FBC (Fana Broadcasting Corporate)


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: Новости и СМИ


This is FBC's official Telegram channel.
For more updates please visit www.fanabc.com

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
Новости и СМИ
Статистика
Фильтр публикаций


መቻል አዳማ ከተማን 2 ለ 0 አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 13፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በ26ኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ መቻል አዳማ ከተማን 2 ለ 0 በሆነ ውጤት አሸንፏል፡፡ የመቻልን ሁለቱንም የማሸነፊያ ግቦች ሽመልስ በቀለ የመጀመሪያው አጋማሽ ተጠናቅቆ በተጨመረ ደቂቃ እና በ49ኛው ደቂቃ ላይ አስቆጥሯል። ውጤቱን ተከትሎ መቻል በ38 ነጥብ 3ኛ ደረጃ ላይ ሲቀመጥ፤ አዳማ ከተማ ደግሞ በ21 ነጥብ…

https://www.fanamc.com/archives/290638


ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) በፖፕ ፍራንሲስ ሕልፈት የተሰማቸውን ሃዘን ገለጹ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 13፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሮማ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ሊቀ ጳጳስ ፖፕ ፍራንሲስ ሕልፈት የተሰማቸውን ሃዘን ገልጸዋል፡፡


ፖፕ ፍራንሲስ ከዚህ ዓለም ድካም አረፉ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 13፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የሮማ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ሊቀ ጳጳስ ፖፕ ፍራንሲስ በ88 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም ድካም አርፈዋል፡፡


የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ሌጎስ የሚያርገውን ሳምንታዊ በረራ በእጥፍ አሳደገ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 13፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ናይጄርያ ሌጎስ ከተማ እያደረገ ያለውን 7 ሳምንታዊ በረራ ከሰኔ 24 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ ወደ 14 ሳምንታዊ በረራ አሳደገ፡፡

ይህም ለደንበኞቹ ይበልጥ ምቹ የበረራ አማራጭ መስጠት የሚያስችል መሆኑን አየር መንገዱ በማኅበራዊ ትሥሥር ገጹ አስታውቋል፡፡


ለ30 ተቋማት ነጻ የዳታ ማዕከል አገልግሎት እየተሰጠ ነው – ወርቁ ጋቸና (ዶ/ር)

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 13፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ለ30 የመንግስት ተቋማት ነጻ የዳታ ማዕከል አገልግሎት እየሰጠ መሆኑን አስታውቋል፡፡ የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተ ወርቁ ጋቸና (ዶ/ር) እንዳሉት ÷ በኢትዮጵያ የሚገኙ ተቋማት ዳታን በአግባቡ ጥቅም ላይ የማዋል ልምዳቸው አነስተኛ ነው፡፡ በሌላ በኩል ዳታን በትክክል የማስቀመጡ ተሞክሮ አነስተኛ መሆኑን ጠቁመው÷ያለውን ዳታ ተረድቶ በአግባቡ…

https://www.fanamc.com/archives/290627


ፖሊስ በርካታ ሕገ-ወጥ የጦር መሣሪያዎችን ከ146 ተጠርጣሪዎች ጋር መያዙን አስታወቀ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 13፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ በበጀት ዓመቱ ዘጠኝ ወራት በርካታ ሕገ-ወጥ የጦር መሣሪያዎችን ከ146 ተጠርጣሪዎች ጋር መያዙን አስታውቋል፡፡

በዚህም መሠረት ሕገ-ወጥ የጦር መሣሪያ ዝውውርን ለመከላከል በተደረገ ኦፕሬሽን፤ 121 የጦር መሣሪያዎችን ከመኖሪያ ቤቶች፣ 8 ሺህ 989 ከፀረ-ሰላም ኃይሎች እና 36 የጦር መሣሪያዎችን በኬላዎች ላይ መያዙን ገልጿል፡፡

በተጨማሪም 6 ሺህ 351 የተለያዩ የጦር መሣሪያ ጥይቶች ከመኖሪያ ቤቶች፣ 8 ሺህ 989 ከፀረ-ሰላም ኃይሎች፣ 51 ሺህ 846 በኬላዎች ተይዘዋል መባሉን የፌደራል ፖሊስ መረጃ አመላክቷል፡፡

እንዲሁም 236 የተለያዩ የጦር መሣሪያ ካዝናዎች በመኖሪያ ቤቶች እና 148 በኬላዎች ላይ መያዛቸው ተጠቁሟል፡፡

በተመሳሳይ 1 ብሬን ከፀረ-ሰላም ኃይሎች፣ 2 ብሬን በኬላዎች የተያዘ ሲሆን፤ 31 የተለያዩ ቦምቦች ከመኖሪያ ቤቶች፣ 25 ቦምቦችን ከፀረ-ሰላም ኃይሎች፣ 122 ቦምቦችን በኬላዎች መያዙን ፖሊስ አስታውቋል፡፡

32 የተለያዩ ሕገ-ወጥ ሽጉጦች ከመኖሪያ ቤቶች፣128 ሽጉጦች ከፀረ-ሰላም ኃይሎች፣ 102 በኬላዎች መያዝ መቻሉንም ጠቅሷል፡፡

1 ስናይፐር ከመኖሪያ ቤቶች እንዲሁም 1 ስናይፐር ከፀረ-ሰላም ኃይሎች በኤግዚቢትነት መያዙን እና 146 ተጠርጣሪዎችም በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን አስረድቷል፡፡

https://www.fanamc.com/archives/290618


ቬይትናም ከአፍሪካ ጋር ለሚኖራት ግንኙነት ኢትዮጵያን እንደበር ትጠቀማለች- ለገሠ ቱሉ (ዶ/ር)

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 13፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ኢትዮጵያ በእስያ ለምትዳርገው ሁለንተናዊ ግንኙነት ቬይትናምን፤ ቬይትናምም በአፍሪካ ለሚኖራት ግንኙነት ኢትዮጵያን እንደ ስልታዊ አጋር ይጠቀማሉ ሲሉ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ለገሠ ቱሉ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ባሳለፍነው ሣምንት በቬይትናም ያደረጉትን ይፋዊ የሥራ ጉብኝት አሥመልክቶ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትሩ ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡ በማብራሪያቸውም፤ ቬይትናም…

https://www.fanamc.com/archives/290605


የምንከተለው የብዝኃ-ዘርፍ ኢኮኖሚ ውጤታማ መሆኑን ከቬይትናም ጉብኝት ተረድቻለሁ- ወ/ሮ ሙፈሪሃት

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 13፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የሥራና ክኅሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል በቅርቡ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተመራ ልዑክ በቬይትናም ያደረገውን ጉብኝት በተመለከተ ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡ በማብራሪያቸውም፤ ቬይትናም በተለያዩ የኢኮኖሚ ዘርፎች የሪፎርም ሥራዎችን በማከናወኗ ከቀውስ አዙሪት በፍጥነት መውጣት የቻለችበትን ሁኔታ አንስተዋል፡፡ ተወዳዳሪ ኢኮኖሚን የመገንባት ተልዕኮ የተሰጠው የሰው ሀብት ልማት ሥራ መሠራቱን አንስተው፤…

https://www.fanamc.com/archives/290612


የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) የቬይትናም ጉብኝት በበርካታ ዘርፎች ልምድ የተቀሰመበት ነው – ቢልለኔ ስዩም

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 13፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የቬይትናም ጉብኝት የሀገራቱን ግንኙነት የሚያጠናክርና በበርካታ ዘርፎች ልምድ የተቀሰመበት ነው ሲሉ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት ፕሬስ ሴክሬታሪያት ሃላፊ ቢልለኔ ስዩም ገለጹ፡፡ ቢልለኔ ስዩም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ባሳለፍነው ሳምንት በቬይትናም ያደረጉትን ይፋዊ የሥራ ጉብኝት አስመልክተው ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡ በማብራሪያቸውም ጠቅላይ ሚኒስትሩ…

https://www.fanamc.com/archives/290607


Видео недоступно для предпросмотра
Смотреть в Telegram
ኢትዮጵያን በመጎብኘት በተለያዩ ዘርፎች ኢንቨስት ያድርጉ - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)


የዕለቱ የውጭ ምንዛሪ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ


ሌስተር ሲቲ ከእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ወረደ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 12፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ 33ኛ ሳምንት መርሐ ግብር ሊቨርፑል ከሜዳው ውጪ ሌስተር ሲቲን 1 ለ 0 አሸንፏል፡፡

በኪንግ ፓዎር ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ የሊቨርፑልን ብቸኛ የማሸነፊያ ግብ አሌክሳንደር አርኖልድ አስቆጥሯል፡፡

ውጤቱን ተከትሎም ሌስተር ሲቲ ከፕሪሚየር ሊጉ መውረዱን ሲያረጋግጥ ሊቨርፑል ደግሞ መሪነቱን ማጠናከር ችሏል፡፡






Видео недоступно для предпросмотра
Смотреть в Telegram
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በገላን ጉራ ከሚገኙ የካሳንቺስ ልማት ተነሺዎች ጋር የትንሳኤ በዓልን ሲያከብሩ ያስተላለፉት መልዕክት


አርሰናል ሲያሸነፍ ማንቼስተር ዩናይትድ ተሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 12፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ 33ኛ ሳምንት መርሐ ግብር አርሰናል ከሜዳው ውጪ ኢፕስዊች ታውንን ሲያሸንፍ ማንቼስተር ዩናይትድ ሽንፈት አስተናግዷል፡፡ ቀን 10 ሰዓት ላይ በተደረገው ጨዋታ አርሰናል ኢፕስዊች ታውንን 4 ለ 0 አሸንፏል፡፡ አርሰናል የጨዋታ ብልጫ በወሰደበት ጨዋታ ሊያንድሮ ትሮሳርድ (2)፣ ጋብርኤል ማርቲኔሊ እና ኢታን ኒዋኔሪ ግቦቹን አስቆጥረዋል።…

https://www.fanamc.com/archives/290596


ከንቲባ አዳነች አቤቤ የትንሣኤ በዓልን ከኮሪደር ልማት ሰራተኞች አከበሩ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 12፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ የትንሣኤ በዓልን ከካዛንቺስ ኮሪደር ልማት ሰራተኞች፣ ኮንትራክተሮች እና አማካሪዎች ጋር የትንሳዔ በዓልን አክብረዋል። ከንቲባዋ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት፤ ሰራተኞችን በማበረታት እንኳን ለትንሣኤ በዓል አደረሳችሁ፤ በዓሉ የሰላም፣ የፍቅር፣ የደስታ እና የመተሳሰብ እንዲሆንላችሁ እመኛለሁ ብለዋል። የኮሪደር ልማት ሰራተኞች ቀን…

https://www.fanamc.com/archives/290593




ሲዳማ ቡና ኢትዮጵያ ቡናን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 12፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በኢትዮጵያ ፕሪሚየርሊግ 26ኛ ሳምንት መርሐ-ግብር ሲዳማ ቡና ኢትዮጵያ ቡናን 1 ለ 0 በሆነ ውጤት አሸንፏል፡፡ በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ቀን 9 ሠዓት ላይ በተካሄደው ጨዋታ ሲዳማ ቡና ፍቅረየሱስ ተክለብርሃን ባስቆጠራት ብቸኛ ግብ ሶስት ነጥብ ይዞ ወጥቷል። የሊጉ ጨዋታ አመሻሽ 12 ሠዓት ላይ ቀጥሎ ሲካሄድ አርባ ምንጭ…

https://www.fanamc.com/archives/290583


Видео недоступно для предпросмотра
Смотреть в Telegram
ዛሬ ለአረጋዊያን እና ለአቅመ ደካሞች የትንሳኤ በዓልን ምክንያት በማድረግ ማዕድ አጋርተናል - ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው

Показано 20 последних публикаций.