Фильтр публикаций


በ #ባሌሮቤ የ5G አገልግሎትን ማስጀመራችንን ተከትሎ ከውድ ደንበኞቻችን ጋር በአዝናኝ የመንገድ ላይ ትርኢት እና ኮንሰርት የነበረን ደማቅ የአብሮነት ቆይታ!

የባሌ ሮቤ ከተማ ነዋሪዎች፣ የከተማዋ  አስተዳድር እና የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች ለ5ጂ መርሐ ግብራችን ድምቀት እና ስኬት ስላደረገላችሁልን ትብብር ልባዊ ምስጋናችንን እናቀርባለን፡፡

#5G #ባሌሮቤ

#ዲጂታል_ኢትዮጵያን_ዕውን_በማድረግ_ላይ

#5G #BaleRobe #Ethiotelecom #telebirr #DigitalAfrica #DigitalEthiopia #RealizingDigitalEthiopia


ሚያዝያን ለኒያ ፋውንዴሽን ጆይ ኦቲዝም ማዕከል!!

በዚህ ወር በማኅበራዊ ትስስር ገፆቻችን በሚቀላቀሉ አዲስ ተከታዮች ብዛት ልክ 30 ብር እንዲሁም በሚጋሩ Share ልክ 10 ብር ለኒያ ፋውንዴሽን ጆይ ኦቲዝም ማዕከል እንለግሳለን!

🤝 እርስዎም ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገፆቻችንን ይከተሉ፤ ፖስቶቻችንን ያጋሩ፤ ለወገን ድጋፍ ይተባበሩ!

ቴሌግራም | ፌስቡክ | ኢንስታግራም | ሊንክዲን | ዩትዩብ | ቲክቶክ

በተጨማሪም በቴሌብር ሱፐርአፕ https://bit.ly/telebirr_SuperApp ለበጎ አድራጎት በሚለው አማራጭ የፈቀዱትን የገንዘብ መጠን በመለገስ ለወገንዎ ተስፋ ይሁኑ!

🙏 ዘላቂ የጋራ ማኅበራዊ ኃላፊነት ለወገን ብሩህ ተስፋ!


#MatchingFundForSustainableFuture
#Ethiotelecom #telebirr #DigitalAfrica #DigitalEthiopia #RealizingDigitalEthiopia

9.1k 0 11 36 44


12k 0 5 29 59

የመግቢያ ትኬትዎ መኪና ያሸልምዎታል!!

#ቴሌብር_አዲስ_ነገር_እስከ_ፋሲካ_ኤክስፖ_2017 የመግቢያ ትኬትዎን በቴሌብር ሲቆርጡ:-

🚘 NETA AYA 2024 ዘመናዊ የኤሌክትሪክ መኪና
🏍 Dodai የኤሌክትሪክ ሞተር ሳይክል
📱 ስማርት ስልኮች
የሚያሸልም የዕጣ ቁጥር ይደርስዎታል።

❇️ ልጆጲያ (Kidzopia): ለሕጻናት ልዩ መዝናኛ እና ትምህርታዊ ፕሮግራሞች
❇️ የጾም ፌስት: የጾም ብፌ በ150 ብር ብቻ

💁‍♂️ በተጨማሪም በቴሌብር ያሻዎትን ሲገበያዩ እስከ ብር 2500 ላለው 10% ተመላሽ ያገኛሉ!

ቴሌብር ሱፐርአፕን https://bit.ly/telebirr_SuperApp ወይም *127# ይጠቀሙ!

📍 በኤግዚቢሽን ማዕከል


ቴሌብር - እጅግ ቀላል፣ ፈጣን፣ ምቹ እና አስተማማኝ!

#Ethiotelecom #telebirr #DigitalAfrica #DigitalEthiopia #RealizingDigitalEthiopia


ኢትዮ ቴሌኮም 114 ተጨማሪ ከተሞችን የ4ጂ ኤል.ቲ.ኢ አድቫንስድ ኔትወርክ ተጠቃሚ አደረገ!

ኢትዮ ቴሌኮም በባሌ ዞን፣ አርሲ ዞን፣ ምስራቅ ባሌ ዞን፣ ምዕራብ አርሲ ዞን እና ምስራቅ ሸዋ ዞን በሚገኙ 114 ተጨማሪ ከተሞች የላቀ ፍጥነት ያለው የ4ጂ ኤል.ቲ.ኢ አድቫንስድ ሞባይል ኔትወርክ አገልግሎት ተጠቃሚ ማድረጉን በታላቅ ደስታ እንገልጻለን!

ኩባንያችን ሲያከናውን የነበረውን መጠነ ሰፊ የ4ጂ ኤል.ቲ.ኢ አድቫንስድ ኔትወርክ ማስፋፊያ ፕሮጀክት በማጠናቀቅ በደቡብ ምስራቅ ሪጂን 58 እንዲሁም በደቡብ ደቡብ ምስራቅ ሪጂን 56 በድምሩ 114 ከተሞችን የአገልግሎቱ ተጠቃሚ አድርጓል።

ይህን ያበሰረው በትላንትናው ዕለት የባሌ ሮቤና የአርሲ ከተሞች የ5ጂ ኔትወርክ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ላይ ነው፡፡ በዚህም ወቅት የ4ጂ ኤል.ቲ.ኢ አድቫንስድ ኔትወርክ የላቀ ፍጥነት ያለው የኢንተርኔት ግንኙነትን እውን በማድረግ አዳዲስ ዕድሎችን በመክፈት ለአካታች የዲጂታል ኢኮኖሚ እድገት የላቀ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው ተብራርቷል።

ኢትዮ ቴሌኮም የላቀ የኢንተርኔት ፍጥነት በመላ ሀገራችን በማስፋፋት አካታች የዲጂታል ኢኮኖሚ በመገንባት ረገድ የበኩሉን ሚና መጫወቱን አጠናክሮ ይቀጥላል፡፡

ዲጂታል ኢትዮጵያን እውን በማድረግ ላይ!

የከተሞቹን ዝርዝር ይመልከቱ፡ https://bit.ly/4lmShKp

#RealizingDigitalEthiopia #4GLTEAdvanced #BaleRobe #Assela


ኢትዮ ቴሌኮም ደቡብ ደቡብ ምስራቅ የተሰኘ አዲስ ሪጅን በማቋቋም ዋና ሥራ አስፈጻሚያችን፣ የባሌ ዞን አስተዳደር፣ የባሌ ሮቤ ከተማ መስተዳደር ኃላፊዎች እና የሀገር ሽማግሌዎች በተገኙበት አስመረቀ!

የደቡብ ደቡብ ምስራቅ ሪጅን ጽ/ቤት መቀመጫውን ባሌ ሮቤ ከተማ ያደረገ ሲሆን 3 የአስተዳደር ዞኖችን (ባሌ ዞን፣ ምስራቅ ባሌ ዞን እና ምዕራብ አርሲ ዞን በከፊል)፣ 29 ወረዳዎችን፣ 38 ከተሞችን እና 471 የገጠር ቀበሌዎችን ያካትታል፡፡

ቀደም ሲል የደቡብ ምስራቅ ሪጅን ጽ/ቤት መቀመጫነቱን አዳማ በማድረግ ለበርካታ አካባቢዎች አገልግሎት በመስጠት ላይ የነበረ ሲሆን በተለይም በቅርቡ አዳዲስ የ4ጂ ኤል.ቲ.ኢ አድቫንስድ ሞባይል ጣቢያዎችን ገንብተን ስራ ማስጀመራችን ለተጨማሪ ሪጅን መቋቋም አስቻይ ሁኔታ ፈጥሯል፡፡

ይህም ደንበኞችን በቅርበት ከማስቻል ባሻገር፣ ከዜጎች ለሚነሱ ጥያቄዎች ፈጣን ውሳኔዎችን በመስጠት ቀልጣፋ አገልግሎት ለመስጠት ያስችላል፡፡ እንዲሁም ከአጋሮች ጋር በቅርበት በመስራት የማህበረሰቡን ህይወት በሚያሻሽሉ የዲጂታል መፍትሄዎችን አካታች የዲጂታል ኢኮኖሚ ለመገንባት ቁልፍ ሚና ይኖረዋል፡፡

ለተጨማሪ መረጃ፡ https://bit.ly/3G2T17e



Показано 7 последних публикаций.