FBC (Fana Broadcasting Corporate)


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: Новости и СМИ


This is FBC's official Telegram channel.
For more updates please visit www.fanabc.com

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
Новости и СМИ
Статистика
Фильтр публикаций


ማስታወቂያ


ትብብርን በማጠናከር የሚገኙ እድሎችን ወደ ሀብትነት በመቀየር የማህበረሰብ ተጠቃሚነትን ማረጋገጥ ይገባል – በለጠ ሞላ (ዶ/ር)

አዲስ አበባ፣ ጥር 27፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በዲጂታል ዘርፉ ትብብርን በማጠናከር የሚገኙ እድሎችን ወደ ሀገር ሀብትነት በመቀየር የማህበረሰብ ተጠቃሚነትን ማረጋገጥ ይገባል ሲሉ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡ ሚኒስቴሩ ከህንድ ኤስ ኤ ኤ አር ሲ ማስትስ ቴክ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ኩባንያ ጋር በዲጂታል ትራንስፎርሜሽን፣ በሰው ሰራሽ አስተውሎት፣ በደመና ማስላት አገልግሎቶች፣ በሶፍትዌር…

https://www.fanabc.com/archives/281565


ሉሲ እና ሰላም በቼክ ሪፐብሊክ ብሔራዊ ሙዚዬም ለእይታ ሊቀርቡ ነው

አዲስ አበባ፣ ጥር 27፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ሉሲ ወይም ድንቅ ነሽ እና ሰላም የተባሉት ዕድሜ ጠገቦቹ የሰው ልጆች ቅሪተ አካላት በቼክ ሪፐብሊክ ብሔራዊ ሙዚዬም ለዕይታ ሊቀርቡ መሆኑን የቱሪዝም ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡ ሉሲ እና ሰላም ከፈረንጆቹ ነሐሴ 25 ቀን 2025 ጀምሮ ነው የባህል ማዕከል በሆነችው የቼክ ሪፐብሊክ መዲና ፕራግ ለተመልካች ክፍት የሚሆኑት፡፡ “የሰው ልጅ…

https://www.fanabc.com/archives/281566




በነፃ ንግድ ቀጣናው ለመሰማራት ፈቃድ የወሰዱ ባለሃብቶች ምርት ማስገባት ጀመሩ

አዲስ አበባ፣ ጥር 27፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በድሬዳዋ ነፃ የንግድ ቀጣና በሎጂስቲክና ንግድ ዘርፍ ለመሰማራት ፈቃድ የወሰዱ ባለሃብቶች ምርቶቻቸውን ከጅቡቲ ማስገባት ጀምረዋል፡፡ በዘርፉ ለመሰማራት ፍቃድ ከወሰዱ የሀገር ውስጥና የውጭ ባለሃብቶች መካከል ምሃን ትሬዲንግ የተሰኘ ኩባንያ ከጅቡቲ ወደብ ወደ ነጻ የንግድ ቀጣናው ምርቶችን እያስገባ መሆኑን የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን አስታውቋል። የመሬት ርክክብ ካደረጉ…

https://www.fanabc.com/archives/281561


የዲጂታል ግብርና ፍኖተ ካርታ ይፋ ሆነ

አዲስ አበባ፣ ጥር 27፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢትዮጵያ ዲጂታል ግብርና ፍኖተ ካርታ በዛሬው ዕለት ይፋ ተደርጓል፡፡ ፍኖተ ካርታውን ግብርና ሚኒስቴር ከኢትዮጵያ ግብርና ትራንስፎርሜሽን ኢንስቲትዩት እና ጌትስ ፋውንዴሽን ጋር በመተባበር ያዘጋጁት ሲሆን÷እስከ ፈረንጆቹ 2032 ድረስ እንደሚተገበር ተመላክቷል፡፡ ፍኖተ ካርታው ለአርሶና አርብቶ አደሮች ሁሉን አቀፍ፣ ዘላቂ እና የበለጸገ ሥነ-ምህዳር የመፍጠር ዕቅድ እንዳለው ተጠቁሟል፡፡ በመርሐ…

https://www.fanabc.com/archives/281558


ኔታኒያሁ እና ትራምፕ በእስራኤል-ጋዛ ተኩስ አቁም ስምምነት ዙሪያ ሊመክሩ ነው

አዲስ አበባ፣ ጥር 27፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የእስራኤል ፕሬዚዳንት ቤኒያሚን ኔታኒያሁ ከአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ጋር በጋዛ ተኩስ አቁም ስምምነትና ኢራን ጉዳይ ላይ ሊመክሩ መሆኑ ተሰምቷል፡፡ መሪዎቹ ዛሬ ይገናኛሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡ ትራምፕ ውይይቱን አስመልክተው ባነሱት ሃሳብ ከእስራኤል እና ከሌሎች ሀገራት ጋር በመካከለኛው ምስራቅ ዙሪያ የሚያደርጉት ውይይቶች ለውጥ እያሳዩ መሆናቸውን ቢያነሱም ዝርዝር መረጃ…

https://www.fanabc.com/archives/281554




የእንስሳት በሽታ በዜጎች ጤናማ አኗኗር ላይ ያለውን ተጽዕኖ በመረዳት ችግሩን በጋራ መፍታት ይገባል-ም/ጠ/ሚ ተመስገን ጥሩነህ

አዲስ አበባ፣ ጥር 27፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የእንስሳት በሽታ በእንስሳት ተዋፅዖ ውጤቶች ምርታማነትና በዜጎች ጤናማ አኗኗር ላይ ያለውን ቀጥተኛ ተጽዕኖ በመረዳት ችግሩን በጋራ ትብብር ልንሻገረው ይገባል ሲሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ተናገሩ፡፡ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ 26ኛው የዓለም እንስሳት ጤና ድርጅት የአፍሪካ አህጉራዊ ጉባኤ አስጀምረዋል። ይህንን አስመልክቶ በማህበራዊ ትስሰር ገፃቸው ÷በሌማት ትሩፋት…

https://www.fanabc.com/archives/281550


የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የስፖርት ፌስቲቫል በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ አሸናፊነት ተጠናቀቀ

አዲስ አበባ፣ ጥር 27፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ላለፉት 10 ቀናት በአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ሲካሄድ የቆየው የተማሪዎች የስፖርት ፌስቲቫል በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ አሸናፊነት ተጠናቅቋል፡፡ በተጨማሪም በምስጉን ዋንጫ የአዲግራት ዩኒቨርሲቲ ተሸላሚ ሆኗል። በማጠቃለያ መርሐግብሩ ላይ የተገኙት የትምህርት ሚኒስቴር ዴኤታ ኮራ ጡሹኔ (ዶ/ር)÷ የውድድሩ ጠቀሜታ የጎላ በመሆኑ ሊቋረጥ እንደማይገባ ተናግረዋል፡፡ ለውድድሩ መሳካት የበኩላቸውን ድርሻ…

https://www.fanabc.com/archives/281547




1 ነጥብ 1 ሚሊየን ኩንታል ዳፕና ዩሪያ የጫኑ መርከቦች ወደብ ደረሱ

አዲስ አበባ፣ ጥር 27፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ለ2017/18 የምርት ዘመን 1 ሚሊየን 100 ሺህ ኩንታል ዳፕ እና ዩሪያ የጫኑ መርከቦች ጅቡቲ ወደብ መድረሳቸውን የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን አስታወቀ፡፡ ይህንን ተከትሎም እስከ ጥር 27 ቀን 2017 ዓ.ም ድረስ ከውጭ የተጓጓዘው የአፈር ማዳበሪያ መጠን ወደ 5 ሚሊየን 392 ሺህ 600 ኩንታል ከፍ ማለቱ ተጠቁሟል፡፡…

https://www.fanabc.com/archives/281543


የታዳጊ ወጣቶች የምዘና ውድድር የስፖርት ስብራትን ለመጠገን ጉልህ ድርሻ እንዳለው ተገለጸ

አዲስ አበባ፣ ጥር 27፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የታዳጊ ወጣቶች የምዘና ውድድር የስፖርት ስብራትን ለመጠገን ጉልህ ድርሻ እንዳለው የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡ ”የታዳጊ ስፖርተኞች ልማት ለአሸናፊ ሀገር” በሚል መሪ ሐሳብ በባህልና ስፖርት ሚኒስቴር አዘጋጅነት በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ሲምፖዚየም እየተካሄደ ነው፡፡ በሲምፖዚየሙ የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ዴኤታ መክዩ መሐመድ÷የታዳጊ ወጣቶች የምዘና ውድድር የስፖርት ስብራትን ለመጠገን…

https://www.fanabc.com/archives/281540


ተጨባጭ የልማት አቅሞችን አቀናጅቶ መጠቀም ስኬትን ያፋጥናል – ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)

አዲስ አበባ፣ ጥር 27፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ተጨባጭ የልማት አቅሞችን አቀናጅቶ መጠቀም በክልሉ የታቀዱ ስራዎች እንዲሳኩ በማድረግ በኩል ፋይዳው የጎላ መሆኑን የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡ የክልሉ የ2017 ግማሽ ዓመት የመንግሥትና የፓርቲ የእቅድ አፈጻጸም በቦንጋ ከተማ እየተገመገመ ይገኛል። የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) በዚህ ወቅት÷…

https://www.fanabc.com/archives/281537


በአፈር መደርመስ አደጋ የ8 ሰዎች ሕይወት አለፈ

አዲስ አበባ፣ ጥር 27፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በጉጂ ዞን ሳባ ቦሩ ወረዳ በባሕላዊ መንገድ ማዕድን በማውጣት ላይ የነበሩ 8 ሰዎች በአፈር መደርመስ አደጋ ሕይወታቸው አለፈ፡፡ አደጋው ትናንት 9 ሰዓት በባሕላዊ መንገድ ማዕድን በማውጣት ሥራ በተሰማሩ ዜጎች ላይ መድረሱን የወረዳው ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ አሸናፊ ዳንቆ ለፋና ዲጂታል ተናግረዋል፡፡ በአደጋው ለሕልፈት የተዳረጉ ሰዎችን…

https://www.fanabc.com/archives/281534


Видео недоступно для предпросмотра
Смотреть в Telegram
-የኢትዮጵያን ብሄራዊ ጥቅም ለማስጠበቅ
- የኦሮሚያ ክልል መንግስት ግምገማ


ባንኩ አሰራሩን ሊያሻሽል እንደሚገባ ተመላከተ

አዲስ አበባ፣ ጥር 27፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢትዮጵያ ልማት ባንክ አሰራሩን ሊያሻሽል እንደሚገባ የመንግስት ወጪ አስተዳደርና ቁጥጥር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አመላከተ፡፡ ቋሚ ኮሚቴው በኢትዮጵያ ልማት ባንክ የማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ የብድር አሰጣጥና አጠቃቀም ስርዓት ላይ ከፌደራል ኦዲተሮች፣ ከልማት ባንክ አስረጂዎች እና ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት አድርጓል። ውይይቱ የተካሄደውም የፌዴራል ኦዲተር ጄኔራል በ2015/16 በጀት ዓመት…

https://www.fanabc.com/archives/281531




የሕዝቡን የልማት ፍላጎት መሰረት በማድረግ በተተገበሩ ኢንሼቲቮች አበረታች ውጤት ተገኝቷል – አቶ ሽመልስ አብዲሳ

አዲስ አበባ፣ ጥር 27፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ባለፉት ዓመታት የሕዝቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ የልማት ፍላጎት መሰረት በማድረግ በተተገበሩ ኢንሼቲቮች አበረታች ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳ ገለፁ። የክልሉ መንግሥት ያለፉት ስድስት ወራት የመንግስትና የፓርቲ የሥራ ዕቅድ ክንውንን የሚገመግም መድረክ በአዳማ ከተማ እየተካሄደ ነው፡፡ ርዕሰ መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳ በዚህ ወቅት እንዳሉት፥…

https://www.fanabc.com/archives/281528


ግለሰቦች የግል መረጃቸውን በመጠበቅ ከማንነት ስርቆት ራሳቸውን እንዲጠብቁ ጥሪ ቀረበ

አዲስ አበባ፣ ጥር 27፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ግለሰቦች የግል መረጃቸውን በመጠበቅ ከማንነት ስርቆት (identity theft) ራሳቸውን እንዲጠብቁ የኢትዮጵያ ኮሙኒኬሽን ባለስልጣን አሳሰበ፡፡ የግለሰብ መረጃ ስምን፣ መለያ ቁጥርን፣ የስልክ ቁጥርን፣ የኮምፒውተር አይፒ አድራሻን፣ የቦታ ዳታን፣የኦንላይን መለያን፣ አካላዊ፣ የጄኔቲክ፣ የአዕምሮ፣ የኢኮኖሚ፣ የባህል ወይም የማህበራዊ ሁኔታዎች ጋር ተያያዥ የሆኑ መለያዎችን ይይዛል፡፡ የግላዊነት መብት በሕገ መንግስቱ ውስጥ…

https://www.fanabc.com/archives/281522

Показано 20 последних публикаций.