የምስራቅ አፍሪካ ባለ ሥልጣናት እና ባለ ሀብቶች ጎፈሬን ጎበኙ!ታላቁ የስፖርት ትጥቅ ብራንድ ጎፈሬ ከኢትዮጵያ አልፎ በአፍሪካ ምህዳሩን እያሰፋ የሚገኝ ሲሆን በተለይ በምስራቅ አፍሪካ ያለውን ተደራሽነት ከፍ በማድረግ ታላላቅ የቀጠናው እንግዶችን አዲስ አበባ በመጋበዝ አዲሱን ፋክተሪ እና ሾው ሩም አስጎብኝቷል።
በትናንትናው ዕለት ከኬንያ እና ዩጋንዳ ሀገራችን ኢትዮጵያ የገቡት የምስራቅ አፍሪካ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች አሶሴሽን እና የዩጋንዳ እግርኳስ ፌዴሬሽን ምክትል ፕሬዝዳንት ሚስተር ጀስተስ ሙጌሻ ፣ የዩጋንዳ ፓርላማ አባል የሆኑት ሚስተር ፓትሪክ ኢሲያጊ፣ በምስራቅ አፍሪካ በሚገኙ ሀገራት ታዋቂ የሆነው የፍሬሽ ዲየሪ ማርኬቲንግ ዳይሬክተር ሚስተር ቪንሰንት ኤድዋርድ ኦሞዝ እንዲሁም የምስራቅ አፍሪካ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች አሶሴሽን ማርኬቲንግ ዳይሬክተር ሚስተር ኦማሪያ ቦስኮ በጎፈሬ መስራች እና ባለቤት አቶ ሳሙኤል መኮንን መሪነት አዲሱን ፋክተሪ የጎበኙ ሲሆን በመቀጠል ደግሞ ስታዲየም አካባቢ የሚገኙትን ሾው ሩም እና ማርኬቲንግ ቢሮዎችን ተዟዙረው ቃኝተዋል። በጉብኝት መርሐ-ግብሩ ላይ የጎፈሬ ቤተሰብ የሆኑት የካፍ ኤሊት ኢንስትራክተር አብርሃም መብራቱ እና ኢንተርናሽናል አልቢትር በዓምላክ ተሰማም ተገኝተዋል።
ከጉብኝቱ በኋላ በቀጣይ ስለሚከወኑ የጋራ ስራዎች ሰፊ ውይይት የተደረገ ሲሆን የስራ ግንኙነት መጀመሩን የሚያበስር መርሐ-ግብርም ተከናውኗል።
@goferesportswear