FBC (Fana Broadcasting Corporate)


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: Новости и СМИ


This is FBC's official Telegram channel.
For more updates please visit www.fanabc.com

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
Новости и СМИ
Статистика
Фильтр публикаций


የወባ ስርጭትን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የባለድርሻ አካላት አጋርነት ወሳኝ ነው – ዶ/ር ደረጄ ዱጉማ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 17፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የወባ ስርጭትን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የሁሉም ባለድርሻ አካላት አጋርነት ወሳኝ መሆኑን የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ደረጄ ዱጉማ ገለጹ፡፡ “ፍትሐዊ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የወባ ማስወገድ ትግበራን እናፋጥን” በሚል መሪ ሃሳብ ዛሬ የተከበረውን የዓለም የወባ ቀንን አስመልክቶ የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ደረጄ ዱጉማ መግለጫ ሰጥተዋል፡፡ ዶክተር ደረጄ ዱጉማ…

https://www.fanabc.com/archives/243755


የስራ ፈጠራን የሚደግፈው ቲምቡክቱ ኢኒሼቲቭ በኢትዮጵያ ስራ ጀመረ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 17፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በአፍሪካ የስራ ፈጠራና ስታርትአፕን የሚደግፈው ቲምቡክቱ ኢኒሼቲቭ በኢትዮጵያ በይፋ ስራ ጀምሯል፡፡ ኢኒሼቲቩ በተባበሩት መንግስታት የልማት ፕሮግራም አነሳሽነት በአፍሪካ በተለይ ኢንቨስትመንትን፣ ስራ ፈጠራንና ስታርትአፕን ለመደገፍ የሚሰራ ነው። ቲምቡክቱ ኢኒሼቲቭ በአህጉሪቱ ግዙፍ የፓንአፍሪካ ስታርትአፕ ምህዳር መፍጠርን ያለመ ነውም መባሉን የዘገበው ኢዜአ ነው፡፡ በኢንሼቲቩ ማስጀመሪያ መርሐ ግብር የኢኖቬሽንና…

https://www.fanabc.com/archives/243749


የስራ ፈጠራን የሚደግፈው ቲምቡክቱ ኢኒሼቲቭ በኢትዮጵያ ስራ ጀመረ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 17፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በአፍሪካ የስራ ፈጠራና ስታርትአፕን የሚደግፈው ቲምቡክቱ ኢኒሼቲቭ በኢትዮጵያ በይፋ ስራ ጀምሯል፡፡ ኢኒሼቲቩ በተባበሩት መንግስታት የልማት ፕሮግራም አነሳሽነት በአፍሪካ በተለይ ኢንቨስትመንትን፣ ስራ ፈጠራንና ስታርትአፕን ለመደገፍ የሚሰራ ነው። ቲምቡክቱ ኢኒሼቲቭ በአህጉሪቱ ግዙፍ የፓንአፍሪካ ስታርትአፕ ምህዳር መፍጠርን ያለመ ነውም መባሉን የዘገበው ኢዜአ ነው፡፡ በኢንሼቲቩ ማስጀመሪያ መርሐ ግብር የኢኖቬሽንና…

https://www.fanabc.com/archives/243749


አቶ በርኦ ሐሰን ከሊቢያ ትራንስፖርት ሚኒስቴር ልዑካን ቡድን ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 17፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዴኤታ በርኦ ሀሰን ከሊቢያ ትራንስፖርት ሚኒስቴርና ልዑካን ቡድን ጋር የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ዘርፍን በተመለከተ ተወያይተዋል፡፡ ሚኒስትር ዴኤታው ከሊቢያ ትራንስፖርት ሚኒስትር መሃመድ ሰላም አልሻቢ በትራንስፖርትና ሎጂስቲክሰ ዘርፍ ጋር በተያያዘ በጋራ ለመስራት መክረዋል፡፡ አቶ በርኦ ሀሰን ኢትዮጵያ እና ሊቢያ የቆየ የዲፕሎማሲ ግንኙነት እንዳለቸው ገልፀው…

https://www.fanabc.com/archives/243746


አቶ አሕመድ ሺዴ ከአሜሪካ ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች ጋር መከሩ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 17፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የገንዘብ ሚኒስትር አሕመድ ሺዴ ከተለያዩ የአሜሪካ ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች ጋር በወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ተወያይተዋል፡፡ የ2024 የዓለም ባንክ እና አይኤም ኤፍ ስብሰባዎች ጎን ለጎን በሚኒስትር አሕመድ ሺዴ የሚመራው ልዑክ ከአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የአፍሪካ ጉዳዮች ረዳት አምባሳደር ሞሊ ፊ፣ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ አምባሳደር ማይክል…

https://www.fanabc.com/archives/243736


የአውሮፓ ቻምበር በኢትዮጵያ የግብር አስተዳደርን በማሻሻል ላይ ያተኮረ የፖሊሲ ሰነድ ይፋ አደረገ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 17፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በኢትዮጵያ የሚገኘው የአውሮፓ ቻምበር በኢትዮጵያ የግብር አስተዳደርን በማሻሻል ላይ ያተኮረ የፖሊሲ ሰነድ ይፋ አደረገ፡፡ የፖሊሲ ሰነዱ በሀገሪቱ የግብር አስተዳደር ሂደት ውስጥ የግሉ ዘርፍ የሚያጋጥሙትን ተግዳሮቶች እንደሚዳስስ ተገልጿል። በመድረኩ የኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር ሀና አርአያ ስላሴ፣ በኢትዮጵያ የአውሮፓ ህብረት አምባሳደር ሮላንድ ኮቢያ፣ በኢትዮጵያ የአውሮፓ ምክር ቤት የቦርድ…

https://www.fanabc.com/archives/243733


ባህላዊ የእርቅና የሽምግልና ስርዓቶችን ለሚስተዋሉ ግጭቶች መፍትሔ ማድረግ እንደሚገባ ተመላከተ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 17፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ባህላዊ የእርቅና የሽምግልና ስርዓቶችን በማልማት ለሚስተዋሉ ግጭቶች መፍትሔ እንዲሆኑ ለማድረግ የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ትኩረት ሰጥቶ መስራት እንደሚገባው የጤና፣ ማህበራዊ ልማት፣ ባህልና ስፖርት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አመላክቷል፡፡ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በመደበኛ ስብሰባው የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር የ2016 በጀት ዓመት የ9 ወራት ዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርትን አድምጧል፡፡ የጤና፣…

https://www.fanabc.com/archives/243730


ጾታዊ ጥቃትና ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶች እየተባባሱ መምጣታቸውን የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት አስታወቀ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 17፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በኢትዮጵያ ፆታዊ ጥቃትና ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶች እየተባባሱ መምጣታቸውን የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አስታወቀ። ምክር ቤቱ ዛሬ ባካሄደው 3ኛ ዓመት 22ኛ መደበኛ ስብሰባ የሴቶችና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴርን የ2016 ዓ.ም የዘጠኝ ወራት የሥራ አፈጻጸም ሪፖርትን አድምጧል። የሴቶችና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ኤርጎጌ ተስፋዬ (ዶ/ር) ባቀረቡት ሪፖርት÷ ባለፉት 9…

https://www.fanabc.com/archives/243726


ለ6 ዓመታት የሚተገበር ውጤታማ የጤና አመራር መርሐ ግብር ይፋ ሆነ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 17፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የጤና ሚኒስቴር ለሚቀጥሉት ስድስት ዓመታት የሚተገበር ሀገር አቀፍ ውጤታማ የጤና አመራር መርሐ ግብር ዛሬ በይፋ አስጀምሯል። የጤና ሚኒስቴር ዴዔታ ዶ/ር አየለ ተሾመ በመርሐ ግብሩ ማስጀመሪያ ላይ እንዳሉት፥ የጤናው ዘርፍ ከፍተኛ ትኩረት ተሰጥቶት እየተሰራ ቢሆንም የሚታዩ ክፍተቶችን ለመሙላት ውጤታማ የጤና አመራር መገንባት አስፈላጊ ነው። ለዚህም ውጤታማ…

https://www.fanabc.com/archives/243723


አቶ ታዬ ደንደአ የፀረሰላም ኃይሎችን በመደገፍ እና የጦር መሳሪያ ይዞ በመገኘት ወንጀል ክስ ተመሰረተባቸው

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 17፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የሰላም ሚኒስትር ዴዔታ የነበሩት አቶ ታዬ ደንደአ የፀረሰላም ኃይሎችን በመደገፍና ጦር መሳሪያ ይዞ በመገኘት ወንጀል ክስ ተመሰረተባቸው። ክሱ የተመሰረተው በፌዴራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ልደታ ምድብ 1ኛ ሕገ-መንግስትና ሕገ-መንግስት ሥርዓት ላይ የሚፈጸሙ ወንጀል ጉዳዮችን በሚመለከተው ችሎት ነው። የፍትሕ ሚኒስቴር የተደራጁና ድንበር ተሻጋሪ ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ዐቃቤ ሕግ በተከሳሽ…

https://www.fanabc.com/archives/243720


ቦርዱ ቀሪና ድጋሚ ምርጫ በሚካሄድባቸው አካባቢዎች የምርጫ አፈፃፀም ጊዜ ሰሌዳን ይፋ አደረገ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 17፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ 6ኛው ዙር ቀሪ እና ድጋሚ ምርጫ በሚካሄድባቸው አካባቢዎች የምርጫ አፈፃፀም ጊዜ ሰሌዳን ይፋ አድርጓል፡፡

6ኛው ዙር ቀሪና ድጋሚ ምርጫ የሚካሄድባቸው አካባቢዎችም በቤንሻንጉል ጉሙዝ፣ አፋር፣ ሶማሌ እና ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልሎች እንደሚገኙ ተመላክቷል፡፡

ቦርዱ ይፋ ያደረገው የምርጫ አፈፃፀም ጊዜ ሰሌዳ እንደሚከተለው ቀርቧል፡-


የሊቢያ ጠቅላይ ሚኒስትር በዓድዋ ድል መታሰቢያ የአበባ ጉንጉን አኖሩ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 17፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የሊቢያ ጠቅላይ ሚኒስትር አብዱልሃሚድ አልዳባቢያ በዓድዋ ድል መታሰቢያ በመገኘት የአበባ ጉንጉን አኑረዋል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትሩ የአፍሪካዊያን ሁሉ ኩራት የሆነው የዓድዋ ድል መታሰቢያ በዚህ መልክ በመገንባቱ እንደተደሰቱ መናገራቸውን የከንቲባ ጽ/ቤት መረጃ ያመላክታል፡፡


በሪጅኑ በተፈፀመ ሥርቆት 2 የከፍተኛ ኃይል ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎች መውደቃቸው ተጠቆመ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 17፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ከለገጣፎ – ቃሊቲ በተዘረጋው ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ መስመር ላይ በተፈፀመ ስርቆት ሁለት የከፍተኛ ኃይል ተሸካሚ ምሰሶዎች መውደቃቸውን የማዕከላዊ አንድ ሪጅን አስታወቀ፡፡ የሪጅኑ የማስተላለፊያ መስመርና ፋይበር ኦፕቲክስ ሥራ አስኪያጅ አቶ በሱፈቃድ በቀለ እንዳስታወቁት÷ በመስመሩ ላይ ሚያዚያ 15 ቀን 2016 ዓ.ም ከሌሊቱ 6 ሰዓት…

https://www.fanabc.com/archives/243714


ከ40 ሚሊየን ብር በላይ የአልባሳት ግዢ ጋር ተያይዞ በሙስና ወንጀል የተከሰሱት ጥፋተኛ ተባሉ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 17፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ከ40 ሚሊየን ብር በላይ የአልባሳት ግዢ ጋር ተያይዞ በከባድ የሙስና ወንጀል የተከሰሱት የጥፋተኝነት ፍርድ ተላልፎባቸዋል። የጥፋተኝነት ፍርድ የተላለፈባቸው የቀድሞ የአዲስ አበባ እሳት እና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን ኮሚሽነር ሰለሞን ፍስሃ እና ነጋዴ የሆኑት ንጉስ አማን ናቸው፡፡ ሌሎች የኮሚሽኑ ሰራተኛ የነበሩ 5 ግለሰቦች ደግሞ በተከሰሱበት…

https://www.fanabc.com/archives/243711


አቶ ሙስጠፌ መሀመድ የሸበሌ ሪዞርት የግንባታ ሂደትን ጎበኙ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 17፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በሶማሌ ክልል ርእሰ መስተዳድር ሙስጠፌ መሀመድ የተመራ የፌደራል እና የክልል ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሀላፊዎች ልዑክ የገበታ ለሀገር ፕሮጀክት አካል የሆነውን የሸበሌ ሪዞርት ግንባታ ሂደት ጎብኝተዋል፡፡ ልዑኩ የችግኝ ተከላም ያካሄደ ሲሆን ÷በመርሀግብሩ ከርእሰ መስተዳድሩ በተጨማሪ የኢፌዴሪ መከላከያ ሚኒስትር እና የፕሮጀክቱ አስተባባሪ አብረሃም በላይ(ዶ/ር)፣ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር…

https://www.fanabc.com/archives/243707


ኢትዮጵያ በኢንተርፖል ዓለም አቀፍ ዓመታዊ ኮንፍረንስ ላይ እየተሳተፈች ነው

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 17፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ በፈረንሳይ ሊዮን ከተማ እየተካሄደ በሚገኘው 19ኛው የኢንተርፖል ዓለም አቀፍ ዓመታዊ ኮንፍረንስ ላይ እየተሳተፈ ይገኛል፡፡ በኮንፈረንሱ የተሳተፉት የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ብሔራዊ ኢንተርፖልና ዓለም አቀፍ የፖሊስ ትብብር መምሪያ ኃላፊ ረዳት ኮሚሽነር ደጀኔ በቀለ፤ ከኮንፈረንሱ ጎን ለጎን ከኢንተርፖል አገልግሎት ማስፋፋት ፕሮጀክት አስተባባሪዎች ጋር ውይይት አድርገዋል፡፡…

https://www.fanabc.com/archives/243704


Видео недоступно для предпросмотра
Смотреть в Telegram
የጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና የሊቢያው ጠቅላይ ሚኒስትር ውይይት


ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከሊቢያ ጠቅላይ ሚኒስትር ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 17፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከሊቢያ ጠቅላይ ሚኒስትር አብዱልሃሚድ አልዳባቢያ ጋር ተወያይተዋል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር)በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት ጽሑፍ ÷ "የሊቢያ ጠቅላይ ሚኒስትር አብዱልሃሚድ አልዳባቢያን በመቀበሌ ደስታ ተሰምቶኛል"ብለዋል።

በውይይታቸውም በቀጠናዊ የሰላም እና መረጋጋት፣ የኢኮኖሚ ትብብር፣ የሰው ሃይል ልውውጥ እና ሌሎች የጋራ ጉዳዮች ላይ መምከራቸውን ተናግረዋል፡፡

የሊቢያ ጠቅላይ ሚኒስትር አብዱልሃሚድ አልዳባቢያ በኢትዮጵያ ይፋዊ የሥራ ጉብኝት ለማድረግ ትናንት ምሽት አዲስ አበባ መግባታቸው ይታወሳል፡፡


አቶ ኦርዲን በምስራቅ እዝ በሐረር ከተማ እየተከናወኑ የሚገኙ ፕሮጀክቶችን ጎበኙ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 17፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪና ካቢኔያቸው በምስራቅ ዕዝ እየተከናወኑ የሚገኙ ፕሮጀክቶችን ጎብኝተዋል፡፡ ርዕሰ መስተዳድሩ በዚህ ወቅት÷ የምስራቅ እዝ በስሩ የሚገኙ ባዶ ባታዎችን በማልማት ረገድ እየተከናወኑ የሚገኙ ሥራዎች አበረታች መሆናቸውን ጠቁመዋል። ሰራዊቱ የሀገርን ዳር ድንበር ከማስከበር ጎን ለጎን የሚያከናውነው የልማት ሥራ በተሞክሮነት የሚወሰድና በእዙና ክልሉ…

https://www.fanabc.com/archives/243699


የሚኒስትሮች ምክር ቤት የተለያዩ ውሳኔዎችን አሳለፈ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 17፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የሚኒስትሮች ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው 31ኛ መደበኛ ስብሰባ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳልፏል፡፡

ምክር ቤቱ ያሳለፋቸው ውሳኔዎች እንደሚከተለው ቀርበዋል፡-

1. ምክር ቤቱ በቅድሚያ የተወያየው የወጪ ንግድ የቀረጥ ማበረታቻ ሥርዓት አዋጅን ለማሻሻል የቀረበው ረቂቅ አዋጅ ላይ ነው፡፡ ለኢንደስትሪ ልማትና ኢንቨስትመንት የሚያስፈልገውን የውጭ ምንዛሪ ግኝት ለማሳደግ፣ በወጪ ንግድ ሥራ ላይ የተሰማሩ ባለሀብቶች በማበረታታት ረገድ የታዩ ውስንነቶችን ለመቅረፍ እና የዘርፉን ተዋንያን የሚያበረታታ ሥርዓት በመዘርጋት ተወዳዳሪነት ማላቅ ይቻል ዘንድ ረቂቅ ማሻሻያ አዋጅ ተዘጋጅቶ ቀርቧል፡፡ ምክር ቤቱም ረቂቅ ማሻሻያ አዋጁ ላይ ከተወያያ በኋላ ግብዓቶችን በማከል ወደ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲተላለፍ በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡

2. በመቀጠል ምክር ቤቱ የተወያየው የፌዴራል ህብረት ስራ ኮሚሽን ለሚሰጣቸው አገልግሎቶች የሚያስከፍለውን የአገልግሎት ክፍያ ለመወሰን በቀረበ ረቂቅ ደንብ ላይ ነው፡፡ ኮሚሽኑ የሚሰጣቸውን አገልግሎቶች ማስፋት፣ የአገልግሎቶቹን የጥራት ደረጃ ማሻሻል፣ ብሎም የተጠቃሚውን ማህበረሰብ አቅም ባገናዘበ መልኩ አገልግሎት ለመስጠት ያወጣውን ወጪ በከፊል መሸፈን የሚያስችል ስርዓት መዘርጋት በማስፈለጉ ረቂቅ ደንቡ ተዘጋጅቶ ለምክር ቤቱ ቀርቧል፡፡ ምክር ቤቱም በረቂቅ ደንቡ ላይ ከተወያየ በኋላ ግብዓቶችን በማከል በነጋሪት ጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በስራ ላይ እንዲውል በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡https://www.fanabc.com/archives/243695

Показано 20 последних публикаций.