Lawyer_Henok Taye⚖️Ethio Law🥇ኢትዮ ሕግ


Гео и язык канала: Эфиопия, Английский
Категория: Право


ስለቤተሰብ ሕግ ፣ስለንግድ ሕግ፣ስለወንጀል ሕግ፣ስለውርስ ሕግ፣ስለውል ሕግ ፣የሰበር አስገዳጅ የሕግ ትርጉሞች የሚያገኙበት ቻናል ነው።
ለጥያቄ እና አስተያየት @lawyerhenoktaye
📞 0953758395 ☎️LL.B)LL.M)
🔔 👇ሌሎች አማራጮችን ለማግኘት
🛑 https://linktr.ee/lawyerhenok?
Youtube 🔥 https://youtu.be/5cnK4gX2Mrg

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Английский
Категория
Право
Статистика
Фильтр публикаций




በማህበራዊ ሚዲያ #በፍትህ_ዘርፍ ላለፋት ዓመታት ለማህበረሰቡ ህግን በማሳወቅ የህግ መረጃን በመስጠት በTelegram,Facebook,Tiktok,youtube,instagram ላይ አስተዋፅኦ ካደረጉ መካከል ተወዳዳሪ እንድሆን በምርጫ ውስጥ ተካትቻለሁ ። ስለሆነም በዚህ ሊንክ ባለው bot ገብታችሁ ከተዘረዘሩት ውስጥ #በፍትህ_ዘርፍ በሚለው ስር የእኔን ስም " #Lawyer_Henok_Taye " ብለው በመፃፍ መምረጥ እንደሚችሉ ለማሳወቅ እወዳለሁ ።
👇⚖️ይህን ሊንክ በመጫን ስሜን ይፃፋ
@BestSocialMediaBot


ለሕዝብ ጥቅም ሲባል የመሬት ይዞታ የሚለቀቅበት፣ ካሳ የሚከፈልበትና ተነሺዎች መልሰው የሚቋቋሙበትን ሁኔታ ለመወሰን የወጣውንና በሥራ ላይ ያለውን አዋጅ ቁጥር 1161/2011 የሚያሻሽል ረቂቅ አዋጅ ከሰሞኑ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ስለመቅረቡ ሪፖርተር ጋዜጣ መጋቢት 29 ቀን 2016 ዓ/ም ባወጣው እትሙ አስነብቧል።

ማሻሻያ ከሚደረግባቸው ጉዳዮች መካከል

1. በፌዴራል መንግሥት ለሚከናወኑ ፕሮጀክቶች የልማት ተነሺ ዜጎች የሚደረግላቸው የካሳ ክፍያዎች በክልል መንግሥታት እንዲፈጸሙ
2. የንብረት ካሳ፣ የልማት ተነሺ ድጋፍ፣ የኢኮኖሚ ጉዳት ካሳ፣ የማኅበራዊ ትስስር መቋረጥና የሥነ ልቦና ጉዳት ካሳ ጋር ተያይዞ የሚነሱ እንዲሁም የፌዴራል መንግሥቱ በሚያከናውናቸው ፕሮጀክቶች ጋር በተያያዘ የሚደረጉ የፍርድ ቤት ክርክሮች በሚኖሩ ጊዜ፣ ፕሮጀክቱን የሚያከናውነው የፌዴራል መንግሥቱ ተቋም ዋና መሥሪያ ቤት በሚገኝበት ሥፍራ ባለ የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ጉዳዩ እንደሚታይ ተደንግጓል።
3. እንዲሁም የፌዴራል መንግሥት ተቋምን የባንክ ሒሳብ ማገድ ወይም ከአፈጻጸም ጋር በተያያዘ የፌዴራል መንግሥት ተቋማት ከፍተኛ አመራሮች ተገደው ፍርድ ቤት እንዲቀርቡ፣ በቀጥታ ከፌዴራል መንግሥት ተቋማት የባንክ ሒሳብ ክፍያ እንዲፈጸም የሚያስገድዱ በፍርድ ቤት የሚሰጡ ትዕዛዞች በፌዴራሉ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት ዕውቅና ሳይኖራቸው ሊሰጡ እንደማይገባቸውም በረቂቅ አዋጁ ተካቷል።

በጋዜጣው በቀረበው ልክ የሚከተለውን ትችቴን አቀርባለሁ።

1. በፌዴራል መንግሥት ለሚከናወኑ ፕሮጀክቶች የልማት ተነሺ ዜጎች የሚደረግላቸው የካሳ ክፍያዎች በክልል መንግሥታት እንዲፈጸም የሚደነግግ የማሻሻያ ድንጋጌ ክልሎች ካሣን ከራሳቸው በጀት መክፈል እንዳለባቸው የሚገልጽ ነው። ከዚህ ጋር በተያያዘ የንብረት ካሳ፣ የልማት ተነሺ ድጋፍ፣ የኢኮኖሚ ጉዳት ካሳ፣ የማኅበራዊ ትስስር መቋረጥና የሥነ ልቦና ጉዳት ካሳ ጋር ተያይዞ የሚነሱ ክርክሮች በፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት እንዲታይ የተባለበት አግባብ መመለክት ያስፈልጋል። ከራሱ በጀት ካሣን በሚከፍለው ክልል እና ካሣው አነሰኝ በሚል በዚያው ክልል በሚኖር ባለይዞታ መካከል የሚነሳ ክርከር የክልል ጉዳይ(state matter) በመሆኑ ለመዳኘት የመጀመሪያ ደረጃ የዳኝነት ሥልጣን ሊኖረው የሚገባው የክልሉ ፍ/ቤት መሆን አለበት። ክልል በከፈለው ካሳ የሚነሳን ክርክር የፌዴራል ፍ/ቤት የመጀመሪ ደረጃ የዳኝነት ሥልጣን እንዲኖረው ማድረግ በክልል ጉዳይ(state matter) ጣልቃ እንደመግባት የሚቆጠር ሲሆን ይህም ክልሎች እራሳቸውን በራስ የማስተዳደር (autonomy) ሕገ መንግስታዊ መርሕ የሚጻረር ነው። ስለሆነም ጉዳዩን የፌዴራል ፍ/ቤት እንዲያየው ተሻሽሎ የቀረበው የአዋጁ ክፍል መቅረት ያለበት ሲሆን ሥልጣኑ የክልል ፍ/ቤቶች ነው ተብሎ መደንገግ አለበት።
2. ሌላው ከፕሮጀክቱ ጋር ተያይዞ የሚነሱ ክርክሮች ፕሮጀክቱን የሚያከናውነው የፌዴራል መንግሥቱ ተቋም ዋና መሥሪያ ቤት በሚገኝበት ሥፍራ ባለ የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ስለመሆኑ የተገለጸው ነው። እንደሚታወቀው የፌዴራል መንግሥት ተቋም ዋና መሥሪያ ቤቶች የሚገኙት አዲስ አበባ ነው፡፡ ስለዚህ ተከራካሪዎች በሁሉም ጉዳይ ጉዳይ ክስ ለማቅረብ አዲስ አበባ መምጣት አለባቸው። ለምሳሌ ሠመራ ከተማ ከሚሰራ የፌዴራል መንግስት የመንገድ ፕሮጀክት ሥራ ጋር በተያያዘ የ20000 ብር ክስ ለማቅረብ የፈለገ ሰመራ የሚኖር አንድ ሰው አዲስ አበባ መምጣት እና ክስ ማቅረብ ሊኖርበት ነው፡፡ ከዚህ ይልቅ ሰመራ የሚገኘኝ የክልል ፍ/ቤት ጉዳዩን በውክልና እንዲያይ ቢደረግ አዲስ አበባ መምታት ሳይጠበቅበት እዚያው ፍትሕን ያገኛል። ይህም የፍትሕ ተደራሽነት (access to justice) መርህ አንጻር መታየት ያለበት ነው። በሌላ በኩል ሁሉንም ጉዳይ የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት እንዲያየው ማድረግ ፍ/ቤቱ ላይ አላስፈላጊ የሥራ ጫና ያስከትላል። ስለሆነም በፌዴራል ፍ/ቤቶች አዋጅ ቁጥር 1234/13 በተደነገገው መሠረት የተወሰነውን ጉዳይ የክልል ፍ/ቤቶች በውከልና እንዲያዩት ማድረግ ፍትህ ፈላጊው ሕብረተሰብ በአከባቢው እንዲዳኝ የሚያደርግ ጊዜና ወጪ ቆጣቢ እንዲሁም የዜጎችን እንግልት የሚቀንስ በመሆኑ ተሻሽሎ የቀረበው የአዋጁ ክፍል ቀርቶ በፌዴራል ፍ/ቤቶች አዋጅ ቁጥር 1234/13 መሠረት በውከልና መመራት ያለበት ነው።
3. የፌዴራል መንግሥት ተቋምን የባንክ ሒሳብ ማገድ ወይም ከአፈጻጸም ጋር በተያያዘ የፌዴራል መንግሥት ተቋማት ከፍተኛ አመራሮች ተገደው ፍርድ ቤት እንዲቀርቡ፣ በቀጥታ ከፌዴራል መንግሥት ተቋማት የባንክ ሒሳብ ክፍያ እንዲፈጸም የሚያስገድዱ በፍርድ ቤት የሚሰጡ ትዕዛዞች በፌዴራሉ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት ዕውቅና ሳይኖራቸው ሊሰጡ አይገባም የሚል ነው። ዳኞች የዳኝነት ተግባራቸውን በሙሉ ነጻነት ያከናውናሉ በማለት በኢፌዴሪ ሕገ-መንግስት አንቀጽ 79 (3) ተደንግጓል። አንድ ዳኛ በመዝገብ ላይ የዕግድም ሆነ የክፍያ ትዕዛዝ ያለ ፍ/ቤቱ ፕሬዚዳንት ዕውቅና ሊሰጥ አይገባም ማለት ያልተገባ ጣልቃ ገብነት ሲሆን ከላይ የተገለጸው የዳኝነት ነጻነት የህገ መንግስታዊ መርሕ የሚጋፋ ነው። በተጨማሪም የፍ/ቤት ፕረዚዳንቶች አስፈጻሚ አካላትን በመፍራት ከላይ የተዘረዘሩ ጥያቄዎች ተቀብለው የመስጠት እድላቸው ከዳኞች ይልቅ ጠባብ ስለመሆኑ አሁን ካለው ነባራዊ ሁኔታ መረዳት ይቻላል። ማለትም ዳኞች ከፕረዝደንቶች ይልቅ የተሻለ ነጻነት ያላቸው በመሆኑ እንዲሁም ፕረዝደንቶች በስብሰባና በሌሎች አስተዳደራዊ ሥራዎች የሚጠመዱ በመሆናቸው ይህንን ጉዳይ ዳኛው ብቻ አይቶ እንዲወስን ማድረግ ፍትሕ ፈላጊው ሕብረተሰብ የተፋጠነ አገልግሎት እንዲያገኝ ይረዳዋል። ስለሆነም ከላይ የተዘረዘሩ ትዕዛዞችን ለመስጠት የፍ/ቤቱ ፕሬዚዳንት ዕውቅና ሊሰጥ ይገባል ተብሎ ተሻሽሎ የቀረበው የአዋጁ ክፍል ሊቀር ይገባል።
4. በአጠቃላይ ረቂቅ አዋጁ ከዜጎች የተፋጠነ ፍትሕ የማግኘት መብት ከማስከበር ይልቅ ለፌዴራል መንግስት ጥቅም ያጋደለ በመሆኑ ለክልል መንግሥታት፣ በየደረጃው ላሉ ኃላፊዎች፣ ለባለድርሻ አካላትና ለሕዝቡ ቀርቦ ውይይት በሚደረግበት ወቅት ይህ ሀሳብ ቢነሳ አዋጁን በተሻለ መልኩ ያዳብረዋል የሚል እምነት አለኝ።
ፋንታሁን አየለ






የፍትሐብሔር ክስ አዘገጃጀት እና በክሱ ላይ መገለጽ የሚገባቸው ነገሮች ከፍ/ሥ/ሥ/ህ/ቁ 222-225
==============================
በአንድ ክርክር የሚዘጋጀው ክስ የአንድን ሰው መብት ማስገኘትም ማሳጣትም ይችላል። የከሳሽ ሀሳብ ግልጽ ካልሆነ ለፍርድ ቤት የተጠየቀውን ዳኝነት በአግባቡ የማይገልጽ ከሆነ ማግኘት የሚገባውን መብት ያሳጣል። አንድ ክርክር ስኬታማ እንዲሆን የሚዘጋጀው ክስ ወሳኝነት አለው። በመሆኑም ከዚህ ቀጥሎ ያሉት አንድ ክስ ስዘጋጅ መያዝ የሚገባቸው ነገሮች ናቸው:-
1. #በክስ ጽሑፍ ላይ ስለሚሰፍሩ ነገሮች
⨳ማናቸውም የክስ ጽሑፍ ከዚህ ቀጥሎ የተመለከቱን ነገሮች የያዘ መሆን አለበት፡፡
⨳ክሱ የሚቀርብለት ፍርድ ቤት የሚያስችልበትን ቦታና ስሙን፡፡
⨳የክሱን አርዕስት፡፡
⨳የከሳሹንና የተከሳሹን ሥም ልዩ መግለጫውን የሚኖርበት ⨳ቦታና መጠሪያው የሚሰጥበትን አድራሻ፡፡
⨳ከሳሽ ወይም ተከሳሽ በሕግ ችሎታ የለውም የተባለ ሲሆን ይህንኑ መግለጽ፡፡
⨳ከሳሹ ክስ የሚያቀርበው በጠበቃነት በነገር ፈጅነት ወይም በወኪልነት እንደሆነ ክሱን ለማቅረብ ያለውን ሥልጣን መግለጽ፡፡
⨳ለክሱ ምከንያት የሆትን ነገሮችና እነዚሁም የተፈጠሩበት ጊዜና ስፍራ፡፡
⨳ፍርድ ቤቱ ነገሩን ለመቀበል ሥልጣን ያለው ስለመሆኑ የሚያስረዳውን ሁኔታ፡፡
⨳ተከሳሹ ለክሱ ምክንያት በሆነው ነገር ውስጥ አግባብ እንዳለው ወይም ተጠሪ የሚሆንበትን ምክንያት ወይም ለሚቀረበው ክርክር በአላፊነት የሚጠየቅበትን ሁኔታ፡፡
⨳አስፈላጊ በሚሆንበት ጊዜ ለክሱ ምክንያት የሆነውን ነገር ግምት፡፡
⨳መንግስት የሚከስበት ወይም የሚከሰስበት ጉዳይ ሲሆን ከዚህ በላይ እንደተነገረው ዝርዝር ነገር መስጠት አስፈላጊ አይሆንም ነገር ግን የከሳሹን ወይም የተከሳሹ መስሪያ ቤትና የባለስልጣኑ ስም ብቻ መግለጽ በቂ ነው፡፡
2.#ከክስ ማመልከቻ ጋር ተያይዘው ስለሚቀርቡ ጽሑፎችና መግለጫዎች
⨳ከሳሹ ከሚያቀርበው የክስ ማመልከቻ ጋር ከዚህ ቀጥሎ የተመለከቱትን ነገሮች አያይዞ ማቅረብ አለበት፡፡
⨳ክርክሩ በሚሰማበት ጊዜ ምስክር ይሆኑኛል የሚላቸውን ሰዎች የስም ዝርዝር ከነ አድራሻው፤የሚጠሩበትን ምክንያት እንዲሁም ማስረጃ ይሆኑኛል የሚላቸውን ጽሑፎች ጽሑፎቹም በእጁ የማይገኘ ሲሆኑ የሚገኙበትን ስፈራና በማን እጅ እንደሚገኙ በመግለጽ አያይዞ ካቀረበው ዝርዝር በቀር ሌላ አስረጅ ወይም ማስረጃ የሌለው መሆኑን አረጋግጦ በማስታወቅ፡፡
⨳ለክሱ መነሻ ወይም መሠረት የሆነውን ሰነድ ዋናውን ወይም ትክክል ግልባጩን፤
⨳የሚያቀርበው ምሰስክር ወይም የጽሑፍ ሰነድ የሌለው ስሆን ይህንኑ ገልጾ ማረጋገጥ፡፡
⨳በክሱ ማመልከቻ ላይ ለተጠቀሱት ተከሳሾች ሁሉ በቂ የሆነ የክስ አቤቱታ ግልባጭ ከዚህ ጋር ተያይዘው የቀረቡትን የጽሑፎችና ሌሎችም ማስረጃወች የምስክሮች ስም ዝርዝር ማናቸውም ለፍርድ ቤቱ የደረሱትን መግለጫዎች ትክክል ግልባጫቸው እንዲደርሳቸው ማድረግ፤
⨳ከዚህ በላይ ባለው ንዑስ ቁጥር የተነገረው ድንጋጌ እንደተበቀ ቢሆንም እንኳ ፍርድ ቤቱ የፈቀደ እንደሆነ ለክሱ መሰረት የሆነውን ሰነድ ትክክል ግልባጭ ለተከሳሹ እንዲደርሰው ከማድረግ ይልቅ ዋናው በፍርድ ቤቱ መዝገብ ቤት እንዲቀመጥና ተከሳሹ መጥቶ እንዲያየው ለማዘዝ ይችላል፡፡
3. #የሚጠየቀውን ዳኝነት በዝርዝር ስለ መግለጽ
⨳ከሳሽ በሚያቀርበው የክስ ማመልከቻ ላይ በተለየ ወይም በምትክ ወይም በተለዋዋጭ የሚጠይቀውን ዳኝነት መግለጽ አለበት ነገር ግን ከሳሹ በክሱ ላይ እንዲሰጠው የሚጠይቀው ዳኝነት ጠቅላላ ሲሆን ፍርድ ቤቱ የክሱን ጭብጥና የማስረጃውን አካባቢ ሁኔታ መሰረት በማድረግ ትክክለኛ መስሎ የታየውን ፍርድ ሊሰጠው ይችላል፡፡
⨳ከሳሹ ክሱን የመሰረተው በብዙ ጉዳዮች ወይም በተለያዩ ነገሮች ላይ የሆነ እንደሆነ በተለይ በየአንዳንዱ ጉዳይ እንዲታይለት የሚጠይቀውን ዳኝነት መግለጽ አለበት፡፡
4. #ለክርክሩ ምክንያት የሆነውን ነገር ለይቶ ስለ መግለጽ
⨳ለክርክሩ መሠረት ወይም መነሻ የሆነው ጉዳይ የተወሰነ ወይም የተለየ ነገር ስሆን በማመልከቻው ላይ ነገሩን አብራርቶ በመለየት መግለጽ አለበት፡፡
⨳ክሱ የሚመለከተው የማይንቀሳቀስ ንብረትን የሆነ እንደሆነ በክሱ ማመልከቻ ላይ ንብረቱን ለይቶ ለማወቅ የሚያስችሉት ምልክቶች መገለጽ ይኖረባቸዋል፡፡ ይኸውም ንብረት የሚለው በአካባቢው ወሰን ወይም በርስት መመዝገቢያ ላይ በተሰጠው ተራ ቁጥር በሆነ ጊዜ የወሰኑ ምልክት ወይም በመዝገብ ላይ የተሰጠው ቁጥር መገለጽ ይገባዋል፡፡
5. #ገንዘብን ለመጠየቅ በሚቀርብ ክስ ላይ ስለሚቀርቡ ዝርዝር መግለጫዎች
⨳ክስ የሚቀርበው በገንዘብ የሆነ እንደሆነ ከሳሹ የሚጠይቀውን ገንዘብ በማመልከቻው ላይ በትክክለኛ ሁኔታ ገልጾ ማስታወቅ አለበት፡፡
⨳ከሳሹ የሚጠይቀው ገንዘብ ልኩ ሊታወቅ የሚችለው በርሱና በተከሳሹ መካከል የሂሳብ ማጣራት ተግባረ ከተፈጸመ በኋላ የሆነ እንደሆነ በሚያቀርበው የክስ ማመልከቻ ላይ ሊጠይቅ የሚገባውን ገንዘብ በግምት ለመግለጸ ይችላል፡፡
⨳ክሱ የቀረበው ተለይቶ የታወቀ ዕቃ ወይም ሌላ ነገር ለማስመለስ የሆነ እንደሆነ ለክሱ መሠርት የሆነውን ነገር ትክክለኛ ዋጋ በማመልከቻው ላይ መገለጽ አለበት፡፡
⨳የቀረበው ክስ የሚያልቅ ወይም የሚበላሽ ወይም እለታዊ አገልግሎት ያለው ነገር የሚመለከት ስሆን በማመልከቻው ላይ የዚሁኑ የዕለት ዋጋ መግለጽ ያስፈልጋል፡፡




የውርስ አጣሪ ሪፖርት እንደ መጨረሻ የፍርድ ውሳኔ ሊቆጠር የሚችልበት የሕግ አግባብ
👉በውርስ ማጣራት ሂደት ተሳታፊ የነበሩ ወገኖች የተለያዩ ክርክሮችን አንስተው ውርሱ በተጣራበት መዝገብ ክርክሮቹ በጭብጥነት ተይዘው እና ማስረጃ ተሰምቶ ድምዳሜ ላይ ከተደረሰ የውርስ አጣሪ የጸደቀበት ውሳኔ ከማስረጃ ያለፈ ውጤት ይኖረዋል።
👉 በውርስ አጣሪ ሪፖርቱ ላይ ተሳታፊ ያልነበረ እና ክርክሩ ያላቀረበ ወገን ደግሞ በውርስ አጣሪ ሪፖርቱ ላይ በፍ/ብ/ስ/ስ/ሕ/ቁ 358 መሰረት መቃወሚያ ማቅረብ ሳይጠበቅበት በክፍፍል ወቅት ክርክሩ ማቅረብ ስለማይከለከል በዚሕ ጊዜ የውርስ አጣሪ ሪፖርቱ የማስረጃ ዋጋ ብቻ ይኖረዋል። በመሆኑም በውርስ ማጣራት ሂደት ተሳታፊ የነበሩ ወገኖች በውርስ ማጣራት መዝገብ ላይ በክፍፍል ወቅት ሊነሳ የሚችል ክርክር ሁሉ አስቀድመው አንስተው ክርክራቸውን በማስረጃ ተጣርቶ ውሳኔ ከተሰጠ ይህ የውርስ አጣሪ ሪፖርት የጸደቀበት ውሳኔ ክርክር ተደርጎ ድምዳሜ ላይ ከተደረሰባቸው ነጥቦች አንጻር የመጨረሻ ውጤት ይኖረዋል ማለት ነው።
ምንጭ, የሰበር መዝገብ ቁጥር 231538 በሚያዚያ 25/2015 የተወሰነ/ያልታተመ/

4.2k 0 122 2 23



ሀገር አቀፍ የህግ ተርጓሚዎች መድረክ የጋራ የአቋም መግለጫ




የቤት ኪራይ .pdf
3.4Мб
የቤት ኪራይ .pdf
የመኖሪያ ቤት ኪራይ ቁጥጥር እና አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 1320/2016
https://t.me/ethiolawtips




የመኖሪያ ቤት ኪራይ ቁጥጥር እና አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 1320/2016


Legal Job Vacancy
Salary 10+

experiance 2 years and more


Legal Job Vacancy

Experience 2 year and more

Deadline April 4/2024..At Addis Ababa ...


ሰ/መ/ቁ 199400 03/02/2014 ዓ.ም የማይንቀሳቀስ ንብረት የአጻጽፍ ስርዓትና የምዝገባ ልዩነት
ውል ለማዋዋል ስልጣን በተሰጠው አካል ፊት ያልተደረገ የማይንቀሳቀስ ንብረት ሽያጭ ውል በፍ/ብ/ሕግ ቁጥር 2878 አግባብ የተመዘገበ ቢሆንም እንኳን ውሉ መደረጉ ከተካደ በሻጭና ገዥ መካከል ህጋዊ ውጤት የለውም።
ምዝገባ በፍ/ብ/ሕግ ቁጥር 1723/1 ስር የተደነገገውን የፎርም ስርዓት የሚተካ ካለመሆኑም በላይ የተዋዋዮቹን መብትና ጥቅም ለማስጠበቅ የተዘረጋ ስርዓት አይደለም።
የተያዘውን ጉዳይ አስመልክቶ ችሎቱ እንዳለው፥
ዉሉ በማዘጋጃ ቤት በሚገኝ ማህደር ዉስጥ ስለሚገኝ እንደተመዘገበ ይቆጠራል ብለዉ ያቀረቡት ክርክርም ቢሆን ይሕ ተግባር ተፈጽሞ ቢሆን እንኳን በፍ/ብ/ሕግ ቁጥር 1723/1 ስር የተደነገገዉን የፎርም ስርዓት የሚተካ ካለመሆኑም በላይ ይህ ተፈጸመ ያሉት ስርዓት የተዋዋዮቹን መብትና ጥቅም ለማስጠበቅ የተዘረጋ ስርዓት ባለመሆኑ ይህ መከራከሪያቸዉ በክልሉ ፍርድ ቤቶች ተቀባይነት በማጣቱ የተፈጸመ ስህተት አላገኘንም፡፡
በፍ/ብ/ሕግ ቁጥር 1723/1 ስር የተደነገገዉ ፎርማሊቲ በተዋዋዮች መካከል በፀና አኳኋን የተደረገ ዉል መኖሩን ለማረጋገጥና በዋናነት የተዋዋዮቹን መብት ለመጠበቅ የተደነገገ ሲሆን በፍ/ብ/ሕግ ቁጥር 2878 እና በሌሎች ከላይ በተጠቀሱት ድንጋጌዎች የተመለከተዉ ምዝገባ (Registration) ደግሞ ተዋዋዮች የማይንቀሳቀስ ንብረት ባለቤትነት ለማስተላለፍ ወይም ባንድ በማይንቀሳቀስ ንብረት ላይ የአላባ ጥቅም መብት ወይም የመያዣ ወይም የሌላ አገልግሎት መብት ለመቋቋም ወይም በድንጋጌዎቹ ላይ የተመለከቱትን ሌሎች መብቶችን ለመመስረት ዉል በመዋዋላቸዉ የሦስተኛ ወገኖች መብትና ጥቅም እንዳይነካ ለሦስተኛ ወገኖች ጥበቃ ለማድረግ ነዉ፡፡ይህ አይነት ምዝገባ (Registration) የሚከናወነዉም ንብረቱ ተመዝግቦ በሚገኝበት አስተዳደር አካል ዘንድ በሚገኘዉ የማይንቀሳቀስ ንብረት መዝገብ ላይ ነዉ፡፡
በመሆኑም ተዋዋዮች የቤት ሽያጭ ዉል የለም በሚል ዉሉን ተካክደዉ በሚከራከሩበት ጊዜ በእርግጥም በፀና አኳኋን የተደረገ ዉል ማድረግ አለማድረጋቸዉን ? ዉሉ የተደረገዉ መቼ ነዉ? የሽያጭ ዉል ከሆነ በምን ያህል ዋጋ ነዉ የተደረገዉ? ለዉሉ ምክንያት የሆነዉ ምን ዓይነት ንብረት ነዉ? የትስ የሚገኝ ነዉ? የሚሉና ንብረቱን ለማስተላለፍ መብት ባለዉ ሰዉ መፈረም አለመፈረሙን የሚመለከትና መሰል የይዘት ክርክሮች የተነሱ እንደሆነ ይህን ለማጣራት ሊቀርብ የሚገባዉ ማስረጃ ዓይነትም በፍ/ብ/ሕግ ቁጥር 1723/1 ስር በተደነገገዉ አግባብ በጽሑፍ ሆኖ ዉል ለማዋዋል ሥልጣን ባለዉ አካል ፊት የተደረገ ዉል ሊሆን ይገባል፡፡
ይህን አስመልክቶም ይህ ሰበር ሰሚ ችሎት በሰ/መ/ቁጥር 78398 በሰ/መ/ቁጥር 188881 እና በሌሎችም ላይ አስገዳጅ የሕግ ትርጉም ሰጥቷል፡፡
https://t.me/ethiolawtips

Показано 17 последних публикаций.