ብፁዕ አቡነ ዳንኤል ዐረፉ
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በ5ኛው ኢትዮጵያዊው ፓትርያርክ በብፁዕ አቡነ ጳውሎስ ነሐሴ 22 ቀን 1997 ዓ.ም ከተሾሙ 17 ጳጳሳት አንዱ የሆኑት ብፁዕ አቡነ ዳንኤል ዐረፉ።
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የድሬዳዋ እና የጅቡቲ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳሳት የነበሩት ብፁዕ አቡነ ዳንኤል ትናንት ከምሽቱ አምስት ሰዓት አካባቢ በመንበረ ፓትርያርክ በሚገኘው ማረፊያ ክፍላቸው እንዳረፉ ለማወቅ ተችሏል።
ብፁዕነታቸው በሰሜን አሜሪካ ለረጅም ዓመታት አገልግሎት በመስጠት እንደሚታወቁ የገለጠው ዐደባባይ ሚዲያ የልብ ሕመም እንዳለባቸው ሐኪም ሲነግራቸው በዚህ ዕድሜዬ ቀዶ ጥገና አይደረግልኝም ወደ አገሬ ሔጄ ለአገሬ አፈር ልብቃ ማለታቸውን ዘግቧል።
የብፁዕነታቸው በረከት ይደርብን።
ነፍሳቸውን በቅዱሳን እቅፍ ያሳርፍልን።
✨✨✨✨✨✨
✝️#
ድምፀ_ተዋህዶ✝️
✨✨✨✨✨✨