸልይና ከእኛ እንደ ክርስቲያን የሚጠበቅብንን ልናደርግ ይገባል።

ኹለተኛው ነጥቤ - የወንድሜን አኬን አካሄድ ማዕከል ያደረገ ይኾናል። ይኸውም በአንድ በኩል አንድን ነገር ለማስረዳት የሚገልጽበት መንገድ ጸነን ማለት ሲኾን በሌላ በኩል ተደጋጋሚ ጊዜ ያቀረባቸውን የስሕተት ትምህርቶችን የሚመለከት ነው። እኔ ከእርሱ ጋር በአካል በተደጋጋሚ ጊዜ ባወራን ጊዜ ያገኘኹትና እንደ ወንድም ደጋግሜ መክሬው ግን እስካሁን አቋም አድርጎ የያዛቸው የስሕተት ትምህርቶችን በቅደም ተከተል ላስቀምጥ፦

1) ነገረ ክርስቶስን በተመለከተ ያቀረበው ስሕተት ነው።
  ይኸውም ኢየሱስ ክርስቶስ በሥጋው ወራት አብን አምልኳል የሚለው ነው። ይህን በተመለከተ እጅግ ስላስደነገጠኝ በጣም ለምኜዋለሁኝ። እባክህን ይህ ክሕደት ነው ተስተካከል ብዬዋለሁኝ በጓደኞቹ ፊት በጉዳዩ የምችለውን ኹሉ ለማለት ሞክሬያለሁኝ። እርሱ ግን ሚዲያ ላይ ከእንግዲህ ወዲህ አላነሣውም ቢኾንም ግን አቋሜ ነው ብሎኝ ነበር። ለዚህ ስሕተት መነሻ ያደረገውም ዮሐ 4፥21-22 ላይ ቅዱስ ቄርሎስ ያብራራውን እና አምብሮስ ዘሚላን ያለውን ነበር። በአቅሜ ለማስረዳት ሞክሬ ነበር። ያልኩትን አሁን አሻሽሎት ከኾነ ተመስገን ነው የምለው። ካልሆነ ግን በፍቅርና ክርስቲያናዊ በኾነ መንገድ እንዲያስተካክል ተማኅጽኖዬን በትሕትና በአደባባይ አቀርባለሁኝ።

2) ለኢየሱስ ክርስቶስ ከተዋሕዶ በኋላ አብ አምላኩ ነው የሚል አንዲት አጠር ያለች ቪዲዮ ሠርቶ ያ ቪዲዮ በብዙዎች ዘንድ ውዝግብን ፈጥሮ እንደ ነበር አስተውሳለኹኝ። ሙስሊሞችም አኬ ማለት ባልፈለገው መንገድ አጣመው ሲያራግቡት ነበር። ወንድማዊ በኾነ መንገድ በተደጋጋሚ ይህንም ጉዳይ በተመለከተ አውርተናል። ቪዲዮውንም እንዲያጠፋ ጽኑ ልመናዬን ከተግሣጽ ጋር በአካል አቅርቤለታለሁኝ። ኋላ ሌሎች መምህራንም ኾነን ተሰብስበን መክረነው ያን ቪዲዮ እንዳጠፋ ነግሮኝ ነበር። አቋሙ ግን እንደ ጸና ቀጥሏል። አብ ለኢየሱስ ከተዋሕዶ በኋላም አምላኩ ነው ማለት ምን ማለት ነው? ሥግው ቃል አንድ ከኾነና ሥጋን በመዋሐዱ ምክንያት ሥግው ቃል ፍጡር ነው የማይባል ከኾነ እንዴት ለሥግው ቃል አብ አምላኩ ሊባል ይችላል? በመጻሕፍት አምላኩ የተባለውን በጥንቃቄ ኾነን ቃል የተዋሐደው ሥጋ ፍጡር መኾኑንና ከተዋሕዶም በኋላ ያ ሥጋ አለመለወጡን ለማስረዳት መኾኑን እንገልጻለን እንጂ ከተዋሕዶ በኋላ ቃል የተለየው ዕሩቀ መለኮት የኾነ ሥጋ እንዳለ አድርገን አናምንም።

    ወንድሜ አክሊል ግን "ቃል የተዋሐደው ሥጋ ስላልተለወጠ አሁንም ያንሳል" ብሎ እንደሚያምን ነግሮኝ ነበር። አምላኬም ያለው በሥጋው ነው፤ ሥጋው ያንሣልና ብሎኝ ነበር። ይህ ደግሞ ምንታዌ ነው። ሥጋ ምንም እንኳን ፍጡርነቱን ባይለቅም ከተዋሕዶ በኋላ ከቃል ስለማይለይ ያንሣል አይባልም። ያንሣል የሚለውን ስሑት ትምህርት አባቶቻችን አውግዘዋል። አባ ጊዮርጊስ በመጽሐፈ ምሥጢር፤ ሊቃውንት በመዝገበ ሃይማኖት ይህ ትምህርት የልዮናውያን እንደ ኾነና በኛ ዘንድ ተቀባይነት እንደ ሌለው አንሥተዋል። ሥጋው ያንሣል ማለት በአንድ በኩል ከመለኮቱ ተለይቷል የሚያሰኝ ሲኾን በሌላ በኩል ያመልካል እንጂ አይመለክም የሚያሰኝ ነው። ይህ ደግሞ ተቀባይነት የለውም። በቀጥታ ምንታዌን የሚያስረዳ ነውና ይልቅስ በአበው ትምህርት ያለው ሥጋ ያለመለያየት በተዋሕዶ ከቃል ጋር አንድ ስለ ኾነ ይመለካል የሚል ነው።

3) ከመ*ና*ፍ*ቃን ጋር ሲወያይ "ለሥግው ቃል አንድ ፈቃድ እንዳለው ነገር ግን የሥጋ ፈቃድ ለመለኮት ፈቃድ ለዘላለም ሲገዛ እንደሚኖር" በተደጋጋሚ ጊዜ አንሥቶ ስምቼዋለሁኝ። ይህም የምሥራቅ ኦርቶዶክሶች ትምህርት ነው። እነርሱ ኹለት ፈቃድ አለ፤ አንዱ ገዥ (የመለኮት ፈቃድ) ሌላኛው ተገዥ (የትስብእት ፈቃድ) ብለው ያምናሉ። መነሻቸው የባሕርይ ተዋሕዶ ስለሌለ ከኹለት ባሕርይ ኹለት ፈቃድና ኹለት ግብር ይመነጫል የሚል አቋም ስላላቸው እንዲያ ብለው ያምናሉ። እኛ ግን ከኹለት ፈቃድ የተገኘ አንድ ፈቃድ ብለን ስለምናምን በሥግው ቃል ውስጥ የምንከፋፍለው ፈቃድ የለም። ፈቃዱ ከኹለት የተገኘ አንድ ነው። ይሄ የመለኮት ይህ ደግሞ የትስብእት ተብሎ ተለያይቶ ፈጽሞ አይነገርም። ይህን አድማሱ ጀንበሬና በመድሎተ አሚን፤ አለቃ አያሌው መች ተለመደና ከተኩላ ዝምድና በሚል መጽሐፋቸው አንሥተውታል። አንዳንድ ቅዱሳን ሊቃውንት በጥንቃቄ የሥጋ ፈቃድ እንዳልጠፋ ለማስረዳት ያነሡት እንጂ እንደ ኬልቄዶናውያን ከፋፍሎ አንዱ ገዥ ሌላው ተገዥ በሚያሰኝ መንገድ እንድንረዳ ለማድረግ ፈጽሞ አይደለም። 

4) "ቃል የተዋሐደው የጎሠቆለ ሰውነትን ነው" ብሎ አውርተንበት ነበር። ይህን የሚመስል አገላለጽ ያቀረቡ ሊቃውንትን ሐሳብ እንዴት መረዳት እንዳለብን አስረድቼው በጊዜው ከዲያቆን ብርሃኑ አድማስም ጋር እንዲያወሩ አድርጌ መ/ር ብርሃኑ በዚህ እና በእመቤታችን ጉዳይ (የጎሠቆለ ሰውነትን ለብሳለች አልለበሰችም በሚለው) ጽሑፍ ጽፎ በቴሌግራም ልኮለት ነበር። እኔም ከመ/ር ብርሃኑ አስቀድሜ ተው አክሊል አካሄድህ ጥሩ አይደለም ብዬ ረዘም ያለ የማብራሪያ ጽሑፍ  ከዓመት ከስድስት ወር በፊት ልኬለት ነበር፤ በተጨማሪ መምህር ግርማ ባቱን ጉዳዩን ነግሬያቸው ተገናኝተው እንዲነጋገሩ አሳስቤ የላኩለትንም ጽሑፍ ለመምህር ግርማ አያይዤ ልኬ አሳይቼው ነበር። ወንድሜ አክሊል ግን እስካሁን ከአቋሙ አልተንቀሳቀሰም።

✨✨✨✨✨✨
✝️#ድምፀ_ተዋህዶ✝️
✨✨✨✨✨✨


ዜና ዕረፍት


ከመጀመሪያው ፓትርያርክ ከብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ባስሊዮስ ፓትርያርክ ዘኢትዮጵያ ጀምሮ ለ59 ዓመታት በመንበረ ፓትርያርክ ጽ/ቤት በተለያዩ መንፈሳዊ ሥራ ዘርፍ ይሰሩ የነበሩ አባ ናሁ ሠናይ ላዳምጠው ከዚህ ዓለም ድካም ዐረፉ ::
በዕድሜ አረጋዊ  የነበሩት አባ ናሁ ሠናይ ባደረባቸው ሕመም ምክንያት በጠበልና በሕክምና ሲረዱ ቆይተው በተወለዱ በ89 ዓመታቸው የካቲት 7 ቀን 2017 ዓ,ም ሌሊት ላይ ከዚህ ዓለም ድካም አርፈዋል፣የአባ ናሁ ሠናይ ላዳምጠው ሥርዓተ ቀብር  በመርሀ ቤቴ በርቃቶ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ቤተ ክርስቲያን ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ፣በሺህ የሚቆጠሩ ምእመናንና ወዳጅ ዘመድ በተገኙበት ተፈጽሟል ።
የአባ ናሁ ሠናይ ዕረፍት የተሰማንን ኃዘን እየገለጽን ለቤተሰቦቻቸውና ለወዳጅ ዘመዶቻቸው መጽናናትን እንመኛለን።
     
ነፍሳቸውን በአጸደ ገነት ያኑርልን  አሜን !!!

     EOTC
✨✨✨✨✨✨
✝️#ድምፀ_ተዋህዶ✝️
✨✨✨✨✨✨


የደብረ ሮሐ ቅዱስ ላሊበላ ገዳም ግለሰቡ ከድርጊቱ እንዲታቀብ ማስጠንቀቂያ ሰጠ።


የቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያንን ቅርጽ በመጠቀም አሸተን በሚል ስያሜ አቶ እንዳለ ተስፋዬ የተባለ ግለሰብ በአሜሪካ የሽቶ ማምረቻ ድርጅት በመክፈት እያሰራጨ መሆኑን ተገልጿል፡፡

ይህም ተግባር የቤተ ክርስቲያኗን መብትና ቅድስና የተዳፈረ እንዲሁም ያለ ገዳሙ ፍቃድ የግሉ የፈጠራ ውጤት አድርጎ በአሜሪካ የአዕምሮ ንብረት ባለቤት አስመዝግቧል ያለው የገዳሙ አሰተዳደር ጽሕፈት ቤት ድርጅቱ ቤተ ክርስቲያኗን ይቅርታ በመጠየቅ  ዲዛይኑን እንዲቀይር በጥብቅ አሳስቧል።
አባ ሕርያቆስ ጸጋዬ የገዳሙ አስተዳዳሪ በማኅበረ ቅዱሳን ከወልድያ ማእከል ሚዲያ ክፍል ጋር በስልክ ባደረጉት ቆይታ ግለሰቡ ከድርጊቱ እንዲታቀብ ቢጠየቅም ቤተ ክርስታያኗ ፈቃድ ሰጥታኛለች ያለ ሲሆን ይህንንም የሚያረጋግጥ ሰነድ በደብራችን አልተገኘም ብለዋል፡፡

አክለውም ድርጅቱ ከተግባሩ የማይመለስ ከሆነ የቤተ ክርስቲያኗ ክብር እንዲከበር ከሚመለከታቸው የቤተ ክርስቲያን አካላት እና ከሀገረ ስብከቱ የሕግ ክፍል ጋር በመሆን እርምጃዎችን ለመውሰድ እንገደዳለን ሲሉ ተናግረዋል።

በማኅበረ ቅዱሳን

✨✨✨✨✨✨
✝️#ድምፀ_ተዋህዶ✝️
✨✨✨✨✨✨


🗓ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ የ2017 ዓ.ም የጾመ ነነዌ የሰላምና የጸሎት አዋጅ መግለጫ

✝️በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!✝️

ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ የተላለፈ የምህላ ሱባዔ፡-

‹‹ቀድሱ ጾመ ወስብኩ ምህላ አስተጋብኡ ሕዝበ ሊቃውንተ ሕዝብ፤ ጾምን ቀድሱ፣ጉባኤውንም አውጁ፤ሽማግሌዎችንና በምድር የሚኖሩትን ሁሉ ወደ ኣምላካችሁ ወደ እግዚአብሔር ቤት ሰብስቡ፤ ወደ እግዚአብሔርም ጩኹ (ኢዩ ፩÷፲፬)
 
ሁላችንም እንደምናውቀው ያለንበት ዓለም የመከራ ዓለም ነው፣ መከራው በኛ ስሕተትና ክፋት የመጣና እየሆነ ያለ መሆኑም ይታወቃል፤ እኛ የምንፈጽመው ጥቃቅንና ትላልቅ ግብረ ኃጢአት እግዚአብሔርን እንደሚያስቈጣ በቅዱስ መጽሐፍ ተረጋግጦ ያደረ ነው፤ ለዚህም ከነነዌ ነዋሪ ሕዝብ የበለጠ ማስረጃ የለንም፤ የነነዌ ከተማ ነዋሪዎች በፈጸሙት ግብረ ኃጢአት እግዚአብሔርን አስቈጥተዋል፤ ድርጊታቸው እግዚአብሔርን የሚያስቆጣ ቢሆንም እሱ ምሕረቱን ማስቀደም ስለፈለገ በዮናስ በኩል አስጠንቅቆአቸዋል፤ የነነዌ ነዋሪዎችም በዮናስ በኩል የደረሳቸውን የንስሓ ጥሪ ወዲያውኑ ተቀብለው በምህላ፣ በጾም፣ በጸሎት ንስሓ ስለገቡ እግዚአብሔር ፍጹም ይቅርታ አድርጎላቸዋል፤

የተወደዳችሁ ኢትዮጵያውያንና ኢትዮጵያውያን ልጆቻችንና ወገኖቻችን !
እኛ ሰዎች ዛሬም በየሰዓቱ ብቻ ሳይሆን በየደቂቃው እግዚአብሔርን የሚያስቆጣ አበሳ እንደምንፈጽም ማወቅ ኣለብን፣

አበሳውና ኃጢኣቱ ሲበዛ እግዚአብሔር እውነተኛ ዳኛ ነውና ወደ ዳኝነት ተግባሩ ይገባል፤ይህ ደግሞ በሰብአ ትካት በሰዶምና በጎሞራ ያስተላለፈውን ዳኝነት ያስታውሰናል፤ አሁን ያለንበት ዘመን ዓመተ ምሕረት በመሆኑ እግዚአብሔር ለጊዜው ቢታገሠንም በኃጢኣታችን የምንጠየቅበት ጊዜ አዘጋጅቶአል፤ ዛሬም ቢሆን የማናስተውለው ሆነን ካልሆነ በስተቀር እግዚአብሔር ተግሣጹን ማስተላለፍ አላቆምም፤ በምድራችን ላይ በምናደርሰው የተዛባ ተግባር በጐርፍ፣ በድርቅ፣ በመሬት መንቀጥቀጥና በአየር መዛባት እየገሠጸን እንደሆነ ማስተዋል አለብን።

እግዚአብሔር ከጥንቱ ከጠዋቱ ጀምሮ ምድርን እንድንከባከባት፤ እንድናበጃት፣ እንድናጠብቃትና እንድናለማት አዞናል፤ ሆኖም ይህን ትእዛዙን ገሸሽ አድርገን በኬሜካልና በመርዛም ጋዝ ምድርን በመበከል፣ ደንዋን በመመጠርና ራቁቷን በማስቀረት በምናደርገው ድርጊት አበሳ እየፈጸምን እንደሆነ ያወቅነው አይመስልም፤ በዚህም ምክንያት በጐርፍ፣ በድርቅ ለሰው ልጆች በማይመች የኣየር ፀባይ ወዘተ . . . ስጋት ውስጥ እየወደቅን ነው፤

በሌላም በኩል በምናወሳስበው የአስተዳደር ርእዮትና መሳሳብ የእግዚአብሔር ገንዘብ የሆነውን ሕዝብ እርስ በርሱ እንዲጋጭና ያላስፈላጊ አደጋ ላይ እንድወድቅ እያደረግን ነው፤ በዚህም ጠንቅ ሰላም እየደፈረሰ፣ ፍቅርና አንድነት እየላላ የሃይማኖት ክብርና ልዕልና እየተነካ ራሳችንንም እየጐዳን ነው፤ በዚህ ሁሉ ተግባራችን  እግዚአብሔርን እያሳዘንን ነው፤ ይህ ሊገባንና ሊቈረቁረን ይገባል።

የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን ምእመናንና ምእመናት
ለችግሮች ሁሉ መፍትሔ አላቸው፤ መፍትሔውም የሚገኘው ከእግዚአብሔርና ከእኛ ነው፤ ከእኛ በንስሓ ተመልሰን ከልብ እግዚአብሔርን ይቅርታ መጠየቅና ከክፉ ተግባራችን በእውነት መጸጸት ይጠበቃል፤ እግዚአብሔር ደግሞ ይህንን ዓይነቱ ንስሓ ከኛ መኖሩ ሲመለከት ምሕረትና ይቅርታን ይለግሰናል፤ በዚህም መፍትሔና ፈውስ ይገኛል፤ ከዚህ አንጻር በአሁኑ ጊዜ ለሀገራችንና ለዓለማችን ስጋት የሆኑ የጦርነት ክሥተቶች፣ የመሬት መንቀጥቀጥ፣ የአየር መዛባት፣የድርቅ መከሠት፣ የጎርፍ መጥለቅለቅ የሰላም መደፍረስ፣ የሰላማውያን ወገኖች መጎዳት፣ የፍቅርና የአንድነት መላላት ወዘተ. . . .ከምድራችን ተወግደው ፍጹም ምሕረትና ሰላም እናገኝ ዘንድ በኃጢኣታችን ተጸጽተን በምህላ ንስሓ መግባት አለብን፤ ከዚህ አኳያ ከጥንት ጀምሮ በቤተክርስቲያናችን ቀኖናዊ ሥርዓት መሠረት


በየዓመቱ የሚጾመው ጾመ ነነዌ ለዚህ አመቺ ጊዜ ስለሆነ ከየካቲት ፫ ቀን ፳፻፲፯ ዓመተ ምሕረት ጀምሮ  ለሦስት ቀናት ከልኂቅ እስከ ደቂቅ ሁላችንም ጠዋትና ማታ በየቤተክርስቲያኑ ዐውደ ምሕረት እየተገኘን በንስሓ በዕንባ በጸሎት በምህላ የእግዚአብሔርን ምሕረትና ይቅርታ እንድንጠይቅ፤ እንደዚሁም በሀገራችንና በውጭ ያላችሁ ሊቃውንተ ሕዝብ ቀኖናውን ጠብቃችሁ ይህንን በማስፈጸም ምህላውን በቀኖናው መሠረት እንድታከናውኑ በእግዚአብሔር ስም አባታዊ መልእክታችንን እናስተላልፋለን።

እግዚአብሔር አምላካችን ምሕረቱን ይቅርታውንና ሰላሙን ለሀገራችንና ለዓለማችን ይስጠን፤ ምህላችንንም ይቀበልልን፤
   “እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ይባርክ” ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን!!
                አባ ማትያስ ቀዳማዊ
ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ
     ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት
                ጥር ፳፱ ቀን ፳፻፲፯ ዓ.ም
                  አዲስ አበባ ኢትዮጵያ


(EOTC Broadcasting Service Agency)

✨✨✨✨✨✨
✝️#ድምፀ_ተዋህዶ✝️
✨✨✨✨✨✨


|°°ለጀማሪ የግእዝ ቋንቋ ወዳጆች ሁሉ
  🙌 ሰላም ጤና ይስጥልን ክቡራት እና ክቡራን የልሳነ ግእዝ ስልጠና በ @ye_mariam_agelgay እየሰጠን እንደሆነ ይታወቃል ሆኖም የጀማሪዎች ስልጠና  በቅርቡ በonline ስለሚጀመር በዚህ #ዙር ላይ 25 ተማሪዎች ብቻ ስለሚካተቱ ከወዲሁዠለጀማሪችሁን እንድታዘጋጁና በፍጥነት እንድትመዘገቡ መልእክታችንን እናስተላልፋለን።
#ለሁለት ወር የመማሪያ ሙሉ ክፍያ #250ብር ብቻ ከነ የምስክር ወረቀቱ ለበለጠ መረጃ በ @asrategabriel ያነጋግሩን አልያም በ +251970908094 ይደውሉልን።

   🤲ሰብሕዎ የልሳነ ግእዝ ማሰልጠኛ ተቋም🧑‍🎓


🗓ጥር ፳፩ (21) እንኳን የአምላክ እናት
ለቅድስተ ቅዱሳን ለንጽኅተ ንጹኀን ወላዲተ አምላክ ማርያም የእረፍቷ መታሰቢያ በዓል በሰላም አደረሳችኹ አደረሰን።


አስተርእዮ ማርያም አስተርእዮ ማለት√√√√  መታየት፣ መገለጥ ማለት ነው። ቃሉ አስተርአየ ታየ፣ ተገለጠ ከሚለው የግዕዝ ግሥ የተገኘ ነው ••••• ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በገባው ቃል ኪዳን መሠረት በሥጋ የተገለጠበት(የታየበት) ፣ አንድነት ሦስትነቱም የተገለጠበት ወቅት በመሆኑ ከልደት በዓል እስከ ጥር መጨረሻ በሙሉ ዘመነ አስተርእዮ በመባል ይታወቃል። የእመቤታችን በዓለ ዕረፍት በዘመነ አስተርእዮ ውስጥ ስለሚከበር “አስተርእዮ ማርያም” ተብሏል።

ልቡናዋ በይኩነኒ የጸና ንጽሐ ሥጋ ፣ ንጽሐ ነፍስ ፣ ንጽሐ ልቡና አስተባብራ የያዘች ወላዲተ አምላክ ምንም እንኳን የአምላክ እናት ብትሆንም ሞተ ሥጋ ለሁሉም ዕጣ ፈንታ በመሆኑ በቃል መነገሩ በልብ መታሰቡ ከፍ ከፍ ይበልና ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ “ተንሥኢ ወንዒ”  የነፍሴ ደስታ የኾንሽ ውድ እናቴ ሆይ ተነሥተሽ ወደ እኔ ነዪ (መኃ ፪፥፲) ብሏታል።

ሞታ ለማርያም የዐጽብ ለኲሉ

ቅዱስ ዳዊት “ነኪር ነገሩ በእንቲአኪ ሀገረ እግዚአብሔር” መዝ.፹፮፥፫ እግዚአብሔር ማህጸንሽን ከተማ አድርጎ ዘጠኝ ወር ከአምስት ቀን የኖረብሽ ሆይ ስለ አንቺ የተነገረው የተደረገው ነገር ዕጹብ ድንቅ ነው እንዳለ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የአምላክ እናት ሆና ማረፏ ይደንቃል። ታላቁ የቤተክርስቲያናችን አባት ቅዱስ ያሬድ ሞቷ የሚያስደንቅ መሆኑን «ሞትሰ ለመዋቲ ይደሉ ሞታ ለማርያም የዐጽብ ለኲሉ፤ ሞት ለማናቸውም ሰው ሁሉ የተገባ ነው የማርያም ሞት ግን ሁሉን ያስደንቃል» በማለት ገልጾታል።

ሞት በጥር ነሐሴ መቃብር

የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን ሞትና ትንሣኤ በነገረ ማርያም አበው እንደሚያስረዱት ዕረፍቷ በጥር ፳፩ እሑድ ነው ። አባቶቻችን በጾመ ፍልሰታ ውዳሴ ማርያም ቅዳሴ ማርያም ሲተረጉሙ የእረፍቷን ነገር እንዲህ ብለው ይተርካሉ።

የእረፍቷስ ነገር እንደምን ነው ቢሉ ስድሳ አራት ዓመት በዚህ ዓለም ኖራ ጥር ፳፩ በእሑድ ቀን ጌታ እልፍ አዕላፋት መላእክቱን አስከትሎ መጥቶ እናቴ ሆይ ከዚህ ዓለም ድካም ላሳርፍሽ መጣሁ አላት። ልጄ ሰማይና ምድር የማይወስኑህ ዘጠኝ ወር ከአምስት ቀን በማህጸኔ ተሸክሜ በድንግልና ወልጄህ እሞታለሁን? አለችው። በሲዖል የሚሰቃዩ ነፍሳትን አሳይቶ እናቴ ሆይ ሞትሽ ለእነዚህ ቤዛ ይሆንላቸዋል አላት። እሊህን ከማርክልኝስ ይሁን አለችው። ቅድስት ሥጋዋን ከቅዱስ ነፍሷ ለይቶ በቃለ አቅርንት በዝማሬ መላእክት አሳረጋት። ደቀመዛሙርቱንም ከያሉበት በደመና ጠቅሶ ካለችበት አድርሶ እመቤታችሁን ስጋዋን በክብር አሳርፉ አላቸው። ሐዋርያት በአጎበር አድርገው ወደ ጌቴሰማኒ ይዘው ሲሄዱ አይሁድ ቀድሞ ልጇን ተነሳ ዐረገ እያሉ ሲያውኩን ይኖራሉ አሁን ደግሞ እሷን ተነሳች ዐረገች እያሉ ሊያውኩን አይደለምን በእሳት እናቃጥላታለን ብለው ተነሱ። ታውፋንያ የሚባል አይሁዳዊ ተራምዶ አጎበሩን ጨበጠው። መልአክ መጥቶ በሰይፍ ሁለት እጁን ቀጣው ከአጎበሩ ተንጠልጥሎ ቀረ። በድያለሁ ማሪኝ ብሎ ቢማጸናት እጁ ተመልሶለታል። ከዚህ በኋላ ዮሐንስን ጨምሮ በደመና ነጥቆ ከገነት አግብቶ ከዕፀ ሕይወት ሥር አኖራት።

ቅዱስ ዮሐንስን እንደምን ሆነች አሉት ከገነት ከዕፀ ሕይወት ሥር አለች አላቸው ቅዱስ ዮሐንስ አይቶ እኛ ሳናይ ብለው በነሐሴ መባቻ ጾም ጀመሩ ሁለት ሱባዔ ሲፈጸምም እሑድ አምጥቶ ሰጥቷቸው ቀብረዋታል በሶስተኛው ቀን ማክሰኞ “ከመ ትንሳኤ ወልዳ” እንደ ልጇ ተነሥታለች። ቅዱስ ቶማስ አልነበረም ደመና ጠቅሶ ከሀገረ ስብከቱ ሲመጣ ስታርግ አገኛት ቀድሞ የልጅሽን ትንሳኤ ሳላይ ቀረሁ ዛሬም ደግሞ ያንችን ትንሳኤ ሳላይ ቀረሁን ብሎ “ወፈቀደ ይደቅ እምደመናሁ” ከሀዘኑ የተነሳ ሊወድቅ ወደደ እመቤታችንም አይዞህ አትዘን እሊያ ትንሳኤየን ዕርገቴን አላዩም አንተ አይተሃል ተነሣች ዐረገች ብለህ ንገራቸው ብላ የያዘችውን ሰበን ሰጥታ ሰደደችው። ከዚህ በኋላ ሂዶ የእመቤታችን ነገር እንደምን ሆነ አላቸው አግችተን ቀበርናት አሉት ሞት በጥር በነሐሴ መቃብር ተው ይህ ነገር አይመስለኝም አላቸው። ቅዱስ ጴጥሮስ አንተ እንጅ ልማድህ ነው አንተ ብቻ ተጠራጥረህ አትቀርም ሰውን ሁሉ ስታጠራጥር ትኖራልህ ብሎ ተቆጥቶ ወደ መቃብሩ ሂዶ ቢከፍተው አጣት ደንግጦ ቆመ ሐዋርያው ቶማስም አታምኑኝም ብየ እንጅ እመቤታችንስ ተነሣች ዐረገች አላቸው የያዘውንም ሰበን ሰጣቸው ለበረከትም ተካፍለውታል። በዓመቱ ሐዋርያት ቅዱስ ቶማስ ትንሣኤሽን ዕርገትሽን አይቶ እኛ ሳናይ ብለው ጾም ጀመሩ በ፲፮ኛው ቀን እመቤታችንን መንበር አድርጎ ቅዱስ ጴጥሮስን ካህን ዘይትራድኦ ቅዱስ እስጢፋኖስን ሠራዒ ዲያቆን አድርጎ በዚያው ላይ ቀድሶ አቁርቧቸዋል። ቤተክርስቲያንም ይህንን መታሰቢያ አድርጋ በየዓመቱ ታከብረዋለች።

የኃጥአንን ለቅሶና ሐዘን አይተሽ ስለእነርሱ ድኅነት(መዳን) ዕረፍትሽን በሀሴት የተቀበልሽ እመቤታችን ሆይ ሐዋርያት በሱባዔ ትንሣዔሽን ለማየት በቅተዋልና እኛም በዓለ ዕረፍትሽን አክብረን ልጅሽ በሰጠሽ ቃል ኪዳን በቀኙ እንቆም ዘንድ ለምኝልን። አሜን።

✨✨✨✨✨✨
✝️#ድምፀ_ተዋህዶ✝️
✨✨✨✨✨✨


Репост из: 🙏ኦርቶዶክሳዊ ዝማሬ🙏
🗓 ነገ ማለትም
ዕለት:- ረቡዕ
#ቀን:- ጥር ፲፬ ፳፻፲፯ ዓ.ም
በቅድስት ቤተክርስቲያናችን


አቡነ አረጋዊ (አመታዊ)
አባ ጳኩሚስ ፣ ቅዱስ ገብረ ክርስቶስ ፣ አቡነ ተስፋ ጽዮን ፣ ሰማዕቱ አብሮኮሮስ ፣ አባ ዘሚካኤል ፣ ሙሴ ጸሊም


አክብረን እና አስበን እንውላለን

እስትንፋስ ያለው ሁሉ እግዚአብሔርን ያመስግን( መዝ 150 - 6 )


✝️ለባለ ማህተቦች✝️ሼር ያድርጉ↗️

✨✨✨✨✨✨✨
✝️#ኦርቶዶክሳዊ_ዝማሬ✝️
✨✨✨✨✨✨✨


​​​​✝️ጾመ ገሀድ✝️


ከዘጠኙ ዓበይት የጌታ በዓላት ሁለቱ የልደትና የጥምቀት በዓላት ተጠቃሾች ናቸው  በሁለቱ በዓላት ቀን ክርስቲያን የሆነ ሁሉ በኀዘን ማሳለፍ እንደሌለበት ቅዱሳት መጻሕፍት ይናገራሉ ምክንያቱም የክርስቶስ ልደትና ጥምቀት የዕዳ ደብዳቤያችን የተቀደደባቸው የድኅነታችን መሠረት የተጣለባቸው ዐበይት በዓላት  ስለሆኑ ነው እነዚህ በዓላት በረቡዕና በዓርብ ቀን ከዋሉ አስቀድመን በዋዜማው ለውጥ አድርገን እንጾማቸዋለን ልደት ረቡዕ ከሆነ ማግሰኞ በዋዜማው፣ ዓርብ ከሆነ ሐሙስ በዋዜማው እስከምሽቱ አንድ ሰዓት (13 ሰዓት) እንጾማቸዋለን በሌሎችም ቀናት በዋዜማቸው በየዓመቱ ይጾማሉ ቀናቱ ሁለት ቢሆኑም  ቁጥራቸው ግን ከሰባቱ አጽዋማት አንዱ ተብለው ነው የሚቆጠሩት፡፡

ገሃድ ሁለት መጠሪያ ስሞች አሉት ገሃድና ጋድ፡፡ ገሃድ ማለት መገለጥ መታየት መታወቅ ማለት ነው ተገለጠ ታየ ታወቀ የተባለውም ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው ምንም ከዚያ በፊት አምላክነቱ የተገለጠባቸው ብዙ መንገዶችና ተአምራት ቢኖሩም አብ በደመና ሁኖ የምወደው ልጄ ይህ ነው በማለት፣ መንፈስ ቅዱስም በርግብ አምሳል ወርዶ በራሱ ላይ በመቀመጥ የክርስቶስ አምላክነት የተገለጠበት ዕለት ስለሆነ ገሀድ መገለጥ ተብሎ ተሰይሟል

➦በሌላም በኩል ጋድ ማለት ለውጥ ማለት ነው ልደትና ጥምቀት ረቡዕና ዓርብ ሲሆኑ ለውጥ ሁኖ የሚጾምበት ማለት ነው ስለዚህ ገሀድ ስንል የክርስቶስን አምላክነት በዕለተ ጥምቀት መገለጥ፣ ጋድ ስንል ደግሞ ለዓርብና ለረቡዕ ጾም ለውጥ ሁኖ የተጾመውን ጾም ማለታችን ነው፡፡ ይህንን ጾም ጥር 10 ቀን የሚነበበው ስንክሳር እንዲህ ሲል ይገልጸዋል፡፡

   

  
🕯 ✝️መልካም በዓል✝️✨🕯

✨✨✨✨✨✨
✝️#ድምፀ_ተዋህዶ✝️
✨✨✨✨✨✨


🗓🤲ሰላም ለሕላዌክሙ ዘአይትአወቅ እምጥንቱ ወዘኢይትረአይ ተፍጻሜቱ ሥሉስ ቅዱስ ዘኢትመውቱ እንዘ ሠለስቱ አሐዱ ወእንዘ አሐዱ ሠለስቱ ለዕበይክሙ ፍፃሜ አልቦቱ 👉

       
መልክአ ሥላሴ


✝️ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን ✝️

📣 እንኳን ለአጋዕዝተ ዓለም ሥላሴ በዓል በሰላም አደረሳችሁ አደረስን 🙏

👉 ጥር ፯(7) በዓለ ሥሉስ ቅዱስ ሶል ጴጥሮስ ዘሮሜ ወኢፍራ ወአትንያኖ ወሉያ ወመይልን ወመሰላዮስ ወማርትያ 👉

✝️ ዘነግህ ምስባክ ✝️

ሣህሉ ለእግዚአብሔር መልአ ምድረ
ወበቃለ እግዚአብሔር ጸንዓ ሰማያት
ወእምእስትንፋስ አፉሁ ኵሉ ኀይሎሙ

✤ ትርጉም ✤

የእግዚአብሔር ቸርነትን ምድርን መላች
በእግዚአብሔር ቃል ሰማዮች ጸኑ
ኀይላቸውም ሁሉ በአፉ እስትንፋስ

             መዝ ፴፪-፭
                    32  5

✤ ወንጌል ✤

ማቴ ም ፳፰ ቁ ፲፮-ፍ.ም
            28    16  ፍፃሜው

✝️ የቅዳሴ ምንባባት ✝️

ቈላስ ም ፪ ቁ ፲-፲፯
፩ ዮሐ ም ፪ ቁ ፳፭-ፍ.ም
ግብ.ሐዋ ም ፳፪ ቁ ፯-፳፪

✝️ ምስባክ✝️

የሐዩ ወይሁብዎ እምወረቀ ዓረብ
ወዘልፈ ይጼልዩ በእንቲአሁ
ወኵሉ ዓሚረ ይድኀረዎ

✝️ ትርጉም ✝️

እርሱ ይኖራል፤ከዐረብ ወርቅ ይስጡታል
ሁልጊዜ ወደርሱ ይጸልያሉ
ዘወትርም ይባረኩታል

             መዝ ፸፩-፲፭
                     71  15

❖ ወንጌል ❖

ማቴ ም ፪ ቁ ፳፩-ፍ.ም
           2     21   ፍፃሜው


✝️ቅዳሴ✝️

ዘእግዚእነ

" በሱራፌል በኪሩቤል የምትቀመጥ አምላካችን እግዚአብሔር የምትመለከት ወንዶቹንና ሴቶቹን ባሮችህን ልጆቻቸውንም ባርክ "

        ቅዳሴ እግዚእነ
          ም ፩ ቁ ፸፰
              1     78


📣📣📣📣📣📣📣📣📣📣

በዓሉን በዓለ ምህረት በዓለ ፀጋ በዓለ በረከት ያድርግልን አምላካችን መድኃኒታችን ዘላለም ሥላሴ በቸርነቱ ይማረን እናታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በምልጃዋ አትለየን ፍቅሯን በልባችን ጣዕሟን በአንደበታችን ታሳድርብን በዕፀ መስቀሉ ይባረከን ይጠብቀን ቤተክርስቲያን ቅድስትን በረድኤት ይጠብቅልን በየሰዓቱ በየደቂቃው ጠባቂ መላዕክት አያሳጣን በቅዱሳኑ ፀሎት ይማረን ዕጣነ አሮን ፀሎተ ምናሴ የተቀበለ ዘላለም ሥላሴ የኛንም ፆም ፀሎት ምስጋና በብሩህ ገጽ ይቀበልልን በዓል ተከትሎ ከሚመጣ መቅሠፍት አምላክ ቅዱሳን ይሰውረን ይጠብቀን ለሃገራችን ስላም ለህዝባችን አንድነትን ይስጥልን ለብርሃነ ጥምቀቱ በሰላም ያድርሰን ህንጻ ስናዖርን ያፈረሰ ዘላለም ሥላሴ የኃጢአተኛን ድልድይ ዘመናችንን ይባርክል


 ✨✨✨✨✨✨
✝️#ድምፀ_ተዋህዶ✝️
✨✨✨✨✨✨


" ልጆቻችን በሰላም መኖር እንዲችሉ፣ በጦርነት እየተሰቃዩ የሕመማቸውን ልክ መናገር የማይቻለን የኦሮሚያና የአማራ ክልል ነዋሪዎች ሰላምን እንዲያገኙ ጥሪ እናስተላልፋለን " - ቅዱስነታቸው

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ  ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት  ወቅታዊ  ጉዳዮችን አስመልክተው አባታዊ የሰላም ጥሪ አስተላለፉ።

ቅዱስነታቸው ፤ በሀገራችን በልዩ ልዩ አካባቢዎች ያሉ ጦርነቶች እንዲቆሙ ጥሪ አቅርበዋል።

" ልጆቻችን በሰላም መኖር እንዲችሉ፣ በጦርነት እየተሰቃዩ የሕመማቸውን ልክ መናገር የማይቻለን የኦሮሚያና የአማራ ክልል ነዋሪዎች ሰላምን እንዲያገኙ አባታዊ ጥሪ በድጋሚ እናስተላልፋለን " ብለዋል።

ቅዱስነታቸው ፤ በትግራይ ክልል ያለው የአስተዳዳሪዎች አለመግባባት በሕዝቡ ላይ ተጨማሪ ችግርና ጭንቀት እያመጣ መሆኑን ጠቁመዋል።

" በትሕትና መንፈስ እርስ በርስ መገናዘብ ተፈጥሮ ዕረፍት ያጣው ሕዝብ መረጋጋት እንዲችል ታደርጉ ዘንድ አደራችን የጠበቀ ነው " ብለዋል።

በተጨማሪም ቅዱስነታቸው በትግራይ ክልል ስለሚገኙ የሃይማኖት አባቶች ጉዳይ በአባታዊ የሰላም ጥሪ መልዕክታቸው አንስተዋል።

" መበደላችሁን እናውቃለን ፣ በኀዘናችሁ ሰዓት አብረን መቆም ባለመቻላችን ማዘናችሁም እርግጥና ተገቢ ነው " ያሉት ቅዱስነታቸው " ነገር ግን ሁሉም ነገር የሚካሰው በእርቅ ሲሆን እኛ የገፋነውን እርቅ ዓለም ሊቀበለው ስለማይችል፤ በእጃችንም የያዝነው መስቀለ ክርስቶስ የሰላም ዓርማ ነውና ልባችሁን ለሰላም፣ ለአንድነት እንድታዘጋጁ እንጠይቃለን " ብለዋል።

በሌላ በኩል ቅዱስነታቸው በመሬት መንቀጥቀጥ እየተጨነቁ ላሉ እና ስለተጎዱ ልጆቻቸው መልዕክት አስተላልፈዋል።

" የመሬት መንቀጥቀጥ ባለበት አካባቢ እየተጨነቃችሁ ያላችሁ ልጆቻችን ረድኤተ እግዚአብሔር ከእናንተ ጋር እንዲሆን ቤተ ክርስቲያን በጸሎት የምታስባችሁ መሆኑን እየገለጽን መላው ኢትዮጵያውያን ለጉዳቱ ተጋላጭ በሆኑ አካባቢዎች ለሚኖሩት ወገኖቻቸው አቅማቸው በፈቀደው መጠን ድጋፍ ያደርጉ ዘንድ አባታዊ መልእክታችንን በእግዚአብሔር ስም እናስተላልፋለን " ብለዋል።

(የቅዱስነታቸው ሙሉ መልዕክት ከላይ ተያይዟል)



✨✨✨✨✨✨
✝️#ድምፀ_ተዋህዶ✝️
✨✨✨✨✨✨


✨የጌታ ልደት✨
    🪔🪔🪔🪔

🗓የጌታ ልደት ክርስቲያናዊ ክብረ በዓል
ከጾም መጨረሻ በኋላ የሚመጣ መልካም ቃላትና በጎ ፈቃድን የምንለዋወጥበት ቀን ብቻ አይደለም፡፡ነገር ግን እውነተኛ በዓል ከደስታውና ከአከባበሩ ጋር በዓሉን ተከትሎ የሚመጣ መልካም ነገርና ጥበብን ሁሉ የምንማርበት ነው፡፡ለመሆኑ ከበዓላት የምንማረው በጎ ነገር ምንድን ነው?                        ፩.ትህትና   
  ከገና በዓል የምንማረው ታላቅ ነገር ትህትና ነው፡፡ጌታችን በቤተልሔም ይሁዳ በከብቶች በረት በመወለዱ ምሳሌውን ትቶልናል፡፡ጌታችን ሲወለድ ብዙ አጀብና ክብር አልነበረም፡፡ወደ ዓለም ሲመጣ ለሁሉም እየታየ በኪሩቤልና በሱራፌል ሠረገላ ላይ ተቀምጦ ለዓለሙ ሁሉ እያወጀ መሆን ይገባው ነበር፡፡ነገር ግን ለውጫዊ ዕይታ ትኩረት አልሰጠም፡፡በቀዝቃዛ ወራት በብርድ ቀን በሌሊት ማንም ትኩረት ሊሰጥ በማይችለው በከብቶች ግርግም ተወለደ፡፡የሚለብሰው በቂ ልብስ አልነበረውም፡፡ የጌታ በከብቶች በረት መወለድ ትህትናን የምንማርበት ትልቁ ትምህርት ቤት ነው፡፡ትሕትናው ባይኖር ኖሮ ይህ በዓል ሰማያዊ መንፈሳዊ የሆነ ምስጢሩ ባልተገለጠ ነበር፡፡የጌታን ትሕትና ገንዘብ ለማድረግ ሞክር፡፡ በሥጋዌው ራሱን ዝቅ አደረገ የባሪያ መልክ ይዞ በሰው አምሳል ተገለጸ፡፡/ፊል 2፡8/፡፡ትሕትናን ከጥልቁ እንፈልገው እንዴት እንደምንጠቀም እንወቅበት መድኃኒታችን በሥጋዌው ያደረገው ይኼንን ነው፡፡                           ፪.የዋኅነት       
  ከልደት በዓል የምንመለከተው ጌታ ፈቃዱን የገለጸው ለተወሰኑ ወገኖች ነው፡፡ሌሎች ምንም እንኳን በሥልጣን ከፍ ከፍ ያሉ ቢሆኑም አልተመረጡም፡፡ለምሳሌ ጌታ ልደቱን የገለጸው ለእረኞች ነው፡፡ሌሎች ጸሐፍት፣ ፈሪሳውያን ካህናትና ሽማግሌዎች ይህንን መልካም ዜና አላዩም፡፡ምክንያቱም የእግዚአብሔር ምሥጢር የሚገለጸው ልበ ንጹሐን ለሆኑ ወገኖች ስለሆነ ነው፡፡ሰብዓ ሰገልና እረኞች የሰሙትን ነገር አመኑ፡፡የዋኻንም ነበሩ፡፡ ታላላቅ ሰዎች እንዲህ ያለ የተዘጋጀና የዋኅ የሆነ ልብ አልነበራቸውም፡፡ ሄሮድስ ይሄንን ሁኔታ በሰማ ጊዜ ውሸትንና ምክንያትን በመፈለግ ለሥልጣኔ ባላንጣ ነው ብሎ ስላሰበ የማሳደድ ዕቅድን አወጣ፡፡ታዲያ እኛ ከየትኛው ወገን ነን ክርስቶስን በየውኀት ከሚቀበሉት ወይስ ከሚያሳድዱት?          
ቅድስት ድንግል ማርያም የዋኅ ልብ የነበራት ነበረች፡፡ስለ እርሷ ከጌታ የተነገረላትን አመነች፡፡ድንግል ሳለች ልጅ እንደምትወልድ አመነች፡፡ዮሴፍ በሕልም የጌታ መልአክ የነገረውን ነገር አመነ፡፡እራሳችንን እንዲህ ብለን እንጠይቅ ‹‹የምንመላለሰው በየዋኅ ልብ ነውን? ወይንስ የተወሳሰበና የሚጠራጠር ልብ ነው ያለን? መልሱን ለእናንተ ትተናል፡፡ እኛ ግን እንደ እርግብ የዋሓን ሁኑ የሚለውን የመጽሐፍ ቅዱስ ቃል እናስታውስዎት፡፡

                                                                     ✍️ብፁእ ወቅዱስ  አቡነ ሺኖዳካከ


✨✨✨✨✨✨
✝️#ድምፀ_ተዋህዶ✝️
✨✨✨✨✨✨


ብፁዕ አቡነ ዳንኤል ዐረፉ

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በ5ኛው ኢትዮጵያዊው ፓትርያርክ በብፁዕ አቡነ ጳውሎስ  ነሐሴ 22 ቀን 1997 ዓ.ም ከተሾሙ 17 ጳጳሳት አንዱ የሆኑት ብፁዕ አቡነ ዳንኤል ዐረፉ።

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የድሬዳዋ እና የጅቡቲ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳሳት የነበሩት ብፁዕ አቡነ ዳንኤል ትናንት ከምሽቱ አምስት ሰዓት አካባቢ በመንበረ ፓትርያርክ በሚገኘው ማረፊያ ክፍላቸው እንዳረፉ ለማወቅ ተችሏል። 
ብፁዕነታቸው በሰሜን አሜሪካ ለረጅም ዓመታት አገልግሎት በመስጠት እንደሚታወቁ የገለጠው ዐደባባይ ሚዲያ የልብ ሕመም እንዳለባቸው ሐኪም ሲነግራቸው በዚህ ዕድሜዬ ቀዶ ጥገና አይደረግልኝም ወደ አገሬ ሔጄ ለአገሬ አፈር ልብቃ ማለታቸውን ዘግቧል።
የብፁዕነታቸው በረከት ይደርብን።
ነፍሳቸውን በቅዱሳን እቅፍ ያሳርፍልን።


✨✨✨✨✨✨
✝️#ድምፀ_ተዋህዶ✝️
✨✨✨✨✨✨


🗓" እኔ በእግዚአብሔር ፊት የምቆመው ገብርኤል ነኝ " (ሉቃ 1:19)


        
✝️ ቅዱስ ገብርኤል ማን ነው ???

❤️ ገብርኤል:- ማለት የእግዚአብሔር አገልጋይ ማለት ነው ከሰባቱ ሊቃነ መላእክት አንዱና ከሊቀ መላእክት ከቅዱስ ሚካኤል ቀጥሎ ስልጣን የተሰጠው ታላቅ መልአክ ነው።

​​እንኳን አደረሰን አደረሳችሁ❣️

👑" እኔ በእግዚአብሔር ፊት የምቆመው ገብርኤል ነኝ " (ሉቃ 1:19)


         ✝️ ቅዱስ ገብርኤል ማን ነው ???

❤️ ገብርኤል:- ማለት የእግዚአብሔር አገልጋይ ማለት ነው ከሰባቱ ሊቃነ መላእክት አንዱና ከሊቀ መላእክት ከቅዱስ ሚካኤል ቀጥሎ ስልጣን የተሰጠው ታላቅ መልአክ ነው።

❤️ለእመቤታችን ለቅስተ ቅዱሳን ለድንግል ማርያም የዓለም ድኅነትን የሚሆን ልጅ እንደ ምትወልድ በታላቅ ምስጋና ያበሠረ! የነቢያትንም ትንቢት የፈጸመ ድንቅ መልአክ ነው።

✨🌿 ለካህኑ ዘጋርያስ የመጥምቀ መለኮት የቅዱስ ዮሐንስን መወለድን ያበሰረ  አብሳሪ መልአክ ነው።

🌹✨ሐምሌ  19  ቀን  ህጻኑን ቅዱስ ቂርቆስን እና እናቱ ቅድስት ኢየሉጣን ከእቶን እሳት ያዳነበት ታላቅ ቀን ነው።

🌹🍃ታህሳስ  19  ቀን  ሃያሉ መልአክ ቅዱስ ገብርኤል ሠልስቱ ደቂቅን ከእቶን እሳት ያዳነበት ታላቅ ቀን ነው።

✝️ ዳንኤልን ከአናብስት አፍ ያዳነም ሃያል መልአክ ነው ሰብአ ሠገልን በኮከብ ምልክት የመራ መልአክም ነው በጨለማ በሞት ጥላ ውስጥ ለሚኖሩ ብርሃንን የገለጸ ሃያል መልአክ ነውና ክብር እና ምስጋና ይገባዋል።

✝️ የመልአኩ የቅዱስ ገብርኤል በረከት፣ ፍቅር፣ ምልጃ አይለየን ሀገራችንን ሠላም ያድርግልን።


🌺እንኳን አደረሳችሁ✝️
🙏

✨✨✨✨✨✨
✝️#ድምፀ_ተዋህዶ✝️
✨✨✨✨✨✨


🗓እንኳን ሃያሉ መልአክ ቅዱስ ገብርኤል
ሠልስቱ ደቂቅን ከእቶን እሳት ላዳነበት ታላቅ ቀን በሰላምና በጤና አደረሳችሁ።


✨✨✨✨✨✨
✝️#ድምፀ_ተዋህዶ✝️
✨✨✨✨✨✨


#ድምፅ_መስጠት_ተጀመረ!

#አንቴክስ_ፉድ_ኤይድ_ፕላስ ባዘጋጀው BIWs prize ብፁዕ አቡነ ኤርምያስን የሰላም ዘርፍ እጩ ተሸላሚ አድርጓቸዋል።

ብፁዕ አቡነ ኤርምያስ በሰላም ዘርፍ ከአምስት እጩዎች ውስጥ ተክትተዋል የዘርፉ አሸናፊ ከሆኑ #10ሚሊየን ብር ይሸለማሉ!!!

ብፁዕነታቸውን BIWን በማስቀደም ኮድ08 (BIW08) በማስገባት በSMS 9355 ላይ አሁኑኑ ይምረጡ!!! 

ድምጽ መስጠቱ እስከ ሐሙስ ታህሳስ 17/2017 ዓም ከቀኑ 6፡00 ሰዓት ድረስ ብቻ ይካሄዳል!

በSMS 9355 ላይ BIW08 በማለት ብፁዕነታቸውን አሁኑኑ  ይምረጡ!!!

#10ሚልዮን #አንቴክስ #ፉድኤይድፕላስ #biwsprize #BTM #ብፁዕአቡነኤርምያስ  #ይምረጡ

Vote Abune Ermias now for the BIWs prize!

#AbuneErmias
#10million #BIWS2024 #Prize  #ANTEXETHIOPIA  #ANTEXTEXTILE  #FOODAIDPLUS #BESHATUTOLEMARIAMMULTIMEDIA


🗓  😊ታፍራለች ⭐️
ልጅቷ ባል ትፈልጋለች ሃይማኖቷ በሚፈቅደው ሕግና ስርዓት መሠረት ዘወትር ወደ እግዚአብሔር ትጸልያለች።

ዳሩ ግን አንድም ቀን እግዚአብሔርን በቀጥታ ጥሩ ባል ጥሩ ትዳር እንዲሰጣት ለምናው አታውቅም። ለምን ቢባል ታፍራለች። "እግዚአብሔር እንዴት ስለ ባል ይጠየቃል?"
የሚል ደካማ አመለካከት አላት። እግዚአብሔርንም ጥሩ ባል ስጠኝ ብላ መለመን ያሳፍራታል። እንዳትተወው ደግሞ ባል ያስፈልጋታል። ታድያ አንድ ቀን ሲጨንቃት እንዲህ ብላ ጸለየች፤ "ፈጣሪዬ እባክህን ለእናቴ ጥሩ አማች ስጣት"

በእርግጥ እግዚአብሔርን ስንለምን "የምትለምኑትን አታውቁምን" ተብለው እንደተወቀሱት ሰዎች እንዳንሆን መጠንቀቅ አለብን። ለብዙዋች ግን የሚያሳፍረው ሳያሳፍራቸው፤ የማያሳፍረው ያሳፍራቸዋል

    📣📣📣📣📣
#ድምፀ_ተዋህዶ
     📣📣📣📣📣


🗓 ነገ ማለትም
#ዕለት:- ረቡዕ
#ቀን:- ታኅሣሥ ፪  ፳፻፲፯ ዓ.ም

በቅድስት ቤተክርስቲያናችን
ሐዋርያዉ ታዴዎስ ፣ ሠለስቱ መዕት ፣ ቅድስት አትናስያ ፣ አቡነ እንድርያኖስ ፣ ቅድስተ ዜና ማርቆስ ፣ አባ ጉባ

አክብረን እና አስበን እንውላለን።

📣📣📣
✔️ የጻድቅ መታሰቢያ ለበረከት ነው። ምሳ ፲፤፯

✔️  መታሰቢያ ለዘለዓለም ይኖራል መዝ.፻፳፮፥፮


✔️ "ቅዱሳን በዓለም ላይ እንዲፈርዱ አታውቁምን? ፩ኛ ቆሮ ፮:፪

የመላዕክት ፣ የቅዱሳን ፣ የሰማዕታት ተራዳይነት እና በረከት ከሁላችንም ጋር ይሁን።

✨#ድምፀ_ተዋህዶ✨


✨አንድ ትእቢተኛና ልብ አውልቅ ተማሪ
መምህሩን ሊሳለቅባቸው አሰበና "የኔታ ገሀነም በየት በኩል ነው ?"

አላቸው።የኔታም የውስጡን አውቀው "ልጄ እመንገዱህ ላይ ነህ ......"አሉት ይባላል

✨#ድምፀ_ተዋህዶ✨


🗓ድጓ ከምን ያድናል❓🧠
አንድ መናፍቅ  ታላቁን የድጓውን መምህር የናቀ መስሎት "የኔታ ድጓ ከምን ያድናል "ሲል ጠየቃቸው እሳቸውም ቀበል አድርገው "እንዲህ ከማለት ያድናል" አሉት ይባላል።
↗️#ድምፀ_ተዋህዶ ↗️

Показано 20 последних публикаций.