ESAT (ኢሳት🇪🇹)®


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: Новости и СМИ


ለማንኛውም አስተያየት እና ጥቆማ 👉 @Esat_tv_comment_bot
🇪🇹ኢሳት የኢትዮጵያ አይን እና ጆሮ🇪🇹

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
Новости и СМИ
Статистика
Фильтр публикаций


የሂዝቦላ መሪ ሀሰን ነስረላህ ተገደለ‼️

የሂዝቦላው መሪ ሀሰን ነስረላህ በትላንትናው ዕለት በቤሩት እስራኤል በከፈተችው የአየር ጥቃት ህይወቱ ማለፉን የእስራኤል ጦር አስታውቋል። በጉዳዩ ላይ ሂዝቦላ ዝምታን መርጧል።

ከሰኞ ጀምሮ እስራኤል በሊባኖስ እየወሰደችው ባለው እርምጃ ከ800 በላይ ሰዎች ተገድለዋል።

@Esat_tv1
@Esat_tv1


መኪና ለመግዛት ወይም ለመሸጥ ከፈለጉ ያለምንም ክፍያ
ይህንን የቴሌግራም መተግበሪያ ይቀላቀላሉ።

https://t.me/Poppycarmarket

☎️ 0911407105   👈 ይደውሉልን


ለተሽከርካሪ ቦሎ፣ ስም ዝውውር እና ለጠፋ መንጃ ፈቃድ እስከ 150 ፐርሰንት የክፍያ ጭማሪ ተደረገ‼️

ለተሽከርካሪ ቦሎ፣ ስም ዝውውር እና የጠፋ መንጃ ፈቃድ ለማውጣት እስከ 150 ፐርሰንት የሚደርስ የክፍያ ጭማሪ መደረጉ ተሰምቷል።

የአሽከርካሪና ተሽከርካሪ ፈቃድና ቁጥጥር ባለሥልጣን ያወጣው ይህ አዲስ የታሪፍ ጭማሪ በተቋሙ ታሪክ ከፍተኛው ነው።

የባለሥልጣን መሥሪያ ቤቱ በአራት ቀን በፊት በቂርቆስ ክፍል ከተማ እንደ ሞዴል ተደርጎ የታሪፍ ክፍያውን ማስከፈል ያስጀመረ ሲሆን ከሰኞ ጀምሮ በሁሉም ክፍለ ከተሞች ተግባራዊ ለማድረግ እቅድ ተይዟል።

በዚህም መሰረት ለቦሎ የነበረ ክፍያ ከ650 ብር ወደ 1,850 ብር ከፍ እንዲል የተደረገ ሲሆን፣ ለስም ዝውውር ከ5,600 ብር የነበረው ወደ 10,000 ብር፣ ለለተሽከርካሪ የአገልግሎት ለውጥ ለማድረግ 17ሺህ 100 ብር የነበረው ወደ 30 ሺህ ፣ የጠፋ መንጃ ፍቃድ ለማውጣት 750 ብር የነበረው ወደ 5 ሺህ ብር ከፍ እንዲል መደረጉን ተሰምቷል።

@Esat_tv1
@Esat_tv1

37k 0 139 411

አረጋዊ ካህን ዐራት ቤተሰባቸውን ጨምሮ ማንነታቸው ባልታወቀ ኃይሎች በአሰቃቂ ሁኔታ ተገደሉ‼️

መልአከ/መ/ ቀሲስ ወልደ ኢየሱስ አያሌው የተባሉ በምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት በሉሜ ( ሞጆ ) ወረዳ ቤተ ክህነት በቢቃ ደ/መ/ቅ/ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን ለ 41 ዓመታት ያህል ከዲቁና እስከ ደብር አስተዳዳሪነት ድረስ በትሕትና ሲያገለግሉ መቆየታቸው ተገልጿል፡፡

ካህኑ ከባለቤታቸውና ከሦስት ልጆቻቸው ጋር ባሰቃቂ ሁኔታ ማንነታቸው ባልታወቁ ኃይሎች በግፍና በአሰቃቂ ሁኔታ መገደላቸውን የሉሜ ወረዳ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት የገለጸ ሲሆን ልጃቸው ዲ/ን መልአክ ወልደ ኢየሱስም የቤተ ክርስቲያን አገልጋይ እንደነበር ተጠቅሷል፡፡

ጸሎተ ፍትሐት ሥርዓቱም የሞጆ ሉሜ ወረዳ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ መልአከ ሰላም ቆሞስ አባ ሰይፈ ገብርኤል ገረመው፣ የአድባራት አስተዳዳሪዎች ፣ አበው ካህናት ሊቃውንት ፣ በርካታ ምእመናን በተገኙበት በሞጆ ደ/ብ/ቅድስት ሥላሴ ቤተ ክርስቲያን እየተከናወነ ይገኛል።

ዘገባው የምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት ሚዲያ ነው

@Esat_tv1
@Esat_tv1


Platinum Mass Gainer

ጤናማ የሆነ ክብደት መጨመር ይፈልጋሉ ከፍተኛ የሆነ የፕሮቲን እና የካርቦሃይድሬት ዉቅር ሲሆን  በአንድ  ማንኪያ:-

👉1,250 ካሎሪ
👉 60  ግራም ፕሮቲን
👉 6 G ግራም ግሉታሚን
👉 9 G ግራም ክሬቲን
👉 2 G ግራም ቢሲኤኤ
👉ቪታሚኖችን

👩🏽‍⚕️ የያዘው ይህ የከፍተኛ የፕሮቲን እና ካርቦሃይድሬት ድብልቅ የጡንቻን ብዛት በፍጥነት እና በብቃት ለማጎልበት የሚረዳዎትን በቂ የፕሮቲን ፍጆታ በማረጋገጥ የሰውነትዎን ጂኤች እና ቴስቶስትሮን ደረጃን ለማሳደግ የሚያስፈልግዎት ውህድ ነው።

አድራሻችን;- ሀዋሳ  አቶቴ ቱርፋት ወርቁ ቡቼ ሞል ፊትለፊት አዲስ የገበያ ማእከል ህንፃ ላይ 2ኛ ፎቅ📍

☎️ +251926482248 ☎️

☎️ 9369 ላይ ይደውሉ   ☎️


በነቀምቴ ከተማ በተደረገ ዘመቻ በርካታ ህገ ወጥ የጦር መሳሪያ በቁጥጥር ስር ዋለ‼️

ዘመቻው የኮሩ ሰራዊት ከከተማው ፓሊስ እና ሚሊሺያ ጋር በመቀናጀት የተደረገ ሲሆን ለጠላት መረጃ የሚያቀብሉ የአባ ቶርቤ ቡድን አባላት ጨምሮ 117 የተለያዩ ዓይነት ሽጉጦች ፣ 646 የሽጉጥ ጥይት፣ 30 ክላሽ፣ 34 ኋላቀር መሳሪያ ፣ 563 የክላሽ ጥይት እና 50 የእጅ ቦምብ በቁጥጥር ስር ማዋል መቻሉን ተናግረዋል።

የነቀምቴ ከተማ ፓሊስ አዛዥ ኮሚሽነር ሻሎም በዳሳ በበኩላቸው በተደረገው ኦፕሬሽን እና በተገኘው ውጤት
ለኮሩ የሰራዊት አባላትና ለፀጥታ ሃይሎች ከፍተኛ ምስጋና አቅርበዋል።

የተገኙ ድሎችን በሚመለከት በነቀምቴ ከተማ ውይይት የተደረገ ሲሆን የተገኘውን ውጤት አጠናክሮ በማስቀጠል የዞኑን ሰላም ማስጠበቅ እንደሚገባ መገለፁን ከሀገር መከላከያ ሰራዊት ማህበራዊ የትስስር ገፅ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።

@Esat_tv1
@Esat_tv1


መንገዶቹ ተዘግተዋል‼️

በአዲስ አበባ መስቀል አደባባይ ከሚከበረው የመስቀል ደመራ በዓል ጋር በተያያዘ ከላይ በምስሉ የተዘረዘሩት መንገዶች ከዚህ ሰዓት አንስቶ ተዘግተዋል።

ከቤት ለስራም ይሁን ለሌላ ጉዳይ የወጣችሁ አማራጭ መንገዶችን ተጠቀሙ።

@Esat_tv1
@Esat_tv1


የመስቀል ደመራ በዓልን ምክንያት በማድረግ ለትራፊክ ዝግ የሚሆኑ መንገዶች‼️

• ከቅዱስ ኡራኤል አደባባይ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ቅዱስ ኡራኤል አደባባይ ላይ

• ከቦሌ አቅጣጫ ወደ መስቀል አደባባይ ለሚመጡ ተሽከርካሪዎች ኦሎምፒያ አደባባይ ላይና ታች እንዲሁም ግራ

• ከመስቀል ፍላወር ወደ ኦሎምፒያ የሚወስደው መንገድ ጋዜቦ አደባባይ ላይ

• ከአጎና ሲኒማ ወደ መስቀል አደባባይ ለከባድ ተሽከርካሪ አጎና ሲኒማ አጠገብ እንዲሁም ለቀላል ተሽከርካሪ ጥላሁን አደባባይ (አራተኛ ክፍለ ጦር ላይ)

• ከለገሀር መብራት ወደ መስቀል አደባባይ ለገሀር መብራት ላይ

• ከቴሌ ማቋረጫ ወደ ስታድዮም ለሚጓዙ ቴሌ ማቋረጫ

• ከራስ ሆቴል ወደ ስታድዮም ለሚመጡ ተሽከርካሪዎች ራስ ሆቴል ላይ

• ከሃራምቤ መብራት ወይም ከአምባሳደር ሲኒማ ወደ መስቀል አደባባይ ሃራምቤ መብራት ላይ

• ከብሔራዊ ቤተ መንግስት ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ብሔራዊ ቤተ መንግስት አጠገብ

• ከዛንቺስ ሼል ወደ ባምቢስ የሚወስደው መንገድ ከዛንቺስ ሼል አጠገብ እንዲሁም

• ከጁፒተር ሆቴል ወደ ECA የሚወሰደው መንገድ ባምቢስ ሳልኮት ህንፃ አጠገብ

እነዚህ መንገዶች ከመስከረም 16 ቀን 2017 ዓ/ም ከረፋዱ 5፡00 ሰዓት ጀምሮ እስከ መርሀ ግብሩ ፍፃሜ ድረስ መንገድ የሚዘጋ ሲሆን÷ በተገለፁት መስመሮች ላይ ተሽከርካሪዎችን ለአጭርም ይሁን ለረዥም ጊዜ ማቆም የተከለከለ መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል።

@Esat_tv1
@Esat_tv1


የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ ፥ በዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል የሚመራውን የህወሓት ቡድን አስጠነቀቁ‼️

ፕሬዜዳንቱ በማስጠንቀቂያቸው " ቡድን " ሲሉ የጠሩት ሃይል የወረዳና የከተማ የህዝብ ምክር ቤቶች ለመረበሽ እየሄደበት ያለው ርቀትና በማድረግ ላይ ያለውን እንቅስቃሴ ማቆም አለበት ብለዋል።

መስከረም 14/2017 ዓ.ም በፕሬዜዳንቱ ፊርማ ተፈርሞ ለሁሉም የወረዳና የከተማ ም/ቤቶች የተፃፈው የማስጠንቀቅያ ደብዳቤ " የህዝብ ምክር ቤቶች የትግራይ ጊዚያዊ መንግስትና የህዝቡ አካል እንጂ የህወሓት መዋቅር አለመሆናቸው አውቆ ' ቡድኑ ' የራሱ መሳሪያ ለማድረግ እያካሄደ ያለውን መሯሯጥና ውንብድና ማቆም አለበት " ይላል።

ስለሆነም ምክር ቤቶቹ የመንግስትና የህዝብ መዋቅር መሆናቸው በማመን ' ቡድኑ' ምክር ቤቶቹ በመጠቀም ያልደገፉትንና ሃሳቡ ያልተቀበሉት የመንግስት ሹመኞች ጥላሸት ለመቀባትና ከሃላፊነት ለማውረድ የሚያደርገው ጥረት መቆም አለበት ሲል አስጠንቅቋል።

ምክር ቤቶቹም ይህንን የመንግሰትና የፓለቲካ ድርጅት የሚቀላቅል ህገ-ወጥ ጣልቃ ገብነት ማውገዝ አለባቸው ብሏል።

" ይህ ሳይሆን ከቀረ ግን ህግና ስርዓት ለማስከበር ሲባል ወደ ህጋዊ ተጠያቂነት መሸጋገር የግድ ይሆናል " በማለት አክለዋል።  

ይህ በእንዲህ እንዳለ በዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል የሚመራው ህወሓት ከቀናት በፊት የጊዚያዊ አስተዳደሩ ካቢኔ  ያወጣውን የአቋም መግለጫ የሚቃወም መግለጫ  አውጥቷል።

በዶ/ር ደብረፅዮን የሚመራው ህወሓት መስከረም 14/2017 ዓ.ም ያወጣው  ባለ 4 ነጥብ የተቋውሞ መግለጫ ፤ " ጊዚያዊ አስተዳደሩ ጊዚያዊ  ስራዎች ለመስራት መቋቋሙ ተዘንግቶ ከተቀመጠለት የቆይታ የጊዜ ሰሌዳ በላይ እንዲቆይና ራሱን ወደ ተሟላ የመንግስት ሃላፊነት  ለመለወጥ የሚያደርገው ጥረት ፀረ ዴሞክራሲና ኢ-ህገመንግስታዊ ነው " ብሏል።

ምንም እንኳን " ኢ-ህገመንግስታዊ " ብሎ ቢገልጽም የአገር ወይም የክልሉ ህገ-መንግስት አንቀፆችን አላጣቀሰም።

የእነ ዶ/ር ደብረፅዮን ቡድን " ጊዚያዊ አስተዳደሩ የተሰጠው ተልእኮ ወደ ጎን በመተው ህወሓት ለማፍረስ ፣ ሰራዊት ለማዘዝና የመንግስትና ህዝብ ሃብት በመጠቀም የትግራይ ህዝብ አንድነት ለመበተን እየሄደበት ያለውን የተሳሳተ መንገድ ሊያቆም ይገባል " ሲል አሳስቧል።

@Esat_tv1
@Esat_tv1




ደብረጺዮን ገብረሚካኤል፣ የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ጀነራል ጻድቃን ገብረተንሳይን "ሥልጣን ለመጠቅለል" እና "የቆየ ቂማቸውን ለመወጣት" ይፈልጋሉ በማለት ቅዳሜ'ለት መቀሌ ውስጥ በተካሄደ ሕዝናዊ ስብሰባ ላይ ወቅሰዋል‼️

ደብረጺዮን፣ በጦርነቱ ወቅት የትግራይ ተዋጊዎች አማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን በደረሱ ጊዜ "እኔ ድርድር ያስፈልጋል" ስል፣ ጻድቃን "ከማን ጋር ነው የምንደራደረው? ውጊያው አልቋል" በማለት ይናገር ነበር ብለዋል። የጊዜያዊ አስተዳደሩ ባለሥልጣናት ሕወሓት ሰላም እንደማይፈልግ አድርገው ያቀርባሉ ያሉት ደብረጺዮን፣ ይህ ግን የተሳሳተ ፍረጃ ነው በማለት ተናግረዋል።

በደቡባዊ ዞን በተካሄደ አንድ መድረክ ላይ ጀነራል ጻድቃን እሱ እና እነ ጌታቸው ሰላም ፈላጊ፤ ባንጻሩ እኛ የጦርነት አቀንቃኞች እንደኾንን አድርገው ተናግረዋል በማለትም ደብረጺዮን ወቅሰዋል።

ደብረጺዮን አያይዘውም፣ እነ ጌታቸው ተኩስ አቁም እንዲፈራረሙ ፕሪቶሪያ ሲላኩ፣ ከተሠጣቸው ሥልጣን ውጭ በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር የሚያቋቁም ስምምነት ተፈራርመዋል በማለት ከሰዋል።

@Esat_tv1
@Esat_tv1


በአፍሪካ እ.ኤ.አ. በ2024 ብቻ 30 ሺህ በዝንጀሮ ፈንጣጣ በሽታ የተጠረጠሩ ሰዎች ተመዝግበዋል‼️

በዓመቱ በአህጉሪቱ በዝንጀሮ ፈንጣጣ ተጠርጥረው ከተመዘገቡ ሰዎች መካከል አብዛኛዎቹ ከዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ መሆናቸውም ድርጅቱ ገልጿል።

በሀገሪቱ በዝንጀሮ ፈንጣጣ በሽታ የተጠረጠሩ ሰዎች ቁጥር በማሻቀቡ ምክንያት የምርመራ ቁሳቁስ እጥረት ጭምር ማጋጠሙን ነው ያስታወቀው።

በዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ 5399፣ በቡሩንዲ 564 እንዲሁም በናይጄሪያ 55 ሰዎች በዝንጀሮ ፈንጣጣ በሽታ የተጠረጠሩ ሲሆን፤ እስካሁን 812 ሰዎች በበሽታው ምክንያት ሕይወታቸው አልፏል።

የዓለም ባንክ ባለፈው ሳምንት የዝንጀሮ ፈንጣጣ በሽታ ስርጭትን ለመቆጣጠር ለ10 ሀገራት የሚሰጥ የ128.89 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር ድጋፍ ለማድረግ መወሰኑን ሲጂቲኤን ዘግቧል።

በአፍሪካ የዝንጀሮ ፈንጣጣ በሽታ ከተሰከሰተባቸው ሀገራት መካከል በዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ፣ ቡሩንዲ፤ ናይጄሪያ፣ ደቡብ አፍሪካ፣ ኡጋንዳ፣ ላይቤሪያ እና ሞሮኮ ተጠቃሽ ናቸው።

የዝንጀሮ ፈንጣጣ (Mpox) በሽታ የሚከሰተው ሞንኪፖክስ በተባለ ቫይረስ አማካይነት ነው ሲሆን፣ ይህም ጉዳቱ ዝቅተኛ ከሆነው የፈንጣጣ ቫይረስ ዝርያ ውስጥ የሚመደብ ነው።

የበሽታው ቫይረስ በመጀመሪያ ላይ ከእንስሳት ወደ ሰው የሚተላለፍ የነበረ ሲሆን፣ አሁን ግን ከሰው ወደ ሰው እየተሰራጨ ይገኛል።

@Esat_tv1
@Esat_tv1


በሱዳን በተከሰተው የኮሌራ ወረርሽኝ የሞቱ ሰዎች ቁጥር 388 ደረሰ‼️

የሱዳን የጤና ጥበቃ ሚኒስትር ሃይታም መሀመድ ኢብራሂም ከአስቸኳይ ስብሰባ በኋላ በትላንትናው ዕለት በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ የኮሌራ ተጠቂዎች ቁጥር 12,896 መደርሱን እና የሟቾች ቁጥር ወደ 388 ከፍ ማለቱን ተናግረዋል።

የታቆረ ውሃ ለበሽታዎች መራቢያ ቦታ ሊፈጥር ይችላል የሚል ተጨማሪ ስጋት ፈጥሯል ተብሏል።

የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር የድንገተኛ አደጋ ኦፕሬሽን ማእከል ባወጣው መግለጫ እንዳስታወቀው ቅዳሜ ዕለት በካሳላ፣ በገዳረፍ፣ በሰሜን፣ በናይል ሪቨር እና በቀይ ባህር ክልሎች 401 አዳዲስ የኮሌራ ተጠቂዎች ተመዝግበዋል ብሏል።

የካሳላ ግዛት ሶስት አዲስ ሞትን ያስመዘገበ ሲሆን በሰሜናዊው ክፍለ ሀገር የሁለት ሞት እና የናይል ወንዝ ደግሞ ከኮሌራ ጋር በተያያዘ አንድ ሞት መመዝገቡን ተናግሯል።

የኮሌራ ወረርሽኙ በ10 ግዛቶች ውስጥ በ54 አካባቢዎች መስፋፋቱ ተነግሯል።

የአደጋ ጊዜ ኦፕሬሽን ማእከሉ አክሎም የሀገሪቱ ጤና ጥበቃ ሚኒስቴር በስምንት ክልሎች 45 የህክምና ማዕከላትን ከፍቶ በየእለቱ ክትትል ከማድረግ በተጨማሪ ለካሳላ ክልል ቀጣይነት ያለው የቴክኒክ ድጋፍ እና ምላሽ መስጠትን ጨምሮ የተለያዩ እርምጃዎችን ወስዷል ብሏል።

በተጨማሪም መድሀኒቶችን እና ሌሎች አስፈላጊ ነገሮችን ለማቅረብ እና ወረርሽኙን ለመከላከል ከሚሰሩ ድርጅቶች ጋር በቅንጅት ለመስራት ቃል ገብቷል።

@Esat_tv1
@Esat_tv1


እስራኤል በዛሬው እለት ሂዝቦላ ይንቀሳቀስባቸዋል ባለቻቸው ከ800 በላይ ቦታዎች ላይ ጥቃት ከፍታለች‼️

° የሊባኖስ የጤና ሚኒስቴር በጥቃቱ ቢያንስ 270 ሰዎች መሞታቸውን ሲግልጽ፤ 21 ህጻናት ናቸው ብሏል።

እስራኤል በዛሬው እለት "የሂዝቦላ ታጣቂዎች የሚንቀሳቀሱባቸው ቦታዎች ናቸው" ባለቻቸው ከ8 መቶ በላይ በሚቆጠሩ ኢላማዎች ላይ የአየር ጥቃት ከፍታለች።

ጥቃቱ የጋዛ ግጭት ከጀመረ በኋላ ከፍተኛው ነው ሲባል በቀጠናው ውጥረት ነግሷል።

ከሟቾቹ መካከል ምን ያህሉ ሲቪሎች ወይም የሂዝቦላህ ታጣቂዎች እንደሆኑ ግልፅ ባይሆንም እስራኤል ጥቃቶቹ ያነጣጠሩት ሂዝቦላ በሚንቀሳቀስባቸው አካባቢዎች እንደሆኑ ገልጻለች።

እስራኤል የጥቃት ትኩረቷን ወደ ሰሜናዊ ድንበር አዙራለች የተባለ ሲሆን በኢራን ይደገፋል የተባለው የሂዝቦላ ጦር ሃማስን በመደገፍ ወደ እስራኤል ሮኬቶችን እያስወነጨፈ ነው ተብሏል።

የእስራኤል የመከላከያ ሚኒስትር ዮአቭ ጋላንት ባሰራጩት የቪዲዮ መልእክት "የሰሜን አካባቢ ነዋሪዎችን በሰላም ወደ ቤታቸው በመመለስ ሂደት ውስጥ ግባችን ላይ እስክንደርስ ድረስ ጥቃቶቹ ይቀጥላሉ" ሲሉ ተናግረዋል።

በጥቃቱ ቢያንስ 270 ሰዎች መሞታቸው ሲገልፅ ከ1,024ሰዎች በላይ መቁሰላቸውን የሊባኖስ የጤና ሚኒስቴር አስታውቋል።

ከተጎጂዎቹ መካከል ሴቶች እና ህጻናትን እንደሚገኙነት የሊባኖስ የሀገር ውስጥ ሚዲያዎች ዘግበዋል። የሊባኖስ ነዋሪዎች ሂዝቦላህ የጦር መሳሪያውን ከሚያከማችባቸው ቦታዎች ለቀው እንዲወጡ እስራኤል ማሳሰቢያ ሰጥታለች ተብሏል።

የሂዝቦላ ጦር ለጥቃቱ ሰጠሁት ባለው አፀፋዊ ምላሸ በእስራኤል ወታደራዊ ካምፖች ላይ ሮኬቶችን ማስወንጨፉን ገልጿል።

እስራኤል ይህን መሰል ጥቃት ስትፈጽም ከ2006 በኋላ ይኽ የመጀመሪያው ነው ተብሏል።

@Esat_tv1
@Esat_tv1


ኢትዮጵያ በፓኪስታን የደረሰውን የሽብር ጥቃት አወገዘች‼️

ኢትዮጵያ በፓኪስታን ካይበር ፓክቱንክዋ በተባለው ግዛት የደረሰውን የሽብር ጥቃት አውግዛለች።

ጥቃቱ በፓኪስታን የኢትዮጵያ አምባሳደርን ጨምሮ በርካታ ዲፕሎማቶችን የያዘ ተሽከርካሪ ላይ መፈጸሙን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል።

ኢትዮጵያ ዲፕሎማቶቹን ሲያጅብ በነበረው የፖሊስ ኦፊሰር ህልፈት ለቤተሰቦች፣ ለፓኪስታን ሕዝብና መንግስት መጽናናትን እንደምትመኝም ሚኒስቴሩ ገልጿል።

@Esat_tv1
@Esat_tv1


Platinum Mass Gainer

ጤናማ የሆነ ክብደት መጨመር ይፈልጋሉ ከፍተኛ የሆነ የፕሮቲን እና የካርቦሃይድሬት ዉቅር ሲሆን  በአንድ  ማንኪያ:-

👉1,250 ካሎሪ
👉 60  ግራም ፕሮቲን
👉 6 G ግራም ግሉታሚን
👉 9 G ግራም ክሬቲን
👉 2 G ግራም ቢሲኤኤ
👉ቪታሚኖችን

👩🏽‍⚕️ የያዘው ይህ የከፍተኛ የፕሮቲን እና ካርቦሃይድሬት ድብልቅ የጡንቻን ብዛት በፍጥነት እና በብቃት ለማጎልበት የሚረዳዎትን በቂ የፕሮቲን ፍጆታ በማረጋገጥ የሰውነትዎን ጂኤች እና ቴስቶስትሮን ደረጃን ለማሳደግ የሚያስፈልግዎት ውህድ ነው።

አድራሻችን;- ሆሳዕና ጮራሞ ሕንፃ 1 ፎቅ የቤት ቁጥር 07 ጎራ በማለት የሚፈልጉትን ያገኛሉ።


ወደ አገር በሚገቡ እቃዎች ላይ መመሪያ ወጥቷል‼️

ገንዘብ ሚኒስቴር

ወደ አገር በሚገቡ እቃዎች ላይ ከተጣለው የማህበራዊ ልማት ቀረጥ ነጻ የሚሆኑ እቃዎችን ለመወሰን ገንዘብ ሚኒስቴር መመሪያ አውጥቷል።

ይኸው መመሪያ” መመሪያ ቁጥር 1023/2017″ ይሰኛል።

በዚህ መመሪያ መሰረት ፥ ለህብረተሰቡ በነጻ የሚሰጡ የትምህርት እና የጤና አገልግሎቶችን ለማስፋፋት እንዲሁም በሰው ሰራሽ እና በተፈጥሮ አደጋ ምክንያት ችግር ላይ የሚገኙ ወገኖችን ለመርዳት ከውጭ አገር በእርዳታ የሚላኩ እቃዎች የማህበራዊ ልማት ቀረጥ የተጣለበትን አላማ ለማሳካት የሚያግዙ በመሆኑ ከቀረጥ ነጻ እንዲሆኑ ተደርጓል።

ከማህበራዊ ልማት ቀረጥ ነጻ የተደረጉ እቃዎች?

የሚከተሉት እቃዎች ከማህበራዊ ልማት ቀረጥ ነፃ ሆነው ወደ ሀገር ይገባሉ፡፡

1. ለሚከተሉት የማህበራዊ አገልግሎት መስጫ ተቋማት ከውጭ አገር በእርዳታ የሚላኩ እቃዎች :-

ሀ/ በመንግስት ባለቤትነት ስር ያሉ ወይም ለህብረሰሰቡ ነጻ አገልግሎት የሚሰጡ :

– የትምህርት ተቋማት፣
– የጤና ተቋማት፣
– የሕጻናት፤ የሴቶች፤ የአረጋውያን፣ የአእምሮ ህመምተኞች እና የአካል ጉዳተኞች መርጃ ድርጅቶች

ለ/ በሰው ሰራሽ እና በተፈጥሮ አደጋ ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኖች የአስቸኳይ ጊዜ እርዳታ ለሚሰጡ ድርጅቶች ከውጭ አገር በእርዳታ የሚላኩ እቃዎች

2. ኢትዮጵያ በፈረመቻቸው ዓለም አቀፍ ስምምነቶች ከቀረጥ እና ታክስ ነጻ ሆነው ወደአገር እንዲገቡ የተፈቀደ እቃዎች።

3. የአገር መከላከያ ሚኒስቴር፣ የፌዴራል እና የክልል ፖሊስ ተቋሞች፣ የብሔራዊ መረጃ እና ደሕንነት አገልግሎት እና ኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር በሕግ በተፈቀደው መሰረት ወደ አገር የሚያስገቧቸዉ የመከላከያ እና የህዝብ ደህንነት መሳሪያዎች፣…

@Esat_tv1
@Esat_tv1


በቤሩት እስራኤል በፈጸመችው የአየር ጥቃት የሟቾች ቁጥር 31 ደረሰ‼️

በሊባኖስ ቤሩት ደቡባዊ ክፍል እስራኤል ባደረሰችው የአየር ጥቃት የሟቾች ቁጥር 31 ደርሷል።

የሊባኖስ ጤና ሚኒስትር ፊራስ አቢያድ እንደገለጹት ከሟቾች ውስጥ ሦስት ህጻናትና ሰባት ሴቶች ይገኙበታል፡፡ የእስራኤል የአየር ጥቃት በሊባኖስ መዲና ሁለት ሕንጻዎችን ያፈራረሰ ሲሆን 68 ሰዎች ላይ ጉዳት ማድረሱንም ሚኒስትሩ አክለዋል።

የከተማዋ ትራንስፖርት ሚኒስትር አሊ ሃሜህ እስራኤል በመኖርያ ሕንጸዎች ላይ ያደረሰችው ፍንዳታ የጦር ወንጀል መሆኑን እና ቀጣናውን ወደለየለት ጦርነት የሚገፋ መሆኑን ተናግረዋል።

እስካሁን 23 ሰዎች በፍርስራሹ ውስጥ ጠፍተዋል ማለታቸውን አልጄዚራ ዘግቧል፡፡ የእስራኤል ጦር ግን ጥቃቱ የሄዝቦላህ ከፍተኛ አመሮችን ኢላማ ያደረገ ነበር ብሏል፡፡ ሄዝቦላህም ኢብራሂም አቂል እና አህመድ መሀመድ ዋሀቢ የተባሉ የጦር አዛዥ ኮማንደሮቹ በጥቃቱ እንደሞቱበት አረጋግጧል።

@Esat_tv1
@Esat_tv1


የ15 ዓመት ታዳጊን ለአራት በመሆን የአስገድዶ መድፈር ወንጀል የፈፀሙ ተከሳሾች በእስራት ተቀጡ‼️

በኮንታ ዞን አመያ ዙሪያ ወረዳ ኦፓላሼ ቀበሌ ለአራት በመሆን የ15 ዓመት ታዳጊን አስገድዶ መድፈር ወንጀል የፈፀሙ ተከሳሾች በእስራት ተቀጡ።

ተከሳሾች በቁጥር አራት ሲሆን አስፋቸው አለሙ፣ አሻግሬ አበራ፤  ማቲዎስ ደዋና እና አስማማው አሉላ የተባሉ ግለሰቦች ናቸው።

ግለሰቦቹ በአመያ ዙሪያ ወረዳ በግምት 8:00 አካባቢ  ጫሬ ዶቄ ቀበሌ ቤተሰብ ለመጠየቅ ወደ ኦፓላሼ ቀበሌ እየሄደች የምትገኝ የ15 አመት ታዳጊ አስገድደው መድፈራቸውን የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች  ክልል ፖሊስ ኮሚሽን የህዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር ኢንስፔክተር ደጀኔ አሰፋ ለብስራት ሬዲዮ  እና  ቴሌቪዥን ተናግረዋል ።

በአስገድዶ መድፈር ወንጀል ጥፋተኛ ሆነው ክስ የቀረበባቸው ወንጀለኞች ጳግሜ 5 ቀን 2016 ዓ.ም  በዋለው ችሎት ከ1ኛ እስከ 3ኛ ተከሳሾች እያንዳንዳቸው 7 ዓመት ፅኑ እስራት  ተቀጥተዋል።

አራተኛ ተከሳሽ ዕድሜው ከ10 እስከ 13 ዓመት በመሆኑ ተከሳሹ  መታሰር የማይችልና እንደዚህ ዓይነት ታዳጊ እስረኞችን ተቀብሎ   በማረምያ ተቋም በዞኑ ባለመኖሩ ምክንያት ቤተሰቡ ፈርሞ ወስዶት ክትትልና በቁጥጥር እንዲያደርግ በማለት ውሳኔ መሰጠቱን ኢንስፔክተር ደጀኔ አሰፋ ለብስራት ሬዲዮ  እና  ቴሌቪዥን ተናግረዋል ።

@Esat_tv1
@Esat_tv1


የሂዝቦላ ከፍተኛ አዛዥ የሆነው ኢብራሂም አቂል ተገደለ‼️

በሊባኖስ ቤሩት ውስጥ እስራኤል በሰነዘረችው የአየር ጥቃት የሂዝቦላ ከፍተኛ አዛዥ የሆነው ኢብራሂም አቂል መገደሉ ተነገረ።

እስራኤል የሂዝቦላ ቡድን ከፍተኛ አዛዥ የሆነውን ኢብራሂም አቂልን ዒላማ አድርጋ የአየር ጥቃቱን መፈጸሟን የሊባኖስ የደህንነት ምንጮች እና የእስራኤል ጦር ራዲዮ ገልጸዋል።

@Esat_tv1
@Esat_tv1

Показано 20 последних публикаций.