ግጥም ለኢየሱስ ️️️📖✍


Гео и язык канала: Эфиопия, Английский
Категория: Другое


እንኳን ወደ ግጥም ቤታችሁ በደህና መጣችሁ ይህ የገጣሚ #አማኑኤል ነጋሽ እና የለሎች ገጣሚያን ግጥም የሚቀርብበት ነው
አዘጋጅ✍️AMANUEL NEGASH(Abu)
ግጥሜን ለኢየሱስ
10,000 members 🏃🏃‍♂️
ለአስተያየት👇
@AbuGitimBot
@abu_ND8
🛑YOUTUBE🛑
https://www.youtube.com/@gitim_alem
Telegram
@gitim_alem

Связанные каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Английский
Категория
Другое
Статистика
Фильтр публикаций


እኔ በተወለድኩበት ወር🤱 ለተወለዳቹ የቻናላችን ቤተሰቦች ዛሬ አሪፍ መንፈሳዊ ቻናል እጋብዛቹሃለው😃

አስታውሱ✴️
ቻናሉን የምጋብዘው እኔ በተወለድኩበት ወር ለተወለደ ብቻ ነው

መዋሸት አይቻልም❌ የተወለዳቹበትን ወር ስትጫኑ መንፈሳዊ ቻናል ከመጣ ተቀላቀሉ
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇


ዘዳግም 33 ፡ 26፤
ይሹሩን ሆይ፥ በሰማያት ላይ ለረድኤትህ፥ በደመናትም ላይ በታላቅነት እንደሚሄድ እንደ እግዚአብሔር ያለ ማንም የለም።


መልካም ቀን ይሁንላችሁ
react 👍 ❤ 🥰


ተከታታይ መንፈሳዊ ልብወለድ

#ሁለት-ሰይፍ
ክፍል ስምንት(ሜርሲ✍️)

"ሄይ... ብዙ አትረበሽ::ቁጭ በል::"
ያልጠበቀው ስለ ነበር ግራ እንደተጋባ ቁጭ ብሎ ተመለከታት::
"ለእኔ አይደለም::ሰዎችን የተሳሳተ ነገር..."
"ሰዎችን ተዋቸው::እኔንም ጨምሮ::ስህተቷን ከመቀበል የምትሸሽ ሰው ሆና የታየችኝ::እናቷ እንዳለችው አርፋ ከሆነም የአንተ ሳይሆን የእሷ ጥፋት ነው ማለት ነው::"
"ይሄን አልጠበቅኩም ከምር::"
"ምን ተነስቼ እንድሄድ ጠብቀህ ነበር!?..እኔም ያለፍኩበት ነገር ስለሆነ እንደዚህ አይነት ሰዎችን አልስታቸውም::" አለች ፈገግ ብላ::
"ለምን እንደ እህቴ መሆን እንደምፈልግ አሁን ገባህ?" ማክቤል ነበር::
ናትናኤል ፈገግ ብሎ አንገቱን በአዎንታ ነቀነቀ::
"ዩ ጋይስ አር አሜዚንግ ከምር::"

*                       *                              *

ናትናኤል ከበሩ ቆሞ ሲመለከታት ቆይቶ በእጁ የያዘውን ጋቢ አልብሷት ከአጠገቧ ይቀመጣል::
ዞራ አይታው:-
"ኦንላይን ሥራ የለም ዛሬ?"
"ዛሬ ትንሽ ልረፍ ብዬ ነው::"
"ምን እንደምትሰራ ማወቅ እችላለሁ?"
ፈገግ ብሎ እያያት:-
"ለአጠያየቅ ትህትናሽ ስል ብቻ እመልሳለሁ::" ስቃ አይኗን ከበሩ ትመልሳለች::
"ፍሪላንሰር ነኝ::ሁለ ገብ ነኝ እዛም እዚህም::ዲጂታል ማርኬቲንግ.. ትሬድ አደርጋለሁ... ኤዲትንግ... ግራፊክስ... ኦንላይን አስተምራለሁም::"
"ርሊይ?"
"ያ.... አይ ምን ገንዘብ የሚያስገኝ ኦንላይን ላይ የሚሰራ ሁሉ ነገር እንዲያልፈኝ አልፈቅድም::"
"ኃጢያትም ቢሆን?"
"እሱን እንኳ አልሞክረውም::"
"ስቀልድህ ነው::" አለች ፈገግ ብላ::
"ኃጢያት ባይሆኑም ወደ ኃጢያት መሩኝ እንጂ::"
በዝግታ ዞራ ተመለከተችው:-
"እንዴት?"
"እረጅም ታሪክ ነው::ሌላ ጊዜ::"
"እዚህኛው ጥያቄዬ ላይ ትህትና የለበትም ማለት ነው::"
"እንደዛ ማለቴ ሳይሆን.."
ሁለቱም ይስቃሉ... ሳቃቸውን የሚያቁአርጥ ድምፅ ሲሰሙ ሳራ ብድግ አለች::
"ማክ.." እየሮጠች ወደ ውስጥ ስትገባ ናትናኤልም እየተከተላት ገባ::
ማክቤል ከመኝታ ክፍል ወደ ሳሎን ባለው ደረጃ በባዶ እግሩ እየተንደረደረ የእናቱን እና የአባቱን ስም እየጠራ ሲወርድ ተመለከቱት::
ሳራ እየተንደረደረች ሄዳ ከስር ተቀብላው አቀፈችው::
"ማክ.. እኔ.. ነኝ... እኔ.. አለሁልህ.... እኔ.. አለሁልህ.. ቅዘት ነው::" እያገላበጠችው እየሳመችው እና እያቀፈችው ናትናኤል የሚሆነውን በዝምታ ይመለከታል::ማክቤል መጥራቱን አቁሞ ሲረጋጋ ወደ ሶፋው በመሄድ ስትቀመጥ እሱ ከሶፋው ወጥቶ ከእግሯ ጭንቅላቱን አስደግፎ አይኖቹን ይጨፍናል::ጋቢውን ከጀርባዋ አንስታ እሱን በማልበስ ፀጉሩን እያሻሸች ወደ ናትናኤል እንባ ባቀረሩ አይኖችዋ ተመለከተች::በዓይኑ ደሕና መሆኗን ሲጠይቃት አፀፋውን ትመልሳለች::
"ሂድ ተኛ::እኔ እጠብቃታለሁ::" አለችው ዝግ ባለ ድምፀት::አንገቱን በአዎንታ በመነቅነቅ በሩን ገርበብ አድርጎ በመውጣት ወደ ክፍሉ ገብቶ ከሶፋው በመቀመጥ በእረጅሙ ይተነፍሳል::
በር ሲንኳኳ ብድግ ይል እና ሲወጣ ሳራንም ከበሩ ያገኛታል::በመገረም እያያት:-
"አንቺ ከማክቤል ጋር ሁኚ::ጥለሽው መውጣትም አልነበረብሽም::እኔ አወራታለሁ::"
"ናቲ.."
"ፕሊስ... ወደ ውስጥ ግቢ::"

እሷ ስትገባ እሱ ወደ በሩ በፍጥነት በመሄድ ይከፍተዋል::ያደረሳት መኪና ሲሄድ ተመልክቶ ወደ እሷ ይዞራል::
"ሄይ ቆንጆው ልጅ.... ክልስ ነህ አይደለ?"
"በአያቴ::"
"ጠርጥሬ ነበር::" አለች በእጇ እያጨበጨበች ድምፁአን ከፍ አድርጋ::
"ሄይ ድምፅሽን ቀንሺ::ማክ ተኝቷል::"
"ኦውው... እኔን ወንድሜን... እሺሺሺ... አልረብሽም::"
ልትገባ ስትል በሩ አደናቅፉአት ልትወድቅ ስትል ደግፎ ይዙአት በሩን በአንድ እጁ ይዘጋዋል::
"ሂሂሂ.... ይሄን ፊልም ላይ ብቻ ነው የማውቀው የነበረው::"
"እባክሽን ዮሃና..."
"ኦውው... ማክ... እሺሺሺሺ...." አንድ ጣቷን በአፉአ በማድረግ ድምፅ ሳታሰማ ትስቃለች::
ወደ በር ሲደርሱ ቆም ይልና :-
"ዛሬ እኔ ጋር ታድሪያለሽ::"
"ህ?" ቀና ብላ ስካር ባጨናበሰው አይኖችዋ ትመለከተዋለች::
"ማክቤል ደህና አይደለም::"
"ኦውው... ከቆንጆው ልጅ ጋር ላድር ነው::"
"እንደዛ አይደለም::" ደንገጥ ብሎ::
"ገብቶኛል ባክህን...." ወደ እሱ ክፍል ይገባሉ::

*                      *                         *

አይኖችዋን በግድ ስትገልጥ ከፊቷ ናትናኤል ተቀምጦ ስትመለከት በርግጋ ትነሳለች::የተኛችበትን ሶፋ ትመለከታለች::
"እዚህ ምን እሰራለሁ!?"
"ምንም ነገር አታስታውሺም?"
"በፍፁም::"
"ሰው እንዴት እራሱን በዚህን ያህል ልክ ይበቀላል!?... ፍትፍት ላዘጋጅልሽ::"
በዓይኗ ሸኝታው ቤቱን ግራ በመጋባት ትቃኛለች::


          Like🥰 Comment📩 Share💫
ቀጣዩ  እንድለቀቅ

ይቀጥላል...

ግጥሜን  ለኢየሱስ
   💙እወዳችኋለሁ 💙
---------------------------------------------------------
SHARE
| @GITIM_ALEM |
| @GITIM_ALEM |
--------------------------------------------------------
SHARE
   Contact me  @abu_ND8


እኔን በኔ ወይስ በሱ

እኔን በኔ ስመለከት
ያለብኝን  ብዙ ድክመት
እያንዳንዱን አስባለሁ
እኔ ይሄ ነኝ እላለሁ
ልለውጠው እጥራለሁ
ሲከብደኝ ደግሞ ተዋለሁ

ኩነኔ ውስጥ እገባለሁ
ራሴን በራሴ አስራለሁ
ና ያለኝን እተዋለሁ
መስጠምም እጀምራለሁ
አገኝለሁ ብዙ ድክመት
እኔን በኔ ስመለከት

በሱ.....

ግሩም ድንቅ ነኝ እላለሁ
እራሴን ከሌላው ጋራ ማወዳደር አቆማለሁ
እዘዘኝ ልምጣ እላለሁ
በውሃው ላይ እራመዳለሁ
እኖራለሁ በጀግንነት
እኔን በሱ ያየሁኝ እለት

ከሳሽ የለብኝ ኩነኔ
መሀሪው ስለለ ጎኔ
አልፈራም ልክ እንዳንበሳ
ጠላቴ ላይ የምነሳ
ስሙ ሆኖኝ ጋሻ ጦሬ
ምክንያት ሆኖኝ ለመኖሬ
አገኛለሁ ብዙ ጉልበት
እኔን በሱ ያየሁኝ እለት

አብም ሲያይ ወደ ምድር
ጻድቋ ልጄ እያለ
ድካሜን በእርሱ ሸፍኖ
አብ አባት ስል አለው ካለ
እኔን በእርሱ የሚያሳየኝ
የየሱስ ደም ከፊት አለ፡፡


ግጥሜን  ለኢየሱስ
   💙እወዳችኋለሁ 💙
---------------------------------------------------------
SHARE
| @GITIM_ALEM |
| @GITIM_ALEM |
--------------------------------------------------------
SHARE
   Contact me  @abu_ND8


ተሰሚ ነህ በሰማይ በምድር
ጉልበት ሁሉ ሚንበረከክልህ
የፈጠርከን እንሰግድልሃለን
ሞገስህን ክብርህን እያየን

ይሹሩን ሆይ በሰማያት ላይ ለእረድኤትህ
በደመናት ላይ እንደሚሄድ
እንደ እግዚአብሔር ያለ ማንም የለም
ኧረ እንደርሱ ያለ ቢፈለግም የለም


✍️ መስከረም ጌቱ
@gitim_alem


ማስታወቂያ
አድሚን(Admin) ሆኖ በዚህ ቻናል
@GITIM_ALEM ከእኔ ጋር መስራት የሚፈልግ ሰው በውስጥ መስመር ያናግረኝ።

አድሚን ለመሆን ቅድሜ ሁነታ
1 መንፈሳዊ ሰው ቃሉን የሚያውቅ
2 ግጥም መጻፍ የሚችል
3 የቴሌግራም አጠቃቀምን የሚያውቅ
@abu_ND8 inbox አድርጉልኝ
#ሸር አድርጉ ለጓደኞቻችሁ


የህይወቴን መልህቅ ሰሪው ተረከብከኝ
ከመንገዳገዴ ከእንቅፍት ያከምከኝ
መንገዴን አልመርጥ ከእንግዲ በኃላ
በወደድኸው ምራኝ ህይወቴን በሙላ (2x)

ኢየሱስ 4x ወዳጄ ጌታዬ ኢየሱስ
መልካም እረኛዬ ኢየሱስ
ኢየሱስ 4x ትሁቱ መምህሬ ኢየሱስ
ደጉ አስተማሪዬ ኢየሱስ

መጠጊያ መተማመኛዬ ጌታዬ
አመለጥሁ ባንተ ተከልዬ
ከጥፍት ባንተ ተከልዬ
ስምህን ጠርቼ አረፍሁኝ ከጭንቀት
ከአዛለኝ የሀጥያት ፍርሀት
ሆነኸኝ የዘላለም እረፍት

የግርግር አለም ምኑ ያስደስታል
አያስተማምንም ሁሉ ይቀየራል
እደበቃለሁ ገብቼ ከእቅፍህ
ጌታዬ አንተን ነው 'ምተማመንብህ

አገኘሁኝ መተማመኛ
ለጠላቶቼ የማይተኛ
እኔም በክንዶቹ አርፋለሁኝ
ሁሉንም በእርሱ ላይ ጥላለሁ (2x)

ስላደረክልኝ መልካም/በጎ ነገር
እኔ ምን እላለሁ ከዚህ በቀር
ጌትዬ ስምህ ይክበር (3x)
ውድዬ አንተው ክበር (3x

ኢየሱስ
ቃለአብ መንግስቱ
| @GITIM_ALEM
| @GITIM_ALEM


ልባርካችሁ 🙌
እግዚአብሔር እጣችሁን ኢየሱስ ያለበት ያድርግላችሁ ። ስትደክሙ ምትወድቁበት እጁ ይሁንላችሁ።
እውዳችኋለሁ ደህና እያደሩ 🥰


#እሽ
#እስት በኢየሱስ ያገኛችሁት ትልቁ በረከታችሁ ምንድነው ?


ልቀጥል እስት ምትስማሙ 👍


እሽ በመጨረሻም

#ኢየሱስ ለእናንተ ማን ነው?
ያለመነ ሰው ኢየሱስ ማን ነው ለናንተ ብል ምን ትመልሳላችሁ


#5 ኢየሱስ ስሞት ማንን ከመስቀል አውርደው ነው እሱን(ኢየሱስን) የሰቀሉት


ልትቀበሉትስ ብትወዱ፥ ይመጣ ዘንድ ያለው ኤልያስ ይህ ነው። ብሎ ኢየሱስ የመሰከረለት ማንን ነው?


#3 አዲስ ኪዳን ሰንት መጽሐፍትን ይዟል?


#ሐዋርያው ጳውሎስ ስንት መጽሐፍ ነው የጻፈው ?


መልሱ ሉቃስ ነው
ሉቃስ የሉቃስን ወንጌል የጻፈ ሲሆን ይህም ከሌሎች ደቀመዛሙርት እንደሰማ ይነገርለታል👏


የወንጌላትን መጽሐፍ ከጻፉ ሰዎች ከኢየሱስ ጋር ያልነበረው ደቀመዝሙር ማን ነው?

መልሱን comment ✍️


መጽሐፍ ቅዱሳ ጥያቄ ተጀምሯል👏


ተዘጋጅታችኋል ሊጀምር?


የክርስቲና እምነት መሰረትን ያካተቱ 10 ጥያቀዎችን አዘጋጅችያለሁ ጓደኞቻችሁን እንድገቡ አድርጉ 3 :00 ስል ይጀመራል
Share አድርጉ
@gitim_alem

Показано 20 последних публикаций.