#update
" ዓቃቢ ህግ በፍርድ ቤቱ በኩል ውሳኔ ከተላለፈ በኃላ ይግባኝ በመጠየቅ ክሱ በዞኑ ከፍተኛ ፍርድ ቤት በኩል እንዲታይ ተደርጓል" - የወምበራ ወረዳ ፍትህ ጽ/ቤት
" ይህንን የፍርድ ዉሳኔ የሰጠዉ ዳኛ ከስራና ከደመወዝ ታግዶ እንዲቆይና ጉዳዩ በኮሚቴ ተጣርቶ እንዲቀርብ ትእዛዝ ተሰጥቷል " - የቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ጠቅላይ ፍ/ቤት
በወምበራ ወረዳ ፍ/ቤት ከዚህ ቀደም ስሙ ያልተጠቀሰው ' ተክለአብ ገለታ ' የተባለው ተከሳሽ የ5 አመት ህጻን ልጅ በመድፈር ወንጀል ተከስሶ #በ6ወር እስራት እንዲቀጣ መወሰኑ ይታወሳል።
ከጉዳዩ ጋር በተያያዘ የወረዳው ፍርድ ቤት ያስተላለፈው ውሳኔ አግባብ አለመሆኑንና አስተማሪነቱን ባለመቀበል ዓቃቢ ህግ በፍርድ ቤቱ በኩል ውሳኔ ከተላለፈ በኃላ #ይግባኝ መጠየቁን የወምበራ ወረዳ ፍትህ ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ መልካሙ አመንቴ ገልፀዋል።
ጉዳዩን አስመልክተው ለወረዳው ኮሚዩኒኬሽን ማብራሪያ የሰጡት የፅህፈት ቤቱ ሃላፊ የወረዳው ፍርድ ቤት ባስተላለፈው የቅጣት ውሳኔ ከተፈፀመው ወንጀል ጋር ተመጣጣኝና አስተማሪ ባለመሆኑ ይግባኝ ተጠይቆ ክሱ በዞኑ ከፍተኛ ፍርድ ቤት በኩል እየታየ መሆኑን አስረድተዋል።
ይህንን ተከትሎ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ጠቅላይ ፍ/ቤት የመዝገቡን የክስ ሂደት ማጣራትና ማስተካከያ እርምጃ እንዲወሰድ ለጉዳዩ ትኩረት በመስጠት ወደ መተከል ዞን ከፍተኛ ፍ/ቤት ኮሚቴ በመላክ ጉዳዩ በአስቸኳይ እንዲጣራ ኮሚቴ መላኩን አሳውቋል።
ጠቅላይ ፍ/ቤቱ " ይህንን የፍርድ ዉሳኔ የሰጠዉ ዳኛ ከስራና ከደመወዝ ታግዶ እንዲቆይና በኮሚቴዉ ጉዳዩ ተጣርቶ ሲቀርብ ቀጣይ በዲስፕሊን ታይቶ በክልሉ ዳኞች አስተዳደር ጉባኤ ተገቢውን የእርምት እርምጃ ይወሰዳል " ብሏል።
የተፈፀመው የወንጀል ድርጊት ቅጣት ማነስ ጋር በተያያዘ ጉዳዩ በመተከል ዞን ከፍተኛ ፍ/ቤት በይግባኝ እየታየ መሆኑን ያረጋገጠው የክልሉ ጠቅላይ ፍ/ቤት የሚሰጠውን ዉሳኔ በቀጣይ መረጃዉን ይፋ እንደሚያደርግ አሳውቋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ መረጃውን ከወምበራ ኮሚኒኬሽን እና ቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ጠቅላይ ፍ/ቤት እንዳገኘው ያሳውቃል።
@TikvahethMagazine