ለ231 ድጋፍ ለሚሹ የህብረተሰብ ክፍሎች የማዕድ ማጋራት ፕሮግራም ተደረገ
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት 231 ለሚሆኑ ድጋፍ ለሚሹ የህብረተሰብ ክፍሎች 1 ሚሊዮን ብር የሚያወጣ የዓይነት ድጋፍ አድርጓል፡፡
የማዕድ ማጋራት ፕሮግራሙ የተካሄደው መጪውን የትንሳዔ በዓል ምክንያት በማድረግ ሲሆን 231 ለሚሆኑ ከአዲስ አበባ ከተማ ለተውጣጡ ድጋፍ ለሚሹ አባዎራ እና እማዎራዎች ለእያንዳንዳቸው 5 ሊትር ዘይት እና 25 ኪ.ግ ዱቄት በመለገስ የማዕድ ማጋራት አድርጓል፡፡
በማዕድ ማጋራት መረሃ ግብሩ ላይ ንግግር ያደረጉት የተቋሙ የሰው ሃብት ስራ አስፈፃሚ ወ/ሮ ዘሪቱ ፍቅሬ ተቋሙ የኤሌክትሪክ አገልግሎት ከማዳረስ ባሻገር በተለያዩ የበጎ አድራጎት ስራዎች ላይ እየተሳተፈ እንደሚገኝ ገልፀው፤ በቀጣይም ይህንኑ የሰብዓዊነት ተግባር ተቋሙ እንደሚያስቀጥል ተናግረዋል፡፡
ተቋሙ ባለፈው ጊዜም የኢድ በዓልን ምክንያት በማድረግ ለሙስሊም ወገኖቻችን ተመሳሳይ ድጋፍ ማድረጉ ይታወሳል፡፡
ወቅታዊና ትክክለኛ መረጃችን ለማግኘት ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገፆቻችንን ይቀላቀሉ!
[Facebook]
http://www.facebook.com/EEUOfficial[Telegram]
https://t.me/eeuethiopia[Website]
http://www.eeu.gov.et[YouTube]
https://www.youtube.com/@EthiopianElectricUtility[Tiwtter]
https://x.com/EEUEthiopia [TikTok]
https://www.tiktok.com/@ethiopian.electri [Whatsapp]
https://web.whatsapp.com/[EEU Customers Digital Support]
https://t.me/EEUCustomersupport