ኢትዮ መረጃ - NEWS


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: Новости и СМИ


ኢትዮጵያን መውደድ ባትችል አትጥላት
ማክበር ባትችል አታዋርዳት
ማራመድ ባትችል አታዘግያት
መጠበቅ ባትችል አትበትናት።
ይህን በማድረግ ታሪክ ባትሠራም ታሪክ አታበላሽም።

ለአስታየት @ethio_merjabot
@biruke_promotion

Связанные каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
Новости и СМИ
Статистика
Фильтр публикаций


ጌታቸው ረዳ‼️

የሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት በድጋሚ የሚያገረሽበት ዕድል ዝግ ነው ሲሉ አቶ ጌታቸው ረዳ ተናገሩ

የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ርዕሰ መስተዳድር ጌታቸው ረዳ ፣ የሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት በድጋሚ የሚያገረሽበት ዕድል ዝግ ነው በማለት ትናንት ከቻይናው ሲጂቲኤን ቴሌቪዥን ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ ተናግረዋል።

ያለፈው ጦርነት የትግራይ ሕዝብ ፍላጎት አልነበረም ያሉት ጌታቸው ፣ የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደርና የትግራይ ሕዝብ ድጋሚ ጦርነት እንዳያገረሽ የተቻላቸውን ጥረት ኹሉ እንደሚያደርጉ አረጋግጠዋል።

ጌታቸው ይህን ያሉት ፣ በአላማጣ አቅራቢያ በትግራይ ኃይሎች እና ባካባቢው ሚሊሻዎች መካከል የተኩስ ልውውጥ በተደረገ ማግስት ነው መባሉን ዳጉ ጆርናል ከዋዜማ ዘገባ ተመልክቷል።

አቶ ጌታቸዉ ይህንን ይበሉ እንጂ አብን፣ ሕወሃት ለአዲስ ዙር ጦርነት ቅስቀሳ እያደረገ ነው ሲል ትናንት ምሽት ባወጣው መግለጫ ከሷል። ፓርቲው፣ በግጭት ማቆም ስምምነቱ መሠረት የሕወሃት ተዋጊዎች ሙሉ በሙሉ ትጥቅ ሳይፈቱና መከላከያ ሠራዊት በትግራይ ክልል ጸጥታ ለማስከበር ሳይሠማራ ሕወሃት ለሌላ ዙር ጦርነት ፕሮፓጋንዳ በመለፈፍ ተጠምዷል ብሏል።

የፌደራሉና የአማራ ክልል መንግሥታት የሕወሃትን የጠባጫሪነት ቅስቀሳ በትኩረት እንዲከታተሉና በአማራ ክልል የሚካሄደው ግጭት "በንግግር" እና "ድርድር" እንዲፈታም አብን ጠይቋል። የአማራ ሕዝብ ሕወሃት ሊያደርስበት የሚችለውን ጥቃት ለመከላከል በአንድነት እንዲቆም የጠየቀው ፓርቲው፣ የትግራይ ሕዝብም ራሱን ከሕወሃት ቀንበር እንዲያላቅቅ ጥሪ አድርጓል።

@sheger_press
@sheger_press


በኢትዮጵያ አየር መንገድ የሚሰሩ የጉምሩክ ሰራተኞች እንደአዲስ ሊዋቀሩ ነው ተባለ‼️

በቅርብ ጊዜያት በርካታ ቅሬታዎችን ያስተናገደው የኢትዮጵያ አየር መንገድ የጉምሩክ የስራ ክፍል፤ ሰራተኞች በአዲስ መልክ እንደሚደራጁ የጉምሩክ ኮሚሽን አስታወቀ።

የጉምሩክ ኮሚሽን ኮሚሽነር ደበሌ ቃበታ በ2016 ስምንት ወራት ውስጥ 49 የጉምሩክ ሰራተኞች እና ከፍተኛ አመራሮች  ላይ አስተዳደራዊ እና ሕጋዊ እርምጃ ተወስዷል ብለዋል።

ኮሚሽኑ በሰራተኝኞቹ ላይ የሚቀርቡትን ቅሬታዎች ለመቅረፍ "ረጅም ጊዜ" የወሰደ ጥናት መካሄዱ ታውቋል።

በጥናቱ መሰረት በኢትዮጵያ አየር መንገድ ውስጥ የሚሰሩ የጉምሩክ ኮሚሽን ሰራተኞን ለመቀየር፣ ለማሸጋሸግ እና በድጋሚ ለማዋቀር ዝግጅት ተደርጓል ተብሏል።

@ethio_mereja_news


የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ፤ የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር በተወሰኑ የክልሉ አካባቢዎች ላይ ትንኮሳ መጀመሩን ገለጸ፡፡

የአማራ ብሔራዊ ክልል መንግሥት ከሰሞኑ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ያወጣውን መግለጫ ተከትሎ ምላሽ ሰጥቷል። ሙሉ መግለጫዉ እንደሚከተለው ቀርቧል...

የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ካቢኔ መጋቢት 16 ቀን 2016 ዓ.ም የአማራ ክልል ተማሪዎች መማሪያ መጻህፍትን እንደሰበብ ተመርኩዞ ያወጣውን የዛቻ እና የጠብ አጫሪነት መግለጫ ተመልክተናል፡፡ ጊዜያዊ አስተዳደሩ የአማራ ክልል የትምህርት ሥርዓትን በማጣቀስ የተሳሳተ ካርታ ተሰርቷል ሲል ያወጣው መግለጫ በተሳሳተ ካርታ ወደ አማራ ክልል ተካተዋል ያላቸውን አካባቢ ሕዝቦች ታሪካዊ እውነታን፣ ተጨባጭ ማስረጃዎችን እና ነባራዊ ሐቅን የካደ፣ አሳሳች እና የጠብ አጫሪነት ፍላጎትን የተሸከመ መግለጫ በመሆኑ እና በትናንትናው እለት ማለትም መጋቢት 18 ቀን 2016 ዓ.ም ደግሞ ከነበረበት አካባቢ በመንቀሳቀስ የራያ አላማጣ ወረዳ ቀበሌዎችን በመያዝ ነዋሪዎችን በመግደል እና በማሰቃየት ላይ ይገኛል፡፡

ጊዜያዊ አስተዳደሩ የአማራ ክልል የተማሪዎች የመማሪያ መጻሕፍ ውስጥ የተሳሳተ ካርታ ተሰርቷል ሲል ባወጣው መግለጫ ሊያመላክታቸው የተፈለጉት አካባቢዎች ካለፉት 30 ዓመታት በፊት ጀምሮ የወልቃይት ጠገዴ፣ ጠለምት እንዲሁም የወፍላ ወረዳዎች እና የራያ የማንነት ጥያቄ ያሉባቸው ወረዳዎች የማንነት እና ራስን በራስ የማስተዳደር ጥያቄዎችን ሲያቀርቡባቸው በነበሩ ቦታዎች ላይ መኾኑ ግልጽ ነው፡፡

አሁን በሥራ ላይ የሚገኘው የሀገሪቱ ሕገ መንግሥት ከመጽደቁ በፊት በተስተዋሉት የአስተዳደራዊ መዋቅሮች እና አደረጃጀት ቅመራ ጅማሬ አንስቶ ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) በሰሜን ዕዝ የሀገር መከላከያ ሠራዊት ላይ አሰቃቂ ጥቃት በመፈጸሙ ምክንያት ጦርነት እስከተቀሰቀሰበት ግዜ ድረስ የወልቃይት ጠገዴ፤ ጠለምት እንዲሁም የወፍላ ወረዳዎች እና የራያ የማንነት ጥያቄ ያለባቸው ወረዳዎች በወቅቱ ለነበረው መንግስት የማንነትና ራስን በራስ የማስተዳደር ጥያቄዎችን በማንሳት መብቶቻቸው እንዲከበሩላቸው ሲጠይቁ የነበሩ መሆኑን በበርካታ ታሪካዊ ሁነቶችና ተጨባጭ ማስረጃዎች የተረጋገጠ ጉዳይ ነው፡፡

ይሁን እንጂ እነዚህ የማንነትና ራስን በራስ የማስተዳደር መብቶቻቸው እንዲከበሩላቸው ሲጠይቁ የነበሩ ሕዝቦች እና አካባቢዎችን ለበርካታ ዘመናት በኃይል ሲገዛ የነበው የቀድሞው የትግራይ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የወልቃይት ጠገዴ፤ ጠለምት እንዲሁም የወፍላ ወረዳዎች እና የራያ የማንነት ጥያቄ ያለባቸው ወረዳዎች ላነሱት ታሪካዊና ሕጋዊ ጥያቄዎች ሕጋዊ አሰራርን የተከተለ ምላሽ ከመስጠት ይልቅ የአካባበው ተወላጆችን፣ የሀገር ሽማግሌዎችን፣ የማንነትና የአስተዳደር ጥያቄ አስተባባሪዎችን በማሰር፣ በማሰደድ እና በመግደል የሕዝቡ ጥያቄ ምላሽ ሳያገኝ እስከ ሰሜኑ የህግ ማስከበር ጊዜ ድረስ እንዲገፋ አድርጎታል ብሏል።


የማንነት እና የአስተዳደር መብት ዙሪያ ላነሳቸው ጥቄዎች የወልቃይት ጠገዴ፣ ጠለምት እንዲሁም የወፍላ ወረዳዎች እና የራያ የማንነት ጥያቄ ያለባቸው ወረዳዎች ትግል በተፋፋመበትና ከፍተኛ መስዋዕትነት ጭምር እየከፈለ በሚገኝበት ወቅት ህወሓት የሠሜን ዕዝ የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊትን አሰቃቂ ጥቃት መሰንዘሩን ተከትሎ የኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዴሞክራሲያዊ መንግስት ሁሉንም ኢትዮጵያዊያንን በማቀናጀት ለሁለት ዓመታት የቆየ የሕግ ማስከበር እርምጃ ለመውሰድ የተገደደበት ሁኔታ መፈጠሩ ይታወሳል፡፡

የማንነትና የአስተዳደር ጥያቄዎቹ ለዘመናት የታፈኑበት ሕዝብም ከማዕከላዊው መንግስት ጎን ተሰልፎ በህ.ወ.ሓ.ት የክህደት ተግባር በኢትዮጵያ ሕልውና እና ሉአላዊነትት ላይ የተጋረጠውን ግልጽ አደጋ እንዲቀለበስ የበኩሉን አስተዋጽዖ ከማበርከቱ ባሻገር በሂደቱ ህወሓት በኃይል ተገፍፎባቸው የነበረውን የማንነትና ጥያቄና ራስን በራስ የማስተዳደር ነጻነት የተቀዳጁበት ሁኔታ ተፈጥሯል፡፡

በዚህም ምክንያት የወልቃይት ጠገዴ፣ ጠለምት እንዲሁም የወፍላ ወረዳዎች እና የራያ የማንነት ጥያቄ ያለባቸው ወረዳዎች ህዝብ እንደማንኛውም የሀገሪቱ ሕዝብ ሁሉ የልማቱ ተሳታፊና ተጠቃሚነት መብቱ ሊቀለበስ የማይችል በመሆኑ በቀድሞው የህ.ወ.ኃ.ት እና በኢ.ፌ.ዲ.ሪ መንግስት መካከል የፕሪቶሪያው ስምምነት ከመፈረሙ በፊት ጀምሮ የአማራ ክልል እንደሌሎቹ ዞኖችና የልማት ትሩፋቶች ሁሉ የአካባቢው ሕዝብም በትምህርቱም መስክ ተጠቃሚ እንዲሆኑ አድርጓል፡፡

አካባቢዎቹን በተመለከተ የነበረው፣ ያለው እና የሚኖረው እውነታ ይሄ ሆኖ ሳለ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ካቢኔ መጋቢት 16 ቀን 2016 ዓ/ም ከፕሪቶሪያው ስምምነት ከመፈረሙ በፊት በስራ ላይ የዋሉ የአማራ ክልል ተማሪዎች እንደሌሎቹ አካባቢዎች የነዚህ አካባቢ ህፃናትም የመማራ መብታቸው እንዲከበር የአማራ ክልል መንግስት ግዴታውን መወጣቱን ሰበብ በማድረግ በአማራ ክልል ላይ ጥቃት ከመፈጸም የማይመለስ መሆኑን የሚገልጽ የጠብ አጫሪ መግለጫ ማውጣቱ ካለፉት ድርብርብ ውድቀቶች ትምህርት አለመውሰድን ከማሳየት የዘለለ ፋይዳ አይኖረውም፡፡

የተፈጠሩ ችግሮችን በህግ አግባብ እንዲፈታ እተደረገ ያለውን ጥረት የአማራ ክልል መንግስት የራሱን ድርሻ እየተወጣ ባለበት ሁኔታ በህዝብ መጎሳቆልና በወጣቶች እልቂት ትምህርት አለመወሰዱና የተለመደ ትንኮሳ በማድረግ ላይ መሆኑ እጅጉን አሳዝኖናል፡፡

ስለሆነም የትግራይ ክልል ግዜያዊ አስተዳደር ለሀገሪቱ ቋሚ ቀውስ ምንጭ ከሚያደርጉት ተግባራት እንዲታቀብ፣ ሀገራችንንና ሁለቱን ክልሎች ወደ ቀውስ ከሚያስገቡ ተግባራት በመቆጠብ ከለመደው አጓጉል የካርታ ፖለቲካ ጨዋታ እንዲወጣና የህዝብን ፍላጎት ማዕከል ባደረጉ ውይይቶች ላይ እንዲያተኩር እንዲሁም አንድ ሀገር ለመገንባት ለሚፈለገው ዘላቂ ሠላም እና ለሕዝቦች አንድነት መጽናት በሚበጅ ሐሳብና ተግባር ላይ እንዲያተኩር እንመክራለን ሲል መግለጫውን አጠናቅቋል፡፡

@ethio_mereja_news


የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) በወቅታዊ ጉዳይ ላይ ትናንት ምሽት ባወጣው መግለጫ ከሰሞኑ በህውሃት በኩል እየተፈፀሙ ነው ያላቸውን ትንኮሳዎች አንስቶ ለአማራና ለትግራይ ህዝብ እንደዚሁም ለአማራ ክልልና ፌደራል መንግስት መልዕክት አስተላልፏል።ከመግለጫ የተወሰዱት 3 ነጥቦች የሚከተሉት ናቸው።

① ✔"የተከበርከው የአማራ ሕዝብ…ትሕነግ የሁሉም ኢትዮጵያውያን ጠላት ቢሆንም ፣ በተለይ የአማራ ህዝብ የቡድኑ ወረራ ቀጥተኛ ሰለባ እና ገፈት ቀማሽ በመሆኑ ጦርነቱን የመመከት ድርብ ኃላፊነት ያለበት መሆኑ ይታወቃል፡፡ በመሆኑም በሁሉም አካባቢዎች የሚገኝው ሕዝባችን ካለፈው የጥፋት ግዜ በመማር ለታሪካዊ ጠላቱ ፕሮፖጋንዳ ጀሮ ባለመስጠት ራስህን ከአራተኛ ዙር ጥፋት ለመከላከል ከመቸውም ጊዜ በላይ በአንድነት እንድትቆም ጥሪያችንን እናስተላልፋለን፡፡"

② ✔"የተከበርከው የትግራይ ሕዝብ በስምህ የሚነግደው … ቡድን ፣ ከመላው ኢትዮጵያውያን ጋር ያለህን ትስስር ለመበጠስ እና ከኢትዮጵያዊ ማንነትህ ለመንቀል በማያባራ የጦርነት አዙሪት ውስጥ እንዳስገባህና አምራች ሀይልህን ፍትሀዊ ባልሆነ ጦርነት ማግዶ ማስፈጀቱ ይታወቃል፡፡ ልጆችህን ከጉያህ እየነጠቀ ፣ ጥሪትህን እያሟጠጠ እና አግቶ በመያዝ ከሌሎች ኢትዮጵያውን ጋር በአንድነት እና በሰላም እንዳትኖር ጋሬጣ የሆነብህን ደም-የማይጠግብ የሽብር ቡድን ከራስህ ላይ አሽቀንጥረህ በመጣል ራስህን ነጻ እንድታወጣ ጥሪያችንን እያስተላለፍን ፣ ከሽብር ቡድኑ እገታ ነጻ ለመውጣት በምታደርገው ተጋድሎ ድጋፋችን እንደማይለይህ ከወዲሁ እናስታውቃለን፡፡ "   

③ ✔"የአማራ ክልል መንግስትና የፌዴራል መንግስት ትህነግ ወያኔ ተደጋጋሚ ወረራ በመፈጸም ታሪክ ይቅር የማይለው ሰፊ ጥፋት በሀገርና በህዝብ ላይ የፈጸመ ሆኖ ሳለ ይህ አልበቃው ብሎ አሁንም ሌላ ዙር ጦርነት ቀስቃሽ ፕሮፓጋንዳ ውስጥ የገባ በመሆኑ ይህንን የወያኔን ጠብ አጫሪነት በትኩረት እንዲከታተሉ በጥብቅ እያሳሰብን ከዚሁ ጋር በተያያዘ በአማራ ክልል ውስጥ የተፈጠረውን ችግር ልዩ ትኩረት ሰጥተው በውይይትና ድርድር ሰላም የማስፈን ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ አሁንም ጥሪ እናቀርባለን።"
የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን)
መጋቢት 17/2016 ዓ.ም አዲስ አበባ ኢትዮጵያ!

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news


#Notcoin

የመጨረሻ እድል ነው 3 ቀን ነው የቀረው ፍጠኑ! ትንሽም ቢሆን ለመጫወት ሞክሩ👇

https://t.me/notcoin_bot?start=r_573809_33859156

3 ቀን ብቻ ነው የቀረው ሁላችሁም የአቅማችሁን coin ሰብስቡ Tap Tab ማረግ ነው! ምንም ልፋት የለወም እዚሁ ቴሌግራም ቦት ላይ coin ሰለምሰበሰቡ ደህንነቱ 100% የተጠበቀ ነው! እንዳይቆጫቹ አሁኑኑ ጀምሩ

ግድ የላችሁም
ችላ አትበሉት👇

Start በማረግ
አሁንኑ ጀምሩ👇👇

https://t.me/notcoin_bot?start=r_573809_33859156


መንግሥት በዋና ከተማ አዲስ አበባ የሚከናወኑ የቤት ፈረሳዎች ከተማዋን ለማዘመንና ለነዋሪዎቿም ምቹ ለማድረግ የታሰበ የልማት እቅድ መሆኑን ይገልጻል። መኖሪያ ቤታቸው ለፈረሰባቸው ወገኖችም ምትክ ቦታ እንደሚሰጥም እንዲሁ። በዛሬው ዕለትም በአዲስ አበባ ከተማ እየተካሄደ የሚገኘው የኮሪደር ልማት ሥራ ሂደት መገምገሙንም ጠቅላይ ሚኒስትር አቢይ አህመድ በማኅበራዊ መገናኛ ገጻቸው አመልክተዋል። በዚህም ቀዳሚ ዓላማቸው አዲስ አበባን ለነዋሪዎቿ የተመቸች ሳቢ ከተማ ለማድረግ ያላቸውን ቁርጠኝነት ማሳካት መሆኑንም ገልጸዋል። «የማልማት ሥራ ሂደቱ በግሉ ክፍለ ኢኮኖሚና በመንግሥት ብሎም አነስተኛ ገቢ ባላቸው የኅብረተሰብ ክፍሎች እና የተለያዩ አካላት የተያዙና የተከራዩ ንብረቶችን የነካ ሊሆን ቢችልም ይህ ለረዥም ጊዜ ፋይዳ ትልም ይዞ የተነሳ ሥራ ሲጠናቀቅ ለሁሉም ባለድርሻ አካል ብሎም ለሰፊው ሕዝብ የሚሰጠው ጥቅም ትልቅ ነው»ም ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ።
ከተማን ለማዘመን በማሰብ የነባር ቤቶች እና መንደሮች መፍረስ አስቀድሞ ከሌሎች ሃገራት ተሞክሮ ቢወሰድበት መልካም እንደነበር የሚጠቁሙ በበኩላቸው ለታሪካዊ ሕንጻዎችና ቅርሶች ተገቢና ሞያዊ ጥንቃቄ እያሳሰቡ ነው። ከበቂ መተላለፊ መንገድ አንስቶ የመጸዳጃ ቤቶች እና የፍሳሽ ማውረጃ መስመሮች ጉድለት የሚታይባቸው ጭርንቁስ መንደሮችን የዋና ከተማዋን ደረጃ በጠበቀ መልኩ ማሻሻል እንደሚያስፈልግ የሚገልጹ ወገኖች ጥንታዊ የከተማ ገጽታዎችን ጠብቆ ማቆየት በሌሎች ሃገራት ለቱሪዝም መስህብነት አይነተኛ ሚና እንዳለውም ያነሳሉ። እርስዎስ ምን ይላሉ?

@ethio_mereja_news


ያሳዝናል‼️

የአለልኝ የሞቱ መንስኤ ከቤተሰብ ጋር በትዳሩ ምክንያት አለመግባባት ነው !

የካናል ፕሉሱ ጋዜጠኛ አብዱ ሞሀመድ

"...ለእረፍት ወደ ቤተሰቦቹ ቤት አርባምንጭ ባለቤቱን ይዞ እንደሄደና ፡ ቤተሰቦቹ ትዳሩን እንዳልወደዱለትና ጭቅጭቅ እንደነበር፡ ከዛም ሞተሩን አሰነስቶ አዲስ ወደሚያሰራው የግል ቤቱ በመሄድ የኤልትሪክ ምሰሶ ላይ ራሱን አጠፋ " ብሏል በዘገባው

ከመሰረተው ትዳር ጋር በተገናኘ ተደጋጋሚ ጭቅጭቆች እንደነበሩ በዩቲዩብ ቻናሉ አጋርቷል።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news


በኢትዮጵያ የኢንተርኔት አገልግሎት ተጠቃሚዎች ቁጥር 41 ሚሊዮን ደረሰ 

በኢትዮጵያ የኢንተርኔት አገልግሎት ተጠቃሚዎች ቁጥር 41 ሚሊዮን መድረሱን የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈጻሚ ፍሬህይወት ታምሩ ተናገሩ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና ሌሎች ከፍተኛ የመንግስት ሃላፊዎች በተገኙበት ዲጂታል ኢትዮጵያን ለማሳካት የተከናወኑ ተግባራትና ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎች ላይ ውይይት ተደርጓል።

በመድረኩ በነበረው የፓናል ውይይት ላይ የተሳተፉት የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈጻሚ ፍሬህይወት ታምሩ በቴሌኮም ዘርፉ የተደረጉ ማስፋፊያዎችና ለውጦችን ዘርዝረዋል።

በዚህም በግልና በመንግስት የቴሌኮም አገልግሎት አቅራቢዎች የሞባይል አገልግሎት ደንበኞች ቁጥር 85 ሚሊዮን መድረሱን ተናግረዋል።

@sheger_press
@sheger_press


“ ህወሓት የፕሪቶርያውን ስምምነት በግልፅ በመጣስ ራያ ላይ ጦርነት ከፍቷል ” - የአላማጣና አካባቢው አመራር‼️
የትግራይ እና አማራ ክልሎች የይገባኛል ጥያቄ ከሚያነሱበት አንዱ በሆነው ራያ አላማጣ አካባቢ ትላንትና " ህወሓት " ተኩስ መክፈቱን፣ በዚህም በሰው ሕይወት ላይ ሞትና የአካል ጉዳት ሙድረሱን አካባቢውን ከሚያስተዳድሩ አመራሮች (ባለስልጣን) አንደኛው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

አንድ የአካባቢው አመራር (ባለስልጣን) ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል፣ “ ራያ ላይ  አዲስ ነገር አለ። ህወሓት የፕሪቶሪያውን ስምምነት በግልፅ በመጣስ ራያ ላይ ጦርነት ከፍቷል ” ብለዋል።

“ ቀን ላይ አንድ ሰው ሕይወቱ አልፏል። ሁለት ቆስለው ወደ ደሴ ሪፈር ተብለዋል። ደንበሩን በማለፍ የራያ አላማጣ ወረዳ አዳዲስ ቀበሌዎች ተቆጣጥሯል ” ሲሉ አክለዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ጦርነቱ የተከፈተው በምን ሰዓት ነው ? በዬት በኩል ነው የተከፈተው ? አሁን ተኩስ አለ ? በቁጥጥር ስር የሆኑት ቀበሌዎች እነማን ናቸው ? ከሰሞኑን ለጦርነት አመላካች ጉዳዮች ነበሩ ? ሲል ለአመራሩ ጥየቄ አቅርቧል።

አመራሩም ፣ “ ጦርነቱን የጀመሩት ሰኞ ሌሊት 6:00 አከባቢ ሲሆን፣ እስከ ቀን 6:30 ድረስ ነበር። መከላከያ ለራያ ምሊሻ ‘ወደ ኋላ ተመለሱ እነርሱም ይመለሳሉ’ በማለቱ ምክንያት ጦርነቱ ቁሞ የራያ ምሊሻ ወደ ኋላ ቢልም TDF መልሶ ቦታውን ተቆጣጥሮታል ” የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።

ተኩሱ የተጀመረበትን ልዩ ቦታ በተመለተ በሰጡት ምላሽም ፣ “ የተጀመረበት ቦታው ‘ጮጓራ’ ይባላል። የራያ አላማጣ ቦታ ነው። አሁንም እሱን በማለፍ ወደ ‘ኮስም’ የሚባል አከባቢ እየተጠጉ ነው። ተጨማሪ ኃይልም እያስጠጉ ይገኛሉ ” ብለዋል።

የአካባቢው አመራር የተኩሱን መነሻ በገለጹበት አውድ ፣ “ የዚህ ዋናው መንስኤ አማራ ክልል #ወልቃይት እና #ራያ በስርዓተ ትምህርቱ ካርታ ላይ ተካተዋል በሚል በወጣው መግለጫ ነው ” ሲሉ አስረድተዋል።

“ የራያ ህዝብ የዘመናት ትግሉ በህጋዊ መንገድ ፍትህ ማግኘት እንጂ ጦርነት አይፈልግም። እነሱ እየተከተሉ ደጋግመው እያቆሰሉት ነው ” ሲሉም አክለዋል።

በህወሓት ተከፈተ ስለተባለው ተኩስ በትግራይ ክልል በኩል እስካሁን በይፋ የተባለ ነገር የለም።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ በትግራይ ያሉ አስታዳዳሪዎችን አግኝቶ የነበረ ሲሆን ስብሰባ ላይ እንደሆኑና ወደ በኃላ ማብራሪያ እንደሚሰጡን ገልጸዋል።

የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ካቢኔ ሰሞኑን በሰጠው መግለጫ፣ “ የአማራ ክልል የትግራይ መሬት በካርታው በማስፈር የትምህርቱ ሰርዓቱ አካል በማድረግ እያስተማረበት ይገኛል " ማለቱ አይዘነጋም።

አስተዳደሩ ፤ በአማራ ክልል መንግሥት በኩል በትግራይ ህዝብ ላይ ግፍ እና በደል ሲፈፀም እንደቆየ አሁንም እንደቀጠለ ገልጾ ክልሉ የሰላም ስምምነቱን የሚያናጋ ጠብ አጫሪ ተግባራትን እየፈፀመ እንደሆነ ከሶ ነበር።

የፌደራል መንግስት በካርታው ላይ ምንም አይነት እርማት እንዳልሰጠ ፣ የአማራ ሕዝብም ሆነ ሌለው የኢትዮጵያ ህዝብ ከጊዚያዊ አስተዳደሩ ጎን እንዲቆሙ ይህ ሳይሆን ቀርቶ ለሚከተለው ነገር ሁሉ ግን የአማራ ክልል ሙሉውን ኃላፊነት ይወስዳል " ሲል አስጠንቅቆ ነበር።

@ethio_mereja_news


የኢትዮጵያ አወ‍እሮፕላን በሱማሌላንድ አየር ክልል እየበረረ በሌላ አቅጣጫ ሲመጣ ከነበረ የኤሚሬትስ አውሮፕላን ጋር ለሁለተኛ ጊዜ ከመጋጨት ለጥቂት ተርፏል ተባለ

በ 37,000 ጫማ ከፍታ ላይ ሲበር የነበረዉ የኤምሬትስ  አየር መንገድ በተመሳሳይ ርቀት ላይ ከነበረው ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ጋር በድጋሚ ከመጋጨት ለጥቂት መትረፍ ተሰማ።

ከሞቃዲሾ የአየር ትራፊክ ተቆጣጣሪዎች በተሰጠዉ ትዕዛዝ በተመሳሳይ የጫማ ከፍታ ላይ ሲበሩ የነበሩት ንብረትነታቸው የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ እና የኢትዮጵያ መንግስት የሆኑት አዉሮፕላኖች በድጋሚ ከመጋጨት አደጋ መትረፋቸው የሶማሌላንድ ሲቪል አቪዬሽን እና ኤርፖርቶች ባለስልጣን ማስታወቁን ዳጉ ጆርናል ሰምቷል። ባለፈው የካቲት ወር በተመሳሳይ አጋጣሚ የኢትዮጵያ እና የኳታር አየር መንገዶች ንብረት የሆኑ አውሮፕላኖች ከመጋጨት ለጥቂት መትረፋቸው ይታወሳል።

እሁድ መጋቢት 15 ቀን 2016 ዓ.ም. በ 37,000 ጫማ ከፍታ ላይ ሲበር የነበረዉ የኤምሬትስ አየር መንገድ አዉሮፕላን UAE722 እና በተመሳሳይ በ 37,000 ከፍታ ላይ ከነበረዉ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የበረራ ቁጥር ETH690 ለመጋጨት ጥቂት ደቂቃዎች ሲቀራቸዉ የሶማሊላንድ የአየር ትራፊክ ተቆጣጣሪዎች እና የኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላን አብራሪ ባደረጉት ጥረት አብራሪው በፍጥነት ከፍታውን በመቀየር ወደ 39, 000 ጫማ ከፍ እንዲል በማድረግ የተፈራው አደጋ ለጥቂት ሳይደርስ እንዲቀር አድርጓል።

በድጋሚ ለተፈጠረዉ ክስተት የሶማሌላንድ የሲቪል አቪዬሽን እና አየር ማረፉያዎች ባለስልጣን  የሞቃዲሾ ትራፊክ ተቆጣጣሪዎችን የወቀሰ ሲሆን።

መሰል ቸልተኝነት እና የእውቀት ማነስ ሞቃዲሾ በሚገኙ የሱማልያ የአቪዬሽን ባለሞያዎች በተደጋጋሚ እየተፈጠረ መሆኑን አለም ይወቅ ሲል አክሏል።

ሁኔታውም የአየር ደህንነትን አደጋ ላይ የሚጥል መሆኑን አፅንኦት በመስጠት ሁኔታውን ኮንኗል።

Via ካፒታል

@ethio_mereja_news


በድሬዳዋ ከተማ የሶስት አመቷን ህጻን አስገድዶ በመድፈር ገድሎ ተሰውሮ የነበረው ተጠርጣሪ በቁጥጥር ስር ዋለ

ግለሰብ በድሬዳዋ ከተማ መልካ ጀብዱ ተብሎ ከሚጠራው አካባቢ በፖሊስ ቁጥጥር ስር መዋሉን ፖሊስ አስታውቋል።

ተጠርጣሪው ግለሰብ ለአስራ አንድ ወራት ከህግ ተሸሽጎ እንደነበር የገለጸው የድሬደዋ ፖሊስ
ህጻን ቢሊሱማ መሃመድ የ3 ዓመት ታዳጊ ክፉን እና ደጉን በቅጡ ለይታ የማታውቅ መሆኑን ገልጿል፡፡

ተጠርጣሪው ግለሰብ  የእንጀራ አባቷ/ ሲሆን ይሄንን የጭካኔ በትር ከመሰንዘሩ በፊት
የቢሊሱማ መሃመድ እናት ከባለቤቷ ጋር በትዳር መቀጠል አልቻለችም በመሃከላቸው መግባባት ባለመኖሩ ተለያይተዋል።

የቢሊሱማ መሃመድ እናት ወደ ሀሮማያ ከተማ በመምጣት ሌላ ትዳር ትመሰርታለች። ለአጭር ቀናት ቢሆንም ቢሊሱማ መሃመድም በእንጀራ አባቷ ማደግ ግድ የሆነባት ሲሆን ተጠርጣሪው ግለሰብ /እንጀራ አባቷ/ አስከፊውን የወንጀል ደርጊት ፈጽሞ እስከተሰወረበት ቀን ድረስ አብራ በጋራ ትኖር ነበር ፡፡

መጋቢት 12 ቀን 2015 ዓ.ም ቀን ግን ተከሳሽ የሶስት ዓመት ህጻን ቢሉስማ አስገድዶ ከደፈራት በኃላ ህይወቷን በማጥፋት ከአካባው ይሰወራል፡፡
ግለሰብቡ ድርጊቱን በመፈጸም ከአካባቢው ተሰውሮ ድሬዳዋ መልካ ጀብዱ ተብሎ ከሚጠራው አካባቢ ለአስራ አንድ ወራት ተሸሽጎ መቆየቱን የመልካ ጀብዱ ፖስ ጣቢያ አዛዥ ም/ኮማንደር ሻምበል ተካኝ ተናግረዋል፡፡

ለአስራ አንድ ወራት ተሸሽጎ የቆየው ተጠርጣሪው ግለሰብ መጋቢት 10 ቀን 2016 ዓ.ም ጠዋት ከተሸሸገበት ወጥቶ ሲንቀሳቀስ ከህብረተሰቡ በደረሰ ጥቆማ ተጠርጣሪው ግለሰብ በቁጥጥር ስር ውሎ ለሀሮማያ ከተማ ፖሊስ ተላልፎ ተሰጥቷል፡፡

ተከሳሹ ግለሰብ/እንጀራ አባቷ/ ፍርድ ቤት ቀርቦ ለምን  ህጻን አስገድዶ በመድፈር ሊገላት እንደቻለ ሲጠየቅ ‹‹ሰይጣን አሳሳተኝ›› በማለት ምላሽ መስጠቱን ፖሊስ አስታውቃል፡፡

የድሬዳዋ ፖሊስ የልጄ ደም ፈሶ እንዳይቀር ስላደረገው ጥረት አመሰግናለሁ ያሉት የቢሊሱማ መሃመድ ወላጅ እናት ወ/ሮ ሮዳ በክሪ ልጄን አጥቼ በሃዘን ተቆራምጄ ባለሁበት ጊዜ የድሬዳዋ ፖሊስ የልጄን ገዳይ ስለያዘልኝ ምስጋና አቀርባለሁ ሲሉ ተደምጠዋል።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news


መርጌታ ቃለ ህይወት  የባህል መዳኒት ቀማሚ እና መስተፋቅር እንሰራልን በሁሉም ከተሞች ያላችሁ አናግሩኝ:

መርጌታ ቃለ ህይወት የባህል መድህኒት አስማት እና ጥበብ ይፈልጋሉ:
የምንሰጣቸው የጥበብ አገልግሎቶች ከዚህ በታች ተዘርዝረዋል
1 ለመፍትሔ ስራይ
2 ለህማም
3 ጋኔን ለያዘው ሰው
4 ቡዳ ለበላው
5 ለቁራኛ
6 የዛር ውላጅ ለተዋረሰው
7 ለአይነ ጥላ
8 ነገረ ራዕይ(ራዕይ የሚያሳይ)
9 ለዓቃቤ ርዕስ
10 ለመክስት
11 ለቀለም(ለትምህርት)
14 ለመስተፋቅር
15 ለሁሉ ሠናይ
16 ለገብያ
17 ለአምፅኦ ብእሲት(ፍቅረኛ ላጣ ወይም ላጣች የሚሰራ)
18 ለመድፍነ ፀር
19 ሌባ የማያስነካ
20 ለበረከት

ውድ  ቤተሰቦች  ለማንኛውም ነገር ያማክሩን    ከስላምታ ጋር።
ከምሰጣቸው በትንሹ ይህን ይመስላል 
ለጥያቄወ 09 75-90-23-15


ኢትዮጵያ ኮከብ ተጨዋቿን አጣች🕯

አዲሱ ሙሽራ ማረፉ ተሰምቷል 🕯

በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የባህርዳር ከነማው ድንቅ የአማካይ ተጨዋች አለልኝ አዘነ በድንገት ህይወቱ ማለፉ ተሰምቷል።

በቅርቡ የጋብቻ ስነ ስርዓቱን በቤተክርስቲያን የፈፀመው አዲሱ ሙሽራ ድንገት ዛሬ ለሊት ህይወቱ ማለፉ ተረጋግጧል ።

ለአርባምንጭ ታዳጊ ቡድን እስከ ዋናው፤ ለሀዋሳ ከተማና  አሁን ለባህርዳር ከተማ በሊጉ የሚጫወተው አለልኝ አዘነ  ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድንም ጥሪ ተደርጎለት አገልግሎት  ሰጥቷል።

አመለ ሸጋው ተጨዋች አለልኝ አዘነ ላለፉት ሁለት አመታት በጣና ሞገዶቹ ቤት አስደናቂ ብቃቱን በማሳየት ክለቡንና ሀገሩን እያገለገለ የሚገኝ ወጣት ተጨዋች ነበር። (ባላገሩ ቴሌቪዥን)

ኢትዮ መረጃ ለወዳጅ፣ ቤተሰቦቹና አድናቂዎቹ መፅናናትን ይመኛል። Rest In Peace🕯

@ethio_mereja_news


በድሬዳዋ ከተማ ሀዘን ላይ ከነበሩ ወላጆቿ ከ2 ሚሊዮን ብር በላይ የሚያወጣ ንብረት የዘረፈችው ግለሰብ  በቁጥጥር  ስር ዋለች!!

የካቲት 14 ቀን 2016 ዓ.ም  ከቀኑ 9 ሰዓት ላይ በድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ወረዳ አራት ልዪ ስሙ መብራት ሃይል  አብዩ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ሀዘን ላይ  ከተቀመጡ ወላጆቿ ከ2 ሚሊዮን ብር በላይ የሚያወጣ ንብረት  ዘርፋ ለማምለጥ  የሞከረችው ግለሰብ በቁጥጥር ስር ውላለች።

ወላጆቿ የስርቆት ወንጀል እንደተፈጸመባቸው ለፖሊስ አመልከተው የነበረ መሆኑን የአካባቢው  ፖሊስ ጣቢያ ወንጀል ምርመራ አስተባባሪ  ተወካይ ዋና ሳጅን ስንዱ ካሳሁን  ተናግረዋል።

ተከሳሿ ግለሰብ በአንድ ትምህርት ቤት አብሯት የሚማሩ ጓደኞቿን ከቤተሰቦቿ ንብረቱን እንዲዘርፉ በመንገር  እና ንብረቱን ሸጠው ከተማ ቀይረው የራሳቸውን ህይወት እንደሚመሩ አሳምናቸው  የነበረ መሆኑ ተጠቁሟል።

ቤተሰቦቿ ሀዘን ላይ ባሉበት ሰዓት ከጓደኛዋ ጋር ተባብራ በሳጥን ተቀምጦ  የነበረ ወድ የሆነ ጌጣጌጥ እና ንብረት ሰርቀው በደላላ አማካኝነት ወርቁን በማሽን አስፈትሸው አብሯት የሰረቀችውን ጨምሮ ሁለት ጎደኞቿን ወደ ሀረር ከተማ  የላከቻቸው መሆኑ ተረጋግጧል ።

ወላጆቿ ጉዳዩን ለፖሊስ ማመልከታቸውን ያወቀችው ልጅ ድርጊቱን መፈጸሟን ፖሊስ ጥርጣሬው ውስጥ  እንዳስገባት ስታውቅ  ድርጊቷን አምና ቃሏን  እንዲሁም ጎደኞቿ ያሉበት ቦታ ልታመለክት ችላለች ።

የድሬዳዋ ፖሊስ ከሀረሪ ፖሊስ ጋር በመነጋገር ባደረገው ጠንካራ ክትትል  በሀረር ከተማ ሆቴል ውስጥ ተከራይተው  በቁጥጥር  ስር ሊውሉ መቻላቸውንና  መዝገቡም እየተጣራ እንደሚገኝ  ዋና ሳጅን ስንዱ ካሳሁን ተናግረዋል።

@sheger_press
@sheger_press


መልካም ዜና ለአንባብያን በሙሉ‼️

የሴራ እርካብ!!
የደም መንበር‼️

በታተመ በጥቂት ቀናት ውስጥ በ #Amazon ላይ በከፍተኛ ሁኔታ ሲሸጥ የነበረው የጋዜጠኛ ያየሰው ሺመልስ መፃፍ እኛ ጋር በpdf ያገኙታል።

ለጥቂት ቀናት በሚቆይ ልዩ ቅናሽ ከኛ ይሸምቱት

መፃፉን ለመግዛት በዚ
አድራሻ ያነጋግሩን 👉 @ethio_journalist


New_No_repayment_alphabet_593858077e.pdf
339.6Кб
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የወሰዱትን ገንዘብ አልመለሱም ያላቸውን 565 ሰዎች ስም ዝርዝር ይፋ አድርጓል ከታች ያለውን አታችመንት ይመልከቱ።

👆🏼👆🏼👆🏼👆🏼

@sheger_press


ለባንክ ጥበቃ የተረከበውን መሳሪያ  ይዞ የተሰወረው ግለሰብ በቁጥጥር ስር ዋለ

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጰያ ካፋ ዞን ጊምቦ ወረዳ ኡፋ ከተማ ታህሳስ 23 ቀን 2016 ዓ.ም ከምሽቱ 2:00 ሰዓት የተሰጠዉን ኃላፊነት ወደጎን በመተዉ  በጥበቃ ሰራተኝነት ከሚሰራበት ቦታ መሳሪያ ይዞ የተሰወረው ግለሰብ በቁጥጥር ስር መዋሉን የዞን ፖሊስ አስታውቋል፡፡

በደብቡ ምዕራብ  ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ፖሊስ ኮሚሽን የህዝብ ግንኙነት እና ኮሚኒኬሽን ዳይሬክተር  ምክትል ኢንስፔክተር ደጀኔ አሰፋ ለብስራት ሬዲዮ እና ቴሌቪዥን እንደተናገሩት በዳሸን ባንክ የጥበቃ ሰራተኛ ሆኖ በሚሰራበት ቦታ  ለጥበቃ ስራ አገልግሎት ተሰጥቶት የነበረዉን አንድ ክላሽ ከመሰል 30 ጥይትና ከአንድ ካርታ ጋር ተረክቦ የነበረው ይዞ መሰወሩ ተገልፆል፡፡

የካፋ ዞን ዐቃቤ ህግ መምሪያ የሙስና ነክ ወንጀሎች ተከሳሽ አንዱአለም ብረሃኑ የማይገባ ጥቅም ለማግኘት በማሰብ በፈፀመዉ በስራ ተግባር የሚፈፀም የመዉሰድና የመሰወር ወንጀል ክስ መሰርቶበታል።የካፋ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤትም የክስ መዝገቡን ሲመለከት ቆይቶ ተከሳሹ በፈፀመው የሙስና ወንጀል በሰዉ እና በኤግዚቢት ማስረጃ  በመረጋገጡ የጥፋተኝነት ብይን አስተላልፏል ።

በዚሁ መሰረት የካፋ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ሰሞኑን ባስቻለዉ የችሎት ተከሳሽ አንዱአለም ብረሃኑ በ1 ዓመት እስራትና በአንድ ሺህ ብር የገንዘብ መቀጮ እንዲቀጣ ተወስኖበታል ሲሉ  ምክትል ኢንስፔክተር ደጀኔ አሰፋ ለብስራት ሬዲዮ እና ቴሌቪዥን ተናግረዋል፡፡

@ethio_mereja_news


የሰአቱ መደመጥ ያለበት መረጃ👇👇
https://youtu.be/GX7O1m9fR2w?si=jrxvHchyWupYiKWp


አሳዛኝ ዜና‼️

በምዕራብ አርሲ ዶዶላ ከተማ ላይ ትላንት ማታ 3:00 አከባቢ የሸኔ ታጣቂዎች አንድ ካህንን ከእነቤተሰቡ እንዲሁም ካገባ ገና ሶስት ወር እንኳ ያልሞላውን ዲያቆን እና አብራው ስትኖር የነበራቸውን እህቱን በአሰቃቂ ሁኔታ ገድለዋቸው ሄደዋል ተብሏል።
ከሁለቱ ቤተሰቦች አጠቃላይ ሰባት ሰዎችን ገድለዋቸው ሄደዋል ብለዋል። አንድ ህፃን እንደ አጋጣሚ ያለቤተሰብ ቀርታ ተርፋለች ብለዋል። ከዚህ በተጨማሪ ለስራ ከሲዳማ ክልል የመጡ አራት ወጣቶችም ተገድለዋል ብለዋል። አጠቃላይ 11 ሰው ሞቷል ብለዋል።ጥቃቱ የተፈፀመው ከገብረክርስቶስ ቤተክርስቲያን 50ሜርቀት ላይ ነው ብለዋል። ግድያውን የፈፀሙት በቢለዋና በጥይት ነው ሲሉ የአዩዘሀበሻ ምንጮች ተናግረዋል(አዩዘሀበሻ)።
ነፍስ ይማር❗

@ethio_mereja_news


በበላይነህ ክንዴ ግሩፕ የተገጣጠሙ የመጀሪያዎቹ በኤሌክትሪክ ሀይል የሚሠሩ የህዝብ ማመላለሻ አውቶብሶች በአዲስ አበባ አገልግሎት መስጠት ጀመሩ!!

አውቶብሶቹን ወደ ስራ ያስገባው በቅርቡ 20 በኤሌክትሪክ ሀይል የሚሠሩ ሚኒባሶችን ወደ ስራ ያስገባው በበላይነህ ክንዴ ግሩፕ እህት ድርጂት ቬሎሲቲ ኤክስፕረስ ነው። ዛሬ ስራ የጀመሩት አውቶብሶች መነሻቸው ቦሌ ሲሆን መዳረሻቸው በእስጢፋኖስ አራት ኪሎ ስድስት ኪሎ ሽሮ ሜዳ ነው።

@ethio_mereja_news

Показано 20 последних публикаций.