FBC (Fana Broadcasting Corporate)


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: Новости и СМИ


This is FBC's official Telegram channel.
For more updates please visit www.fanabc.com

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
Новости и СМИ
Статистика
Фильтр публикаций


ጠ/ሚ ዐቢይ (ዶ/ር) ከእንግሊዝ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 10፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከእንግሊዝ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አንጄላ ሬይነር ጋር በሁለትዮሽ ጉዳዮች ላይ ተወያይተዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው÷ ዛሬ ከእንግሊዝ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አንጄላ ሬይነር ጋር በዋና ዋና የሁለትዮሽ እና የባለብዙ ወገን ጉዳዮች ላይ ውጤታማ ውይይት አድርጌያለሁ ብለዋል፡፡ ኢትዮጵያ እና እንግሊዝ ረጅም…

https://www.fanabc.com/archives/283038


ኢትዮጵያ እና ዩናይትድ ኪንግደም በትብብር በሚሠሩበት ጉዳይ ላይ መከሩ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 10፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ከዩናይትድ ኪንግደም ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አንጄላ ሬይነር ጋር የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩትን ጎብኝተዋል፡፡ በዚሁ ወቅት ሀገራቱ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስን ጨምሮ በቴክኖሎጂ እና ሌሎች የትብብር መስኮች በጋራ ለመሥራት የሚያስችል ፍሬያማ ውይይት ማድረጋቸውን ነው አቶ ተመስገን በማኅበራዊ ትሥሥር ገጻቸው የገለጹት፡፡ የምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሯ…

https://www.fanabc.com/archives/283031


የዩኤን ዲፒ የአፍሪካ ቀጣና ዳይሬክተር የመዲናዋን የመልሶ ማልማት ሥራ አደነቁ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 10፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ የተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም (ዩኤንዲፒ) የአፍሪካ ቀጣና ዳይሬክተር አሁና ኤዚያኮንዋ ጋር ተወያይተዋል። በዚሁ ወቅት ዳይሬክተሯ አዲስ አበባን ለነዋሪዎቿ ምቹ ለማድረግ በተጀመረው የመልሶ ማልማት ሥራ መደነቃቸውን ከንቲባዋ በማኅበራዊ ትሥሥር ገጻቸው ገልጸዋል፡፡ በከተማው ልማት የነዋሪዎች ተጠቃሚነትን ያረጋገጠ አካታች የልማት ስትራቴጂ መተግበሩን…

https://www.fanabc.com/archives/283025


የመንግሥታቱ የዘላቂ ልማት መፍትሔ ጥምረት የአፍሪካ ቢሮውን በአዲስ አበባ ከፈተ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 10፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የተባበሩት መንግሥታት የዘላቂ ልማት መፍትሔ ጥምረት የአፍሪካ ቢሮውን በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ስር ከፈተ፡፡ የጥናትና ምርምር ሥራዎችን በማከናወን ለፖሊሲ አውጭዎች ግብዓት የሚሆኑ ሳይንሳዊ መፍትሔዎችን ቢሮው እንደሚያቀርብም በዚሁ ወቅት ተገልጿል፡፡ የጥምረቱ ፕሬዚዳንት ጀፍሪ ሳክስ (ፕ/ር) እንዳሉት÷ የጥምረቱ ተቀዳሚ ዓላማ በዓለም ላይ ኢኮኖሚያዊ ብልጽግና እና ማኅበራዊ ፍትሕ ማስፈን…

https://www.fanabc.com/archives/283022


የህብረቱ ጉባዔ ለከተማችን ድምቀትና የኢኮኖሚ መነቃቃት ፈጥሯል-ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 10፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ)የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባዔ ለከተማችን ድምቀትና የኢኮኖሚ መነቃቃት ፈጥሯል ሲሉ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለፁ፡፡ 38ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባዔ በደማቅ ሁኔታ ሲካሄድ ቆይቶ ትናንት ማምሻውን ተጠናቅቋል፡፡ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ጉባዔውን አስመልክቶ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ÷”የህብረቱ ጉባዔ ለከተማችን ድምቀትና የኢኮኖሚ መነቃቃት…

https://www.fanabc.com/archives/283018


38ኛው የአፍሪካ ኅብረት የመሪዎች ጉባኤ በዓለም አቀፍ መገናኛ ብዘኃን እይታ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 10፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የአፍሪካ ሀገራት መሪዎችና ዓለም አቀፍ ተቋማት የሥራ ኃላፊዎችን እንዲሁም ዲፕሎማቶችን ያሰባሰበው 38ኛው የአፍሪካ ኅብረት የመሪዎች ጉባኤ በዓለም አቀፍ መገናኛ ብዙኃን ሰፊ ሽፋን አግኝቷል፡፡ ለሁለት ቀናት በአዲስ አበባ የአፍሪካ ኅብረት አዳራሽ የተካሄደው ዓመታዊ የመሪዎች ጉባኤ በርካታ ሐሳቦችን፣ የጎንዮሽ ውይይቶችን እና የቀጣይ የጋራ አጀንዳዎች ላይ መክሮ ፍፃሜውን…

https://www.fanabc.com/archives/283015


ባጃጅ የሠራው የ14 ዓመት ታዳጊ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 10፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ)የ14 ዓመት ታዳጊና የ8ኛ ክፍል ተማሪ የሆነው አብዱልሃፊዝ ጸጋዬ የሚኖረው በጉራጌ ዞን ሙኽር አክሊል ወረዳ ነው። የተለያዩ የፈጠራ ሥራዎች የሠራው አብዱልሃፊዝ እስካሁን ወደ አምስት የሚጠጉ የፈጠራ ሥራዎች መሥራቱንም ገልጿል። ከእነዚህም ውስጥ በኤሌክትሪክ እና በፀሐይ ብርሃን የሚሰራ ባለ ሦስት እግር ተሽከርካሪ ይገኝበታል። ከቴክኖሎጂው ጋር የተዋወቀው የሰባት ዓመት…

https://www.fanabc.com/archives/283012


አየር መንገዱ በዢያሜን እና ሳኦፖሎ ከተሞች መካከል ከ33 ሺህ ቶን በላይ ጭነት ማጓጓዙን ገለጸ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 10፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢትዮጵያ አየር መንገድ በቻይናዋ ዢያሜን እና በብራዚሏ ሳኦፖሎ ከተሞች ካከል በሁለት ዓመትታ ብቻ ከ33 ሺህ ቶን በላይ የእቃ ጭነት ማጓጓዙን አስታወቀ። የአየር መንገዱ ካርጎና ሎጂስቲክስ አገልግሎት ወደ ዢያሜን እና ሳኦፖሎ ከተሞች የዕቃ ጭነት አገልግሎት መስጠት የጀመረበትን ሁለተኛ ዓመት አክብሯል፡፡ በዚህ ወቅት አየር መንገዱ በሁለት ዓመታት…

https://www.fanabc.com/archives/283006


Видео недоступно для предпросмотра
Смотреть в Telegram
መነሻው ሲታወስ!
“የአዲስ አበባ ለውጥ የጀመረው ከስድስት አመታት በፊት ነበር። በቢሯችን ግድግዳዎች መሃል፤ ታሪክ፣ ተፈጥሮና ምናብ በተገጣጠሙበት አንድነት ፓርክ ነበር የተነሳነው። ለኢትዮጵያ ታላቅ ሕልም አለን!” - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)።


በጋምቤላ ክልል እየተከናወኑ ባሉ መሠረተ ልማቶች ዙሪያ ውይይት ተደረገ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 10፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስትር ጫልቱ ሳኒ በጋምቤላ ክልል እየተከናወኑ ባሉ መሠረተ ልማቶች ዙሪያ ከክልሉ ከፍተኛ አመራሮች ጋር በጋምቤላ ከተማ መክረዋል፡፡

በውይይቱ ሚኒስቴሩ በ12 ክልሎችና በ27 ከተማ አስተዳደሮች በዘርፉ እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን የመደገፍና የመከታተል ስራዎችን እያከናወነ እንደሚገኝ ሚኒስትሯ ጫልቱ ሳኒ ተናግረዋል።





https://www.fanabc.com/archives/282998


Видео недоступно для предпросмотра
Смотреть в Telegram
👉 የሚኒስትሮች ምክር ቤት ውሳኔዎች

👉 የዩናይትድ ኪንግደም ምክትል ጠ/ሚ ጉብኝት


8ኛው የአፍሪካ ቢዝነስ ፎረም በአዲስ አበባ እየተካሄደ ነው

አዲስ አበባ፣ የካቲት 10፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) 8ኛው የአፍሪካ ቢዝነስ ፎረም በአዲስ አበባ ከተማ መካሄድ ጀምሯል፡፡ ፎረሙ “ከእመርታ ወደ ብልጽግና፤ የአፍሪካን ቀጣናዊ የእሴት ሰንሰለቶች አቅም ማጠናከር” በሚል መሪ ሃሳብ ነው እየተካሄደ የሚገኘው፡፡ በመድረኩ የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ፣ የግሉ ዘርፍ ተዋናዮች፣ የልማት ድርጅቶች፣ የተለያዩ ሀገራት አምባሳደሮች፣ የፋይናንስ ተቋማት እና የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች…

https://www.fanabc.com/archives/282993


ፍትህ ሚኒስቴር የሚሰጣቸውን አገልግሎቶች በዲጂታል መታወቂያ ብቻ ሊያደርግ ነው

አዲስ አበባ፣ የካቲት 10፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በሚኒስቴር መስሪያ ቤቱና ተጠሪ ተቋማቱ የሚሰጡ አገልግሎቶችን በዲጂታል መታወቂያ ብቻ ለማድረግ እየሰራ መሆኑን ፍትህ ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡ በፍትህ ሚኒስቴር እና በተጠሪ ተቋማት የሚሰጡ አገልግሎቶችን በብሔራዊ መታወቂያ ብቻ ማድረግ የሚያስችሉ የቅድመ ዝግጅት ስራዎች እየተሰሩ እንደሆነ የፍትህ ሚኒስትር ዴኤታ በላይሁን ይርጋ ተናግረዋል። በዚህ ዓመት ለጠበቆች የመታወቂያ መስጠት እና…

https://www.fanabc.com/archives/282989


የሚኒስትሮች ምክር ቤት በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔዎችን አሳለፈ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 10፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የሚኒስትሮች ምክር ቤት በዛሬው ዕለት ባካሄደው 42ኛ መደበኛ ስብሰባ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳለፈ፡፡

ውሳኔዎቹ እንደሚከተለው ቀርበዋል፡-

በቅድሚያ ምክር ቤቱ የተወያየው የኢትዮጵያ የአደጋ ሥጋት ሥራ አመራር ረቂቅ አዋጅ ላይ ነው፡፡ አዋጁ በተቋሙ የተጀመረውን የሪፎርም ስርዓት ወደ ተግባር በመለወጥ በኢትዮጵያ የህዝቡን የእርስ በእርስ መረዳዳት ባህል የማጎልበትና ተረጂነትን በዘላቂነት በሀገር አቅም መወጣትን ማዕከል በማድረግ የአደጋ ጉዳት ሰለባ ለሆኑ ዜጎች ከሰብአዊ ድጋፍ መርሆዎች፣ ከዘላቂ የልማት ፕሮግራሞችና ከሰላም መስፈን ጋር በማስተሳሰር ማህበራዊ፤ ኢኮኖሚያዊና ሞራላዊ ጉዳቱን ለመቀነስ የሚያስችል ነው፡፡ ምክር ቤቱም በጉዳዩ ላይ በሰፊው ከተወያየበት በኋላ ግብአቶችን በማከል ወደ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲተላለፍ በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡https://www.fanabc.com/archives/282983


5 ሺህ በላይ ዜጎችን የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ የሚያደርጉ ፕሮጀክቶች ተመረቁ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 10፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) 5 ሺህ 828 ዜጎችን የኤሌክትሪክ ሃይል ተጠቃሚ የሚያደርጉ የካራ ዱስና ካራ ቆርጮ የፀሐይ ሃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች ተመርቀው ለአገልግሎት ክፍት ሆነዋል፡፡ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የፕሮጀክት ፖርትፎሊዮ ሥራ አስፈጻሚ አቶ ክንፈ ነጋሽ በዚህ ወቅት እንዳሉት÷ፕሮጀክቶቹ 425 ኪሎ ዋት የኤሌክትሪክ ሃይል የማመንጨት አቅም አላቸው፡፡ የፀሐይ ሃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶቹ…

https://www.fanabc.com/archives/282975


በአፍሪካ ህብረት ጉባዔ የተሳተፉ መሪዎች ወደ ሀገራቸው እየተመለሱ ነው

አዲስ አበባ፣ የካቲት 10፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በ38ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባዔ ላይ የተሳተፉ መሪዎች ወደ ሀገራቸው እየተመለሱ ነው። በዚህ መሰረትም የጋምቢያ ም/ፕሬዚዳንት ሙሐመድ ቢ.ኤስ ጃሎ፣ የአፍሪካ ልማት ባንክ ፕሬዚዳንት አኪንውሚ አዴሲና (ዶ/ር)፣ የሴራሊዮን ፕሬዚዳንት ጁሊዬስ ማዳ ቢዮ፣ የጅቡቲ ፕሬዚዳንት ኢስማኤል ኦማር ጊሌ፣ የታንዛኒያ ፕሬዚዳንት ሳሚያ ሱሉህ እና የማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ ፕሬዚዳንት…

https://www.fanabc.com/archives/282970


በአፍሪካ ህብረት ጉባዔ የተሳተፉ መሪዎች ወደ ሀገራቸው መመለስ ጀመሩ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 10፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ)በ38ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባዔ ላይ የተሳተፉ መሪዎች ወደ ሀገራቸው መመለስ ጀምረዋል።

በዚህ መሰረትም የአልጄሪያ ፕሬዚዳንት አብዱልመጅድ ተቡን፣ የርዋንዳ ፕሬዚዳንት ፖል ካጋሜ ፣ የፍልስጤም መሪ መሐሙድ አባስ፣ የባርባዶስ ጠቅላይ ሚኒስትር ሚያ አሞር ሞተሊ እና የደቡብ አፍሪካ ፕሬዚዳንት ሲሪል ራማፎሳ በአዲስ አበባ የነበራቸውን ቆይታ አጠናቅቀው ተመልሰዋል።

ለመሪዎቹ የመንግስት ከፍተኛ ስራ ሃላፊዎች በቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ የክብር አሸኛኘት ያደረጉላቸው መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል።


የዩናይትድ ኪንግደም ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አንጄላ ሬይነር ወደ ምድረ ቀደምቷ ኢትዮጵያ እንኳን በደህና መጡ።

በታላቅ የለውጥ ጉዞ ላይ በምትገኘው ኢትዮጵያ የሚኖርዎት ጉብኝትና ቆይታ ስኬታማ እንዲሆን እመኛለሁ፡፡

ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ

Показано 18 последних публикаций.