Фильтр публикаций


ማስታወቂያ


ማስታወቂያ
-----
ለእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች በሙሉ


"ዓድዋ የጥቁር ህዝቦች ድል ” በሚል መሪ ቃል የዓድዋ ድል በዓል በእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ተከበረ፡፡
----
የካቲት 21/2017ዓ.ም፤ እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ

በበዓሉ የዓድዋ ድል ተግዳሮቶች ፣ትሩፋቶች እና አስተምሮቶች፣The Dramatic Irony Of Ethiopia’s victory at Adwa እና የዓድዋ ድል እሳቤ እና ትውልድ፣በክብርት ዶ/ር እጅጋሁ ሽባባው ሙዚቃ የሚሉ ጥናታዊ ጽሁፎች ቀርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል፡፡

በበዓሉ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ምርምርና ማህበረሰብ አገልግሎት ም/ፕሬዝዳንት ክንዴ ብርሃን (ዶ/ር) "ዓድዋ የጥቁር ህዝቦች ድል” በሚል መሪ ቃል ስናከበር የዓድዋ ድል የነጭን የተሳሳተ የዘረኝነት እና የበላይነት አስተሳሰብ በመሰረታዊነት የቀየረ የጥቁር ህዝቦች ሁሉ የድል በዓል በመሆኑ ብለዋል፡፡ ዶ/ር ክንዴ አያይዘውም እኛ ኢትጵያዊያን የዓድዋ ድልን በየዓመቱ ከመዘከር ባሻገር አንድነታችንን እንደ ትናንት የአድዋ ጀግኖች አባቶቻችንና እናቶቻችን ማጠናከር እና የዓድዋ ድልን የይቻላል መንፈስን በመላበስ ተከባበብረንና እጅ ለእጅ ተያይዘን ጠንካራ ሀገር እንድትኖረን የድርሻችንን ልንወጣ ይገባል ብለዋል፡፡
https://www.facebook.com/100069178971700/posts/pfbid02xPH9Wj2AZHABEh543oHArX89jNxnhSMToNwsSmsHb7NCJAoKPWj21V8eki2dCacal/?app=fbl


እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ከቻግኒ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ጋር የመግባቢያ ስምምነት ሰነድ ተፈራረመ።
-----
የመግባቢያ ስምምነት ሰነዱ ሁለቱ ተቋማት በጋራ ለመስራት በሚያስችሏቸው ጉዳዮች ዙሪያ ያተኮረ መሆኑ ተገልጿል።
በፊርማ ስነ ስርዓቱ ላይ የተገኙት የምርምርና ማህበረሰብ አገልግሎት ም/ፕሬዝደንት ክንዴ ብርሃን (ዶ/ር) ዩኒቨርሲቲው ከዚህ ቀደም ከእንጅባራ ጠቅላላ ሆስፒታል እና ከአማራ ክልል ጤና ቢሮ ጋር የመግባቢያ ስምምነት ሰነድ መፈራረሙን አስታውሰው የጤና ሳይንስ ተማሪዎችን በንድፈ ሃሳብ ከሚማሩት በተጨማሪ በተግባር የተደገፈ ትምህርት ለመስጠት ከአቅራቢያ ሆስፒታሎች ጋር ለመስራት በሚያግዝ መልኩ የስምምነት ሰነዱ ፊርማን አስፈላጊነት ተናግረዋል።

የቻግኒ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ስራ አስኪያጅ አቶ አዳነ ገበየሁ በበኩላቸው የሰምምነት ሰነዱ የአካባቢውን ማህበረሰብ ጤና ከማሻሻሉ በተጨማሪ የሆስፒታሉን ደረጃ የሚያሳድግልን ነው ሲሉ ተናግረዋል።

የስምምነት ሰነዱ አጠቃላይ ሃሳብ የህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ዲን በሆኑት ዳንኤል አዳነ (ረ/ፕሮፌሰር) የቀረበ ሲሆን ዓላማውም በሁለቱ ተቋማት መካከል የመማር ማስተማርን፣ጥናትና ምርምርን፣የማህበረሰብ አገልግሎትን፣የመድሃኒትና የቁሳቁስ ድጋፎችን እና የአቅም ግንባታ ስልጠናዎችን ያካተተ ነው።

በስምምነት ፊርማ ስነ ስርዓቱ ላይ የዩኒቨርስቲው ከፋተኛ አመራሮች እና የቻግኒ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ኃላፊዎች እንዲሁም የህክምና እና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ መምህራን እና የሚመለከታቸው አካላት ተገኝተዋል።
የካቲት 20/2017 ዓ.ም እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ


"የማዕድን ሀብት ልማት ለሀገራችን የኢኮኖሚ ግንባታ!" በሚል መሪ ቃል ከአጋር አካላት ጋር የውይይት
መድረክ ተካሄደ፡፡

የካቲት 20/2017 ዓ፣ም፤እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ

እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ የምህድስና እና ቴክኖሎጂ ኮሌጅ ከማዕድን ልማት ዘርፍ ባለድርሻ አካላት ጋር ማዕድን
ልማት ላይ ያተኮረ የውይይት መድረክ አካሂዷል፡፡

በውይይቱ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ምርምርና ማህበረሰብ አገልግሎት ምክትል
ፕሬዝዳንት እና የፕሬዝዳንት ጽህፈት ቤት ተወካይ ክንዴ ብርሃን(ዶ/ር) ዪኒቨርሲቲው የማዕድን ሀብት ዙሪያ
ለመስራት የማዕድን ዘርፍን ለማሳደግ እና በቴክኖሎጂ ለመደገፍ የማዕድንን ትምህርት ክፍል በመክፈት የተማረ የሰው ሀይል በማፍራት፣ ጥናት እና ምርምር በማድረግ፣ ስልጠና በመስጠት እና ማህበረሰቡ
ከዚህ ዘርፍ ተጠቃሚ እንዲሆን እንደሚሰራ ተናግረዋል፡፡

ዶ/ር ክንዴ አያይዘውም የዚህ መድረክ ዓላማ የኒቨርሲቲው ያለውን የተማረ የሰው ሀይል ተጠቅሞ በሀገራችን፣ በክልላችን እና በብሄረሰብ አስተዳደሩ የሚገኙ ጠቃሚ የማዕድን ሀብት ማውጣት በሚቻልበት ሁኔታ ላይ መነጋገር፣ መወያየት እና አቅምን መገንባት አስፈላጊ በመሆኑ ነው ብለዋል፡፡ ውይይቱ
ያሉንን ሀብት ለመለየት፣ እንዴት መጠቀም እንደሚቻል፣ ለሚያጋጥሙ ችግሮች መፍትሄዎችን ለመፈለግ እና በቀጣይ በማዕድን ልማት ዙሪያ በጋራ መስራት ስለሚቻልበት ሁኔታም ለመምከር የሚያስችል መሆኑንም ጨምረው ገልጸዋል፡፡
https://www.facebook.com/100069178971700/posts/pfbid0cLjmbK8Kf2CRsFPqf7Fj9oSdMKJwEubgiB8sc1cC7NQmGUV1DsBrk3Hnu2HuqNrFl/?app=fbl


ማስታወቂያ
-----
ለርቀት ትምህርት አመልካቾች በሙሉ፦



Показано 7 последних публикаций.