Фильтр публикаций




ገንዘብ እንዲከፍል የተወሰነበት የፍርድ ባለእዳ አፈጻጸም መዝገብ ሳይከፈት ገንዘቡን በፍርድ ባለመብት የባንክ አካውንት ቢያስገባ እና አፈጻጸሙ ሲጀመር የፍርድ ባለእዳ የተከፈለኝ ገንዘብ የለም ብሎ ቢከራከር አፈጻጸሙን የያዘው ፍርድ ቤት ገንዘቡ ከፍርድ ቤት ውጭ ተከፍሏል አልተከፈለም የሚለውን ማጣራት አለበት ከታች ያለው ውሳኔ

እዚህ ጋር የሚነሳው በሰበር መዝገብ ቁጥር 98263 ቅጽ 17 ላይ በፍርድ የተወሰነን ነገር በእርቅ ጨርሰናል ብሎ ፍርዱን ለማስለወጥ እርቁ ፍርድ ቤት ቀርቦ መመዝገብ እንዳለበት;ይህም መደረግ ያለበት በፍርድ የተገኘን መብት ፈጽሚያለው አልፈጸምኩም በሚል መቋጫ የሌለው ክርክር ስለሚከፍት ነው ከሚለው የሰበር አቋም ጋር እንዴት ይታያል


ሰ.መ.ቁ 235053 መጋቢት 29 2015ዓ.ም
====================
ካርታ ይሰረዝልኝ እንዲሁም ንብረት የጋራ መሆኑ በፍርድ እንዲረጋገጥልኝ በሚል የቀረበ የዳኝነት ጥያቄ ከአስተዳደር ስነ-ስርዓት አዋጅ ቁጥር 1183/2012 አንቀጽ 44 እና 49 ከደነገጉት እንዲሁም የፌዴራል ጠቅላይ ፍ/ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በመ.ቁ 220042 እና በመ.ቁ 220582 ከሰጠው የህግ ትርጉም አንጻር ሲታይ ከካርታ ይሰረዝልኝ በተጨማሪ የንብረት ባለቤትነት በፍ/ቤት ውሳኔ እንዲረጋገጥ ዳኝነት የተጠየቀበት በመሆኑ ጉዳዩን የማየት የዳኝነት ስልጣን ያለው [የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የአስተዳደር ችሎት ሳይሆን] የፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት ነው።
👇👇👇⚖️
https://t.me/ethiolawtips


በሕጋዊ ይዞታ ላይ የተፈጠረ የሁከት ድርጊት እንዲወገድ በቀረብ ክስ ላይ ጣልቃገቦች ከሁከቱ ወጭ አዲስ የዳኝነት ክርክር ማቅርብ የማይችሉ እና እራሱን ችለው መክሰሰ የሚገባ ሰለመሆኑ የተወሰነ
====================
በሕጋዊ ይዞታ ላይ የተፈጠረ የሁከት ድርጊት እንዲወገድ ባቀረበው ክስ ላይ መውጫ ተዘግቶብናል በማለት ያቀረቡት የጣልቃገብነት ክርክር አብሮ ተስተናግድ የአመልካችን ክስ ውድቅ መደረጉ ተገቢ አለመሆኑ ።በመሠረቱ በፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 1149 መሠረት ሁከት እንዲወገድ እና መውጫ መግቢያ ተከልክለናል በማለት የሚቀርበው ክስ ደግሞ በቀጥታ የሚመለከተው የንብረት አገልግሎት ስለመሆኑ ከፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 1221 ድንጋጌ ይዘት መገንዘብ ይቻላል።
👇👇
https://t.me/ethiolawtips


ከወንጀሉ ክብድትና ቅጣት አንፃር ተከሳሹ ዋስትና መብቱ ቢጠበቅ ተመልሶ የሚመጣ አይመስለኝም በማለት በወ/ሰ/ሰ/ህ/ቁ 67(ሀ) መሰረት የዋስትና ግዴታውን አያከብርም በሚል ጥያቄ ላይ ሰበር በቂና ምክንያታዊ ህጋዊ ማስረጃ ሳይቀርብ ከወንጀሉ ክብደት ብቻ በመነሳት ዋስትናው ሊገደብ አይገባም በማለት አስገዳጅ የህግ ትርጉም
በወ/ስ/ስ/ህ/ቁ 67(ሀ) ሰ/መ/ቁ 269430 በቀን 29/02/2017 ዓም ሰጥቷል
https://t.me/ethiolawtips


የነበረን ቤት ባለበትም ሆነ አፍርሶም ማደስ ከፍ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ 1179 ድንጋጌ አንፃር አንድ ሰው በሌላ ሰው ይዞታ ላይ ባለይዞታው ሳይቃወም ቤት ቢሰራ የተሰራው ቤት ባለቤት እንደሚሆን ከተደነገገው ጋር የሚገናኝ አይደለም።ስለዚህ ቤቱን አፍርሶ ስለሰራ ወይም አድሶ ስለሰራ ባለይዞታ ሳይቃወም አፍርሼ የሰራሁት ወይም ያደስኩት ቤት በመሆኑ የቤቱ ባለቤት ነኝ ለማለት አይቻልም።ሲል የፌ/ሰ/ሰ/ፍ/ቤት በሰ/መ/ቁ 222277 አስገዳጅ የህግ ትርጉም ሰጥቷል።
👇👇??🔥
https://t.me/ethiolawtips



Показано 7 последних публикаций.