ማህበረ ቅዱሳን ( Mahibere Kidusan)


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: Религия


The channel of mahibere kidusan

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
Религия
Статистика
Фильтр публикаций




ልጆቼ! የእግዚአብሔር ትእዛዝ እንዴት ቀላል እንደሆነ የምታስተውሉ ሁኑ፡፡ ምክንያቱም ታስሬ አስፈትታችሁኛልና ሳይሆን ጠይቃችሁኛልና፤ ታምሜ አድናችሁኛልና ሳይሆን ጠይቃችሁኛልና፤ ተርቤ በየዓይነቱና ውድ የሆነ መዓድ ሳይሆን አንዲት ዳቦ አብልታችሁኛልና፤ ተጠምቼ በየዓይነቱና ውድ የሆነ መጠጥ ሳይሆን አንዲት ቀዝቃዛ ኩባያ ውኃ አጠጥታችሁኛልና ነው የሚለን፡፡

በጣም የሚያቀለው ደግሞ እነዚህን ቀላል ትእዛዛት በራሳችን ጥረት የምናደርጋቸው አይደሉም፡፡ ምክንያቱም በቃሉ "ያለ እኔ ምንም ልታደርጉ አትችሉም" ስለሚለን ጸጋ መንፈስ ቅዱስን አጋዥ አድርገን ነው፡፡ እንግዲያውስ ድሀ ስለሆንኩ እነዚህን ማድረግ አልችልም ብለን ራሳችን ሰነፎች የምናደርግ አንሁን፡፡ ሺህ ጊዜ ደሀ ብንሆን ሁለት ሳንቲም ከሰጠችው መበለት በላይ ድሀ ልንሆን አንችልምና፡፡ ስለዚህ ስንፍናን ከእኛ እናርቅ፡፡

ልጆቼ! እነዚህን በእርሱ እርዳታ ስላደርግንስ ምን እንደምንባል ትገነዘባላችሁን? “ኑ እናንተ የአባቴ ብሩካን!” ካላደረግንስ? “እናንተ ርጉማን ከእኔ ዘንድ ሂዱ!” እንግዲያውስ ለእኛ ሳይሆን ለሰይጣንና ለመላእክቱ የተዘጋጀውን እሳት ከሚያገኘን ዓለም ከተፈጠረ ጀምሮ ለእኛ የተዘጋጀውን መንግሥት እንወርስ ዘንድ ዛሬ አብዝተን ዘይት የምንገዛ እንሁን፡፡ እንደነዚያ ሰነፍ ደናግላን እዚያ መግዛት በማይቻልበት ቦታ ሄደን ከምንጠይቅ ዛሬ ሳይመሽብን የሚበቃንን ያህል ዘይት እንግዛ፡፡ ዘይቱ የሚገዛውስ የት ነው? የታመሙት ጋር፤ እስረኞች ጋር፤ ቁርና ሀሩር በሚፈራረቅባቸው ወንድሞቻችናነ እኅቶቻችን ጋር፡፡

ልጆቼ! እንደ ነዌ እዚህ ምድር ባለጸጎች ሆነን ያኔ ከምንለምን ዛሬ አልዓዛርን ልናስበው ይገባል፡፡

ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ


ይሁን እንጅ እስራኤል ሁሉ ለእግዚአብሔር በኵር ሆነው ሊዘልቁ ባለመቻላቸው፣ ለደብተራ ኦሪት ለክህነት አገልግሎት ተመራጭ ባለመሆናቸው እግዚአብሔር ከነገደ ሌዊ አሮንና ልጆቹን ለቤተ መቅደሱ አገልግሎት በመለየቱና በመምረጡ ደቂቀ ቆሬና ሌሎቹ ወደ ቅድስተ ቅዱሳኑ መግባት የክህነትን ሥራም መሥራት ፈልገው በሙሴ ላይ ማመጻቸውን፣ ወደ ቅድስተ ቅዱሳኑ ገብተው ማጠን መፈለጋቸውና ማዕጠንተ ወርቁን ይዘው ያለጸጋቸው በፈጸሙት ተግባር ደቂቀ ቆሬ ተቀሥፈዋል፤ ዳታንና አቤሮንን መሬት አፏን ከፍታ ውጣቸዋለች እሳትም ከሰማይ ወርዳ ያጥኑ የነበሩትን ሁለት መቶ ኀምሳ ሰዎች በልታቸዋለች፡፡ (ዘፍ.፲፮፥፩-፴፭) የዘመናችንን ደቂቀ ቆሬዎች፣ ዳታንና አቤሮንን ግን እግዚአብሔር ምድር ከፍቶ እንዳያሰምጣቸው እሳት ከሰማይ ወርዶ እንዳያቃጥላቸው ታግሧቸዋል፡፡ ምክንያቱም ዓመቱም ዓመተ ምሕረት ዘመኑም ዘመነ ምሕረት ዘመነ ንስሓ ነውና፡፡ በዚህ ምክንያት ድፍረት ተሞልተው፣ ቤተ ጸሎት የተባለችውን የክርስቶስ ቤት ቤተ ምስያጥ ወፈያት ያደረጉ ደቂቀ ቆሬዎች ዛሬም በቤተ ክርስቲያን ለክብረ ክህነት ዝቅ ማለት ምክንያት ናቸው፡፡

ለ.ሳይማሩ የተሾሙ ካህናት መኖር፡-

ክህነት ባለፉት ክፍሎች እንዳየነው ትልቅ ኃላፊነትን የሚጠይቅ ማዕረገ ሹመት ነው፡፡ ምዕራፍ ቁጥር ጠቅሶ ምሥጢር አደላድሎ፣ የራቀውን አቅርቦ፣ የረቀቀውን አጉልቶ፣ የጎደለውን ሞልቶ፣ በምሳሌ አዋዝቶ ማስተማርን፣ አስተምሮ ማሳመንን፣ አሳምኖ ማጥመቅን፣ አጥምቆ ማቁረብን፣ ናዝዞ መፍታትን፣ በአፍኣም በጽሑፍም መናፍቃንን ተከራክሮ መርታትን ምእመናንን መጠበቅን የሚጠይቅ ተግባር ነው፡፡

አንድ ካህን በውስጥ በአፍኣ ለሚያገለግለው አገልግሎት ጥበብ መንፈሳዊ ጥበብ ሥጋዊ ዕውቀትም ያለው መሆን አለበት፡፡ አሁን አሁን ዕውቀት አልባ የክህነት ሰዎች ትልቅ የዘመናችን የቤተ ክርስቲያን ተግዳሮት ሆነዋል፡፡ ‹‹ሕዝቤ ከዕውቀት ማጣት የተነሣ ጠፍቷል›› እንዳለ ነቢዩ ሆሴዕ ከዕውቀት ማጣት የተነሳ ለጠፋው በድቅድቅ ጨለማ ውስጥ ላለው፣ በምንደኞችና በሐሰተኛ ነቢያት ለተወሰደው ምእመን ሃይማኖታዊ የዕውቀት ብርሃንን ሊያበራ የሚገባው ካህን እየጠፋ በመምጣቱና የዕውቀት ጾመኞች በመብዛታቸው ክብረ ክህነት ተፈትኗል የሚል አረዳድ አለን፡፡ (ሆሴ.፬፥፮)

ካህን በእግዚአብሔርና በሕዝቡ መካል ሆኖ የሚያስታርቅ፣ ለማስተማር የተሾመ ነውና ሕዝቡን የሃይማኖትን ትምህርት ገልጦ በማስተማር በሕገ እግዚአብሔር በሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን እንዲኖሩ ማጽናት የሚችል የተማረ የተመራመረ መሆን አለበት፡፡ ምክንያቱም ‹‹ካህኑ የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር መልክተኛ ነውና ከንፈሮቹ ዕውቀትን ይጠብቁ ዘንድ ይገባዋል፡፡ ሰዎችም ሕግን ከአፉ ይፈልጉ ዘንድ ይገባቸዋል›› ተብሏልና፡፡ (ሚል.፪፥፯) በፍትሐ ነገሥትም ካህን ወንጌልን በማስተማር ምእመናንን የሚረዳ፣ እውነተኛ ትምህርት በማስተማር ሰውን ማጽናናት የሚቻለው፣ ክደው ሊያስክዱት የሚተናኮሉትን የሚከራከራቸው መሆን አለበት የሚል ሥርዓት ተሠርቷል፡፡ (ፍት. መን. አንቀጽ ስድስት ክፍል አንድ)

ምንም እንኳን መጻሕፍት ይህን ቢሉም በተጨባጭ አሁን ያለችው ቤተ ክርስቲያን ላይ የተሾሙና እየተሾሙ ያሉ አንዳንድ የክህነት ሰዎች (ከዲያቆን እስከ ኤጲስ ቆጶስ) ሐዋርያዊ ተልዕኳቸውን ለመወጣት የሚያስችል መንፈሳዊና ሥጋዊ ዕውቀት የጎደላቸው መሆን ግልጽ ተግዳሮት ከመሆኑም በላይ ሞኝ ባያፍር የሞኝ ዘመድ ያፍር እንዲሉ ምእመናንንና ቤተ ክርስቲያንን የሚያስነቅፍ ለክብረ ክህነት የማይመጥን ተግባር ያለ ዕውቀት እየፈጸሙ ለክብረ ክህነት መቀነስ ወይም መጓደል ምክንያት ሲሆኑ ይታያል፡፡

ሐ. የሥነ ምግባር ጉድለት መኖር፡-


ቤተ ክርስቲያን አቻ የማይገኝላት ትልቋ የሥነ ምግባር ትምህርት ቤት ናት፡፡ የተጣመመ የሚቃናባት፣ የታመመ የሚፈወስባት፣ ቀማኛው መጽዋች፣ ንፉጉ ለጋስ፣ ርኩሱ ቅዱስ፣ ዘማዊው ድንግል ኃጥኡ ጻድቅ የሚሆንባት የሥርዓት፣ የምግባር ማዕከል ናት፡፡ ቤተ ክርስቲያን የሥነ ምግባር ትምህርት ቤት ስትባል መምህራኖቿ ደግሞ ባለክህነቶቹ ዲያቆናቱ፣ ካህናቱና ጳጳሳቱ መሆናቸው ግልጽ ነው፡፡ የሰብእና መገንቢያ፣ የምግባር የትሩፋት ማዕከል፣ የሞራል ከፍታ ማሳያ፣ የሕግና ሥርዓት ምንጭ የነበረች ቤተ ክርስቲያን አሁን ስለምን የሥርዓት አልበኞች፣ የጨካኞችና የመዝባሪዎች መነኻሪያ ተደርጋ እስክትታይ ወረደች? ብሎ መጠየቅ ይገባል፡፡

አሁንም መልሱ ከክብረ ክህነት መጓደል ያደርሰናል፡፡ ድፍረት፣ ትዕቢት፣ ፍቅረ ዝሙት፣ ፍቅረ ንዋይ፣ ፍቅረ ሥልጣን፣ ዘረኝነት፣ ጎሰኝነት ፖለቲካ የተሸከሙ፣ ለእግዚአብሔርም ለክፉ ሥጋዊ ፍላጎታቸውም ባሪያ ለመሆን የሚሞክሩ፣ በጥቅሉ የመንፈስ ፍሬዎች የማይታይባቸው ክፉ ሠራተኞች በክህነትና በካህናት ስም መዋቅሯ ውስጥ ስለተሰገሰጉ ነው፡፡ (ገላ.፭፥፳፪) ንጹሓን የሚሸማቀቁባት፣ ፍትህ ርትዕ የጠፋባት፣ መገፋፋትና መነቃቀር መገለጫዋ እስኪመስል፣ በፖለቲካ የሤራ አስተሳሰብ የሚመሩ ብዙ ሥርዓት አልበኞች መዋቅሯን ተብትበው በመያዛቸው ነው ብለን እናምናለን፡፡

በዚህ ምክንያት ክብረ ክህነት እየተናቀ፣ አላፊ አግዳሚው ባልሰላ ምላሱ፣ ባልተሞረደ ጥርሱ የሚያላምጣት ቤተ ክርስቲያን፣ የጸኑት ልጆቿ አንገት የሚደፉበት፣ ያልጸኑት ተስፋ ቆርጠው ወደ ሌላ እምነት ቤት የሚሄዱበት፣ ቤተ ክርስቲያን በዘርፈ ብዙ የመልካም አስተዳደር ችግር ውስጥ እንድትወድቅ ያደረገ የሥነ ምግባር ችግር አለ፡፡ ምንም እንኳን መጽሐፍ ‹‹ያለ ሥርዓት የሚሔዱትን ገሥጿቸው›› ቢልም ታላላቆቹ፣ አዋቂዎቹ በአርአያ ክህነት በግርማ ሽበት፣ በምግባር በትሩፋት የሚታወቁት ዝምታን በመምረጣቸው ቤተ ክርስቲያን በፈተና እንድትሞላ ክብረ ክህነት እንዲቃለል፣ ሥርዓት እንዲጠፋ ምክንያት ሆኗል ብለን እናምናለን፡፡

በጥቅሉ ክህነት በዘመናችን በብዙ ተግዳሮቶች ውስጥ ያለ፣ ልዩ ትኩረትን የሚሻ ዐቢይ ጉዳይ ነው፡፡ ያልተማሩ ከድንቁርናቸው፣ ሥርዓት አልበኞቹም ከክፉ መንገዳቸው እንዲላቀቁ፣ በቆሬ መንገድ የቆሙ ከመንገዳቸው እንዲመለሱ የሚያደርግም ኃይል ነው፡፡ ሆኖም ግን ለቤተ ክርስቲያን ክህነት ጸጋቸው፣ አገልግሎት መለያቸው፣ ሥርዓት መገለጫቸው ሆነው በአርአያ ክህነት የሚመላለሱ፣ በክብረ ክህነት የሚገለጹ የክህነት ሰዎችን ለማፍራት የሠራነው ሥራ የለም፡፡

በምድር ያለች ሰማያዊት የሆነች ቤተ ክርስቲያናችን የምትከፈትበት ቁልፍ ክህነት እንዲከበር ምን እናድርግ? ክብረ ክህነት ነገ ምን መልክ ይኑረው? ክብረ ክህነት እንዲመለስ፣ የቤተ ክርስቲያን የስሟ መጠሪያ የመልኳ መታያ ሆኖ እስከ ምጽአት እንዲዘልቅ ከማን ምን ይጠበቃል? የሚሉ ጉዳዮችን ‹‹ክብረ ክህነት ነገ›› በሚል ክፍል አምስትን እናቀርብላችኋለን፤ ቸር እንሰንብት!


‹‹ነገን ዛሬ እንሥራ››

ክፍል አራት

ክብረ ክህነት ዛሬ


ክህነት የቤተ ክርስቲያን መመሥረቻና የመንግሥተ እግዚአብሔር መግቢያ ቁልፍ ነው፡፡ ቤተ ክርስቲያን የተመሠረተችው ዐለት በተባለ ቅዱስ ጴጥሮስ ክህነት ላይ ነው፡፡ (ማቴ.፲፮፥፲፰) አንድ ቤት በአሸዋ እና በድቡሽት ላይ ቢሠራ ነፋስ ይገለብጠዋል፤ ጎርፍ ይጠራርገዋልና በማይናወጥ ጽኑ ዐለት ላይ ማነጽ የብልህ እና አዋቂ ግንበኛ ግብሩ በመሆኑ የቤተ ክርስቲያን ባለቤት ቤቱን በጴጥሮስ ዐለት ላይ መሥርቷት ዘመናትን ተሻግራ ለትውልድ ክብር ሆና ዘልቃለች፡፡ ለቤተ ክርስቲያን የውስጥ ጌጥ የውጭ ፈርጥ፣ የታች መሠረት የላይ ጉልላት ክህነት መሆኑን መረዳት አይከብድም፡፡

’’ኢኀደጋ ለምድር እንበለ ካህናት ወዲያቆናት፣ እምቅድመ ዓለም ወእስከ ለዓለም፤ ቸሩ አምላካችን እግዚብአሔር ለዘለዓለም እስከ ለዓለም ምድርን ያለ ካህናትና ዲያቆናት አልተዋትም’’ እንዲል፤ (የኅዳር ጽዮን ዋዜማ) ቤተ ክርስቲያናችንን ያለ ክህነትና ካህናት ፈጽሞ ያልተዋት ቢሆንም አሁን ግን ክብረ ክህነት በዘመናችን በርካታ ተግዳሮቶች ተጋርጠውበታል፡፡

ሀ. ያልተካኑ ሰዎች በክህነት ቦታ መሰየማቸው፡-

ቤተ ክርስቲያን ውስጥ አንዳንዶቹ ሳይጠሩ ተጠርተናል፣ ሳይመረጡ ተመርጠናል፣ ሳይካኑ ተክህነናል በማለት እንደ ደቂቀ ቆሬ፣ እንደ ደቂቀ ኤልያብ እንዲሁም የፋሌት ልጅ በድፍረት የተነሡ፣ መቅደሱን የሚያረክሱ፣ ከዕውቀትም ከሃይማኖትም ያነሱ ደፋሮች ቤተ ክርስቲያንን እግር ከወርች አስረው የያዙበት ዘመን በመሆኑ ክብረ ክህነት ችግር ላይ ወድቋል፡፡ (ዘኍ.፲፮፥፩-እስከ ፍጻሜ) በኦሪት ዘፍጥረት አንድ ታሪክ አለ፡፡ ሙሴ ሕዝበ እስራኤልን ባሕር ከፍሎ ጠላት አስጥሞ በኵረ ግብጽን አጥፍቶ በኵረ እስራኤልን ሁሉ ለራሱ በኩር ማድረጉ የተመዘገበ ታሪክ ነው፡፡(ዘፀ. ፲፪፥፩-፲፪)


The opulent man is the resemblance of our Lord. The ardour are various grace we are endowed from God. The faithful servant who served in faithfulness are all the righteous, saints and holy people who lived on earth in service of the Lord by the ardour they are given with diligence. The lazy and wicked servant represents those sinners who did not profit by the ardour given to them.

The Lord approaching in control of them is the truth about the Lord’s second coming for judgment in giving each of us the value of work. The Lord telling each servant to “Enter into the joy of your Lord” is the affirmation of righteous entrance to the Kingdom of Heaven. The order of punishment on the wicked and lazy servant to be “cast the unprofitable servant into the outer” is the indication of sinners to be thrown to hell.

Dear Brethren, we then shall ask ourselves if we are like the faithful servants. We ought to understand the vitality of faithfulness and generosity in good service. Being faithful is the submission to God, obedience and living by His law without any qualm but with absolute faith which safeguards us from being falsifiers, thieves, adultery and heresies. It also enables us to serve with our skill, talents and bequest. He has taught us to praise Him with our words, sing in harp and mesenko for Him, prostrate by our knees and love Him with all our heart.

He has shown us to generously, in goodness and kindness share our possession to others. If we have one bread, to give the half to others; share our cloth or shoe if we have extra; to feed and water the hunger and thirsted from our buffet; sympathize those in tribulation and misery as well as to take care the sick people. Then brethren, as a good children of God, we shall become faithful and generous servant!
May God’s mercy and benevolence be with us, Amen!


Who is faithful servant?

Foremost, service is bestowed for the Almighty Lord; God, Who is the creator of all. Primarily who served Him by praising “Holy Holy Holy” were Angles in the heavens. Then followed the first man kind Adam, where he lived in praising and prayer in heaven.

After his defying the Lord’s command though, Adam has lived in misery and chaos tortured and lured by the devil’s scam. Onwards, enemy Satan has been tempting humans into his trap, dragging us out of the true and righteous path for failure. (Genesis 1:8, Book of Aximaros the sixth day)

This is certainly tragic and sorrowful to acknowledge, but our Lord and Savior Jesus Christ has told Saint Apostles “In the world you will have tribulation; but be of good cheer, I have overcome the world.” Even if our enemy brings tribulations, misery and anguish upon human race in failing us, if we are to endure all the suffering and pass all the tribulations in good service, we will enter in God’s Kingdom. (John 16:33)

A good service is what we serve by our personhood, goodness, sincerity, humility, knowledge and energy in prayer, fasting, alms giving, deeds of benevolence and love. Humans in addition to praising the Lord, needs to live daily in trepidation of God to serve Him. A human with trepidation of God, afar from harm and sin and become good person. He/she will also have a social life filled with sincerity and humility; Does not also desists from doing righteous for others. Moreover, with the spiritual and carnal knowledge as well as the energy, serve the Lord. This is known as a faithful and generous servant. Let us mention one story in scripted in the Holy Bible, in Matthew’s gospel (25:14-30)

“For the kingdom of heaven is like a man traveling to a far country, who called his own servants and delivered his goods to them. And to one he gave five talents, to another two, and to another one, to each according to his own ability; and immediately he went on a journey. Then he who had received the five talents went and traded with them, and made another five talents. And likewise he who had received two gained two more also. But he who had received one went and dug in the ground, and hid his lord’s money.

After a long time, the lord of those servants came and settled accounts with them. “So he who had received five talents came and brought five other talents, saying, ‘Lord, you delivered to me five talents; look, I have gained five more talents besides them.’ His lord said to him, ‘Well done, good and faithful servant; you were faithful over a few things, I will make you ruler over many things. Enter into the joy of your lord.’ He also who had received two talents came and said, ‘Lord, you delivered to me two talents; look, I have gained two more talents besides them.’ His lord said to him, ‘Well done, good and faithful servant; you have been faithful over a few things, I will make you ruler over many things. Enter into the joy of your lord.’

“Then he who had received the one talent came and said, ‘Lord, I knew you to be a hard man, reaping where you have not sown, and gathering where you have not scattered seed. And I was afraid, and went and hid your talent in the ground. Look, there you have what is yours.’

“But his lord answered and said to him, ‘You wicked and lazy servant, you knew that I reap where I have not sown, and gather where I have not scattered seed. So you ought to have deposited my money with the bankers, and at my coming I would have received back my own with interest. So take the talent from him, and give it to him who has ten talents.

‘For to everyone who has, more will be given, and he will have abundance; but from him who does not have, even what he has will be taken away. And cast the unprofitable servant into the outer.”


 
ይህ በእርግጥ አስከፊና አሳዛኝ ቢሆንም ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለቅዱሳን ሐዋርያት  ‹‹በዓለም ሳላችሁ መከራ አለባችሁ፤ ነገር ግን አይዞአችሁ፤ እኔ ዓለምን አሸንፌዋለሁ›› በማለት እንደ ነገራቸው ምንም እንኳን ጠላታችን መከራ አጽንቶና ተስፋ አስቆርጦ ብኩንና ከንቱ ሊያደርገን ቢጥርም መከራውን አልፈን፣ ሥቃያችንን ተቋቁመንና ችግራችን ተወጥተን በመልካም አገልግሎት ወደ አምላካችን መንግሥት መግባት ይቻለናል፡፡ (ዮሐ.፲፮፥፴፫)
 
መልካም አገልግሎት ለእግዚአብሔር አምላክ በሰውነታችን በበጎነታችን፣ በቅንነታችን፣ በትሕትናችን፣ በዕውቀታችንና በጉልበታችን የምናቅርበው የጸሎት፣ የጾም፣ የምጽዋት፣ የትሩፋትና የፍቅር አገልግሎት ነው፡፡ አምላካችንን ከማመስገን በተጨማሪ ዘወትር እርሱን በመፍራት በዕለት ኑሮአችን ልናስበውና ልናገለግለው ይገባል፡፡ ፈሪሃ እግዚአብሔር ያለው ሰው በምንም ዓይነት ሁኔታ ውስት ቢሆን ክፋትና ኃጢአት ከመሥራት ርቆ ይኖራልና፡፡ በቅንነትና በትሕትና የተሞላ የማኅበራዊ ሕይወትም ይኖረዋልና፡፡ ለሌሎች ሰዎችም መልካም ከማድረግ አይቦዝንም፡፡ ከዚህም አልፎ ተርፎ ባካበተው የመንፈሳዊ እና ዓለማዊ ዕውቀት እንዲሁም ባለው ጉልበት አምላኩን ዘወትር ያገለግላል፤ ይህም ተግባሩ ለጌታው የታመነ ታማኝና ቸር አገልጋይ ያሰኘዋል፡፡  
 
በመጽሐፍ ቅዱስ የሐዲስ ኪዳን ክፍል ወንጌል ላይ ቅዱስ ማቴዎስ የጻፈውን አንድ ታሪክ እናንሣ፤ ‹‹አንድ ወደ ሌላ አገር የሚሄድ ባለጸጋ ባሮቹን ጠርቶ ያለውን ገንዘብ እንደ ሰጣቸው እንዲሁ ይሆናልና፤  ለእያንዳንዱ እንደ ዓቅሙ ለአንዱ አምስት መክሊት፣ ለአንዱ ሁለት፣ ለአንዱም አንድ ሰጠና ወደ ሌላ አገር ወዲያው ሄደ። አምስት መክሊትም የተቀበለው ሄዶ ነገደበት ሌላም አምስት አተረፈ፤ እንዲሁም ሁለት የተቀበለው ሌላ ሁለት አተረፈ። አንድ የተቀበለው ግን ሄዶ ምድር ቈፈረና የጌታውን ገንዘብ ቀበረ።››
 
ከብዙ ዘመንም በኋላ የእነዚያ ባሮች ጌታ መጣና ተቆጣጠራቸው። አምስት መክሊት የተቀበለውም ቀረበና ሌላ አምስት መክሊት አስረክቦ “ጌታ ሆይ፥ አምስት መክሊት ሰጥተኸኝ ነበር፤ እነሆ፥ ሌላ አምስት መክሊት አተረፍሁበት” አለ። ጌታውም “መልካም፥ አንተ በጎ ታማኝም ባሪያ፤ በጥቂቱ ታምነሃል፥ በብዙ እሾምሃለሁ፤ ወደ ጌታህ ደስታ ግባ” አለው።
 
ሁለት መክሊትም የተቀበለው ደግሞ ቀርቦ “ጌታ ሆይ፥ ሁለት መክሊት ሰጥተኸኝ ነበር፤ እነሆ፥ ሌላ ሁለት መክሊት አተረፍሁበት” አለ። ጌታውም “መልካም፥ አንተ በጎ፥ ታማኝም ባሪያ፤ በጥቂቱ ታምነሃል፥ በብዙ እሾምሃለሁ፥ ወደ ጌታህ ደስታ ግባ” አለው።
 
አንድ መክሊትም የተቀበለው ደግሞ ቀርቦ “ጌታ ሆይ፥ ካልዘራህበት የምታጭድ፣ ካልበተንህበትም የምትሰበስብ ጨካኝ ሰው መሆንህን አውቃለሁ፤ ፈራሁም ሄጄም መክሊትህን በምድር ቀበርሁት፤ እነሆ፥ መክሊትህ አለህ” አለ። ጌታውም መልሶ እንዲህ አለው፦ “አንተ ክፉና ሃኬተኛ ባሪያ፥ ካልዘራሁበት እንዳጭድ ካልበተንሁበትም እንድሰበስብ ታውቃለህን? ስለዚህ ገንዘቤን ለለዋጮች አደራ ልትሰጠው በተገባህ ነበር፤ እኔም መጥቼ ያለኝን ከትርፉ ጋር እወስደው ነበር። ስለዚህ መክሊቱን ውሰዱበት፤ ዐሥር መክሊትም ላለው ስጡት፤ ላለው ሁሉ ይሰጠዋልና ይበዛለትማል፤ ከሌለው ግን ያው ያለው እንኳን ይወሰድበታል። የማይጠቅመውንም ባሪያ በውጭ ወዳለው ጨለማ አውጡት፤ በዚያ ልቅሶና ጥርስ ማፋጨት ይሆናል።›› (ማቴ.፳፭፥፲፬-፴)
 
ባለ ጸጋ የተባለው ጌታችን ነው፡፡ መክሊት የተባለው ደግሞ ከአምላካችን የተጠን የተለያዩ የአገልግሎት ጸጋዎች ናቸው፡፡ በታማኝነት ያገለገሉት ሰዎች ምሳሌ በምድራዊ ሕይወታቸው በተሰጣቸው ጸጋ በትጋት አምላካቸውን አገልግለው በመልካም ዕረፍት ገነት የገቡት ቅዱሳን ሰዎች ናቸው፤ መክሊቱን የቀበረው ሰነፍ አገልጋይ ደግሞ በተሰጣቸው ጸጋ በታማኝነት ማገልገል  ሲገባቸው ያላገለገሉ ሰዎች ምሳሌ ነው፡፡
 
ጌታቸው ሊቆጣጠራቸው የመምጣቱ ነገር ጌታችን በዕለተ ምጽአት ለፍርድ ሲመጣ ለሁሉም በሠራው ሥራ መጠን ዋጋ ለመስጠት እንደሚመጣ የሚያመለክት ነው፡፡ ያገለገሉትን ታማኝ አገልጋየችም ለእያንዳንዱ  ‹‹ወደ ጌታህ ደስታ ግባ!››  ማለቱ ታማኝ አገልጋዮች መንግሥተ ሰማያትን እንደሚወርሱ የሚያረጋግጥ ነው፡፡ ሰነፉ አገልጋይ ወደ ጨለማና ጥርስ ማፋጨት ወዳለበት ቦታ መወርወሩም ኀጥአን ወደ ገሃነመ እሳት መጣላቸውን የሚያሳይ ነው፡፡
 
ሊቁ ቅዱስ ያሬድ ‹‹ጌታውን ያስደሰተው አገልጋይ ታማኝና ቸር አገልጋይ ነው›› በማለት የተናገረው ይህን የወንጌል እውነት የሚገልጽ ነው፡፡ ታማኝነትና ቸርነት ለአገልግሎታችን እጅጉን አስፈላጊዎች ናቸው፡፡ ታማኝ መሆን ያለ ጥርጥርና በፍጹም እውነት ለአምላካችን መገዛት፣ መታዘዝና መኖር እንዲሁም በሕጉ መኖር ነው፡፡ ይህም ለእርሱ ታምነን ያለ ሐሰት፣ ያለ ስርቆት፣ ያለ አመንዝራነት እና ያለ ክህደት ወዘተ. እንድንኖር ይረዳናል፡፡ በተሰጠንም ክሂሎት፣ ተሰጥኦና ትሩፋት ማገልገል ያስችለናል፡፡ በአንደበታችን እንድናመሰግናው፣ በእጆቻችን አጨብጭበን፣ በጣቶቻችን በገና ደርድረንና መሰንቆ መትተን እንድንዘምርለት፣ በጉልበታችን እንድንሰግድለት በልባችን እንድናፈቅረው አስተምሮናል፡፡   
 
ቸር በመሆን ለሌሎች በለጋስነት ካለን ነገር በመስጠትና በማካፈል መኖርን አሳይቶናል፡፡ አንድ ዳቦ ያለው ግማሹን ለሌላው እንዲያካፈል፣ ሁለት ልብስ ወይም ጫማ ያለው ለሌለው እንዲሰጥ፣ ከማዕዳችን ለተራቡ እንድናበላ፣ ከማድጋችን ለተጠሙ እንድናጠጣ፣ ለተቸገሩትና ላዘኑት ቸርነት በማድረግ እንድናስተዛዝን፣ የታመሙትን እንድናስታምም የአምላካችን ቅዱስ ቃል ያዘናል፡፡ እኛም እንደ መልካም ልጆቹ ለእርሱ በመታዘዝ ታማኝና ቸር አገልጋይ እንሁን!
 
የአምላካችን እግዚአብሔር ቸርነትና ረድኤት አይለየን፤ አሜን!    


‹‹ጌታውን ያስደሰተው አገልጋይ ታማኝና ቸር አገልጋይ ነው››  ቅዱስ  ያሬድ
      
  ሚያዚያ ፬፤፳፻፲፮ ዓመተ ምሕረት
 
ከማንም አስቀድሞ አገልግሎት ለአምላካችን እግዚአብሔር ይገባል፤ በጥንተ ተፈጥሮ በመጀመሪያው ቀን የተፈጠሩት መላእክት ፈጣሪያቸውን ዘወትር ያለማቋረጥ ‹‹ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ›› እያሉ እንደሚያመሰግኑት ሊቁ ቅዱስ ኤጲፋንዮስ በመጽሐፈ አክሲማሮስ ገልጾልናል፡፡ (አክሲማሮስ ዘእሑድ) በዕለተ ዓርብ ሰው ሲፈጠር እንደ መላእክቱ የፈጠረውን ጌታውን እንዲያመሰግን፣ እንዲያገለግል እንዲሁም ስሙን እንዲቀድስና ክቡርን እንዲወርስ በመሆኑም የቀደመ ሰው አዳምም አምላኩን እያመሰገነና በገነትም በጸሎት እየተጋ ኖሯል፡፡      
 
በመጽሐፍ ቅዱስና በሌሎች ቅዱሳት መጻሕፍት ተመዝግቦ እንደምናገኘው ጥንተ ጠላት ዲያብሎስ አምላኩን ለማመስገን ባለመፍቀዱ ተረግሞ ወደ ምድር ከተጣለ በኋላ የሰውን ዘር በተለያዩ መንገዶች በማሳት፣ ከቀናው መንገድና ከጽድቁ ጎዳና በማስወጣት ፈጣሪያቸውን እንዳያገለግሉ ያደርጋል፡፡ (ዘፍ.፩-፰፣ አክሲማሮስ ዘዓርብ)   




ከጌዲኦ፣ ቡርጂ እና አማሮ ዞኖች ሀገረ ስብከት የተወጣጡ ሠልጣኞ የተተኪ መምህራን ሥልጠና ጀመሩ።

ማኅበረ ቅዱሳን ከደብረ ይድራስ ቅዱስ ጊዮርጊስ ፍሬ ሃይማኖት ሰ/ት/ቤት ጋር በመተባበር ከጌዲኢ ዞን ቡርጂ እና አማሮ ሀገረ ስብከት ሠልጣኞችን በመልመል የተተኪ መምህራን ሥልጠና አስጀምሯል።

መጋቢት 30 ቀን 2016 ዓ.ም  የሥልጠናውን ማስጀመሪያ እና የእንኳን ደህና መጣችሁ መርሐ ግብር በሰ/ት/ቤቱ አዳራሽተከናውኗል።

በመርሐ ግብሩ ላይ የማኅበረ ቅዱሳን ትምህርት እና ሐዋርያዊ አገልግሎት ማስተባበሪያ ም/ኃላፊ የሆኑት ዲ/ን ኃይሌ አርአያ የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር አድርገዋል።

ም/ኃላፊው በንግግራቸው ሠልጣኞች በቆይታቸው የተዘጋጁላቸውን የሥልጠና ዓይነቶች በትጋት መውሰድ እንደሚገባቸው ጠቁመዋል። በተጨማሪም የፍሬ ሃይማኖት ሰ/ት/ቤት ም/ሊቀ መንበር የሆኑት ቀሲስ ታደሰ እንደገለጹት ሠልጣኞች ተገቢውን ዕውቀት ይዘው እንዲሄዱ በሰ/ት/ቤቱ በኩል አስፈላጊው ዝግጅት በሙሉ እንደተጠናቀቀ ገልጸዋል።

ሠልጣኞቹ በቆይታቸው  የተለያዩ የሥልጠና ርእሶች እና የውይይት ሐሳቦች እንደሚዳሰሱላቸው ለማወቅ ተችሏል


No One Knows the Day or Hour

 “But of that day and hour no one knows, not even the angels in heaven, nor the Son, but only the Father.  Take heed, watch and pray; for you do not know when the time is.  It is like a man going to a far country, who left his house and gave authority to his servants, and to each his work, and commanded the doorkeeper to watch. Watch therefore, for you do not know when the master of the house is coming in the evening, at midnight, at the crowing of the rooster, or in the morning lest, coming suddenly, he finds you sleeping.  And what I say to you, I say to all: Watch!”

Dear brethren! as time is of the value and we are not to know the second coming of our Lord on Judgement day, it is better to realize the warrant of Him to always be good, generous, gentile, faithful in prayer, fasting, diligence and Christian endeavors within the Orthodox Incarnation religion. We shall be alerted in living by His law and order of the Church and await His loving words to enter us in His kingdom saying “‘Come, you blessed of My Father, inherit the kingdom prepared for you from the foundation of the world:  for I was hungry and you gave Me food; I was thirsty and you gave Me drink; I was a stranger and you took Me in; I was naked and you clothed Me; I was sick and you visited Me; I was in prison and you came to Me.’ (Matthew 25:34-36).

Better to crave our destiny to heaven facing all the hardships and scarification for the soul than to be said, “Depart from Me, you cursed, into the everlasting fire prepared for the devil and his angels:  for I was hungry and you gave Me no food; I was thirsty and you gave Me no drink; I was a stranger and you did not take Me in, naked and you did not clothe Me, sick and in prison and you did not visit Me.’  (Matthew 25: 41-43)

May God’s mercy and benevolence be with us, Amen!


All this He did for the acknowledgement of Him as the Lord Who came down from the heavens for the salvation of human race upon those believing His holy words, miraculous of His hands and work of redemption. Yet, during His preaching the gospel, the Lord has warned about the second coming of Him for Judgement at the end of the age, through the disciples on mount of olive, accord their query. The apostle Saint Mark states it in his gospel as follows: - (Mark 13፡3-37)

The Signs of the Times and the End of the Age

Now as He sat on the Mount of Olives opposite the temple, Peter, James, John, and Andrew asked Him privately, “Tell us, when will these things be? And what will be the sign when all these things will be fulfilled?”

And Jesus, answering them, began to say: “Take heed that no one deceives you. For many will come in My name, saying, ‘I am He,’ and will deceive many. But when you hear of wars and rumors of wars, do not be troubled; for such things must happen, but the end is not yet. For nation will rise against nation, and kingdom against kingdom. And there will be earthquakes in various places, and there will be famines [a] and troubles. These are the beginnings of sorrows.

“But watch out for yourselves, for they will deliver you up to councils, and you will be beaten in the synagogues. You will be brought before rulers and kings for My sake, for a testimony to them.  And the gospel must first be preached to all the nations.  But when they arrest you and deliver you up, do not worry beforehand, or premeditate what you will speak. But whatever is given you in that hour, speak that; for it is not you who speak, but the Holy Spirit.  Now brother will betray brother to death, and a father his child; and children will rise up against parents and cause them to be put to death.  And you will be hated by all for My name’s sake. But he who endures to the end shall be saved.

The Great Tribulation

 “So when you see the ‘abomination of desolation,’ spoken of by Daniel the prophet, standing where it ought not” (let the reader understand), “then let those who are in Judea flee to the mountains.  Let him who is on the housetop not go down into the house, nor enter to take anything out of his house.  And let him who is in the field not go back to get his clothes.  But woe to those who are pregnant and to those who are nursing babies in those days!  And pray that your flight may not be in winter. For in those days there will be tribulation, such as has not been since the beginning of the creation which God created until this time, nor ever shall be.  And unless the Lord had shortened those days, no flesh would be saved; but for the elect’s sake, whom He chose, He shortened the days.

 “Then if anyone says to you, ‘Look, here is the Christ!’ or, ‘Look, He is there!’ do not believe it. For false Christ’s and false prophets will rise and show signs and wonders to deceive, if possible, even the elect.  But take heed; see, I have told you all things beforehand.

The Coming of the Son of Man

 “But in those days, after that tribulation, the sun will be darkened, and the moon will not give its light;  the stars of heaven will fall, and the powers in the heavens will be shaken. Then they will see the Son of Man coming in the clouds with great power and glory.  And then He will send His angels, and gather together His elect from the four winds, from the farthest part of earth to the farthest part of heaven.

The Parable of the Fig Tree

 “Now learn this parable from the fig tree: When its branch has already become tender, and puts forth leaves, you know that summer is near.  So you also, when you see these things happening, know that it is near—at the doors!  Assuredly, I say to you, this generation will by no means pass away till all these things take place.  Heaven and earth will pass away, but My words will by no means pass away.


Mount of Olive- The Second Coming of the Lord

Apostasy era was when we have witnessed the Lord’s presence for the first time Who wear the flesh and blood of human to appear on earth, for all the work of Him in redeeming the world. He was born from Holy Mother Saint Mary, clothed, breath fed like a baby, grew in few and limited within a height and weight of man, walked, talked and ate as one of us, was hungered, sorrowed, mourned, suffered much for His unconditional and true love.  

His words healing the soul, hands curing many maladies and the revelation of Him proved as Holy Son of the Holy Father on river Jordan upon His baptism in the hands of Saint John the Baptist and His Divinity on the high mountain locally known as “Debre Tabor” in front of the disciples. (Matthew 3:13-17, 17:1-8).


“መቅደስም ትይዩ በደብረ ዘይት ተቀምጦ ሳለ፥ ጴጥሮስና ያዕቆብ ዮሐንስም እንድርያስም ንገረን፥ ይህ መቼ ይሆናል? ይህስ ሁሉ ይፈጸም ዘንድ እንዳለው ምልክቱ ምንድር ነው? ብለው ለብቻቸው ጠየቁት። ኢየሱስም መልሶ እንዲህ ይላቸው ጀመር። ማንም እንዳያስታችሁ ተጠንቀቁ። ብዙዎች እኔ ነኝ እያሉ በስሜ ይመጣሉና፥ ብዙዎችንም ያስታሉ። ጦርንም የጦርንም ወሬ በሰማችሁ ጊዜ አትደንግጡ፤ ይህ ሊሆን ግድ ነውና፥ ነገር ግን መጨረሻው ገና ነው። ሕዝብ በሕዝብ ላይ መንግሥትም በመንግሥት ላይ ይነሣልና፤ በልዩ ልዩ ስፍራ የምድር መናወጥ ይሆናል፤ ራብ ይሆናል፤ እነዚህ የምጥ ጣር መጀመሪያ ናቸው።

እናንተ ግን ለራሳችሁ ተጠንቀቁ፤ ወደ ሸንጎ አሳልፈው ይሰጡአችኋል፤ በምኵራብም ትገረፋላችሁ፤ ምስክርም ይሆንባቸው ዘንድ ስለ እኔ በገዥዎችና በነገሥታት ፊት ትቆማላችሁ። አስቀድሞም ወንጌል ለአሕዛብ ሁሉ ይሰበክ ዘንድ ይገባል። ሲጐትቱአችሁና አሳልፈው ሲሰጡአችሁም ምን እንድትናገሩ አስቀድማችሁ አትጨነቁ፤ ዳሩ ግን በዚያች ሰዓት የሚሰጣችሁን ተናገሩ፤ የሚነግረው መንፈስ ቅዱስ ነው እንጂ እናንተ አይደላችሁምና።

ወንድምም ወንድሙን አባትም ልጁን ለሞት አሳልፎ ይሰጣል፤ ልጆችም በወላጆቻቸው ላይ ይነሣሉ። ይገድሉአቸውማል፤ በሁሉም ዘንድ ስለ ስሜ የተጠላችሁ ትሆናላችሁ፤ እስከ መጨረሻ የሚጸና ግን እርሱ ይድናል። ነገር ግን በነቢዩ በዳንኤል የተባለውን የጥፋት ርኵሰት በማይገባው ስፍራ ቆሞ ብታዩ፥ አንባቢው ያስተውል፤ በዚያን ጊዜ በይሁዳ ያሉ ወደ ተራሮች ይሽሹ፤ በሰገነትም ያለ ወደ ቤት አይውረድ፤ ከቤቱም አንዳች ይወስድ ዘንድ አይግባ፤ በእርሻም ያለ ልብሱን ይወስድ ዘንድ ወደ ኋላው አይመለስ።

በዚያን ወራትም ለርጉዞችና ለሚያጠቡ ወዮላቸው። ነገር ግን ሽሽታችሁ በክረምት እንዳይሆን ጸልዩ፤ በዚያን ወራት እግዚአብሔር ከፈጠረው ከፍጥረት መጀመሪያ ጀምሮ እስከ አሁን ድረስ ያልሆነ ደግሞም የማይሆን የመከራ ዓይነት ይሆናልና። ጌታስ ወራቶቹን ባያሳጥር፥ ሥጋ የለበሰ ሁሉ ባልዳነም፤ ነገር ግን ስለ መረጣቸው ምርጦች ወራቶቹን አሳጠረ።

በዚያን ጊዜም ማንም እነሆ፥ ክርስቶስ ከዚህ አለ፥ ወይም እነሆ፥ ከዚያ አለ ቢላችሁ አትመኑ፤ ሐሰተኞች ክርስቶሶችና ሐሰተኞች ነቢያት ይነሣሉና፥ ቢቻላቸውስ የተመረጡትን እንኳን ያስቱ ዘንድ ምልክትና ድንቅ ያደርጋሉ። እናንተ ግን ተጠንቀቁ፤ እነሆ፥ አስቀድሜ ሁሉን ነገርኋችሁ። በዚያን ወራት ግን ከዚያ መከራ በኋላ ፀሐይ ይጨልማል፤ ጨረቃም ብርሃንዋን አትሰጥም፤ ከዋክብትም ከሰማይ ይወድቃሉ፤ የሰማያትም ኃይላት ይናወጣሉ። በዚያን ጊዜም የሰው ልጅ በብዙ ኃይልና ክብር በደመና ሲመጣ ያዩታል። በዚያን ጊዜም መላእክትን ይልካል፤ ከአራቱ ነፋሳትም ከምድር ዳርቻ እስከ ሰማይ ዳርቻ የተመረጡትን ይሰበስባቸዋል። ምሳሌውንም ከበለስ ተማሩ፤ ጫፍዋ ሲለሰልስ ቅጠልዋም ሲያቈጠቍጥ፥ ያን ጊዜ በጋ እንደ ቀረበ ታውቃላችሁ፤ እንዲሁ ደግሞ እናንተ ይህን ሁሉ መሆኑን ስታዩ ቀርቦ በደጅ እንደ ሆነ እወቁ። እውነት እላችኋለሁ፥ ይህ ሁሉ እስኪሆን ድረስ ይህ ትውልድ አያልፍም።ሰ ማይና ምድር ያልፋሉ ቃሌ ግን አያልፍም።

ስለዚያች ቀን ወይም ስለዚያች ሰዓት ግን የሰማይ መላእክትም ቢሆኑ ልጅም ቢሆን ከአባት በቀር የሚያውቅ የለም። ጊዜው መቼ እንዲሆን አታውቁምና ተጠንቀቁ፤ ትጉ፤ ጸልዩም። ቤቱን ትቶ ወደ ሌላ አገር እንደ ሄደ ሰው ነው፤ ለባሮቹም ሥልጣን ለእያንዳንዱም ሥራውን ሰጥቶ በረኛውን እንዲተጋ አዘዘ። እንግዲህ በማታ ቢሆን ወይም በእኩለ ሌሊት ወይም ዶሮ ሲጮህ ወይም በማለዳ ቢሆን ባለቤቱ መቼ እንዲመጣ አታውቁምና፤ ድንገት መጥቶ ተኝታችሁ እንዳያገኛችሁ ስለዚህ ትጉ። ለእናንተም የምነግራችሁ ለሁሉ እላለሁ፤ ትጉ።”

ወንድሞች ሆይ! ጊዜ ዋጋው የላቀ በመሆኑና የጌታችንንም የፍርድ ቀን የሚያውቅ አለመኖሩን በቅዱስ ወንጌል ስለተነገረን በበጎነት፣ በቅንነትና በእምነት ጽናት ሆነን በጸሎት እንዲሁም በጾም፣ በትጋትና በክርስቲያናዊ ምግባር በመታነጽ በሃይማኖት ልንኖር ይገባናል፡፡ ዘወትርም ለሕጉ በመገዛትና ትእዛዙን በመፈጸም እስከ መጨረሻው ጸንተን “ንጉሡም በቀኙ ያሉትን እንዲህ ይላቸዋል። እናንተ የአባቴ ቡሩካን፥ ኑ፤ ዓለም ከተፈጠረበት ጊዜ ጀምሮ የተዘጋጀላችሁን መንግሥት ውረሱ። ተርቤ አብልታችሁኛልና፥ ተጠምቼ አጠጥታችሁኛልና፥ እንግዳ ሆኜ ተቀብላችሁኛልና፥ ታርዤ አልብሳችሁኛልና፥ ታምሜ ጠይቃችሁኛልና፥ ታስሬ ወደ እኔ መጥታችኋልና” ልንባል ያስፈልጋል፡፡ (ማቴ.፳፭፥፴፬‐፴፮)

ዕድል ፈንታችን መንግሥተ ሰማያት መውረስ ይሆን ዘንድም በምድራዊ ሕይወታችን መከራ ሥቃይ ተቀብለንና ለነፍሳችን መሥዋዕት መክፈል ይገባል እንጂ “እናንተ ርጉማን፥ ለሰይጣንና ለመላእክቱ ወደ ተዘጋጀ ወደ ዘለዓለም እሳት ከእኔ ሂዱ። ተርቤ አላበላችሁኝምና፥ ተጠምቼ አላጠጣችሁኝምና፥ እንግዳ ሆኜ አልተቀበላችሁኝምና፥ ታርዤ አላለበሳችሁኝምና፥ ታምሜ ታስሬም አልጠየቃችሁኝምና” ከመባል ይሠውረን፡፡ (ማቴ. ፳፭፥፵፩‐፵፫)
የአምላካችን ቸርነትና ረድኤት አይለየን፤ አሜን!


ደብረ ዘይት፡- ዳግም ምጽአት

ዘመነ ሥጋዌ የጌታችን መገለጥ ለመጀመሪያ ጊዜ የተመለከትንበት፣ ይህም ከሰማያት ወርዶ እኛን ለማዳን ከንጽሕት ቅድስት ድንግል ማርያም ከሥጋዋ ሥጋ ከነፍሷ ነፍስ ነሥቶ ሰው በመሆን ዓለምን ያዳነበት ነው፡፡ እርሱ እንደ ሰው ተወልዶ፣ እንደ ሕፃናት በጨርቅ ተጠቅልሎ፣ ጡት ጠብቶ፣ በየጥቂቱ አድጎ፣ በአጭር ቁመት በጠባብ ደረት ተወስኖ፣ በእግር ተመላልሶ፣ እንደ ሰው ተርቦና ተጠምቶ፣ ኀዘን መከራን ተቀብሎ በፍጹም ፍቅሩ አድኖናል፡፡

ፈውሰ ነፍስ በሆኑት ትምህርቶቹ ዓለምን አጣፍቶ፣ አዳኝ በሆኑት እጆቹ ልምሾዎችን፣ ድዊዎችንና አንካሶችን አድኖ፣ ጎባጣን አቅንቶ፣ የዕውራንን ዓይን አብርቷል፡፡ የእግዚአብሔር አንድያ ልጅ መሆኑንም በፈለገ ዮርዳኖስ በመጥምቀ መለኮት እጅ ተጠምቆ አስመስክራል፡፡ ብርሃነ መለኮቱ በታየበት በደብረ ታቦር ተራራም አምላክነቱን ገልጧል፡፡ (ማቴ.፫፥፲፫-፲፯፣፲፯፥፩-፰)

ይህን ሁሉ ያደረገው ሰዎች አምላክነቱን አውቀን፣ ከሰማየ ሰማያት የወረደውና መከራን ተቀብሎ በመስቀል ላይ የሞተው ለእኛ ድኅነት መሆኑን እንዲሁም ድንቅ ሥራውን የፈጸመበት ይህን ጥበቡን ተረድቶና፣ የእጁን ሥራ፣ የቃሉን ተእምራት ያመነውን ሁሉም እንደሚድነን ሲያበስረን ነው፡፡ በተጓዳኝም በመዋዕለ ስብከቱ ስለ ዳግም ምጽአቱና ምልክቶቹ በደብረ ዘይት ተራራ ላይ በዝርዝር በደቀ መዛምርቱ በኩል አሳውቆናል፡፡ ሐዋርያው ቅዱስ ማርቆስ በወንጌሉ እንዲህ ይገልጸዋል፡፡ (ማር.፲፫፥፫-፴፯)




The Ethiopian Orthodox Incarnation Church has named the fourth week of “The Great Lent” with the healed person in Bethsaida “The Impotent Man,” accordingly and commemorates it by the cured ailments of Lord and by helping out the poor. We shall then visit the sick, free the prisoners, feed the hungered, water the thirst, clothe the deprived and sympathize the depressed as we learned from our Lord.

On the Sabbath, it is the day we commemorate and glorify God’s healing and redemption. Prophet David sings as, “for He will deliver the needy when he cries, the poor also, and him who has no helper.” (Psalm 72:12) Righteous Job has witnessed saying, “How have you helped him who is without power? How have you saved the arm that has no strength?” (Job 26:2)

Prophet David’s words “Let all those who seek You rejoice and be glad in You; Let such as love Your salvation say continually, “The Lord be magnified!”, we shall also be happy about God. (Psalm 40:16)
Readings: -(Galatians 5:1 and James 5:14)
(Acts 3:1)
“Mesebak” Prophets David’s words in rhyme: - “The Lord will strengthen him on his bed of illness; You will sustain him on his sickbed. I said, “Lord, be merciful to me; Heal my soul, for I have sinned against You.” (Psalm 41:3-4)
May God’s mercy, benevolence and blessing be with us, Amen!


Those are elderly by love of money, youngsters by fornication, women by jewelries, Priests by conceit and monks by greed)

The Angel of God come down from the heavens and stirring up the water and only one who entered the pool was cured. The meaning of the water is baptism and the Angel who stirred it is the resemblance of priests who comes down to sanctify the water and on the sixth day; Sabbath, only one person was being cured which signifies the mercy of our fathers that is not seized and the truth about erratic of it, shows its un-absoluteness.

Lord and Savior Jesus Christ saw the impotent lying there, and knew that he already had been in that condition a long time, He said to him, “Do you want to be made well?” The sick man answered Him, “Sir, I have no man to put me into the pool when the water is stirred up; but while I am coming, another steps down before me.” Lord Jesus said to him, “Rise, take up your bed and walk.” And immediately the man was made well, took up his bed, and walked. And that day was the Sabbath. (John 5:6-9)

Lord Jesus whom Saint Paul witnessed for in his epistle to the Hebrews saying, “For the word of God is living and powerful, and sharper than any two-edged sword, piercing even to the division of soul and spirit, and of joints and marrow, and is a discerner of the thoughts and intents of the heart” asked the impotent man if he wished to be healed. (Hebrew 4:12) As it is stated, “For who knows what is good for man in life, all the days of his vain life which he passes like a shadow? Who can tell a man what will happen after him under the sun?” who can know and give us what we seek without us asking Him, but our God. (Ecclesiastes 6:12)

However, he was going to betray Him later on and for him not accuse the Lord saying, “He cure me without my permission, telling to carry my bed,” he asked his own permission, also for his conscience to castigate him.

The reason our Lord told the impotent man to “Rise, take up your bed and walk”: -
• is as Saint Esdros said, which the Lord will to reveal His miraculous as the bed was made up of strong metal
• the second is for the impotent man not to say “I have also payed sacrificed for my healing as I left my bed for Him.” and thus he told Him to “take up your bed and walk.”

Unfortunate though! The impotent man who was embedded for 38 years and had no one to take care, forgot His healer. He did not even know Who He was. The Evangelist John said, “But the one who was healed did not know who it was.” (John 5:13) The Lord Who has done all this was forgotten. Just as today, who has not forgotten God Who healed us from our aliments, tribulations and scarcity like the impotent man? And who has remembered Him listening to His words and seeing His miraculous? Is there anyone who stood up with the counsel of God to listen and witness His words? Any person who listen to His words?

Prophet Jeremiah said, “For who has stood in the counsel of the Lord, and has perceived and heard His word? Who has marked His word and heard it? (Jeremiah 23:18) We have also forgotten The Lord’s sacrifice who has freed us from the Adam’s infirmity and mock are told to look into our heart by Prophet Isaiah as, “Now therefore, do not be mockers.” (Isaiah 28:22)

The impotent was unaware of Who cured him. when he found Him in the synagogue, he went and told the Jews it was Lord Jesus who cured him. “Afterward Jesus found him in the temple, and said to him, “See, you have been made well. Sin no more, lest a worse thing come upon you.” (no. 14) But forgetting his healer, the impotent man slapped his Lord and therefore his hands dried and slimmed.

Now a days as well, alike the impotent man, many of our hearts has dried, personhood slimmed, consciously blinded, broken heart, seeking cure surrounding the baptism site, churches, parishes and monasteries. We seek healing and salvation. We can be healed if we hold on to the hope of God just like the impotent man.


The Impotent Man

There was once an impotent man during the apostasy age, embedded for 38 years at Bethsaida pool, in Jerusalem nearby the temple. His luck was so unfortunate that disabled him to enter the pool for cure whilst the Angel of God stirred it up once a while, that is on the first Sabbath. (John 5:4)

The Bethsaida had five porticoes and steps for the aliment to enter the pool and be baptized for their cure. The resemblance of the water is the Jews, the five porticoes resembles Torah and the five books of Mosses in which they were fenced by. The way one entered first to the pool and be cured, is the resemblances of the unity of theirs named “House of Israeli.” The other resemblance of the five porticoes is the “Five Sacrament of the Church.” Those who hope and in faith of them, are endowed Childhood of Holy Trinity. The five types of aliment are the resemblances of the five gender laity alongside their tribulations.


ማኅበረ ቅዱሳን ለሁለት ቀናት ሲያካሂድ የነበረውን የ2016 ዓ.ም የ6 ወር የሥራ አመራር ጠቅላላ ጉባኤውን አጠናቀቀ::

ትናንት መጋቢት 21/2016 ዓ.ም በመጀመሪያ ቀን ውሎው የሥራ አመራር የ6ወር ቃለ ጉባኤ ፣ የሥራ አመራር ጉባኤ ጽ/ቤት ፣ የሥራ አሰፈጻሚ ጉባኤ ፣ የኤድቶሪያል አገልግሎት ማስተባበሪያ እና የኦዲት አገልግሎት ሪፖርቶች ቀርበው ተወያይቷል ፡፡

በዛሬው ሁለተኛ ቀን ውሎውም በወቅታዊ የቅድስት ቤተ ክርስቲያን ጉዳዮችና የማኅበረ ቅዱሳን የአገልግሎት ድርሻ ላይ በሰፊው ተወያይቶ ውሳኔ አሳልፏል::

ብፁዕ አቡነ አብርሃም የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ የባህር ዳርና የሰሜን ጎጃም አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ተገኝተውም ለተሳታፊዎቹ አባታዊ ቡራኬና ቃለ ምእዳን አስተላልፈዋል::

የማኅበረ ቅዱሳን ሰብሳቢ ሊቀ ትጉሃን ቀሲስ ዶ/ር ሙሉጌታ ስዩም በማጠቃለያ መልዕክታቸው ’’በፈተና ውስጥ ሁነንም ቢሆን ለቅድስት ቤተ ክርስቲያን አገልግሎት እንትጋ፤ የማኅበረ ቅዱሳንን እሴቶችና መርሆዎችንም እንጠብቅ፤ በጸሎትና በመንፈሳዊ ሕይወታችንም እንበርታ’’ ብለዋል::

የማኅበረ ቅዱሳን ዋና ጸሐፊ መምህር ዋሲሁን በላይ በበኩላቸው የማኅበሩ አባላት የማኅበረ ቅዱሳንን መዋቅር በመጠበቅ የአገልግሎት ኃላፊነታቸውን እንዲወጡና ለቅድስት ቤተ ክርስቲያን አገልግሎት ካለፈው ጊዜ በላይ እንዲተጉ መልእክት አስተላልፈዋል::

Показано 20 последних публикаций.