ማኅበረ ቅዱሳን ( Mahibere Kidusan)


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: Религия


The channel of mahibere kidusan

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
Религия
Статистика
Фильтр публикаций




ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ 
ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት  ወቅታዊ  ጉዳዮችን አስመልክተው  አባታዊ የሰላም ጥሪ አስተላለፉ።


በማኅበረ ቅዱሳን የጎንደር ማእከል “አደራ አለብኝ” በሚል መሪ ቃል መርሐ ግብር አከናወነ።

ጥር ፪ ቀን ፳፻፲፯ ዓ.ም

“አደራ አለብኝ” በሚል መሪ ቃል የማኅበረ ቅዱሳን ጎንደር ማእከል ታኅሣሥ 27 ቀን 2017 ዓ.ም በማእከሉ የስብከተ ወንጌል አዳራሽ የድኅረ ግቢ ጉባኤ መርሐ ግብር ማካሄዱ ተገልጿል፡፡

በመርሐ ግብሩ ከ140 በላይ የግቢ ምሩቃን የተሳተፉ ሲሆን "የአገልግሎት በር" በሚል ርዕስ ሥልጠና ተሰጥቷል።

በተለያዩ የአገልግሎት ዘርፎች ለረዥም ጊዜ ያገለገሉ አባላት የልምድ ልውውጥ በማካፈል አባላት ሥራ፣ ሁኔታ፣ ቦታና ጊዜ ሳይገድባቸው ባሉበት ሆነው ሐዊርያዊ አገልግሎታቸውን መፈጸም እንደሚገባቸው መልእክት ተላልፏል።


የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ልደት በዓል የእንኳን አደረስዎ መርሐ ግብር ተከናወነ።

ጥር ፩ ቀን ፳፻፲፯ ዓ.ም

የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ልደት በዓል የእንኳን አደረስዎ መርሐ ግብር በጽርሐ ተዋሕዶ ተካሂዷል።

በመርሐ-ግብሩ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት፣ የየመምሪያ ኀላፊዎች የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የሥራ ኃላፊዎች፣ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት ሠራተኞች የአድባራትና ገዳማት አስተዳዳሪዎች እና ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።

የአዲስ አበባ ገዳማትና አድባራት አስተዳዳሪዎች በጽሑፍ የተደገፈ የእንኳን አደረሰዎ መልእክት ያስተላለፉ ሲሆን በዓሉን የተመለከተ ዝማሬ በሊቃውንት ቀርቧል።

ቅዱስ ፓትርያርኩም በመርሐ ግብሩ ለተገኙት እንግዶች የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት አስተላልፈዋል።

ምንጭ የኢ/ኦ/ተ/ቤ መገናኛ ብዙኃን አገልግሎት ስርጭት ድርጅት/EOTC


በማኅበረ ቅዱሳን ዲላ ማእከል አቡነ ጎርጎርዮስ ት/ቤት የልደት በዓልን ምክንያት በማድረግ ለነዳያን የምግብና የስጦታ መርሐ ግብር ተካሄደ።

በዲላ አቡነ ጎርጎርዮስ ት/ቤት በተቋቋመው የበጎ አድራጎት ማኅበር ኮሚቴ ከተለያዩ ምእመናን የአልባሳትና የምግብ ግብዓቶችን በማሰባሰብ ድጋፍ ለሚፈልጉ ወገኖቻችን የማዕድ ማጋራትና የአልባሳት ስጦታ አካሂዷል።

የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓልን ምክንያት በማድረግ በተከናወነው በዚህ መርሐ ግብር ላይ የዲላ ወለሜ ደብረ ሰላም ቅዱስ ዑራኤል ደብር አስተዳዳሪ የሆኑት መልአከ ሰላም ቀሲስ አምሳሉ "በጎ ኅሊና ይኑርህ " በሚል መሪ ቃል ትምህርተ ወንጌል የሰጡ ሲሆን የማኅበረ ቅዱሳን የዲላ ማእከል የአቡነ ጎርጎርዮስ ት/ቤት ርእሰ መምህር በሆኑት አቶ ታደለ በጌዴኦ ቋንቋ የመርሐ ግብሩን ዓላማ እና መልእክት አስተላልፈዋል።



Показано 6 последних публикаций.