HAppy Mûslimah


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: Религия


አጫጭር ኢስላማዊ ታሪኮች ብቻ
ONLY SHORT ISLAMIC STORY‼️
Fôr Any Cømments👉 @NihalllAb

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
Религия
Статистика
Фильтр публикаций


የ 200 ብር ካርድ የሚያስሸልም ጥያቄ!

ረሱል ( ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም )
በስንት አመታቸው ነበር ወደ አኼራ የሄዱት ?
ሀ , 51
ለ , 60
ሐ, 63
መ, 40
ረ ,መልስ የለም

🕑ማሳሰቢያ ቀድሞ ለመለሰ ነው🕐




"አንቺ ልጅ ወዴት ነው ጥድፊያው?"

"እማ መድረሣ ነውዋ!"

"በዛሬ ቀን? እቤት ያሉት እንግዳስ ነይ ጊቢ አሁን....." እናት ተቆጣች።
"ምንድነው ምትጨቃጨቁት? እቤት ሰው ተቀምጦ የለ ኧረ አደብ ያዙ ሴቶች" አባት ፊቱን አጨፈገገ።
"ታዲያ ልጅህን ቅጣ እንጂ እንደ አሮጊት ተሸፋፍና መድረሣ መድረሣ ስትል"...
"ዝም ስንልሽ ጭራሽ ባሰብሽ አይደል እንደውም ከዛሬ ጀምሮ አትሄጅም ለወትሮም ለእውቀት ሣይሆን ስራ ላለመስራት ነበር... እንደውም ሂጂ ከእንግዶቹ ፊት ቡና ቁይላቸው!!"

"የፈለጋችሁትን ብላችሁ ብታዙኝም ከጌታዬ መንገድ ግን ልታርቁኝ አትችሉም" እንደ ሁል ቀኗ አባሽ ያጣው እንቧዋን እየጠረገች መንገዷን ቀጠለች.....
.
.
.
.
ይገርማል! ልጆች ወደ እውነተኛው መንገድ በመሄድ ላይ ሣሉ ወላጆች እንቅፋት ሲሆኑባቸው። እንደው እንኳን ከመጥፎ መንገድ አርቀው ፤ ቀጥተኛው መንገድ መምራቱን ባይችሉ፤ በልጆቻቸው ቀናው መንገድን ቢመሩ ምነኛ ያማረ ቤተሰብ ይኖር ነበር።

@heppymuslim29


በአላህ መንገድ ሲታገል ከርሞ ወደ ኮርዶቫ ሲዘልቅ ዕለቱ ዒድ አል አድሀ ጠዋት ነበር። ሙጃሂዶቹ በፈረሶቻቸው ጀርባ ላይ ተፈናጠዋል። በድካም የሚንጠፈጠፈውን ላባቸውን ከግንባራቸው ላይ እየጠራረጉ አቧራና ደም ባጨማለቀው ልብሳቸው ወደ ኢድ መስገጃው ሜዳ በማቅናት ላይ ሳሉ እድሜዋ የገፋች አዛውንት ከሡልጣን መንሱር ፊት ቆማ የፈረሱን ልጓም ይዛ ከመንገዱ በማስተጓጎል እንዲህ ያለችው:-

"በዛሬው የዒድ ቀን ከእኔ በቀር ሁሉም ሙስሊሞች ደስተኞች ናቸው"
ሐጂብ መንሱር ንግግሯን ሲሰማ ደነገጠ "ለምን?" ሲልም ጠየቀ።
ዕንባ ባቀረረው ዓይኗ እየተመለከተችው እንዲህ አለችው "በረባህ ምሽግ ከመስቀል ጦረኞች ጋር ሲፋለም የተማረከ አንድ ፍሬ ሙጃሂድ ልጅ አለኝ እሱ በጠላት እስር ቤት ውስጥ ሆኖ እንዴት መደሰት ይቻለኛል?"

   ሐጂብ ንግግሯን ሲሰማ ፊቱን ወደሠራዊቱ አዞረ። የፈረሱን ልጓም አጥብቆ ያዘና በጂሃድ ሜዳ የአፈር ትቢያውን ገና ላላራገፈው ሙጃሂድ፣ ከድካም ጀርባውን ላላሳረፈው ሠራዊት "ከፈረሳችሁ ላይ እንዳትወርዱ" በማለት ትዕዛዝ አስተላለፈ።

   የፈረሱን ልጓም እየጎተተ ጀርባው ላይ እንደተፈናጠጠ ወደ ረባህ ምሽግ ሰራዊቱን ይዞ ገሰገሰ። የአሮጊቷን ልጅ ጨምሮ ሙስሊም እስረኞችን አስፈትቶ ከተማዋን በድል ከፍቶ ተመለሰ።

ዒዱኩም ሙባረክ
@heppymuslim29


🔊
    ምርጥ ተክቢራ!!

እየሰማችሁም እየከበራችሁም!!
   ከቢሩ…… 🔊አላሁ አክበር
   ከቢሩ…… 🔊አላሁ አክበር
   ከቢሩ…… 🔊አላሁ አክበር


ይህን👇👇👇👇👇ዱዐ
: لا إله إلا الله وحده لا شريك له له الملك وله الحمد وهو على كل شيئ قدير
በጣም አብዝተህ በለው ምክንያቱም የዐረፋ ቀን ከሚባሉ ዱዐዎች ሁሉ የሚበልጥ ዱዐ ነውና

በዱአቹ አትርሱኝ


አስላሙ አሌይኩም ያጀመዓ

አንድ Giveaway ለቤተሰቦች አዘገጅተናል ስጦታውም የአንድ ዓመት ወንጀላችሁን እና የወደፊት የአንድ ዓመት ወንጀልን ነገን በፆም ከሰለፍን የምናገኘው ስጦታ ነው በመቀጣል ሱቢህን ዛሬን ሰግደን ሊነገጋ አከባቢ ላይ ሁለት ረካ ብቻ ከሰገድን ተናፋቅውን መካ መዲና ሄዳን ሀጅ እንደደረግን ይቆጣረል እና ከዚህ የበለጠ ስጦታ አለ ወይ🙄🎁


9ኛው ቀን /ዐረፋ
ከሐጅ ቀናት ሁሉ ትልቁ እና ዋናው ነው። "የዐረፋ ቀን" በመባልም ይታወቃል። በዚህ ቀን ሐጃጆች በተከበረው የዐረፋ ኮረብታ ላይ በመቆየት ዱዓእ ሲያደርጉ ይውላሉ። ዐረፋ ላይ ላልተገኘ ሑጃጅ ላልሆነ ሰው በፆም መዋል ይወደዳል።
ቀኑ ታላቅ ቀን ነው። ቀኑን መፆምም ትልቅ ምንዳ አለው። " ከአላህ ዘንድ የሁለት ዓመት ኃጢአትን ያሰርዛል ብዬ አስባለሁ ።" ብለዋል የአላህ መልዕክተኛﷺ

ዙል-ሂጃ 9 የነገው ቅዳሜ ነውና ዕለቱን
በፆም፣በዚክርና መልካም በተባሉ ስራዎች
እናጅበው።
@heppymuslim29


Copy!!
አረፋህ ሊመን አረፈህ!

ነገ ቤት የማፅጃ ወይ መጋረጃ የማውረጃ ቀን አይደለም። ነገ አላህ የሰማይ ባለሟሎች ላይ በአረፋ ሰዎች የሚኩራራበት፤ የሰው ልጆች ከእሳት በገፍ ነፃ የሚባሉበት ከሁሉ በላይ ዱአዎች በሙሉ ተቀባይነት የሚያገኙበት እለት ነው።

ለይለቱል ቀድር ባትታወቅ የውሙ አረፋ ትታወቃለች። በለይለቱል ቀድር መላእክት ቢወርዱ በአረፋ አላህ (እሱን በሚመጥን አወራረድ) የሚወርድበት ነው!

ነገ አላህ በጊዜ ፀጋ ላጣቀማችሁ አንድ to do list ላካፍላችሁ

ጠዋት

ከፈጅር በፊት ከለይሉ ጥቂቱን መስገድ፣ ስሁር መመገብ እና ኢስቲግፋር ማብዛት!

ከሰላት በኋላ ቀጥታ ተክቢራ መጀመር ከዛም ፀሀይ እስክትወጣ ቁርአን፣ተህሊል፣ተህሚድ በአጠቃላይ በዚክር ማሳለፍ(አዝካረ ሰባህ ሳይረሳ)

ፀሀይ ስትወጣ የፀሃይ መውጣትን ሰላት እዛው ከመስገጃችን ሳንነሳ በመከወን ከረሱሉ (ሰ.ዐ.ወ) ጋር ሀጅ የማድረግን ምንዳ እንጎናጸፍ

ለቀን ኢባዳ ያግዘናል ብለን ካሰብን መጠነኛ እኝቅልፍ እንተኛ። ስንነሳ በትንሹ 4 ረክኣ ሰላተ ዱሃ እንስገድ!

ከሰአት

ከዝሁር ሰላት በኋላ ቁርዐናችንን እንቀራለን። የአረፋ ኹጥባ(ከመስጂደ ነሚራህ የሚተላለፈውን) መልእክት በጥብቅ መከታተል

ልባችንን ሊያረጥብ የሚችል መፅሐፍ ወይም ቪድዮ እንመልከት

ከአስር ቀጥሎ እንዲሁ በቁርአን እና በዚክር መግሪብ 1 ሰአት አቅራቢያ እስኪቀረው ማሰለፍ!

የእለቱ ወሳኝ ሰአት ይህ ነው።
የተሰበረ የሚጠገንበት፤ የታመመ የሚፈወስበት፤ ተስፋ የቆረጠ ተስፋው ነፍስ ሚዘራበት ድንቅ ሰአት!

ዱኣ!!! ዱኣ ብቻ!
በዚህ ቀን ከእሳት ነፃ አለመባል ኪሳራ ነው።

"አረፋ ተራራ ላይ መቆም ያልቻለ
አላህ ያሳወቀው ድንበር ላይ ይቁም

ሙዝደሊፋ ላይ ማደር ያልቻለ
በአላህ ትእዛዝ ላይ ይደር...ያቀርበዋልና!

ሚና ላይ እርዱን መከወን ያልቻለ
ምኞቱን ይረድ! ከፍ ይላልና።

ወደ ቤቱ በርቀት ምክንያት መድረስ ያልቻለ
ከደም ስሩ ቅርብ ወደ ሆነው የቤቱ ጌታ ይከጅል!" ኢብኑ ረጀብ

@heppymuslim29


ሐጀር ወንድ ልጅን በሰላም ተገላግላ የአራስነት ጊዜዋን በቅጡ ሳትጨርስ የነቢዩላህ ኢብራሂም የመጀመርያ ሚስት ሳራ የቅናት መንፈስ አደረባት። አዲሱን ልጅ ከነሚስቱ ራቅ ወዳለ በረሀ ጥሏቸው እንዲመጣ አዘዘችው።

ኢብራሂም ሐጀርንና ኢስማዒልን ይዞ በረሀውን እየሰነጣጠቀ ጉዞ ማድረግ ጀመረ። ከዕልህ አስጨራሽ አድካሚ ጉዞ በኋላ ከምድረ በዳው የዐረብያ ምድር ምንም የሚላስ የሚቀመስ ከሌለበት ተራራ ስር የያዘውን ስንቅ አስቀምጦላቻው ወደ መጣበት ሊመለስ እግሩን አነሳ። "ውሀ እንኳ በሌለበት በዚህ በረሀ ትተከን ለመሄድ ስትነሳ በራስህ ወይስ አላህ አዞህ?" በማለት ጠየቀች ሐጀር።"ከአላህ ታዝዤ" አላትና ዱዓ አድርጎ ወደመጣበት ተመለሰ

ሐጀር ኩርምት ብላ ከበረሐው መሀል ከተመች። አየሩ በጣም ሞቀታማ መሬቱም በንዳዱ ግሏል። የያዘችውም ውሀ አልቆ ጥም አቃጥሏታል። ወደ ሆዷ ያስገባችው ፈሳሽ ባለመኖሩ በአንቀልባዋ የታቀፈችው ልጇ ከጋቷ የወተት ጠብታ ጠፍቶ ረሀቡን መቋቋም አቅቶት እያመረረ ይጮኻል። እናት በጀርባዋ እያዘለች ሌላ ጊዜም በደረቷ እያቀፈች ለቅሶውን እያባበለች በሐዘን ተከዘች።

ልጇን ከድንኳኑ አስተኝታ ከአንዱ ወደ ሌላው ስትሯሯጥ ሰፋ እና መርዋ በተባሉ ተራራዎች ጫፍ ወደሚገኝ ሸለቆ መሐል ደረሰች። ውሀ ፍለጋ በተስፋ እየሮጠች ወደ ሰፋ ተራራ ወጣች ግና አላገኘችም። ወደ ሸለቆው ወርዳ መርዋ ተራራን እየሮጠች ወጣች እርጥበት እንኳ የለም። ከሰፋ ወደ መርዋ ተራራ ለ7 ግዜ ውሀ ፍለጋ በሩጫ እየተመላለሰች ድካሟን መቋቋም በማትችለው ሁኔታ ላይ ደረሰች። ጉሮሮዋ ደረቀ። ውሀ ፍለጋ ዳገት መውጣት ተሳናት። ልጇን ወዳስቀመጠችበት ቦታ አቀናች።

ህፃኑ እያለቀሰ ሲፈራገጥ በእግሩ መሬቱን ሲጭር ከመሬቱ ውሀ ፈልቆ ተመለከተች። ውሀውን ጠጥታ ልጇን አጥብታ ለአላህ ምስጋናዋን አደረሰች።

በውሀ ጥም ተቃጥለው ያንን በረሀ የሚያቋርጡ ነጋዴዎች በድንገት ምንጩን ተመለከቱና ከውሀው በክፍያ ታስጎነጫቸው ዘንድ ለመኗት። ከውሀው ፈቅዳላቸው በምትኩ ተምር ተቀበለቻቸው።

በውሀ ችግር የሚታወቀው የዐረብያ ምድር በሀጀር ምክንያት በፈለቀው የውሀ ምንጭ ወሬው ተጥለቀለቀ። የተለያዩ የዐረብ ነገዶች ከሀጀር አቅራቢያ እየሰፈሩ ቤታቸውን ቀለሱ። አካባቢውንም ገነቡ።

የማወጋችሁ ስለመካ ነው
@heppymuslim29






👉 በነዚህ ውድ ቀናቶች ውስጥ ከሚፈፀሙ ታላላቅ ኢባዳዎች ውስጥ አንዱ ተክቢራ ነው። አላህ በቁርአኑ መልእክተኛው በሀዲሳቸው ተክቢራ በማለት ላይ ከመጠቆምና ከማመላከት ውጪ ይህን ተክቢራ ይበል በሚል የመጣ የተክቢራ አይነት የለም። ስለዚህ አንድ ሰው በየትኛውም አላህ ማላቂያ ተክቢራ ማድረግ ይችላል። ነገር ግን ከቀደምት የዲን ሊቃውንቶች ከሰለፎቻችን የተገኙ የተክቢራ አይነቶች አሉ። እነሱን መጠቀም ግን የተሻለ ይሆናል። ከነዚህ ተክቢራዎች መካከል፦

①) አንደኛ
«الله أكبر، الله أكبر، لاإله إلا الله، والله أكبر، الله أكبر ، ولله الحمد»
♦️ኡመር፣ አልይ፣ ኢብኑ መስኡድ፣ አቡሀኒፋ፣ ሰውርይ፣ ኢስሀቅ፣ ኢብኑ ተይምያ፣ ኢብኑ ረጀብ ሸኽ አልባንይና ኢብኑ ኡሰይሚን ይህንን መርጠዋል።
*ـ•┈┈┈┈•✿❁✿•┈┈┈┈•ـ​*

②) ሁለተኛ
«الله أكبر كبيرًا، الله أكبر كبيرًا، الله أكبر وأجل، الله أكبر ولله الحمد»
♦️ከኢብኑ አባስ ተወርቷል። ኢብኑ አቢሸይባ መርጦታል። አልባንይ ሶሂህ ነው ብለውታል
*ـ•┈┈┈┈•✿❁✿•┈┈┈┈•ـ​*

③) ሶሰተኛ
«الله أكبر كبيرًا، والحمد لله كثيرًا، وسبحان الله بكرة وأصيلا»
♦️ኢማሙ ሻፍእይና ኢማሙ ነወውይ መርጠውታል።
*ـ•┈┈┈┈•✿❁✿•┈┈┈┈•ـ​*

④) አራተኛ
«الله أكبر، الله أكبر، الله أكبر، لا إله إلا الله، والله أكبر، ولله الحمد»
♦️ከኢብኑ አባስ ተወርቷል።
*ـ•┈┈┈┈•✿❁✿•┈┈┈┈•ـ​*

⑤) አምስተኛ
«لا إله إلا الله، والله أكبر، الله أكبر، ولله الحمد".»
♦️ኡመርና ኢብኑ መስኡድ ብለውታል።
*ـ•┈┈┈┈•✿❁✿•┈┈┈┈•ـ​*

⑥) ስድስተኛ
«الله أكبر، الله أكبر، الله أكبر»
♦️ከኢብኑ አባስ፣ ከኢማሙ ማሊክና ሻፍእይ ተወስቷል።
*ـ•┈┈┈┈•✿❁✿•┈┈┈┈•ـ​*

⑦) ሰባተኛ
«الله أكبر، الله أكبر، الله أكبر كبيرًا ".*»
♦️ከሱፍያን ተወርቷል። ኢብኑ ሀጀር መርጦታል።
*ـ•┈┈┈┈•✿❁✿•┈┈┈┈•ـ​*

⑧) ስምንተኛ
«الله أكبر، الله أكبر، الله أكبر، ولله الحمد، الله أكبر وأجل، الله أكبر على ما هدانا»
♦️ከኢብኑ አባስ ተወርቷል። አልባንይ ሶሂህ ነው ብለውታል።

➡️ በተገኘ አጋጣሚ እየቀያየርን በሆነ ጊዜ አንዱ በሌላ ጊዜ ሌላውን መጠቀም እንችላለን።

@heppymuslim29


የዙል-ሒጃህ ማስታወሻ

🔅ዛሬ ሃሙስ ዙል-ቀዕዳህ 29 ሲሆን ምናልባትም ይህ ወር በ29 ካለቀ ነገ ጁሙዓህ ዙል-ሒጃህ 1 ስለሚሆን ኡድሒያ የማረድ እቅድ ያለው ሰው የዛሬ ቀን ጸሐይ ከመጥለቋ በፊት ሰውነት ላይ መነሳት ያለባቸው ጸጉሮችንና ጥፍርን ማንሳት ተገቢ ነው።

🔅ነቢዩ ﷺ በሐዲሣቸው የሚከተለውን ብለዋል፥ "አንዳችሁ ኡድሒያ ለማረድ ካሰበ የዙል-ሒጃህ ወር ከገባ በኋላ እርዱን እስኪፈጽም ድረስ ከጸጉሩና ከጥፍሩ ምንም አይንካ (አያንሳ)"

🔅ይህን ትዕዛዝ እንደ ግዴታ በማየት "ኡድሒያ የሚያርድ ሰው የዙል-ሒጃህ ጨረቃ ከታየበት ጊዜ አንስቶ የዒድ ሰላት ተሰግዶ እስኪታረድ ድረስ ጸጉርና ጥፍርን መቁረጥ ክልክል (ወንጀል) ነው" የሚሉ ሊቃውንት ስላሉ ከወዲሁ ጥፍርንና በሸሪዓህ የሚፈቀድን ጸጉር ማንሳት ይገባል።

🔅ይህ ህግ የሚመለከተው ኡድሒያ የሚያርደውን አባወራ ብቻ ነው።

@heppymuslim29


🕋 አስር ቁም ነገሮች ስለ ዙል ሒጃ አስር ቀናቶች

=========================

// የተለየ ደረጃ እንዳላቸው ሚጠቁሙ ማስረጃዎች//

❶ በነዚህ አስር ለሊቶች አላህ ቁርአን ላይ ምሎባቸዋል።
{ﻭَﺍﻟْﻔَﺠْﺮِ . ﻭَﻟَﻴَﺎﻝٍ ﻋَﺸْﺮٍ } ‏[ ﺍﻟﻔﺠﺮ 2-1: ‏]
(( በንጋት እምላለ ⓵ በአስሩም ለሊቶች ⓶))
{ሱረት ፈጅር 1-2}

ኢብን ከሲር በዚህ የቁርአን አየቀፅ የተፈለገው አስሩ የዙል ሒጃ እንደሆነ ይጠቅሳል። ይህንን ደግሞ ኢብን አባስ: ኢብን ዙበይር: ሙጃሒድ እና ሌሎችም ብለውታል።

❷ በሀዲስም እንደመጣው የአላህ መልእክተኛ ﷺ እንዲህ ብለዋል

‏« ﻣﺎ ﺍﻟﻌﻤﻞ ﻓﻲ ﺃﻳّﺎﻡ ﺃﻓﻀﻞ ﻓﻲ ﻫﺬﻩ ﺍﻟﻌﺸﺮﺓ ‏»
>
ጅሀድም ቢሆን? ብለው ሰሀቦች ጠየቋቸው።
አሏቸው። {ቡኻሪ ዘግቦታል}

❸ አላህ እንዲህ ማለቱ

ﻭَﻳَﺬْﻛُﺮُﻭﺍ ﺍﺳْﻢَ ﺍﻟﻠَّﻪِ ﻓِﻲ ﺃَﻳَّﺎﻡٍ ﻣَّﻌْﻠُﻮﻣَﺎﺕٍ { ‏[ ﺍﻟﺤﺞ 28: ‏]
(( አላህንም በታወቁት ግዜያቶች ሊያወሱ)) {ሀጅ 28}

ኢብን አባስ አሱሩ ቀናቶች ብሎ ፈስሮታል

❹ በሌላ ሀዲስም እንደመጣው የአላህ መልእክተኛ ﷺ እንዲህ ብለዋል

‏« ﻣﺎﻣﻦ ﺃﻳّﺎﻡ ﺃﻋﻈﻢ ﻋﻨﺪ ﺍﻟﻠﻪ ﺳﺒﺤﺎﻧﻪ ﻭﻻ ﺃﺣﺐ ﺇﻟﻴﻪ ﺍﻟﻌﻤﻞ ﻓﻴﻬﻦ ﻣﻦ ﻫﺬﻩ ﺍﻷﻳﺎﻡ ﺍﻟﻌﺸﺮ، ﻓﺄﻛﺜﺮﻭﺍ ﻓﻴﻬﻦ ﻣﻦ ﺍﻟﺘﻬﻠﻴﻞ ﻭﺍﻟﺘﻜﺒﻴﺮ ﻭﺍﻟﺘﺤﻤﻴﺪ ‏» . ‏( ﺭﻭﺍﻩ ﺍﻟﻄﺒﺮﺍﻧﻲ ﻓﻲ ﺍﻟﻤﻌﺠﻢ ﺍﻟﻜﺒﻴﺮ ‏)
> {ኢማሙ ጠበራኒ ዘግበውታል}

➠ ኢብን ሀጀር እንዲህ ይላል

"ያ ግልፅ የሚሆነው አስሩ የዙልሒጃ ቀናቶች ከሌሎች የተለዩበት ምክንያት የኢባዳ እናቶች ስለ ተሰበሰቡበት ነው እነሱም #ሰላት_ፆም_ሰደቃ_ሀጅ ይህ በሌላ ግዜ አይመጣም።

========================

// በነዚህ አስር ቀናቶች የሚወደድ ተግባር//

--------- ❺ ሰላት

_ዋጅብ ሰላት ላይ ከሌላው ግዜ በበለጠ መልኩ ይበልጥ መጠናከር ሱና ሰላትንም ማብዛት ይወደዳል።
_ምክንያቱም ሰላት ከትልልቆቹ መልካም ስራዎች መሐከል ነው በነዚህ ቀናቶች ደግሞ መልካም ስራ አብዙ ተብሏል

-------- ❻ ፆም

____ መልካም ስራ ከሚለው ውስጥ ፆምም ስለሚገባ። የአላህ መልእክተኛም ዘጠኙን የዙልሒጃ ቀናቶች ይፆሙ እንደነበር የመጣ ሐዲስ ስላለ
_ኢማመ ነወዊ ዘጠኙን የዙልሒጃ ቀናቶች መፆም የጠነከረ ሱና መሆኑን ይገልፃሉ

---------- ❼ ተክቢራን ማብዛት

____ ከላይ ተራ ቁጥር ❹ ላይ የጠቀስነው ሀዲስ ለዚህ በቂ ማስረጃ ነው። ኢብን ኡመርና አቡ ሑረይራ ወደ ሱቅ ወጥተው ተክቢራ ያደርጉ ነበር ሰዎችም የነሱን ተክቢራ ሰምተው ተክቢራ ያደርጉ ነበር።

ተክቢራውን ጮክ ብሎ ማለቱ ይወደዳል

------------ ❽ ከሰሀቦች እና ታብእዮች የመጡ የተክቢራ አይነቶች

◅ﺍﻟﻠﻪ ﺃﻛﺒﺮ، ﺍﻟﻠﻪ ﺃﻛﺒﺮ، ﺍﻟﻠﻪ ﺃﻛﺒﺮ ﻛﺒﻴﺮًﺍ .
◅ ﺍﻟﻠﻪ ﺃﻛﺒﺮ، ﺍﻟﻠﻪ ﺃﻛﺒﺮ، ﻻ ﺇﻟﻪ ﺇﻻّ ﺍﻟﻠﻪ، ﻭﺍﻟﻠﻪ ﺃﻛﺒﺮ، ﻭﺍﻟﻠﻪ ﺃﻛﺒﺮ، ﻭﻟﻠﻪ ﺍﻟﺤﻤﺪ .
◅ ﺍﻟﻠﻪ ﺃﻛﺒﺮ، ﺍﻟﻠﻪ ﺃﻛﺒﺮ، ﺍﻟﻠﻪ ﺃﻛﺒﺮ، ﻻ ﺇﻟﻪ ﺇﻻّ ﺍﻟﻠﻪ، ﻭﺍﻟﻠﻪ ﺃﻛﺒﺮ، ﺍﻟﻠﻪ ﺃﻛﺒﺮ، ﻭﻟﻠﻪ ﺍﻟﺤﻤﺪ .


---------❾ የአረፍ ፆም

____የሁለት አመት ወንጀል እንደሚያስምር ኢማም ሙስሊም በዘገቡት ሀዲስ ላይ መጥቷል

ﻗﺎﻝ ﻋﻦ ﺻﻮﻡ ﻳﻮﻡ ﻋﺮﻓﺔ : ‏« ﺃﺣﺘﺴﺐ ﻋﻠﻰ ﺍﻟﻠﻪ ﺃﻥ ﻳﻜﻔﺮ ﺍﻟﺴﻨﺔ ﺍﻟﺘﻲ ﻗﺒﻠﻪ ﻭﺍﻟﺴﻨﺔ ﺍﻟﺘﻲ ﺑﻌﺪﻩ ‏» ‏( ﺭﻭﺍﻩ ﻣﺴﻠﻢ ‏) .

---------❿ ሰደቃ

_ መልካም ስራ በነዚህ ቀናቶች የተወደደ ነው ተብሏል። ሰደቃም ደግሞ ከመልካም ስራዎች ውስጥ ነው።

@heppymuslim29


አንድ ልጅ አባቱን "የፈጣሪ መጠን ምን ያህል ነው?" ሲል ጠየቀው።

ከዚያም አባትየው ወደ ሰማይ አሻቅቦ አውሮፕላን ተመለከተና ልጁን "የዛ አውሮፕላን መጠን ምን ያህል ነው?" ሲል ጠየቀው።

ልጁም "በጣም ትንሽ ነው። እምብዛም አይታይም" መለሰ።

አባትየው ወደ አውሮፕላን ማረፊያ ወሰደውና እየተጠጉት "እና አሁን የዚህኛው መጠን ምን ያህል ነው?" ጠየቀው።

ልጁ "ዋው አባቴ ይህ ግዙፍ ነው" መለሰ።

አባቱ "ፈጣሪም እንዲህ ነው። መጠኑ በአንተና በእርሱ መካከል ባለው ርቀት ይወሰናል። ወደ እሱ በቀረብክ መጠን እርሱ በህይወትህ ውስጥ ግዙፍ ይሆናል" አለው ይባላል ።

@heppymuslim29


"ለይላ …በጀነት እና እሣት መካከል"

ያለፈችበት ፈተና ብዙ ቢሆንም ነፍሷ እንድትቆሽሽ ግን አንድም ቀን ፈቅዳ አታውቅም፡፡ እንኳን ሰው አየሩም በተበከለበት ዘመን ብዙዎች ሲለወጡ፣ በርካቶች ከአቋማቸው ሲወርዱና በወንጀል ዉሽንፍር ሲመቱ እሷ ግን አልተለወጠችም፡፡ በጥንካሬዋ ኖረች፣ በትጋቷ ቀጠለች …

ያልሠጧት ሥም የለም፡፡ ጎታታ፣ ጀዝባ፣ ያልገባት፣ ጥሬ፣ አስመሳይ፣ ሌባ …

‹ለቁምነገር ነው የምንፈልግሽ › እያሉ ይቀጥሯታል፡፡

እሷ የሚመጣላት ቁምነገር አንድ ብቻ ነው - ‹ ትዳር› ፡፡ ….. መስሏትም ትሄዳለች። ወፍ የለም...

የነሱ ቁምነገር ደግሞ ሌላ ነው ‹ ዝሙት› ፡፡ ቀለል አድርገው ሲጠይቁ ደግሞ ግርም ይላታል፡፡ ዉይ ወንዶች ትላለለች መልሳ፤ በጅምላ ትሞልጫቸዋለች …

ትቀርባለች፣ ትግባባለች፡፡ ሄደው ሄደው የሆነ ቦታ ላይ ሲደርሱ ሰበብ ፈልገው ይጣሏታል፡፡ በዚሁ ምክንያት ማጣት የማትፈልጋቸውን ብዙ ወንድሞች አጥታለች፡፡ በራሷ ነገር ሲጣሏት ይዐጅባታል። እስቲ ሐራም እንጂ ምን ቀረባቸው? እንደውም ከጥፋት ስላዳንኳቸው ሊያመሰግኑኝ ሲገባ ትላለችም፣ ትጠይቃለችም።

ሰው ናትና አንዳንድ ጊዜ ድክም ይላታል፡፡ የሀሳብ ተመሳሳዮቿ ሲመናመኑ ይከፋታል። ብቸኝነት ይሰማታል፡፡ ኮንፊደንሷ እንደመሸርሸር ይላል፡፡ ጥንካሬዋ ያረገርጋል፤ ወኔዋ ሊከዳት ይደርሳል፡፡ ዓላማዋም ሊፈርስ ይቃረባል፡፡ ጫፍ ደርሣ የተመለሠችባቸው ጊዜዎች እጅግ ብዙ ናቸው፡፡

ትወዛገባለች፣ ግራ ይገባታል … ከራሷ ጋር ታወራለች፡፡ ወደፊት ትራመዳለች፣ ወደኋላ ትመለሣለች፡፡ መልሳ ጥርሷን ትነክሳለች .. ልብሴን የኔ ላልሆነ ወንድ አላወልቅም! ገላዬንማ አላረክስም!፤ በማንም ገልቱ አልነጀስም! ገና ለገና ያገባኛል ብዬማ አልጋደምም!፣ ባገኘሁበት አልወድቅም!፡፡

ከሁለት ስሜቶቿ ጋር ትታገላለች፡፡ አንደኛው …ባንች የተጀመረ አይደለም፣ አዲስ ነገር አልሠራሽም፣ ሁሉም የሚያደርገውን ነው ያደረግሽው፣ አታካብጂ ቀለል አድርገሽ እዪው … ይላታል፡፡ ያስመስልባታል። ይወተውታታል… በዚህ ምላሣቸው ቅቤ የሆኑ ወንዶች፤ በዚያ ፈታ በይ ዘና ብለው የሚሰብኩ ተንኮለኞች በየአጋጣሚው ይፈታተኗታል፣:ያዳክሟታል፣ ይገዘግዟታል፡፡ ያወሯታል፤ አትስማማም፡፡ ሊንቋት፣ ሊስቁባት፣ ሊያፌዙባት ይሞክራሉ፡፡ ቀረብሽ፣ ጅል ይሏታል፡፡ አንዳንዴ ትጠራጠራለች … ‹ እውነት ሞኝ ነኝ እንዴ! ...ትክክል አይደለሁም እንዴ?› ብላ ከራሷ ጋር ትፋጠጣለች፡፡ደግሞ የገዛ ዉስጧ ያንሾካሹክበታል፤ በግራ በኩል ይመጣባታል …. ጊዜሽን ተጠቀሚ፣ በወጣትነትሽ ዘና በይ፣ ሞኝ አትሁኚ አትጃጃዪ ….

በቀኝ ደግሞ ኡስስ ይላታል፡፡ ፈጣሪሽን ልታስቆጪ ነው፣ ስብእናሽን ልታወርጂ ነው፣ ራስሽን ልታስንቂ፣ ክብርሽን ልታዋርጂ ነው፡፡

ከራስ ጋር ከተደረገ የብዙ ጊዜ ግብግብ በኋላ ግን አንድ ቀን ለመሸነፍ ቆረጠች፡፡ ለመሸነፍም ይቆረጣል ለካ! … አዎን ቆረጠች፡፡ የሆነ ቀን …

ገላዋን ታጠበች፣ ልብሷን ቀየረች......። መልሳ ራሷን ጠየቀች .. ሰው ወደ ቆሻሻ ነገር ሊሄድ ብሎ እንዴት ሰውነቱን ይታጠባል! ዝሙት ፊት ለመቅረብ እንዴት ንፁህ ሆኖ ይሄዳል? ወደ መስጊድ የሚሄድ ይመስል ሰው እንዴት ለንፅሕናው ይጨነቃል! … ራሷን ታዘበች፣ ራሷን በንቀት ቁልቁል አየች፣ ተጠየፈች። እያወራች፣ እየታገለች ለባብሳ ጨረሠች፡፡

ከቤቷ ወጣች፣ ለመጀመሪያ ጊዜ ግራ ቀኟን ተመለከተች፡፡ ሰው ሁሉ ወዴት እንደምትሄድ የሚያውቅባት መሠላት፡፡ ተመለሽ፣ ተመለሽ አላት፡፡ ዉስጧ ቢታገላትም ሀሳቧን እየተከላከለች ወደፊት ገሠገሠች፡፡ ነፍስያና ሸይጣን አጀቧት፤ አይዞሽ እያሉ ሽኟት።

ከጌታዋ ተነጥላ እየሄደች እንደሆነ ተሠማት፣ ከጉያው የራቀች ያህል በረዳት.... ቀዘቀዛት። ከሱ የምትለይበት የመጨረሻ ቀን መሆኑ ታወቃት፡፡ ፈጣሪዋ እያታዘባት፣ መላዕክትም እየረገሟት እንደሆነ ታያት ….

ሄደች... በሩ ላይ ደረሠች፡፡ ልታንኳኳ እጇን ሠነዘረች ፡፡ ለአፍታ ቆም ብላ አሠላሠለች፤ የፈፀመች ያህል ተሰማት፡፡ ለመጀመሪያ ጊዜ ባዕድ የሆነ ወንድ ልትነካ ነው፤ ስታስበው ሠቀጠጣት፡፡ አባጨጓሬ የነካች ያህል ቅፍፍ አላት፡፡ ይህን አላህ የጠላውን ነገር ባደርገው እሺ ጀነት ጀሀነሙ እንኳን ይቅር ከዚያ በመለስ ኑሮዬ አዕምሮዬ ሰላም ይሠጠኛል? ቆሜስ መሄድ እችላለሁ ወይ? ብላ ጠየቀች። ከቁጥጥር ውጭ ሆነች። እሪ! አለች ድንገት፡፡ ብንን ብላ ብታይ ግራ ቀኟን ብታይ ሰው የለም፡፡
አዑዙ ቢላህ! … አዑዙ ቢላህ … እያለች ፊቷን አዞረች፡፡ ጫማዋን አውልቃ ሮጠች። ትንፋሿ ቁርጥ ቁርጥ ይላል …እንዴት እንደደረሠች ሳታውቅ ቤቷ ደረሠች፣ ተንደርድራ ክፍሏ ገባች፣ አልጋዋ ላይ ተደፋች ስለ መጥፎ ሀሳቧ አምላኳን ተማፀነች፣ ይቅር እንዲላትም አልቅሳ ለመነች፡፡

ቀጥላም ፎከረች፡፡ በእልህና በቁጭት ሞገተች፡፡ …
ሐራምን እንቢ ባልኩና ሐላልን በመረጥኩ እስቲ ሲጥለኝ አያለሁ!፣ እስቲ የምኞቴን እንደማይሠጠኝ እታዘባለሁ!፡፡ ካልተሳካልኝ፣ ጥሩ ትዳር ካልተመሰረትኩ ... ታዲያ እኔ ምኑን አመንኩ!፣ ምኑን አምላክ አለኝ ብዬ ተማመንኩ!!

ትልቅ እፎይታና እርጋታ ተሰማት፡፡ ከታላቅ ዉድቀት መዳኗ ታወቃት። የኩራት ፈገግታ ፈገግ አለች፡፡ ዳግም ወደ ጠንካራ ሀሳቧ ተመለሠች፡፡

ሐላል ካልሆነ ጥንቅር ብሎ ይቅር!
አምላኬን ከማስቆጣ
ሺህ ዓመት ቆሜ ልቅር!!
.....

@heppymuslim29


በአቀራሩ መላዕክት የተገረሙበት ሶሃባ
ኡሰይድ ኢብኑ ሁደይር (ረዲየሏሁ አንሁ)
➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖

ኡሰይድ ኢብኑ ሑዶይር በአንድ ምሽት የቤት ውስጥ ሥራዎቹን በመፈፀም ላይ ነበር። የሕያ የተባለ ልጁም ከጎኑ ተኝቷል።ጥቂት ፈንጠር ብሎም ለጂሃድ የተዘጋጀ ፈረሱ ታስሯል። ሌሊቱ ነፋስና ውሽንፍር የሌለበት ፀጥ ያለ ነበር። የከዋክብቶች ዓይን መሬትን በአትኩሮት የሚመለከቱ ይመስላሉ። ኡሰይድ ይህን ግርማ ሞገስ የተላበሰ ሌሊት ቁርኣን በማንበብ ሊያስጌጠው ፈለገ። ማንበቡን ጀመረ።

«አሊፍ ላም ሚም ዛሊከል ኪታቡ ላ ረይበ ፊህ… … ዩቂኑን።»

ፈረሱ ቁርኣን ሲሰማ የታሰረበትን ገመድ እስኪበጥስ ድረስ በደስታ ዘለለ። በሁኔታው የተገረመው ኡሰይድም ዝም አለ። ፈረሱም እንቅስቃሴውን አቆመ። ማንበቡን ቀጠለ፡-

«ኡላኢከ ዐላ ሁደን ሚን ረብቢሂም ወኡላኢከ ሁሙል ሙፍሊሑን።»

ፈረሱ አሁንም የደስታ እንቅስቃሴውን ቀጠለ። ካለፈው በበለጠ ሁኔታ። ኡሰይድ ዝም አለ። ፈረሱም እንዲሁ ይህንኑ ድርጊት ደጋግሞ ፈጸመ።
ፈረሱም ምላሽ መስጠቱ አልቀረም፡፡ ቁርኣን ማንበቡን ሲቀጥል ፈረሱም ደስታውን ይቀጥላል። ሲያቆም ደግሞ እርሱም እንቅስቃሴውን ይገታል። ልጁ የሕያን ፈረሱ እንዳይረግጥበት በመስጋቱም ሊቀሰቅሰው ተጠጋ። በቅጽበት ወደ ሰማይ እይታውን አቀና። ታይቶ የማይታወቅ ጽልመታዊ ዳመና አስተዋለ። በደመናው ላይ
የተንጠለጠለ የሚመስል ብርሃን መታየት ጀመረ። ከአድማስ አድማስ ብርሃን ፈነጠቀ። ይህ ብርሃን ግን ከእይታው እስኪሰወር ድረስ ወደ ላይ እየራቀው ሄደ።

🌅ሲነጋ ወደ መልዕክተኛው ﷺ በመሄድ ያጋጠመውን ክስተት አወሳላቸው።

«መላእክት ናቸው። አንተን ሲያዳምጡ ነበር ኡሰይድ ሆይ! ማንበብህን ብትቀጥል ኖሮ ለሰዎች ግልጽ በሆነ መልኩ በታዩ ነበር።»

አጂብ!!!
📒:سور من حياة الصحابة
@heppymuslim29


የተራዊሕ ለቅሶ ይፈቀዳል ወይስ አይፈቀድም?

ቀናት እየነጎዱ ነው፡፡ ረመዷን በተለይ ከ15 ቀን በኋላ አትደርሱብኝም፣ አትይዙኝም…. በሚል መልኩ እየፈረጠጠ ነው፡፡ የረመዷን ወዳጆችም ረመዷን ከማለቁ በፊት በስስት እያለቁ ነው፡፡

የማታውን ተራዊሕ በሁለት በሁኔታቸው የተለያዩ የአላህ ባሮች መካከል ነበር ቆሜ የሰገድኩት፡፡ የቁኑት ዱዓእ ላይ ስንደርስ በቀኜ በኩል የነበረው ተንሰቅስቆና ድምፅ አውጥቶ ማልቀስ ጀመረ፡፡ በግራዬ በኩል ያለው ደግሞ አሁንም አሁንም የአልቃሹን ሁኔታ የጎሪጥ አሻግሮ ይመለከታል፡፡ አልተመቸው ይሆን? ምን ይነፋረቅብናል? እያለ ይሆን … ብቻ ዉስጡን ባላውቅም ሀሳቡ እንደተሰረቀና ተረጋግቶ መስገድ እንዳልቻለ በግልጽ ያስታውቃል፡፡

በሶላት ወቅት አላህ ዘንድ ያለን ደረጃ የሰማይ እና የምድር ያህል የሚራራቅበት ሁኔታ አለ፡፡ አልቃሹ ይሁን ዝም ባዩ በላጩን የሚያውቀው አላህ ብቻ ነው፡፡

ቁርኣንን ሰምቶ መልእክቱ እያስተነተኑ ማልቀስ ነቢያዊ ሱና ነው፡፡ በአንድ ወቅት ነቢዩ (ሰ.ዐ.ወ.) ለዐብደላህ ኢብኑ መስዑድ “ቁርአንን አንብብልኝ” አሉት፡፡ “በርስዎ ላይ ወርዶ እንዴት አነብልዎታለሁ?” አላቸው፡፡ “ከሌላ ሰው መስማት ደስ ይለኛል” አሉት፡፡ ከአን-ኒሳእ ምዕራፍ አነበበላቸው፡፡ “ወጂእና ቢከ ዐላ ሃኡላኢ ሸሂዳ” የሚለው አንቀጽ ላይ ሲደርስ “ይብቃህ” አሉት፡፡ ዘወር ሲሉ ዐብደላህ የረሱሉን ሰ.ዐ.ወ. ፊት ተመለከተ፡፡ ዐይናቸው በእንባ ርሶ ነበር፡፡ ያለ ድምፅ እንባቸው ዝምብሎ ይፈስ ነበር።

በቁርኣን ማንባት የአላህ መልካም ባሮች ምልክት ነው፡፡ አላህ ሱ.ወ. ሲገልፃቸው  “የአልረሕማን አንቀጾች በነሱ ላይ በተነበቡ ጊዜ ሰጋጆችና አልቃሾች ኾነው ይወድቃሉ፡፡” ይላቸዋል፡፡ (መርየም ፡58)

ቁርኣን ሲነበብ ማልቀስ ሕያው ቀልብ መሆን ምልክት ነው፡፡ አልቃሾችም የአላህ ፍራቻ የሰረፀባቸው ናቸው፡፡ በሶላት ላይ ቁርኣንን ሰምቶ ማልቀስ የተከለከለ አይደለም፡፡ ሶላትንም አያበላሽም። የርሳቸው ለቅሶ ድምፅ ያወጣ አልነበረም፡፡ ሳቃቸዉም እንደዚያው ነው ይላሉ አንዳንድ ዑለሞች፡፡ ድምፅ የለውም።

ቁርኣንን ሲያነቡ አናቅፁን እያስተነተኑ የጀመሩትን መጨረስ የሚከብዳቸው ብዙ ነበሩ፡፡ አቡበክር ረ.ዐ. ለሶላት ሲቆሙና ቁርኣንን ሲያነቡ ከለቅሶ የተነሳ ድምፃቸው በትክክል አይሰማም ነበር ይባላል፡፡ ዑለሞቹ በቁርኣን እንደሚለቀሰው ሁሉ መልዕክቱን እያሰቡ በዱዓ ማልቀሱም ችግር የለውም ብለዋል፡፡

በሁሉም ዉስጥ ግን መጠንቀቁ ተገቢ ነው‼️ ነፍስያ እንዳትጫወትብን፣ ዒባዳችን ለይዩልኝና ይስሙልኝ እንዳይሆን ራስን መቆጣጠር ያስፈልጋል፡፡ ቀደምት ደጋግ የአላህ ባሮች ለቅሶአቸው እንዳይታይባቸው በእጅግ ይጠነቀቁ ነበር፡፡ አንድ ቀን ሳይታወቅባቸው ዕድሜ ልክ ያለቀሱ ነበሩ። አላህን አስታዉሳ በድብቅ ማንም በሌለበት ያለቀሠች ዐይን ለጀነት የታጨች መሆኗንም ነቢዩ ሰ.ዐ.ወ. ተናግረዋል፡፡

የምንለምነው አምላክ ሰሚ፣ ተመልካች እና ሁለመናችንን አዋቂ ነው፡፡ ስለሆነም ብሶታችንና ሓጃችንን ለማሰማት የግድ መጮህ አይጠበቅብንም። ዱዓችንም ሆነ ለቅሶአችን በድብቅ ቢሆን ይመረጣል፡፡ አላህ (ሱ.ወ.) እንዲህ ይላል “ ጌታችሁን ተዋርዳችሁ በድብቅም ለምኑት እርሱ ወሰን አላፊዎችን አይወድምና፡” (አል-አዕራፍ 55)

የአላህ ባሮችን አታልቅሱ ማለት ይከብዳል፡፡ ግና በተለይ በጀማዓ በሚሰገድበት ወቅት ለቅሶው ድምፅ የማይወጣበት ሌሎችን በማይረብሽና ትኩረት በማይሰርቅ ከራስ ጋር በሆነ መልኩ ቢሆን ይመረጣል፡፡  በለቅሶ የሚሸነፍና የማያስችለው ሰው ከሆነ ግን ምንም ማድረግ አይቻልም፡፡
ወሏሁ አዕለም

@heppymuslim29


ከአጠገቤ የተቀመጠ ልጅ ነው። በግምት አስራ ሁለት / አስራ ሶስት አመት ይሆነዋል። የልጅ መዳፎቹን ዘርግቶ መለመን ይዞዋል። ጠበቅኩት። እንደ ልጅኛ ከማስበው በላይ ዱዐውን አርዝሞታል። ሲጨርስ ምን ብለህ ዱዐ አደረግክ? ብዬ ጠየቅኩት
.
በልጅነት ጥርሶቹ ፈገግታውን እያካፈለኝ " ለኔ እና ለእናቴ የሚለፋን ሰው ጠብቀው።" እያልኩኝ ነበር አለኝ።
የልጁ አባት ይህንን ጊዜያዊ አለም ተሰናብተው ከሄዱ አመታት አልፈዋል። የቲም ነው።
ልጅ የህይወት ሽንቁራቸውን ለመሙላት ለሚጥር ሰው የዱዐ መዳፎቹን ዘርግቶ ይለምናል።
:


በረመዳን ላይ የቲሞችን እናስታውስ። እንዘይር። ከተትረፈረፈው ምግብ እናካፍል። መስጠት ውስጥ ሰላምን መሰጠት አለ። የቲሞችን መንከባከብ የሀቢበላህን ጉርብትናን የሚያስገኝ ተግባር ነው። የቲሞችን እናስታውስ..
በፍቅር መዳፍ እንደባብሳቸው...
ባዶነትን፣ ብቸኝነታቸውን ገሸሽ እናድርግላቸው። ስለ ማፍጠሪያቸው እንዳይጨነቁ እናድርግ።

@heppymuslim29

Показано 20 последних публикаций.