የኢቢኤስ አዲስ ነገር ዲጂታል ሚዲያ የመጋቢት 4 / 2017 ዓ.ም የእኩለ ቀን የሀገር ውስጥ ዋና ዋና ዜናዎች፦🎯ትግራይ ክልል ወደ አላስፈላጊ ብጥብጥና ጦርነት እንዳይገባ ሁሉም የበኩሉን ሊወጣ እንደሚገባ የትግራይ ክልል ጊዚያዊ አስተዳደር አቶ ጌታቸው ረዳ ገለጹ፡፡
🎯የሕዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት ዛሬ ረፋዱን 19ኛ መደበኛ ስብሰባው የኢትዮጵያ የተመሰከረላቸው የሒሳብ ባለሙያዎች ኢንስቲትዩት ማቋቋሚያ ረቂቅ አዋጅን መርምሮ አጽድቋል።
🎯ኢትዮ ጅቡቲ ምድር ባቡር የቀጥታ ኤሌክትሪክ መስመር ተጠቃሚ መሆኑን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት አስታወቀ፡፡
🎯በደቡብ ሱዳን እየተባባሰ በመጣው ግጭት ሳቢያ ወደ ጋምቤላ ክልል የሚሸሹ ስደተኞች ቁጥር መጨመሩ በክልሉ ላይ ጫና አሳርፏል ተብሏል።
🎯በአራት ኪሎ አደባባይ የእግረኞች መተላለፊያ ዋሻ በአግባቡ ያልተጠቀሙ 345 እግረኞች የገንዘብ ቅጣት መቀጣታቸውን የትራፊክ ቁጥጥር ባለሥልጣን ገልጿል።
🎯የአዲስ አበባ ነዋሪዎች በነፃ የስልክ መስመር 8882 በመደወል የፀጥታ ችግር መንስዔዎችን መጠቆም እንደሚችሉ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሰላምና ፀጥታ ቢሮ አስታወቀ።
ዜና አዲስ ነገር ነው! አዲስ ነገርም ዜና ነው!"
የኢቢኤስ አዲስ ነገር ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ#EBS
#EBSTVNEWS
#EBSTVSPORT
#_7696_WN
https://t.me/ebstvnews