Ethiopian Electric Utility


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: Карьера


EEU Official Telegram Channel
Web: www.eeu.gov.et

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
Карьера
Статистика
Фильтр публикаций


Видео недоступно для предпросмотра
Смотреть в Telegram
የስድስቱ ከተሞች ፕሮጀክት አካል የሆነው የጎንደር ከተማ መልሶ ግንባታ ፕሮጀክት የአፈጻፀም ደረጃ !!


የቦሌ ለሚ አራብሳ የጋራ መኖሪያ ቤቶች የሃይል አቅርቦት ችግር ተፈታ

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የቦሌ ለሚ አራብሳ የጋራ መኖሪያ ቤቶች እና በአካባቢው ይስተዋል የነበረው የኃይል መቆራረጥ ችግር መቅረፍ መቻሉን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የምስራቅ አዲስ አበባ ሪጅን ዳይሬክተር አቶ ብርሃኑ ዋቅጅራ ገልፀዋል፡፡

ዳይሬክተሩ አክለውም በአካባቢው ይስተዋል የነበረውን የሃይል መቆራረጥ ችግር መቅረፍ የተቻለው የኤሌክትሪክ መሰረተ-ልማት ማስፋፊያ ግንባታ በመደረጉ ነው ብለዋል፡፡

ለአካባው 5 ነጥብ 4 ኪሎ ሜትር ባለ ጥንድ የኤሌክትሪክ መስመር ዝርጋታ እና 96 የኮንክሪት ምሰሶ ተከላ ስራ መከናወኑን አቶ ብርሃኑ አስታውቀዋል፡፡

የተዘረጉት የኤሌክትሪክ መስመር ሽፍን በመሆናቸው በዝናብ እና በንፋስ ወቅት በሽቦዎች መቀራረብ እና መነካካት የሚፈጠርን የኃይል መቆራረጥ ችግር መቆራረጡን መቀነስ ተችሏል፡፡

የአሌክትሪክ መስመር ማስፋፊያ ሥራውን ለማጠናቀቅ አንድ ወር ጊዜ የፈጀ ሲሆን የኤሌክትሪክ መሰረተ-ልማቱን ለመዘርጋት ከ17 ሚለየን ብር በላይ ወጪ መደረጉን ዳይሬክተሩ ገልፀዋል፡፡

ቀድሞ የነበረው የኃይል መቆራረጥ ችግር ተማሪ ለመሸኘት፣ ለማንበብ፣ ምግብ ለማብሰል እንዳስቸገራቸው በአካባቢው የሚኖሩ የህብረተሰብ ክፍሎች ተናግረዋል፡፡

ነዋሪዎቹ ከበዓል ወዲህ የተቋሙ የስራ ሃላፊዎች ችግሩን ተረድተው በሰጡት አቅጣጫ መሰረት በአከሳባቢው ይስተዋል የነበረው የኃይል መቆራጥ ችግር መቀረፉን ተናግረው በዚህ መልኩ በወጥነት ሊቀርብላቸው እንደሚገባ ጠቁመዋል፡፡

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት


በአዲስ አበባ፣ሐረር እና ጎንደር ከተሞች የቅድመ ጥገና ሥራ ለማከናወን ሲባል በዕቅድ የኃይል አቅርቦት የሚቋረጥባቸውን ቦታዎች ለማየት ድረ-ገፃችንን ይጎብኙ፡-http://www.eeu.gov.et/power-interruption/detail/1137?lang=am


ተቋማችንን የሚመለከቱ ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት ከታች ያስቀመጥነውን የቲክቶክ አካውንት ማስፈንጠሪያ በመጫን እንድትቀላቀሉ በአክብሮት እንጠይቃለን።
👉https://www.tiktok.com/@ethiopian.electri?_t=8rnUn6BN6uO&_r=1
#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት


Видео недоступно для предпросмотра
Смотреть в Telegram
የአገልግሎት አሰጣጥና የአዲስ ሃይል ጥያቄ ምላሽ በወልድያ ሪጅን!!


የኃይል ስርቆት በፈፀሙ ግለሰቦች ላይ እርምጃ ተወሰደ

በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ደቡብ አዲስ አበባ ሪጅን ቆጣሪዎችን በመነካካት የኃይል ስርቆት በፈፀሙ የወፍጮ ቤት፣ የዳቦ እና የእንጀራ መጋገሪያ ቤት ባለቤቶች ላይ እርምጃ ወስዷል፡፡

በዚህ በጀት አመት ብቻ 18 ዘመናዊ ቆጣሪዎች ላይ የኃይል ስርቆት የተፈፀመ ሲሆን ሪጅኑ በስርቆት ያጣውን ከ4 ሚለየን ብር በላይ የኃይል ፍጆታ ሂሳብ ገንዘብ ማስከፈሉን በሪጅኑ የኢነርጂ ማኔጅመንት ኃላፊ አቶ ለሚ አዱኛ ተናግረዋል፡፡

አቶ ለሚ አክለውም 11 ሥርቆት የፈፀሙ ድርጅቶች ላይ ከ5 ሺህ እስከ 10 ሺህ ብር ቅጣት እንዲቀጡ ማድረጉንና በስርቆት ወቅት ለተበላሹ ቆጣሪዎች 18 ሺህ ብር እንዲከፍሉ መደረጉን ተናግረዋል፡፡

የኃይል ስርቆት መረጃው የተገኘው ተቋሙ በሚጠቀመው መተግበሪያ አማካኝነት ሲሆን በዚህ ዓመት ብቻ በኃይል ሥርቆት ላይ በተሳተፉ ስምንት ደንበኞች ላይ ክስ ተመስርቶ ክትትል እየተደረገባቸው እንደሆነና ሦስቱ በሂደት ላይ መሆናቸውን ሃላፊው ተናግረዋል፡፡

ተቋሙ የንባብ ጥራት ለመጨመር እና የኃይል ስርቆትን ለመከላከል ዘመናዊ ቆጣሪዎችን እየተገበረ ሲሆን የፍጆታ የንባብ ጥራት ለመጨመር እና የኃይል ስርቆትን ለመከላከል የዘመናዊ ቆጣሪዎችን እየተገበረ የሚገኝ መሆኑ የሚታወስ ነው፡፡

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት


በአዲስ አበባ ከተማ የቅድመ ጥገና ሥራ ለማከናወን ሲባል በዕቅድ የኃይል አቅርቦት የሚቋረጥባቸውን ቦታዎች ለማየት ድረ-ገፃችንን ይጎብኙ፡- http://www.eeu.gov.et/power-interruption/detail/1135?lang=am


Видео недоступно для предпросмотра
Смотреть в Telegram
በቦሌ ለሚ የጋራ መኖሪያ ቤቶች አካባቢ ይስተዋል የነበረውን የሃይል መቆራረጥ ችግር ለመቅረፍ የተከናወነ የማስፋፊያ ስራና በአካባቢው የሚገኙ ደንበኞች አስተያየት !


የተቋሙ የግማሽ ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም ግምገማ ተጀመረ

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የ2017 በጀት ዓመት የመጀመሪያው ግማሽ ዓመት የዕቅድ አፈፃፀም ግምገማ መካሄድ ጀመረ፡፡

ለሶስት ቀናት በሚቆየው በዚህ የዕቅድ አፈፃፀም ግምገማ ተቋሙ በግማሽ አመቱ ያከናወናቸው ዋና ዋና ተግባራት፣ የታዩ ጠንካራ ጎኖች፣ ያጋጠሙ ችግሮች እንዲሁም የተቋሙ የቀጣይ የትኩረት መስኮች ላይ ውይይት የሚደረግ ይሆናል፡፡

በተጨማሪም የበጀት ዓመቱ የተቋሙ የሶስት ዓመት ስትራቴጅክ ዕቅድ ማጠናቀቂያ ዓመት በመሆኑ በዕቅድ በአፈፃፀሙ ላይ ውይይት የሚደረግ ይሆናል፡፡

ዛሬ የተጀመረው የዕቅድ አፈፃፀም መድረክ ተቋሙ አዲስ የአሠራር ስርዓት ማሻሻያ ተግባራዊ ካደረገ በኋላ እየተካሄደ ያለ የመጀመሪያ መድረክ ነው፡፡

በዚህም ሁሉም ሥራ አስፈጻሚዎች የመጀመሪያውን መንፈቅ ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርታቸውን ካቀረቡ በኋላ ውይይት ተደርጎ የቀጣይ አቅጣጫም እንደሚቀመጥ ይጠበቃል፡፡

በግምገማ መድረኩ የተቋሙን ዋና ሥራ አስፈፃሚ ክቡር ኢንጂነር ሽፈራው ተሊላን ጨምሮ ሥራ አስፈፃሚዎች፣ የሪጅን አስተባባሪዎችና ዳይሬክተሮች እንዲሁም የመሠረታዊ ሠራተኞች ማህበር ሰብሳቢን ጨምሮ ሌሎች የስራ አመራሮችም ተሳታፊዎች ናቸው።

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት


በአዲስ አበባ እና ሐረር ከተሞች የቅድመ ጥገና ሥራ ለማከናወን ሲባል በዕቅድ የኃይል አቅርቦት የሚቋረጥባቸውን ቦታዎች ለማየት ድረ-ገፃችንን ይጎብኙ፡- http://www.eeu.gov.et/power-interruption/detail/1128?lang=am


ለጥገና ሥራ ሲባል በእቅድ የሚቋረጥ የኃይል አቅርቦት።

እሑድ ጥር 4 ቀን 2017 ዓ.ም በቃሊቲ ጂአይኤስ ጣቢያ ትራንስፎርመሮች ላይ የጥገና ሥራ ይከናወናል።

ስለሆነም ከጠዋቱ 1:00 እስከ 8:00 ሰዓት ድረስ በሀይሌ ጋርመንት፣ በአፍሪካ ህብረት የምርምር ማእከል ፣በሰፈራ በቡልቡላ እና በአቦ ኮንዶሚኒየሞች፣ በኦሮሚያ ውሃ ሥራዎች፣ በቃሊቲ ኢንዱስትሪ መንደር፣ በወርቁ ሰፈር ፣በገላን ጎሮ፣ በቃሊቲ እና አካባቢው ኤሌክትሪክ ተቋርጦ የሚቆይ ስለሆነ ክቡራን ደንበኞቻችን ይህንኑ በመገንዘብ ከወዲሁ ተገቢውን ቅድመ ዝግጅት እንድታደርጉ በአክብሮት እናሳስባለን ።

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

7.5k 0 17 22 26

ወርሃዊ የኤሌክትሪክ ፍጆታ ሂሳብ በወቅቱ አለመፈፀም ለተጠራቀመ የፍጆታ ሂሳብና ቅጣት የሚዳርግ መሆኑን ያውቃሉ? እንግዲያውስ እንንገርዎ!! ወርሃዊ የኤሌክትሪክ ፍጆታ ሂሳብ በወቅቱ አለመፈፀም ለተጠራቀመ የፍጆታ ሂሳብና ቅጣት ይዳርጋል፡፡ ስለሆነም ውድ የድህረ ክፍያ አገልግሎት ተጠቃሚ ደንበኞቻችን ወርሃዊ የኤሌክትሪክ ፍጆታ ሂሳባችሁን በተቀመጠው የጊዜ ሰሌዳ መሰረት በወቅቱ እንድትፈፅሙ እናሳስባለን፡፡

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት


የቢሾፍቱ ቁጥር 2 አገልግሎት መስጫ ማዕከል 901 አዳዲስ ደንበኞችን ተጠቃሚ አደረገ

በፊንፊኔ ዙሪያ የቢሾፍቱ ቁጥር 2 አገልግሎት ማእከል በያዝነው 2017 በጀት ዓመት 9 መቶ አንድ የሚሆኑ አዳዲስ ደንበኞችን የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ ማድረግ ችሏል፡፡

ለአዳዲስ ደንበኞች ቅድሚያ እየሰጠ በመሥራት ላይ የሚገኘው ማዕከሉ በበጀት ዓመቱ በፕሮጀክት እና በራስ ኃይል የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማቶች ማስፋፊያ ሥራዎችን ያከናወነ ሲሆን 2.88 ኪሎ ሜትር ዝቅተኛ መስመር፣ 2.5 ኪሎ ሜትር የመካከለኛ መስመር እና 8 አዳዲስ ትራንስፎርመሮችን መትከል ችሏል፡፡

ባሳለፍነው ሩብ ዓመት በማዕከሉ 212 የሚሆኑ ስማርት ቆጣሪዎች የተገጠሙ ሲሆን ከነዚህ መካከልም ትልልቅ ኢንዱስትሪዎች ዋነኞቹ ሲሆኑ ለአብነት ያህል የብረት ማቅለጫ፣ የአበባ ልማት፤ የምግብ እና የፕላስቲክ ፋብሪካ፤አግሮ ኢንዱስትሪና መሰል ትላልቅ ተቋማትን ያካተተ ነው፡፡

ስማርት ቆጣሪ ከተቀየረ በኋላ የማዕከሉ ገቢ በእጥፍ ያደገ ሲሆን በየዕለቱ ንባብ ስለሚያደርግ ተቋሙ ማግኘት የሚገባውን ገቢ በአግባቡ ማግኘት ችሏል፤ በዚህም ማዕከሉ በአራት ወራት ውስጥ ከታቀደው 96.91 በመቶ አፈጻጸም ከእጥፍ በላይ በማሳካት 278.02 በመቶ አስመዝግቧል ችሏል፡፡

ማዕከሉ አጠቃላይ 25 ሺ 823 ደንበኞች ያሉት ሲሆን 15 ሺ 26 ያህሉ የድህረ ክፍያ ተጠቃሚዎች ሲሆኑ ቀሪዎቹ 10 ሺ 850 የቅድመ ክፍያ ደንበኞች ናቸው፡፡

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት


በአዲስ አበባ ከተማ የመስመር ዝርጋታ ሥራ ለማከናወን ሲባል በዕቅድ የኃይል አቅርቦት የሚቋረጥባቸውን ቦታዎች ለማየት ድረ-ገፃችንን ይጎብኙ፡-
http://www.eeu.gov.et/power-interruption/detail/1124?lang=am


ከፍለው ትራንስፎርመር ሲጠብቁ የነበሩ ደንበኞች የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ ሆኑ

የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ ለመሆን ከፍለው ትራንስፎርመር ሲጠብቁ ሲጠባበቁ የነበሩ የኢንዲስትሪ፣ ኮሜርሻል እና የአጠቃላይ የኤሌክትሪክ ኃይል ፈላጊ ደንበኞች የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ ማድረግ ተችሏል፡፡

ትራንስፎርመር የቀረበላቸው ደንበኞች በአዲስ አበባ ባሉ አራቱም ሪጅኖች እና ለሸገር ሪጅን መሰመር እና ሌሎች መሰረተ-ልማት ተሟልቶላቸው ወረፋ ሲጠባበቁ የነበሩ ናቸው፡፡

በአጠቃላይ ከቀረቡት 210 ትራንስፎርመሮች ውስጥ 90 በምስራቅ አዲስ አበባ ሪጅን፣ 43 ሸገር ከተማ፣ 34 ደቡብ አዲስ አበባ፣ 23 ምዕራብ አዲስ አበባ ሪጅን፣ 20 ሰሜን አዲስ አበባ ለሚገኙ ደንበኞች የተሰራጩ ትራንስፎርመሮች ናቸው፡፡

የትራንስፎርመሮቹ መገዛት ከፍለው ሲጠባበቁ የነበሩ ደንበኞች ቅሬታ ሙሉ በሙሉ እንደሚፈታ እና የተቋሙን የኃይል ፍጆታ ገቢ የሚጨምር ነው፡፡

ትራንስፎርመሮቹን ለመግዛት 300 ሚሊየን ብር አጠቃላይ ወጪ የተደረገባቸው ሲሆን የትራንስፎርመር ተከላው በአዲስ አበባ ከተማ በአስር ቀን ውስጥ በሸገር ከተማ ደግሞ እስከ ጥር ወር መጨረሻ ይጠናቀቃል ተብሎ ይጠበቃል፡፡

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት


ተቋርጦ የነበረው የኃይል አቅርቦት ወደ አገልግሎት ተመልሷል

ከግንቢ- ነጆ እና አሶሳ በተዘረጋው 132 ኪ.ቮ ከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ታወር በመውደቁ ምክንያት ከግንቢ፣ ነጆ፣ መንዲ፣ ግዳሚ እና አሶሳ ሃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች የኤሌክትሪክ ሃይል ሲያገኙ በነበሩ አካባቢዎች ተቋርጦ የነበረው የኃይል አቅርቦት ወደ አገልግሎቱ ተመልሷል፡፡

የጥገና ስራው ተጠናቆ አገልግሎቱ እስኪመለስ ድረስ በትዕግስት ለጠበቃችሁን ክቡራን ደንበኞቻችን ከልብ እናመሰግናለን ።

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት


ሁለቱ ተቋማት አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት ለደንበኞች ለማቅረብ ውይይት አደረጉ

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት እና የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከፍተኛ የሥራ ሃላፊዎች ዛሬ ባደረጉት ውይይት አስተማማኝ የሆነ የኃይል አቅርቦት ለደንበኞች ለማድረስ እንደሚሠሩ ገልጿዋል።

በተደረገዉ የጋራ ውይይት የተለያዩ ሃሳቦች የተነሱ ሲሆን በተለይም ከኃይል አቅርቦት ጋር እና ከሃይል መቆራረጥ ጋር በተያያዘ እንዲሁም ለቅድመ መከላከል ጥገናም ሆነ ለማሻሻያና መልሶ ግንባታ ስራ የሚቋረጥ የሃይል መቋረጥ ላይ ሁለቱ ተቋማት በቅንጅት ሊሰሩ እንደሚገባ መግባባት ላይ ደርሰዋል፡፡

በውይይቱ በየጊዜው እየጨመረ የመጣውን የሃይል ፍላጎት ለማሟላት እና ጥራት ያለው የኤሌክትሪክ አገልግሎት ለደንበኞች ለመስጠት በየደረጃው ያሉ ሃላፊዎች በቅንጅት መሥራትና ከደንበኞች የሚነሱ ቅሬታዎችን መፍታት እንደሚገባ ተጠቅሷል።

ተቋማቱ እየሠጡት ያለው አገልግሎ ለሃገር ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ዕድገት መሠረት በመሆኑ ያልተቆራረጠና ጥራ ያለው የኃይል አቅርቦት ለመስጠት መደረግ ስለሚገባቸው ተግባራት ዙሪያ አቅጣጫ አስቀምጠዋል።

መሠል የምክክር መድረክ በሁለቱ ተቋማት መካከል ያለውን ቅንጅታዊ አሰራር ለማሻሻል ከፍተኛ ጠቀሜታ እንዳለው ተመላክቷል።

ውይይቱ በሁለቱም ተቋማት ዋና ስራ አስፈጻሚዎችን ጨምሮ ሌሎች ከፍተኛ የስራ አመራር አባላት መካከል የተካደ ነበር።

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት


በአዲስ አበባ እና ሐረር ከተሞች የቅድመ ጥገና ሥራ ለማከናወን ሲባል በዕቅድ የኃይል አቅርቦት የሚቋረጥባቸውን ቦታዎች ለማየት ድረ-ገፃችንን ይጎብኙ፡-

http://www.eeu.gov.et/power-interruption?lang=am


ለጥገና ሥራ የሚቋረጥ የኤሌክትሪክ አቅርቦት

ከደሴ ወልዲያ 66 ኪሎ ቮልት እና ከኮምቦልቻ አለማጣ በተዘረጋ 230 ኪሎ ቮልት የኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ መስመር ላይ የጥገና ስራ ስለሚከናወን ከጥር 03 ቀን እስከ ጥር 06 ቀን 2017 ዓ.ም ድረስ ወልዲያ ከተማ ውሃ በከፊል፣ ሳንቃና አካባቢው የሀይል አቅርቦት ተቋርጦ ይቆያል።

ስለሆነም በተጠቀሱት አካባቢዎች የምትገኙ ክቡራን ደንበኞቻችን ይህንን ተገንዝባችሁ አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት እንድታደርጉ በአክብሮት እናሳስባለን፡፡
#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት


ወርሃዊ የኤሌክትሪክ ፍጆታ ሂሳብ በቀላሉ፣ ባሉበት ሆነው ከዚህ በፊት በሚከፍሉበት የጊዜ ሰሌዳ መሰረት በቴሌ ብር፣ በሲቢኢ ብር፣ በሞባይል ባንኪንግ፣ በአዋሽ ብር ፕሮ ወይም በኤም ፔሳ በኩል ይፈፅሙ፡፡ፍጆታዎ በስልክዎ! ዘመናዊ የክፍያ አማራጭ በመምረጥ ኑሮዎን ያቅሉ!

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

Показано 20 последних публикаций.