⚖Ethiopian law by Daniel Fikadu Law office⚖


Гео и язык канала: Эфиопия, Английский
Категория: Право


ዳንኤል ፍቃዱ ተስፋዬ በሁሉም የፌደራል ፍርድ ቤቶች ጠበቃና የህግ አማካሪ
ስልክ - 0913158507 ወይም 0978554559
Daniel Fikadu Tesfaye Certified Attorney of law at all Federal Courts of Ethiopia.
Email- nurotekore@gmail. Com
⚖️⚖️Ethiopian Law by Daniel Fikadu channel ⚖️⚖️⚖️

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Английский
Категория
Право
Статистика
Фильтр публикаций






በእስር ላይ የሚገኘው ጆን ዳንኤል የሚባለው ድምጻዊና ቲክቶከር፣ በማረሚያ ቤት ውስጥ ከሌሎች እስረኞች ጋር በስልክ የተነሳቸው ፎቶ ግራፎች በማህበራዊ ሚዲያ መሠራጨቱን ተከትሎ፣ የማረሚያ ፖሊስ ፎቶውን የተነሱበትና የተለቀቀበትን ስልክ አግኝቻለሁ፣ በእስረኞቹ ላይም እርምጃ እወስዳለሁ ብሏል።

የፌዴራል ማረሚያ ቤት "ቅጣት የሚሰጠውን" መመሪያ ዛሬ እንደገና ለሕዝብ ይፋ አድርጓል። ለግንዛቤ እንዲረዳ ይኸው፦

⚫ በፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን የሕግ ታራሚዎችና የቀጠሮ እስረኞች በተሻሻለ የሥነ ስርዓት ጥፋት ቅጣት አፈፃፀም መመሪያ ቁጥር 5/2009 በክፍል 02 አንቀጽ 11 ቁጥር 35 የተከለከሉ ነገሮችን ማለትም (ጫት፣ ተቀጣጣይ ነገሮች፣ ስልክ፣ ሲም ካርድ ፣ ሲጃራ፣ ጋንጃ፣ ቡሪ፣ አንጋዳ፣ አልኮል መጠጥና …ወዘተ) ወደ ማረሚያ ቤትና ማረፊያ ማዕከል ለማስገባት መሞከር ወይም የገባውን መጠቀም የሚያስከትላቸው የቅጣት አይነት፡-
⚫ ለ4 ወር እንዳይጎበኝ መከልከል ወይም
⚫ ለ3 ወር ለብቻ ለይቶ ማሰር ወይም
⚫ ከ5 ወር ከ1 ቀን አስከ 6 ወር ለሚደርስ ጊዜ በማረሚያ ቤት ሆኖ ሥራ በመስራት ከሚያገኘው ገቢ 1/3ኛውን በመቀነስ ሥራ ማሰራት ወይም ማግኘት ከሚገባው የአመክሮ እስራት 3/4ኛውን መከልከል፡፡

🔴ቁጥር 36 የተከለከሉ ነገሮች (አደንዛዥ እጽ፣ ጦር መሳሪያ እና ተቀጣጣይ ነገሮች ወደ ማረሚያ ቤት እና ማረፊያ ማዕከል ለማስገባት መሞከር ወይም አስገብቶ መገኘት ወይም ሌሎች እንዲያስገቡ መተባበር፣ ወይም ጉዳት ማድረስ (በወንጀል ያለው ተጠያቂነት እንደተጠበቀ ሆኖ) የሚያስከትለው የቅጣት አይነት፡-
🔴 ለ4 ወር እንዳይጎበኝ መከልከል ወይም ፣
🔴 ለ3 ወር ለብቻ ተለይቶ መታሰር ወይም፣
🔴ከ5 ወር ከ1 ቀን እስከ 6 ወር ለሚደርስ ጊዜ ከሚያገኘው ገቢ 1/3ኛውን በመቀነስ ሥራ ማሰራት ወይም ማግኘት ከሚገባው የአመክሮ እስራት 3/4ኛውን መከልከል፡፡

🔵ቁጥር 37 የተከለከሉ ነገሮች (ሀሺሽ፣ ፈንጂ፣ እና ተቀጣጣይ ነገሮች…ወዘተ) ወደ ማረሚያ ቤት እና ማረፊያ ማዕከል ለማስገባት መሞከር ወይም ማስገባት ወይም የገባውን መጠቀም የወንጀል ተጠያቂነት እንደተጠበቀ ሆኖ የሚያስከትለው የቅጣት አይነት፡-

🔵ለ4 ወር እንዳይጎበኝ መከልከል ወይም ፣
🔵ለ3 ወር ለብቻ ለይቶ ማሰር ወይም፣
🔵ከ5 ወር ከ1 ቀን እስከ 6 ወር ለሚደርስ ጊዜ በማረሚያ ቤት ሆኖ ከሚሰራው እና ከሚያገኘው ገቢ 1/3ኛውን በመቀነስ ሥራ ማሰራት ወይም ማግኘት ከሚገባው የአመክሮ እስራት 3/4ኛውን መከልከል፣ የሚሉት ይገኙበታል፡፡(ዘ-ሐበሻ መረጃ)


ከ5 ሺህ በላይ ሰራተኞች ውላቸው እንዲቋረጥ መመሪያ ተሰጠ።

ጤና ሚኒስቴር በሲዲሲ እና ዩኤስኤይድ (USAID) ድጋፍ የተቀጠሩ ከ5 ሺህ በላይ ስራተኞችን ውል እንዲቋረጥ መመሪያ ሰጠ።

ጤና ሚኒስቴር ከአሜሪካ መንግሥት በሲዲሲ (CDC) ወይም ዩኤስኤይድ (USAID) አማካኝነት በተገኘ የበጀት ድጋፍ የሚከናወን ማንኛውም ስራም ሆነ ክፍያ እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር ከጃንዋሪ 24 ,2025 ጀምሮ እንዲቋረጥ ማሳሰቢያ እንደደረሰው ገልጿል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ የተመለከተው እና በጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ደረጀ ዱጉማ ተፈርሞ ለሁሉም የክልል ጤና ቢሮዎች የተሰራጨው ደብዳቤ " በጤና ሚኒስቴር ድጋፍ የተቀጠሩ እና ተቋማችሁ ከCDC ወይም USAID ጋር በሚያደርገው ውል መሰረት የተቀጠሩ ሰራተኞችን በተመለከተ ስራ ላይ እንዲውል አሳስባለሁ " ይላል።

ዶ/ር ደረጀ ዱጉማ የደብዳቤውን #ትክክለኛነት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አረጋግጠዋል።

ሚኒስትር ዴኤታው በሰጡን ተጨማሪ ማብራሪያ በመላው ሃገሪቱ በሲዲሲ እና ዩኤስኤይድ አማካኝነት በኮንትራት እያገለገሉ ያሉ ሰራተኞች ቁጥር 5 ሺህ እንደሚሻገር ገልጸዋል።

ሚንስትሩ " ሰው እንዲዘጋጅ ነው እንጂ የአሜሪካ መንግሥትም ሃሳቡን ሊቀይር ይችላል የተቀየረ ነገር ካለ የሚቀጥል ይሆናል አሁን ባለው ሁኔታ ግን ድጋፉን ካቋረጠ ሌላ መፍትሄ ማፈላለግ ያስፈልጋል " ብለዋል።

" ለዚህ ደግሞ ሰራተኞቻችን እንዲዘጋጁ ከመንግስት ጋርም ንግግር እየተደረገ ነው ያለው የመንግስት ሰራተኞች ስራውን እንዲያስቀጥሉ የCDC እና USAID ሰራተኞች ስራውን እንዲያቆሙ ተወስኗል " ብለዋል።

ሚኒስትር ዴኤታው በዝርዝር ምን አሉ ?

" እኛን በዋናነት የሚመለከተን በጀቱ በቀጥታ በእኛ በኩል ስለሚመጣ የሲዲሲ ሰራተኞችን ነው ዩኤስኤይድ ግን ቅጥር የሚያከናውነው በራሱ በኩል ነው ውሉንም የሚያቋርጡት ራሳቸው ናቸው።

የአሜሪካ መንግሥት ሃሳቡን ቀይሮ ሌላ መረጃ የሚያስተላልፍ ከሆነ እኛም ሌላ መረጃ የምናስተላልፍ ይሆናል አሁን ባለው የአሜሪካ መንግስት ውሳኔ ግን ኮንትራታቸውን ማቋረጥ አስፈላጊ በመሆኑ ይህንን ደብዳቤ አስተላልፈናል።

ከ5 ሺ በላይ ይሆናል ትክክለኛ ቁጥራቸውን ለማወቅ መረጃ የመሰብሰብ ስራ እየሰራን ነው ሁሉም በኮንትራት ናቸው ኮንትራታቸው በየአመቱ ይታደሳል ስራቸውም ከኤች አይ ቪ ጋር የተገናኙ ስለሆነ አብዛኞቹ የቆዩ ሰራተኞች ናቸው።

በጣም አስፈላጊ በመሆናቸው ነበር በዚህ ያህል በጀት ተቀጥረው ሲሰሩ የነበረው 15 እና 20 ዓመት የሞላቸውም አሉ ስራው ላይ ችግር ሊያመጣ ይችላል።

በአንድ ጊዜ ይሄን ያህል ሰው ከሴክተሩ ከተቀነሰ ችግር ሊፈጠር ይችላል ዋናው ነገር ግን ስራው እንዳይስተጓጎል ሃላፊነቱን ላለው የመንግስት ሰራተኛ እያስተላለፉ መሄድ ያስፈልጋል።

ቀላል ስራ አይደለም የሚጠብቀን የሚቻለውን ሁሉ እናደርጋለን።

የመጨረሻ ውሳኔዎችን አልሰማንም ከአሜሪካ መንግሥት በየጊዜው የተለያዩ ውሳኔዎች እየተላለፈ ስለሆነ ዛሬ ሌላ ነገ ሌላ ነው የሚባለው ሁሉም የአፍሪካ ሃገራት ተመሳሳይ ነገር ነው እያደረጉ ያሉት ከሁሉም ጋር ውይይት እየተደረገ ነው።

የዓለም ጤና ድርጅትም በቦርድ ደረጃ ከሁሉም የአፍሪካ ሃገራት ጋር ውይይቶችን እያደረገ ይገኛል።

ሰራተኞችም እንዲያውቁ እኛም ጫናውን ለማሳወቅ እና መፍትሄው አብሮ ለመፈለግ እንዲቻል ለመንግሥትም አሳውቀናል ስራ እንዳይጎዳ ከፍተኛ ጥንቃቄ ይደረጋል።

በዚሁ ከቀጠለ ሌላም ከባባድ ውሳኔዎች ሊወሰን ይችላል የመድኃኒት ግዢ እና ሌሎችም ድጋፎች ሊቋረጡ ይችላሉ አይታወቅም እንዳይቋረጥ እና እንዲቀጥል እኛም እንደሃገር የምንችለውን ጫና እናደርጋለን።


ከዩ.ኤስ.ኤይድ የገንዘብ ድጋፍ የሚያገኙ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ሃብትና ገንዘብን ለሶስተኛ ወገን እንዳያስተላልፉ ማስጠንቀቂያ ተሰጠ

****
በአሁኑ ወቅት ከዩ.ኤስ.ኤይድ የገንዘብ ድጋፍ የሚያገኙ ድርጅቶች በማናቸውም መልኩ ሃብትና ገንዘብን ለሶስተኛ ወገን ማስተላለፍ የተከለከለ መሆኑንና ይህነ በሚተላለፉ ተቋማት ላይ እርምጃ እወዳለሁ ብሏል።

ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ለሁሉም የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች በጻፈው እና ለካፒታል በደሰረዉ ደብዳቤ ላይ እንደተገለፀዉ ያለ ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ግልፅ ፍቃድ ንብረት የማስተላለፍ፣ የማስወገድ ወይም የመሸጥ ወይም ከመደበኛ/ፕሮጀክት ስራዎች ጋር ተያያዥ በሆኑ ጉዳዮች ላይ ብቻ እንዲንቀሳቀሱ ጠይቋል።

ይሁን እንጂ በማናቸውም መልኩ ሃብትና ገንዘብን ለሶስተኛ ወገን ማስተላለፍ የተከለከለ መሆኑን የገለፀው ባለስልጣኑ ይህንን ማሳሰቢያ በመተላለፍ በሚንቀሳቀሱ ድርጅቶች ላይ ተገቢውን እርምጃ እንደሚወስድ ጠቁሟል።

ከሰሞኑ በአሜሪካ ተራድኦ ድርጅት (ዩ.ኤስ.ኤይድ) በኩል የእርዳታ ማቆም ውሳኔ ጉዳዩን በቅርበት እየተከታተለ መሆኑንና ዝርዝር ሁኔታዎችን መሰረት በማድረግ በቀጣይ አስፈላጊው ድጋፍና ክትትል የሚያከናዎን መሆኑን ተቆጣጣሪ አካሉ አስታውቋል ።#CapitalNews


capital market amharic.pdf
268.2Кб
የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለስልጣን adv.


foundamental principles of evidence law.pdf
4.0Мб
⚖️ 𝟭𝟬 𝗙𝘂𝗻𝗱𝗮𝗺𝗲𝗻𝘁𝗮𝗹 𝗣𝗿𝗶𝗻𝗰𝗶𝗽𝗹𝗲𝘀 𝗼𝗳 𝗘𝘃𝗶𝗱𝗲𝗻𝗰𝗲 𝗟𝗮𝘄: 𝗔 𝗚𝘂𝗶𝗱𝗲 𝘁𝗼 𝗦𝘁𝗿𝗲𝗻𝗴𝘁𝗵𝗲𝗻𝗶𝗻𝗴 𝗟𝗲𝗴𝗮𝗹 𝗔𝗿𝗴𝘂𝗺𝗲𝗻𝘁𝘀 📜

Evidence law serves as the backbone of justice, ensuring that courts rely on admissible, credible, and relevant information. I’m excited to share "10 Fundamental Principles of Evidence Law", which provides a structured understanding of how evidence is evaluated in legal proceedings.

🔑 𝗞𝗲𝘆 𝗣𝗿𝗶𝗻𝗰𝗶𝗽𝗹𝗲𝘀 𝗖𝗼𝘃𝗲𝗿𝗲𝗱 𝗶𝗻 𝘁𝗵𝗲 𝗚𝘂𝗶𝗱𝗲:
✅ 𝗥𝗲𝗹𝗲𝘃𝗮𝗻𝗰𝗲 𝗮𝗻𝗱 𝗔𝗱𝗺𝗶𝘀𝘀𝗶𝗯𝗶𝗹𝗶𝘁𝘆 – Only evidence that directly impacts the case is accepted.
✅ 𝗕𝘂𝗿𝗱𝗲𝗻 𝗼𝗳 𝗣𝗿𝗼𝗼𝗳 – Understanding who must prove what in different legal situations.
✅ 𝗣𝗿𝗲𝘀𝘂𝗺𝗽𝘁𝗶𝗼𝗻 𝗼𝗳 𝗜𝗻𝗻𝗼𝗰𝗲𝗻𝗰𝗲 – A cornerstone principle in criminal trials.
✅ 𝗛𝗲𝗮𝗿𝘀𝗮𝘆 𝗥𝘂𝗹𝗲 – Why second-hand information is often inadmissible.
✅ 𝗕𝗲𝘀𝘁 𝗘𝘃𝗶𝗱𝗲𝗻𝗰𝗲 𝗥𝘂𝗹𝗲 – Ensuring original and primary sources are presented in court.


በሞት የተለዩ ተጠርጣሪዎችን ንብረት እንዲወረስ የሚያደርገው የንብረት ማስመለስ አዋጅ ተግባራዊ ሊደረግ ነው‼️
ምንጩ ያልታወቀ ንብረትን በተመለከተ ተጠርጣሪው በሞት ቢለይ ወይም ከሀገር የሸሸ ቢሆንም ንብረቱ እንዲታገድና ጉዳዩ ተጣርቶ ግለሰቡ በሌለበት እንዲወረስ እንደሚደረግ ተገለፀ፡፡

በአዲሱ የንብረት ማስመለስ አዋጅ በጥፋተኝነት ላይ ያልተመሰረተ የንብረት ማስመለስ አዋጁ እንደሚያካትት ሲገለፅ ይህም ተጠርጣሪው በሞት ቢለይ ወይም ከሀገር የሸሸ ቢሆን ንብረቱ እንዲሁ የሚቀር ሳይሆን እንዲታገድና ጉዳዩ ተጣርቶ ግለሰቡ በሌለበት እንዲወረስ ይደረጋል ሲል ፍትህ ሚኒስትር አስታውቋል።

የጸደቀው የንብረት ማስመለስ አዋጅ ተፈጻሚ ሲሆንም ምክንያታዊ ያልሆኑ ክሶች እንዳይመጡ ተጠርጣሪው ግለሰብ ስለ ጉዳዩ ቀርቦ እንዲያስረዳ ዕድል የሚሰጥና በፍርድ ቤት ትዕዛዝ ብቻ ተፈጻሚ የሚሆን ነውም ብሏል።

አዋጁ በህገ-ወጥ መንገድ በወንጀል የተገኘ ንብረትን በአግባቡ በማስመለስ የሀገርንና የህዝብን ሀብት ከወንጀል ለመጠበቅ የሚሰራበት ነው ተብሏል።

የማይመለስ ጉዳት ማለትም ንብረቱ ከሃገር ሊሸሽና ሌሎች ተመሳሳይ ጉዳት ደርሶ ከሆነ ጊዜያዊ እግድ በራሱ በፍትህ ሚኒስቴር ያለፍርድቤት ትዕዛዝ እንደሚሰጥም ተገልጿል።

አዋጁ አንድ ግለሰብ በቅን ልቦና ባለማወቅ ንብረቱ ህገ-ወጥ መሆኑን ሳያውቅ የገዛ ቢሆን ንብረቱ እንዳይወረስ ተገቢውን ጥበቃ የሚሰጥ ነው ተብሏል።

በአዋጁ ላይ በተደነገገው መሰረትም ህገ-ወጥ ንብረት በማፍራት የተጠረጠረ ሰው ያለደረሰኝ በሰውም ሆነ ሌሎች ያስረዱልኛል ባላቸው ማስረጃዎች ጥፋተኛ አለመሆኑን ማስረዳት የሚያስችል መመሪያ እንዳለውም ተነስቷል።

አዋጁን ለማስፈጸም ከተለያዩ ሀገራት ጋር በትብብር የሚሰራ ሲሆን ንብረቱ ኢትዮጵያ ቢሆንም በውጭ ሀገራት በህገ-ወጥ መንገድ የተገኘ መሆኑ ከተረጋገጠ ለማስመለስ የሚሰራበት ነው ተብሏል።


የስልጠና ፕሮግራም ፤

*******

የኢትዮጵያ ፌደራል ጠበቆች ማህበር ባለፈው ህዳር ወር በኡጋንዳ ካምፓላ በተደረገው 29ኛው ጉባኤ በታሪክ ለመጀመሪያ ግዜ የ ምስራቅ አፍሪካ የህግ ማህበረሰብ ን East African Law Society በአባልነት መቀላቀሉ እና የማህበራችን መሪ አቶ ቴዎድሮስ ጌታቸው የተቋሙ የበላይ አመራር Governing Council አባል ሆነው መመርጣቸው ይታወሳል::

ይህንኑ ተከትሎም ትብብሩ ለኢትዮጵያውያን የህግ ባለሙያዎች የተሻሉ እድሎችን እንዲያስገኝ የተለያዩ ተግባራት እየተከናወኑ ይገኛሉ:: ከነዚህም በ EALS የሚዘጋጁ አለምአቀፍ ስልጠናዎች ዋነኞቹ ሲሆኑ የባለሙያዎችን አቅም በመገንባት ረገድ የተሻለ ጥቅም የሚያስገኙ ናቸው::

በመሆኑም ነገ ማክሰኞ ጥር 27 ቀን 2017ዓ.ም በኢትዮጵያ ሰአት አቆጣጠር ከቀኑ 8:00 ሰአት ጀምሮ " በግል ዳታ/መረጃ አጠባበቅና የህግ ባለሙያዎች ሚና" The Critical Role of Advocates in Personal Data Protection and Privacy." በሚል ርእስ ዌብናር ይካሄዳል:: መላው የማህበሩ አባላት ከዚህ በታች በተመለከተው መስፈንጠሪያ ሊንክ በመመዝገብ በስልጠናው እድል እንድትጠቀሙ ጥሪ እናቀርባለን::

ቀጣይ የስልጠና ዝርዝር ፕሮግራሞችን አስከትለን የምናሳውቅ ይሆናል::

🔒 How Safe Is Your Personal Data?

In today’s digital world, personal data is a valuable asset—but are we doing enough to protect it? ⚖️🔍

Join us TOMORROW for a thought-provoking webinar on "The Critical Role of Advocates in Personal Data Protection and Privacy." 📜💼

In partnership with Hilton Law, this exclusive session will uncover:
✅ The hidden risks in data collection & processing
✅ Legal loopholes & enforcement challenges in East Africa
✅ How advocates can drive real change in data protection

🔗 REGISTER HERE now: http://bit.ly/EALS-DPP-Webinar

Don’t miss this crucial conversation! 🚀

መረጃውን #share #like በማድረግ እንድታጋሩልን እንጠይቃለን::

መረጃዎች በፍጥነት እንዲደርሷችሁ ገፃችንን በሚከተለው መስፈንጠሪያ ይቀላቀሉ::

የሊንክደን ገፃችን LinkedInn Page - https://www.linkedin.com/company/ethiopian-federal-advocates-association/

ፌስቡክ- https://www.facebook.com/ethiopianbarassociation?mibextid=9R9pXO

የቴሌግራም ገፅ- https://t.me/ethiopianfederalbarassociation

የኢትዮጵያ ፌደራል ጠበቆች ማህበር
ጥር 26 ቀን 2017ዓ.ም
አዲስ አበባ ፤


*Law Scholarships In UK 2025 World-Class Education*
Apply Link: https://learningplateform.org/law-scholarships-in-uk/
We will try to cover everything including Eligibility Criteria, the application process, frequently asked questions, and best practices to follow to win these scholarships So let’s get started.


"አገር በሕግና በሕግ አግባብ ብቻ እንድትመራ እንታገላለን"

የጣሪያ ግድግዳ/የንብረት ግብር ተብሎ የወጣውን መመሪያ አስመልክቶ ፍርድ ቤት ባሳለፈው ውሳኔ ላይ የእናት ፓርቲ መግለጫ።

እናት ፓርቲ የአዲስ አበባ ከተማ ፋይናንስ ቢሮ ላይ ክስ የመሰረተው ሐምሌ 17 ቀን 2015  ሲሆን በቀን 29/2/2016 ችሎቱ ክሳችንን እንድናሻሽል ብይን በመስጠቱ ክሳችንን አሻሽለን አቅርበናል። ስለሆነም የክሱ ሂደት ምን እንደነበረና ምን እንደሚመስል  በየደረጃው የነበሩ ክርክሮችን በተመለከተ በጥቅሉ በዚህ መግለጫ እናቀርባለን።
የክሱ ምንነት፦ የንብረት ግብር ማስተባበሪያ ጊዜያዊ ፕሮጀክት ጽ/ቤት አጥንቶ ያቀረበውና በአዲስ አበባ ፋይናንስ ቢሮ አማካይነት ሚያዚያ 3 ቀን 2015 በተጻፈ ደብዳቤ ሸኝነት ለሁሉም የከተማው አስተዳደር መዋቅሮች የተላለፈው የንብረት ግብር መመሪያ ሕግን ባልተከተለ መንገድና የከተማ አስተዳደሩ ባልተሰጠው ስልጣን የወጣ መመሪያ በመሆኑ ፓርቲያችን የአዲስ አበባ ከተማ ሕዝብን በመወከል መመሪያው እንዲሻርልን ለፍርድ ቤቱ ክሳችንን አቅርበናል።

የክሱ አመሰራረት፦ እናት ፓርቲ ለኢትዮጵያ ሕዝብ መብት መከበር በሰላማዊ ፖለቲካ ለመታገል በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የተመዘገበ አገራዊ ፓርቲ ሲሆን በማንኛውም የኢትዮጵያ ዜጋ ላይ  በደል አጋጥሟል ብሎ ሲያስብ ፖለቲካውን በፖለቲካ ሂደት፤ ፍትሕ ማግኘት የሚገባውን ጉዳይ ደግሞ ወደ ፍርድ ቤት አቅርቦ የመከራከር ሕገ መንግስታዊ መብት እንዳለን በሕገ መንግሥቱ አንቀጽ 37 ን.አ. 2 በግልጽ ተደንግጓል። ስለሆነም ይህ ሕገወጥ የጣሪያ ግድግዳ/የንብረት ግብር በአዲስ አበባ ሕዝብ ላይ በዘፈቀደ የተጫነ በመሆኑና እናት ፓርቲም ለሕዝብና በሕዝብ የተቋቋመ ፓርቲ እንደመሆኑ ሕዝቡ ላይ የፍትህ በደል ሲደርስ ሕግ እንዲከበር ዜጎች መብታቸው እንዳይጣስ ተገቢውን ሰላማዊ ትግል የማድረግ ግዴታ ያለበት በመሆኑ የአዲስ አበባን ሕዝብ በመወከል የወጣው የንብረት ግብር መመሪያ የሕግ መሠረት የሌለውና በሕግ ሥልጣን ሳይሰጠው ያወጣው መመሪያ በፍርድ እንዲሰረዝ ለፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ አስተዳደር ችሎት የቀረበ ክስ ነው።

ተጠሪ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር እናት ፓርቲ ለመሠረተው ክስ ሶስት የመጀመሪያ ደረጃ መቃዎሚያ ያቀረበ ሲሆን እነሱም 1ኛ ፓርቲው የከስ ምክንያት የለውም  2ኛ የቀረበው ክስ ፓርቲው መብትና ጥቅማቸው አረጋግጠው ያቀረቡት ክስ አይደለም 3ኛ ክሱ በይርጋ የታገደ ነው በማለት ወደ ፍሬ ነገር ክርክር ሳይገባ ውድቅ ተደርጎ መዝገቡ ሊዘጋ ይገባል በማለት ተከራክረዋል።

ፍርድ ቤቱ ተጠሪ ላቀረበው የመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያ የሚከተለውን  ብይን ሰጥቷል፦ የመጀመሪያውን መቃወሚያ በተመለከተ የከስ ምክንያት የለውም የሚለውን አስተዳደሩ ሚያዚያ 3 ቀን 2015 ያወጣው የንብረት ግብር የሕግ መሰረት የሌለውና መመሪያ እንዲያወጣ በሕግ ስልጣን ሳይሰጠው ያወጣው መመሪያ በፍርድ ሊሰረዝ ይገባል የሚል ሲሆን ይህ ደግሞ በአዋጁ መሰረት የክስ ምክንያት ያለው ስለሆነ በዚህ ጉዳይ የቀረበው መቃወሚያ ፍርድ ቤቱ እንዳልተቀበለው ብይን ሰጥቷል።

በሁለተኛ ደረጃ የቀረበው መቃወሚያ ፓርቲው ያቀረበው ክስ መብትና ጥቅማቸውን አረጋግጠው ያቀረቡት ክስ  አይደለም የሚል  ሲሆን ፍርድ ቤቱም ፓርቲው ህዝብን መሠረት አድርጎ የተቋቋመ  ፓርቲ በመሆኑ የህዝብ መብትን ጥቅም ለማስከበር እና ህግ ለማስከበር ክስ ለመመስረት መብትና ጥቅም ስላለው በዚህ ዙሪያ የቀረበውን መቃወሚያ  ፍርድ ቤቱ አልተቀበለውም።

በሦስተኛ ደረጃ አስተዳደሩ ያቀረበው መቃወሚያ  ፓርቲው ያቀረበው ክስ በይርጋ ሊታገድ ይገባል የሚል  ሲሆን ፍርድ ቤቱም የአስተዳደር መመሪያ እንዲሰረዝ የሚቀርብ አቤቱታ  በማንኛውም ጊዜ መቅረብ እንደሚችል  በዚህ ጉዳይ ላይ የይርጋ ተፈጻሚነት የለውም በማለት የአዲስ አበባ ፋይናንስ ቢሮ ያቀረበውን ሶስቱንም መቃወሚያዎች ፍርድ ቤቱ ውድቅ በማድረግ  ወደ ፍሬ ጉዳይ ክርክር ታሻግሯል።

የክስ መስማትና የፍሬ ነገር ክርክር፦ ዋናው ክስ ሰኔ 5 ቀን 2016 በፍሬ ነገር ላይ ቀደም ብሎ የቀረበው የጽሑፍ መከራከሪያ ነጥባችንን በማጠናከር የቃል ክርክር አድርገናል። ተጠሪ የአዲስ አበባ አስተዳደር ፋይናንስ ቢሮም በኹለት አቃብያነ ሕግ ተወክሎ ቀደም ሲል በጽሑፍ ያቀረቡትን  የመከራከሪያ መልስ በቃልም እየተጋገዙ ተከራክረዋል። ሦስቱ ዳኞችም በርካታ ጥያቄዎችን በመጠየቅ የራሳቸውን ግንዛቤ ወስደዋል።

የፍርድ ቤቱ ፍርድና ውሳኔን በተመለከት፦ ችሎቱ ጉዳዩን መርምሮ እልባት ለመስጠት ጭብጦች ይዟል።  
በዚሁ መሠረት በተጠሪ(የአዲስ አበባ ፋይናንስ ቢሮ)  ሚያዝያ 3 ቀን 2015 በተጻፈ ደብዳቤ ወደ ትግበራ እንዲገባ የተደረገውና በንብረት ክፍል ማስተባበሪያ ጊዜያዊ ፕሮጀክት ጽ/ቤት  የተዘጋጀው የንብረት ግብር ማሻሻያ ጥናት ሰነድ መመሪያ መሆኑን፤ መመሪያውም በፌደራል ሥነ ሥርዓት አዋጅ ቁጥር 1182/15 ውስጥ የተደነገገዉን የመመሪያ አወጣጥ መርሆችን በመከተል የወጣ አለመሆኑን፤ መመሪያው የወጣውም የንብረት ግብር አዋጅ ባልወጣበትና ተጠሪ መሥሪያ ቤት ስልጣን ሳይኖረው የወጣ መሆኑንና ይህ የንብረት ግብር  ለማሻሻል በሚል የተደረገው ጥናት  በእነዚህ ምክንያቶች ተከልሶ ሕጋዊነቱን የሚያጣ መሆኑን ችሎቱ ደምድሟል።

በመጨረሻም ሚያዝያ 3 ቀን 2017 ዓ.ም. በደብዳቤ ቁጥር ፋ/ቢ2/64/2249 በፋይናንስ ቢሮ በኩል ወደ ተግባር እንዲለወጥ የተጻፈው የግብር ማሻሻያ ጥናት ሰነድ በፍርድ ቤቱ መመሪያ መሆኑ ስለተረጋገጠ በፌደራል አስተዳደር ስነ-ስርዓት አዋጅ ቁጥር 1182/2013 አንቀጽ 56(2) መሠረት ተፈጻሚነት ሊኖረው አይገባም ተብሎ መመሪያው እንዲሻር ፍርድ ቤቱ ጥር 9 ቀን 2017 ዓ.ም. ባስቻለው ችሎት  በሙሉ ድምጽ ውሳኔ ሰጥቷል።

ውሳኔው በተሰጠ የሰዓታት ልዩነት ተጠሪ የከተማ አስተዳደሩ ፋይናንስ ቢሮ በውሳኔው ላይ ለጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ እስከሚል አፈፃፀሙና በጉዳዩ ላይ ለሚዲያ መግለጫ እንዳይሰጥ ለፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ፕሬዚደንት  የዕግድ ትዕዛዝ እንዲሰጥለት በቃለ መሃላ አስደግፎ አቤቱታ ያቀረበ በመሆኑ ክብርት ፕሬዝዳንቷም ለ15 ቀን አፈፃፀሙ እንዲሁም ለሚዲያ መግለጫ እንዳይሰጥ የዕግድ ትዕዛዝ ሰጥተዋል፡፡
ይሁንና እስከ ዛሬ ጥር 26 ቀን ድረስ ቢሮው ያቀረበዉ ይግባኝ ባለመኖሩና የእግድ ትእዛዙ የጊዜ ገደብም ያበቃ በመሆኑ  ፓርቲያችን የፍርድ አፈፃፀም ስልጣን ላለዉ የአፈፃፀም ፍርድ ቤት ፋይል ለመክፈት በዝግጅት ላይ ይገኛል፡፡ የከፍተኛ ፍርድ ቤት ፕሬዚደንትም ለ15 ቀናት የሰጡት የአፈፃፀምና ለሚዲያ መግለጫ እንዳይሰጥ የእግድ ትዕዛዝ ቀነ ገደብ ያበቃ በመሆኑ ይህንን ጋዜጣዊ መግለጫ በዛሬው ዕለት ልንሰጥ ችለናል፡፡ (ሙሉዉን የፍርዱን ሂደትና ዉሳኔ በአጠቃላይ 30 ገፅ ማግኘት ለምትፈልጉ የምናደርሳችሁ መሆኑን እንገልፃለን፡፡)

በማጠቃለያ እናት ፓርቲ በሕጋዊ መንገድ ተመዝግቦ ሰላማዊ የፖለቲካ ትግል እንደሚያደርግ ፓርቲ ይህ የአዲስ አበባ ከተማ ኗሪ በሙሉ የአነባበት ግብር የሕግ አግባብ ተከትሎ እንዲሻር ያስደረገበት አድካሚ ጉዞ ለሕዝባችን ጥብቅና መቆሙን ከማሳየት ባሻገር አንደኛው የሰላማዊ ትግል እንቅስቃሴው አካል መሆኑን ለመግለጽ ይወዳል። ፓርቲያችን በቀጣይም በሕዝባችን ላይ ከሕግ አግባብ ውጪ የሚጫኑበትን ሸክሞች ወደ ፍርድ ቤት እያቀረበና በሕግ እየሞገተ የሚያስወግድ መሆኑንና ለዚህም በቁርጠኝነት እንደሚሠራ ይገልጻል።




Репост из: ይግባኝ ምክረ ሕግ
3ኛ
ድጋሜ ጥያቄ

📌ይህ ጥያቄ በዋና ጥያቄ የመለሱትን በመስቀለኛ ጥያቄ ሲጠየቁ በምስክርነት ቃልዎት ላይ ስህተት ወይም ልዩነትን ፈጥረው እንደሆነ ለማቃናት የሚቀርብ ጥያቄ ነው። በዋና ጥያቄ ላይ እንዲህ ብለህ መስክረህ በመስቀለኛ ጥያቄ ደግሞ እንዲህ ብለሃል የትኛው ነው እውነተኛ? በሚል መልኩ የሚቀርብልዎት ጥያቄ ነው።
📌ድጋሜ ጥያቄን ሲመልሱ እንዲህ ስለተባለው ጉዳይ ልናገር የፈለኩት እንዲህ በማለት ነው ብለው መልስዎትን በግልጽ ይስጡ።
4ኛ
የማጣሪያ ጥያቄ

📌የሚመሰክሩት ለከሳሽ፣ ለተከሳሽ ወይም ለጣልቃ ገብ ጥቅም ብቻ ብለው ሳይሆን ለትክክለኛ ፍትሕ በመሆኑ የሚሰጡትን ቃል ትክክለኛነትና እውነትነት ለማጥራት በማሰብ የምስክርነት ቃልዎትን ከሚቀበለው ዳኛ የሚቀርብልዎት ጥያቄ ነው።
📌የማጣሪያ ጥያቄ በማንኛውም ሰዓት እና ጊዜ እንዲህ ሲሉ ምን ለማለት ፈልገው ነው? በሚል አግባብ ሊቀርብልዎት ይችላል።
ይግባኝ መብት ነው
©️ጠበቃ ቴዎድሮስ አብዲሳ
☎️ 09 10 61 69 50
በማንኛውም የፌዴራል ፍርድ ቤት
ጠበቃና የሕግ አማካሪ


Репост из: ይግባኝ ምክረ ሕግ
#ምስክሮች_በፍርድ_ቤት_ሊጠየቋች_የሚችሉ_አራቱ_ጥያቄዎች
📌በፍርድ ቤት ክርክር ላይ አንድን ጉዳይ ለማስረዳት ከሚቀርቡ የማስረጃ ዓይነቶች ውስጥ ዋነኛው የምስክርነት ቃል ነው። የምስክርነት ቃል በዋነኝነት ከሳሽና ተከሳሽ ስለሚከራከሩበት ነገር የሚያስረዱ ግለሰቦች ናቸው።
👉በምስክርነት የተቆጠረ ግለሰብ እነዚህን አራት ዓይነት ጥያቄዎችን ሊጠየቅ ይችላል።
1ኛ
ዋነኛ ጥያቄ
📌ጥያቄው የሚቀርበው በምስክርነት ከቆጠረዎት ወገን በኩል ሲሆን ተከራካሪው በቆጠረዎት አግባብ ጉዳዩን እንዲያስረዱለት የሚያቀርብልዎት ጥያቄ ነው። የትኛውም ተከራካሪ ወገን በምስክርነት ሲቆጥርዎት ያውቁልኛል በማለት በመሆኑ ስለተጠየቁት ጉዳይ በሚያውቁት ልክ የሚያውቁትን በአግባቡ ቀጥተኛ መልስ መስጠት ወይም የማያውቁትን ደግሞ ስለዚህ ጉዳይ የማውቀው ነገር የለኝም በማለት ወይም እርግጠኛ ባልሆኑበት ጉዳይ እርግጠኛ ባልሆንም በግምት ይህ ይመስለኛል በማለት ምላሽ ይስጡበት።
2ኛ
መስቀለኛ ጥያቄ
📌ይህ ጥያቄ በዋና ጥያቄ ላይ ለሰጡት የምስክነት ቃል በተቃራኒ ተከራካሪ ወገን የሚቀርብልዎት ጥያቄ ስለሆነ በትኩረት አዳምጠው ምላሽ መስጠት ይገባዎታል።
📌የመስቀለኛ ጥያቄ መሠረታዊ ዓላማው ቀድሞ ከሰጡት የምስክርነት ቃል ውስጥ ስህተትን ፈልጎ ማውጣት በመሆኑ ምስክር ለቆጠረዎት ወገን እና ለእውነታው ሲሉ ባለመደናገጥ ተረጋግተው ይመልሱ።
📌ልብ ሊሉት የሚገባው ነጥብ በዋና ጥያቄ ላይ ስላልተናገሩት ጉዳይ ጥያቄ ቢቀርብልዎት ስለዚህ ጉዳይ የተናገርኩት ነገር የለም፤ ብለው ምላሽ ይስጡ።


Репост из: Ethiopian Legal insight
በስንት ሰዓት ላይ ሲፈፀም ነው ወንጀል በሌሊት ተፈፀመ የሚባለው ?

እንደሚታወቀው በኢፌድሪ የወንጀል ህግ አንቀፅ 84(1) ስር ከተደነገጉት የወንጀል ቅጣትን ከሚያከብዱ ጠቅላላ ምክንያቶች መካከል በንዑስ ፈደል (ሐ) ላይ የተገለፀው ወንጀልን በሌሊት መፈፀም አንዱ ነው፡፡አንዲሁም አንድን የስርቆት ወንጀል ከባድ ስርቆት ከሚያሰኘው መካከል አንዱ በወንጅል ህጋችን አንቀፅ 669(3)(ለ) ላይ በሌሊት መፈፀሙ ሲሆን በሌሎችም የወንጀል ህግ ልዩ ክፍል በሌሊት ወንጀልን መፈፀም ወንጀሉን ከባድ እንደሚያደርጉት ተደንገጎ ይገኛል፡፡ታዲያ ይህ ሌሊት የሚባለው ስንት ሰዓት ሲሆን ነው? የሚለውን በምናይበት ጊዜ በእንግሊዝኛው ‹‹night›› የሚለው ብላክስ ሎው የህግ መዝገበ ቃላት the time from sunset to sunrise በግርድፉ ፀሀይ ከምትጠልቅበት እስከምትወጣበት ያለው ጊዜ ነው በማለት ይገልፀዋል፡፡በኢትዮጵያ ቋንቋዎች ጥናትና ምርምር ማዕከል የተዘጋጀው የአማርኛ መዝገባ ቃላትም ‹‹ሌሊት›› የሚለውን ቃል ከብላክስ ሎው መዝገባ ቃላት ጋር በተመሳሳይ መንገድ ይተረጉመዋል፡፡ይህም ማለት ከቀኑ 12፡00 ሰዓት እስከ ሌሊቱ 12፡00 ሰዓት ያለው ጊዜ ማለት ነው በመሆኑም አንድ ሰው ከምሽቱ 1፡00 ሰዓት ላይ ወንጀል ቢፈፅም ወንጀሉን በሌሊት ፈፅሞታል ተብሎ ቅጣቱ ሊከብድበት ይችላል ማለት ነው፡፡ነገር ግን የፌደራል ጠቅላይ ፍ/ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በሰ/መ/ቁ 220926 ባልታተመ ውሳኔው የወንጀል ድርጊቱ ከምሽቱ 5፡00 ሰዓት ላይ የተፈፀመ ከሆነ በሌሊት ባለመሆኑ በወ/ህ/ቁ 84(1)(ሐ) መሰረት ቅጣት ማክበጃ ምክንያት ሊሆን አይገባም፡፡ሲል ትርጉም ሰጥቶበታል፡፡

ሌጋልቴክን አውርደው ይመዝገቡ
https://play.google.com/store/apps/details?id=com.ethiopianlegaltech.eli


ሕገ መንግሥቱ ሳይሻሻል እንዲህ ተብሎ መቀመጡ በሚል ለቀረበው ጥያቄ፣ ‹‹ሕገ መንግሥቱ የሚሻሻልባቸው ጉዳዮች ሊኖር ይችላሉ ተብሎ በምክክር ኮሚሽን ይኼው ምክር ቤት በሰጠው ኃላፊነት ብዙ ነገሮች እየተሠሩ ባሉበት፣ ወደፊት ምንም አይመጣም ብሎ ማሰብ የሚያስኬድ አይደለም፤›› ሲሉም አስረድተዋል፡፡
‹‹እንደተባለው በሕገ መንግሥቱ አንቀጽ 5 አማርኛ የፌዴራል የሥራ ቋንቋ ይሆናል የሚል አለ፣ ትክክል ነው፡፡ ነገር ግን አማርኛ ብቻ የሚል ነገር የለም፣ ወደፊት  ሌሎች ሲጨመሩ የፌዴራል የሥራ ቋንቋዎች ይሆናሉ፤›› በማለት አብራርተዋል፡፡#Reporter


ከሕገ መንግሥቱ ጋር ይጣረሳል በሚል ከፍተኛ ክርክር የተደረገበት የአጠቃላይ ትምህርት ረቂቅ አዋጅ ፀደቀ
***
‹‹ሕገ መንግሥቱ ወደፊት ይሻሻላል ብሎ ሕግ ማውጣት የሕግ አስተሳሰብ ሳይሆን የፖለቲካ አስተሳሰብ ነው›› የሕግ ምሁራን

በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሕገ መንግሥት ጥያቄ ተነስቶበት ከፍተኛ ክርክር የተደረገበት የአጠቃላይ ትምህርት ረቂቅ አዋጅ በአብላጫ ድምፅ ፀደቀ፡፡
የፀደቀው የአጠቃላይ ትምህርት አዋጅ ምክር ቤቱ አጠቃላይ ትምህርትን በሕገ መንግሥቱ፣ አገሪቱ በፈረመቻቸው ዓለም አቀፍ ስምምነቶች፣ እንዲሁም በቀረፀችው የትምህርት ሥልጠና ፖሊሲ መሠረት ለሁሉም ዜጎች በፍትሐዊነት ተደራሽ መሆኑን በማረጋገጥ፣ የትምህርት ጥራትን ያመጣል ተብሏል፡፡
ሐሙስ ጥር 22 ቀን 2017 ዓ.ም. በተካሄደው 17ኛ መደበኛ ስብሰባ አባላቱ ሕገ መንግሥቱን የሚቃረን ድንጋጌ መካተቱን በመጥቀስ፣ የምክር ቤት አባላት በረቂቁ ላይ ብርቱ ውይይትና ክርክር ካካሄዱ በኋላ፣ የተቃውሞ ድምፆች ቢሰሙም፣ አዋጅ ቁጥር 1368/2017 ሆኖ በአሥር ድምፀ ተዓቅቦ፣ በሁለት ተቃውሞና በአብላጫ ድምፅ ፀድቋል፡፡
ረቂቅ ሕጉ ከወራት በፊት ከሚኒስትሮች ምክር ቤት ወደ ሕግ አውጪው ፓርላማ ሲመራ፣ በረቂቁ አንቀጽ 28 ላይ አንድ ተጨማሪ የአገር ውስጥ ቋንቋ ከፌዴራል የሥራ ቋንቋዎች መካከል፣ የተማሪ ወይም የወላጅ ምርጫን ታሳቢ በማድረግ፣ በየደረጃው ባለው የትምህርት መዋቅር ተወስኖ እንደ አንድ የትምህርት ዓይነት ከሦስተኛ ክፍል ጀምሮ እስከ አሥረኛ ክፍል እንደሚሰጥ ተደንግጎ ነበር፡፡ ረቂቁ ከፌዴራል የሥራ ቋንቋዎች መካከል ቢልም በሕገ መንግሥቱ የፌዴራል የሥራ ቋንቋ አማርኛ መሆኑን አስቀምጧል፡፡
የአጠቃላይ ትምህርት ረቂቅ በሕግ አውጪው ፓርላማ መሪነት ለወራት ውይይት ሲካሄድበት ከቆየ በኋላ በመደበኛው ስብሰባ እንዲፀድቅ ሲቀርብ ደግሞ፣ በመጀመሪያው ረቂቅ ላይ ከፌዴራል የሥራ ቋንቋዎች መካከል አንድ ተጨማሪ የአገር ውስጥ ቋንቋ ከሚለው ጎን በሕገ መንግሥቱ ሲረጋገጥ የሚፈጸም መሆኑን በማሻሻያ ተደንግጎ ቀርቧል፡፡
ይሁን እንጂ ከምክር ቤት አባላት መካከል በሕገ መንግሥቱ ሳይገለጽ ወደፊት ሕገ መንግሥቱ ሲሻሻል በሚል አዋጅ እንዴት ሊወጣ ይችላል? የሕግ ክፍተት አይደለም ወይ? ሲሉ ጥያቄ አቅርበዋል፡፡

በፀደቀው አዋጅ አንቀጽ 28 ንፁስ አንቀጽ ሁለት ከፌዴራል የሥራ ቋንቋዎች መካከል አንድ ተጨማሪ የአገር ውስጥ ቋንቋ ለተማሪዎች ይሰጣል ተብሎ መደንገጉ፣ በሕገ መንግሥቱ ከተቀመጠው ድንጋጌ ውጪ መሆኑን የምክር ቤት አባላት አቅርበዋል፡፡
በሕገ መንግሥቱ ስለቋንቋ በሚያብራራው አንቀጽ 5 ላይ የፌዴራሉ መግሥት የሥራ ቋንቋ አማርኛ መሆነ በግልጽ መሥፈሩ አንዱ መከራከሪያ ነበር፡፡
የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ ኢዜማ አባሉ አቶ ባርጠማ ፈቃዱ በሰጡት አስተያየት፣ ሁለት ወይም ሦስት ቋንቋ በአገሪቱ ቢኖሩ የሚስማሙ መሆናቸው፣ ነገር ግን በሕገ መንግሥቱ አማርኛ የፌዴራል መንግሥት የሥራ ቋንቋ ስለመሆኑ እንጂ፣ በረቂቁ እንደተደነገገው ቋንቋዎች መኖራቸውን አያመላክትም ብለዋል፡፡ ‹‹ከፌዴራል የሥራ ቋንቋዎች መካከል አንዱ ተጨማሪ ቋንቋ በማለት ሕገ መንግሥት ሲስተካከል ብለን አዋጅ ማውጣት እንችላለን ወይ? ሕገ መንግሥቱ መሻሻል እንዳለበት ሁላችንም እናምናለን፡፡ ነገር ግን ሳናሻሽለው በዚህ መንገድ አዋጅ ማውጣት ይቻላል ወይ?›› ሲሉ ጠይቀዋል፡፡
በተመሳሳይ የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) የምክር ቤት ተወካይ አበባው ደሳለው (ዶ/ር) በአንቀጽ 28 ላይ ስለቀረበው ድንጋጌ ከሕገ መንግሥቱ ጋር መጋጨት ሲያብራሩ፣ የኢትዮጵያ የፌዴራል የሥራ ቋንቋ አማርኛ ነው ተብሎ የተቀመጠ ቢሆንም ድንጋጌው ስህተት ያለበት ነው ሲሉ ተከራክረዋል፡፡
በሕገ መንግሥቱ አንቀጽ 9 መሠረት ከሕገ መንግሥቱ ጋር የሚቃረን ማንኛውም ሕገ ተፈጻሚነት እንደሌለው መደንገጉን ጠቅሰው፣ ‹‹በዚህ የተነሳ የማይፈጸም ሕግ የምናወጣው ለምንድነው? አዋጆች ሲወጡ አሁን ያለውን የሕዝቦችን ችግር ለመፍታት በመሆኑ፣ ወደፊት የሚተገበር ነገር ግን የአሁኑን ችግር የማይፈታ አዋጅ ለምን መደንገግ አስፈለገ?››  ሲሉ ጠይቀዋል፡፡
በተመሳሳይ አቶ ጋሻው ዳኛው የተባሉ የብልፅግና ፓርቲ የምክር ቤት ተወካይ በበኩላቸው፣ የትኛውም ሕግ የሚመነጨው ከሕገ መንግሥት በመሆኑ ሕገ መንግሥቱን የሚጣረስ መሆን የለበትም ብለዋል፡፡ ‹‹ግልጽ ያልሆነልኝ ነገር ሕገ መንግሥቱ ሲሻሻል ብሎ ሕግ ማውጣት ምን ማለት ነው?›› ሲሉም ጥያቄ አቅርበዋል፡፡
‹‹ሕገ መንግሥቱ ሲሻሻል ተግባራዊ ይሆናል ብሎ ሕግ ማውጣት ሕገ መንግሥቱ ሲሻሻል ምክር ቤት የለም ወይ? ይህ በምን አግባብ ነው ተግባራዊx የሚደረገው? አንድ ሕግ ሕገ መንግሥቱን የሚፃረር ከሆነ ተግባራዊ አይሆንም ተብሎ ተደንግጐ እያለ፣ ባልተሻሻለ ሕገ መንግሥት ገና ይሻሻላል ብሎ ሕግ ማውጣት የሚቻል ሆኖ አልተሰማኝም፣ ትክክል ነው ብዬም አላስብም፤›› ሲሉ አስተያየታቸውን አክለዋል፡፡
ከሕግ አወጣጥ አንፃር ሪፖርተር ያነጋገራቸው የሕገ መንግሥት ጉዳዮች ተመራማሪና የሕግ ባለሙያው አቶ ሙሉጌታ አረጋዊ በሰጡት አስተያየት፣ ሕገ መንግሥት ማለት የሕጎች ሁሉ የበላይ መሆኑን ጠቅሰው፣ ‹‹መጀመሪያ ሕገ መንግሥቱ እንደሚሻሻል ማንም ሰው እርግጠኛ ባልሆነበትና የሚሻሻልም ከሆነ መቼ እንደሚሻሻል ባልታወቀበት ሁኔታ ይህ ድንጋጌ መቀመጡ አልገባኝም፤›› ብለዋል፡፡
ምክር ቤቱ ሕገ መንግሥቱ ወደፊት ይሻሻላል ብሎ ካሰበ፣ በተሻሻለ ጊዜ የሚፈልገውን አዋጅ ማሻሻል ወይም አዲስ አዋጅ ማውጣት እንጂ፣ ሕገ መንግሥቱ ሲሻሻል ይፈጸማል በሚል ዕሳቤ ዛሬ አዋጅ እንዲያወጣ ሥልጣን እንዳልተሰጠው አስረድተዋል፡፡
‹‹ይህ ትርጉም የሌለው ነው፤›› የሚሉት አቶ ሙሉጌታ፣ ‹‹ይህ ሲሆን ያ ይሆናል ተብሎ የሚቀመጠው በውል ሕግ (Contrat Law) አሠራር ለአብነት ያህል ሰብሉ ከገባ በኋላ፣ ለእኔ ትሸጥልኛለህ ዓይነት ለወደፊቱ ልትዋዋልና ልትፈራረም ትችላለህ፤›› ሲሉ ገልጸዋል፡፡
‹‹በዚህ መጠን ሕገ መንግሥቱ ሲሻሻል እንዲህ ይሆናል ሲባል አይቼም ሰምቼም አላውቅም፤›› የሚሉት አቶ ሙሉጌታ፣ ‹‹ራሱ ሕግ አውጭው ሥራው ምን እንደሆነ በትክክል ያወቀ አልመሰለኝም፤›› ብለዋል፡፡
ለወደፊቱ ተብሎ ሲቀመጥ እኔ ለዘለዓለም እቆያለሁ ዓይነት ትርጉም ያለው ነው የሚሉት የሕገ ባለሙያው፣ ጉዳዩ የፓርቲ ፕሮግራም ይመስላል  ሲሉ አስረድተዋል፡፡
የፀደቀው አዋጅ ሕገ መንግሥቱ እስኪሻሻል ተፈጻሚ እንደማይሆን ጠቅሰው፣ ይህ የሕግ አስተሳሰብ ሳይሆን የፖለቲካ አስተሳሰብ ነው ብለዋል፡፡
የአጠቃላይ የትምህርት ረቂቅ አዋጁን ውይይት በበላይነት ሲመራ የቆየው የምክር ቤቱ የሰው ሀብት ልማት ሥራ ሥምሪትና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ነገሪ ሌንጮ (ዶ/ር) በሰጡት አስተያየት፣ ‹‹አዋጁ የትምህርት አዋጅ እንጂ የፌዴራል የሥራ ቋንቋ አለመሆኑን እንረዳለን፤›› ብለዋል፡፡
የቋንቋ ጉዳይ በትምህርትና ሥልጠና ፖሊሲው በግልጽ የተቀመጠ ነው ያሉት ሰብሳቢው፣ የፌዴራል ቋንቋዎች ይሆናሉ ተብለው የተለዩ ቋንቋዎች መኖራቸውን፣ ቋንቋዎቹም ወደፊት በሕገ መንግሥት እንደሚረጋገጡ ተመላክቷል ብለዋል፡፡ ‹‹በሕገ መንግሥቱ ሲረጋገጥ መባሉ፣ ለሕገ መንግሥታችን ክብር መስጠት ግዴታ ስለሆነ ነው፤›› የሚል ምላሽ ሰጥተዋል፡፡


560_የኢሚግሬሽንና_ዜግነት_አገልግሎት_ሠራተኞች.pdf
1.2Мб
ደንብ ቁጥር 560/2017
የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት የሠራተኞች መተዳደሪያ ደንብ
Regulation No. 560/2024
Immigration and Citizenship Service Employees Administration Regulatio


559_የኢሚግሬሽን_የሚኒስትሮች_ምክር_ቤት_ደንብ.pdf
823.9Кб
የኢሚግሬሽን የሚኒስትሮች ምክር ቤት ማሻሻያ ደንብ ቁጥር 559/2017
Council of Ministers Immigration Amendment Regulation No 559/202


የሕገ መንግሥት ጉዳዮች አጣሪ ጉባዔ ጥር 22 ቀን 2017 ዓ.ም ባካሄደው መደበኛ ስብሳባ የሕገ መንግሥት ትርጉም አያስፈልጋቸውም በማለት የወሰናቸው መዝገቦች ዝርዝር
ተ.ቁ መዝገብ ቁ.
1. 5035/12
2. 5371/13
3. 5748/13
4. 5759/13
5. 6390/14
6. 6424/14
7. 6425/14
8. 6443/14
9. 6453/14
10. 6454/14
11. 6462/14
12. 6463/14
13. 6464/14
14. 6465/14
15. 6543/14
16. 6544/14
17. 6546/14
18. 6547/14
19. 6548/14
20. 6551/14
21. 6554/14
22. 6568/14
23. 6572/14
24. 6573/14
25. 6574/14
26. 6575/14
27. 8608/16
28. 9211/17

*ማስታወሻ*
1. ቁጥራቸው የቅርብ ጊዜ የሆኑት ጉዳዮች ቀድመው የታዩበት ምክንያት በጉባዔው መመሪያ መሰረት ቅድሚያ አግኝተው ምርመራቸው የተጠናቀቀ (የወንጀል፣ የአካል ጉዳተኞች፣ የአሰሪና ሰራተኛ፣ ከፍ/ቤት ሪፈራል የተላኩ፣ የታገዱ መዝገቦች) መሆናቸውን እየገለፅን ከዚያ ውጭ ያሉት ግን እንደ አመጣጥ ቅደም ተከተላቸው የተስተናገዱ ናቸው፡፡
2. ከላይ የተዘረዘሩትን ውሳኔዎች የውሳኔ ግልባጭ ከሁለት ሳምንት በኋላ በጉባዔው ፅ/ቤት በመቅረብ ማግኘት የሚቻል መሆኑን እንገልፃለን፡፡

የሕገ መንግሥት ጉዳዮች አጣሪ ጉባዔ

Показано 20 последних публикаций.