መሪጌታ አምደብርሃን የባህል ህክምና መስጫ ማዕከል 🌿🌿🌿


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: Эзотерика


☑ ከጥንት አባቶቻች በተቸረን ሰሎሞናዊ ጥበብ ተፈጥሮ ያበቃላቸው የእፅዋት መድሀኒቶችን በመጠቀም ክፉ ዓይነ ጥላ ፣ በቤተሰብ ወይም በዘር የሚተላለፉ መናፍስት መፍትሔዎቻቸው ይተነተናሉ።
☑ አድራሻ ቁጥር 1 ምዕራብ ጎጃም ቡሬ ቁጥር 2 አ/አ እንዲሁም በተለያዩ የክልል ከተሞች እንልካለን
📞#0918487073
📞#0920253444
0918834904
መልዕክት ካለዎት @merigetaamedeberhan

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
Эзотерика
Статистика
Фильтр публикаций


የባህል ሕክምና ከዘመናዊ ሕክምና የተለየ ጥበብን እንደሚፈልግ ባለሙያዎች ይናገራሉ፡፡ በተፈጥሮና በሳይንስ መካከል ያለውን ሚዛናዊነት የማስጠበቅ ባህሪ እንዳለውም የዘርፉ ባለሙያዎች ይስማማሉ፡፡ አንድ የባህል ሐኪም ለታማሚው ፈውስ ለመስጠት የታማሚውን አካላዊ፣ አዕምሯዊና መንፈሳዊ ሁኔታ በጥልቀት ማጤን ይጠበቅበታል፡፡ ይህም የተለየ ጥበብንና ተሰጥኦን የሚጠይቅና ለተመረጡ ሰዎች ብቻ የሚሰጥ ፀጋ ተደርጎ ይታሰባል፡፡

በባህላዊ ሕክምና መድኃኒቱ ከሚቆረጥበት ዕለትና ጊዜ ጀምሮ መደረግ ያለባቸው ጥንቃቄዎች አሉ፡፡ ዕፀዋት የተፈጠሩት በዕለተ ማክሰኞ ነው ተብሎ ስለሚታመን ባህላዊ ሐኪሙ ለመድኃኒትነት የሚውሉ ዕፀዋትን የሚቆርጠው በዚሁ ዕለት ነው፡፡ መድኃኒቱን ለመቁረጥ ከመውጣቱ አስቀድሞ መደረግ ያለባቸው የተለያዩ ጥንቃቄዎችም አሉ፡፡

ለምሳሌ አንድ የአፋር ብሔረሰብ የባህል ሐኪም የሚከተላቸው የመድኃኒት ዕፀዋት አቆራረጥ ሥነ ሥርዓት አሉት፡፡ የአፋር ብሔረሰብ ባህላዊ እሴቶች በሚል ርዕስ በተዘጋጀው መጽሔት መሠረት፣ ሐኪሙ መድኃኒት ለመቁረጥ ከቤቱ መውጣት ያለበት በቀን በተወሰኑና ሰው በማይበዛባቸው ሰዓታት ነው፡፡ መድኃኒት ለመቁረጥ በአካልም ሆነ በአዕምሮ ንፁህ መሆን ግድ ነው፡፡ በአዕምሮ ተንኮል እያሰላሰሉ መድሐኒት መቁረጥና ለታማሚው መስጠት ዋጋ ዋጋ የለውም ተብሎ ይታሰባል፡፡ ለዚህም በተቻለው ሁሉ ተንኮል አለማሰብ አለበት፡፡ መድሐኒቱን ከመቁረጡና ከቆረጠ በኋላ ከቅዱስ ቁርዓን ውስጥ የተወሰኑ አንቀጾችን መቅራት አለበት፡፡

አንዳንድ በምሽት ሲቆረጡ ዕርኩስ መንፈስ የማዝያስ ባህሪ ያላቸው ዕፀዋት አሉ ተብሎ ስለሚታሰብ አብዛኞቹ የብሔረሰቡ የባህል ሐኪሞች መድኃኒት መቆረጥ ያለበት በቀን እንደሆነ ይስማማሉ፡፡ በረመዳን ወር፣ በአረፋና በመውሊድ በዓላት ዕለት የመድኃኒት ዕፅ አይቆረጥም፡፡ ዝናብ በሚዘንብበት ጊዜ መድኃኒት መቁረጥም አይመከርም፡፡ የተቆረጠው መድኃኒት ቤት እስኪገባ ድረስ በምንም ዓይነት ውኃ ሊነካው አይገባም፡፡

በዚህ መለኩ መድኃኒቱ ከተቆረጠ በኋላ ሕክምናውን ለመስጠት ከታማሚው ጋር ቤተሰባዊ ግንኙት መፍጠር ያስፈልጋል፡፡ ሕክምናው ከተደረገለት በኋላ መድኃኒቱ እስኪያሽረው ከማድረግ መቆጠብ የሚገባው አንዳንድ ነገሮችም አሉ፡፡  በክልሉ የባህል ሕክምና ዕውቀት ያላቸው፣ ሕክምናውን ከአሥር ዓመት ዕድሜአቸው ጀምሮ መስጠት ይችላሉ፡፡

አንድ አንድ በኤፍራጥስ እና በጢግሮስ
ወንዞች ዳርቻ ላይ ይኖሩ የነበሩ የሱሜሪያ (በአሁኑ ኢራቅ) ሕዝቦች ከክርስቶስ ልደት በፊት ከ4,000 ዓመታት በፊት፣ እንዲሁም ግብፆች ከ3,700 ዓመታት ከክርስቶስ ልደት በፊት ባህላዊ መድኃኒቶችን መጠቀም እንደጀመሩ የተለያዩ የታሪክ ድርሳናት ያሳያሉ፡፡

ዘመናዊ ሕክምና አስኪጀመር ድረስ ፈውስ የሚገኘውም በባህላዊ ሕክምና ነበር፡፡ ትልቅ በጀት ተይዞለት በቂ ጥናት በሚደረግበት በዘመናዊ ሕክምና የተሻለ ሕክምና ማግኘት እንደሚቻል ብዙዎች ያምናሉ፡፡ ይሁንና በአፍሪካና በእስያ የሚገኙ 80 በመቶ የሚሆኑ ሰዎች የባህላዊ ሕክምና ተጠቃሚ መሆናቸውን መረጃዎች ያሳያሉ፡፡ አንዳንድ ጥናቶች ደግሞ አራት ቢሊዮን የሚሆነው የዓለም ሕዝብ የባህላዊ ሕክምና ተጠቃሚ መሆኑን ያመለክታሉ፡፡

የዓለም ጤና ድርጅት በተለያዩ የዓለም ክፍሎች ከሚሰጡ ባህላዊ የሕክምና ዓይነቶች፣ በቻይና ለሚሰጡ የባህል ሕክምናዎች ዕውቅና ከሰጠ ሰነባብቷል፡፡ በባህላዊ ሕክምና ቀዳሚ የሆነችው ይህች አገር እ.ኤ.አ. በ2012 በባህላዊ ሕክምና ብቻ 83 ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር ማግኘት ችላለች፡፡ ይህ እ.ኤ.አ. 2011 በዘርፉ ካገኘችው ገቢ የ20 በመቶ ብልጫ ነበረው፡፡

ከሌሎቹ አገሮች አንፃር የባህላዊ ሕክምናዎችን ብዙም እንደማይጠቀሙ በሚነገርላቸው በዩናይትድ ኪንግደም አካባቢዎች ለባህላዊ ሕክምና በየዓመቱ 230 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር እንደሚወጣ የዓለም የጤና ድርጅት ከዓመታት በፊት ያወጣው ሪፖርት ያሳያል፡፡ እ.ኤ.አ. በ2020 የዓለም የባህላዊ መድኃኒቶች ገበያ 115 ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር ይደርሳል የሚል ትንበያም አለ፡፡

በዚህ መጠን የአገርን ኢኮኖሚ እያንቀሳቀ የሚገኘው ባህላዊ ሕክምናን ምዕራባውያን ሰፊ ጥናት እያደረጉበት ይገኛል፡፡ በአንፃሩ ግን የበርካታ ባህላዊ መድኃኒቶች መፍለቂያ በሆነችው አፍሪካ በተለይም ኢትዮጵያ ለባህላዊ መድኃኒቶች ተገቢው ትኩረት ሳይሰጥ ቆይቷል፡

ከቻልን ለትብብር እንኳን አቅሙ ባይፈቅድልን ቀደምት የሆነው ሀገራዊ ጥበብን ስሙን ባናጠለሸው ምክሬ ነው።

አምደ ብርሃን!
ለበለጠ መረጃ 0918834904 ብለው ይደውሉ።










ሊያደርስብን ይችላል፡፡

መተት እና የዓይነ ጥላ መንፈስ በልዩነታቸው መተት የሚከብድበት አንዱ መተት አጋንንት እራሱን መቀየር መቻሉ ነው፡፡ መተት በሆድ ውስጥ አውሬ ሆኖ ይቀመጣል፡፡ ለምሳሌ አንድ ሰው በሻይ፣በጠላ፣በሚሪንዳ መተት ተመትቶ ቢሰጠው ያንንም ቢጠጣ ወደ ሆዱ ከገባበት ቀን ጀምሮ ጤና ማጣት፣ህመም መሰማት ይጀምረዋል፡፡ ይህ በሚጠጣ ነገር ወደ ሆዱ የገባው መተት ሰውዬው ሳያውቀው ከቆየ፣ሥጋዊ በሽታም ከመሰለው በጊዜ ሂደት ሆዱ ውስጥ የገባው መተት እራሱን በመቀየር እባብ፣እንቁራሪት፣አይጥ ወዘተ ሆኖ ውስጡ ተቀምጦ ሥጋውን በመብላት ደሙን በመጠጣት ለከፍተኛ ጤና መታወክና ጉዳት ይዳርገዋል፡፡ ይህ ብቻ አይደለም ሊገድለውም ይችላል፡፡

ዛሬ ሆዳችንን እያመመን፣የሆድ ህመማችን ትልቅ ጭንቀት ፈጥሮብን በየ ሆስፒታሉ ሄደን መፍትሔ የምናጣው መተት ቢሆንስ? ምክንያቱም በመተት ወደ ሆድ ገብቶ ደዌና አውሬ ሆኖ የተቀመጠው ነገር በሕክምና ምርመራና መሣሪያዎች አይታይም ይሠወራቸዋል፡፡ ሴቶችም በመተት ማኅፀናቸው ላይ ደዌና አውሬ ሆኖ ይቀመጣል፡፡ እንደ ጽንስ ይገላበጣል፣እንደ አውሬ ይጮኻል፡፡ በሕመም ያሰቃያቸዋል ግን በሕክምና የሕመማቸው ምክንያት አይታወቅም መፍትሔም አይገኝም፡፡ እህቶቼ መተት ቢሆን ማን ያውቃል?

ስለዚህ የመተት አጋንንት ውስጣችን ከገባ እራሱን እየቀያየረ የተለያየ በሽታ ይሆናል፡፡ በሚበላና በሚጠጣ ወደ ሆዳችን የገባው፣በቁሳቁስ ወደ እኛ የሰረጸው መተት ሆዳችንን ሊያሳምመን፣ለአእምሮ ሕመም/እብደት/ ሊዳርገን፣እጅ እግራችንን ሽባ ሊያደርገን፣ለወገብ ለልብ ወዘተ ሕመም ሊዳርገን ይችላል፡፡ መተትም አደገኛ የሚያደርገው ይህ ነው፡፡

ዓይነ ጥላ ሕይወታችንን የማጎሳቆል ሥራ የሚሠራው በስውር ነው፡፡ መተት ግን በግልጥ ነው፡፡ ዓይነ ጥላ በውስጣችን አሸምቆ ተደብቆ ከእኛው ጠባይ ጋር ተስማምቶ አድብቶ ነው የሚኖረው፡፡ መተት ግን ጥቃቱ የሚታይና ግልጥ ነው፡፡ የዓይነ ጥላ አጋንንት የሚጎዳን በጊዜ ሂደት ነው፡፡ መተት ግን በድንገት ነው፡፡
መተት ብዙ ጊዜ የተንኮለኞች የቅናት እና የክፋት እጅ ስለሆነ ተጠንቅቀን የምናመልጠው ሳይሆን በጸሎት የምንከላከለው ነው፡፡ አንድ አባት አንድ ወጣኒን ‹‹ልጄ ጀርባህ ላይ ግንድ ከሚጫንህና ሰው ከሚጫንህ የቱ ይሻልሃል›› አሉት፡፡ ወጣኒውም ብልህ ኖሮ ‹‹አባቴ ጀርባዬ ላይ ግንድ ቢጫነኝ ሰው ያወርድልኛል፤ሰው ከተጫነኝ ማን ያወርድልኛል›› አላቸው፡፡ ዛሬም በመተት ሰዎች ሕይወታቸውን ተጭነዋቸው የሚያወርድላቸው አጥተው ከቤሰተብ፣ከትዳር፣ከሥራ ተለይተው በየ ጸበሉና በየ ገዳሙ የሚንከራተቱትን ፈጣሪ ይቁጠራቸው፡፡

ወዳጆቼ ሰውና አጋንንት በማበር በመተት በዚህ ደረጃ የሚፈትኑን፣ሕይወታችንን የሚያበላሹት አንድም ለፈተና፣ለጸጋ፤ለክብር፤አንድም በእኛ የእውነተኛ አምልኮት ድክመት ነው፡፡ ሰማያዊ አምልኮት፣ጾም፣ጸሎት ስግደት በሌለበት ሕይወታችን በመተት አጋንንት ብዙ ነገር በማጣት ብንኖር ፈጣሪን ከመውቀስ እራስን መለስ ብሎ መፈተሹ አይከፋም፡፡

አስደናቂው ነገር የመተት እና የዓይነ ጥላ መንፈስ ሁለቱም ውስጣችን ካሉ ይተባበራሉ፡፡ አጋንንት ለክፉ ተግባራት እርስ በእርሳቸው ሲተባበሩ እኛ ግን ለመልካም ነገር እርስ በእርሳችን አንተባበርም፡፡ በተቃራኒው በምቀኝነት ጎራ ተሰልፈን አንዳችን ለአንዳችን ሕይወት መበላሸት ምክንያት እንሆናለን፡፡  የመተትም የዓይነ ጥላውም ሥራቸው፣ዓላማቸው ሕይወታችንን ማበላሸት ስለሆነ እራሳቸውን ላለማጋላጥ ተደብቀው ይኖራሉ፡፡ ደግነቱ ዓይነ ጥላው ከተጋለጠ፣መተቱም ይጋለጣል፡፡ አንዱ ሲያዝ አንዱም ይያዛል፡፡

ተወዳጆች ሆይ ትዕግስተኛው ኢዮብ ‹‹በምድር ላይ የሰው ሕይወቱ ብርቱ ሰልፍ አይደለምን›› ብሎናል፡፡ ስለዚህ በምድር እሰከ ኖርን ድረስ በሕይወታችን በአጋንንት ብርቱ ሰልፍ ሊገጥመን ስለሚችል አምልኮታችን በማጠንከር፣በጾም በጸሎት በስግደት በመበርታት  ልንዋጋ ይገባል፡፡ /ኢዮ 7÷1/

‹‹ሕዝቤ እውቀት ከማጣቱ የተነሳ ጠፍቶአል›› ት.ሆሴ 4÷6

‹‹ከትውልዱ ማን አስተዋለ?›› ት.ኢሳ 53÷8

‹‹ፈረስ ለጦርነት ቀን ይዘጋጃል፤ድል ግን ከእግዚአብሔር ዘንድ ነው›› ምሳ 21÷31

እውቀታችንን ሰዎች በመተት/በአጋንንት/ ግፊት እና በቅናት እንዴት ይወስዱታል?

የእኛን እውቀት ሰዎች በመተት ለራሳቸው ሊጠቀሙበት ይችላሉን?

በአጋንንት ጥበብ እውቀታችን ወደ ሌላ ሰው ሊተላለፍ ይችላል?

እውቀታችን መወሰዱን በምን እናውቃለን?

ይቀጥላል …


መተት


የመተት አጋንንት ከዓይነ ጥላ የሚለይበት እና አንድ የሚሆንበት!

ተወዳጆች ሆይ ከዚህ በፊት በዓይነ ጥላ መንፈስ መግቢያ ላይ አጋንንት ዓላማቸው አንድ ቢሆንም በሥራ ድርሻቸው እና በተንኮል ተልዕኮአቸው የተለያዩ መሆናቸውን በሰፊው አይተናል፡፡ በዚህ ክፍል የመተት እና የዓይነ ጥላ አጋንንት አስገራሚ አንድነታቸው እና ልዩነታቸውን እናያለን፡፡ ይህን እንድታውቁ የምፈልገው ለግንዛቤ ብቻ ሳይሆን የሰው ልጅ በአጋንንት ተንኮል ውስጥ ምን ያህል አጋንንታዊ ሱታፌ እንዳለው እንድትረዱና ሰው መልአክም ሰይጣንም የመሆን ሁለት ተቃራኒ ጠባይ በውስጡ እንዳለው እንድትገነዘቡና የፈተና ስልታቸውን እንድትሉ ነው፡፡

ወዳጆቼ ሰው የቅድስና ጠባይን ከተላበሰ ሥጋ ለበስ መልአክ መሆን ይችላል፡፡ ሰው የርኩሰትን ጠባይ ከተላበሰ ሥጋ ለበስ ሰይጣን መሆን ይችላል፡፡ በተለይ የለበሥነው ሥጋ የዕድቅ አደጋ ስለሆነ ከመልአካዊ ጠባይ ይልቅ ሰይጣናዊ ጠባይ በእኛ ሊታይ ይችላል፡፡ ለዚህም ነው ‹‹ሰው ሲከፋ ባለ ሁለት እግር አውሬ ይሆናል›› የሚባለው፡፡

መተት ከዓይነ ጥላ አጋንንት ጋር አንድ የሚያደርገው ሁለቱም የሰውን ልጅ ውድ ሕይወት ማበላሸት፣ውጥኑን፣እቅዱን ማኮላሸት ላይ ስለያተኩሩ ነው፡፡ መተትም ዓይነ ጥላም በሰው ልጅ ሕይወት ውስጥ ጣልቃ በመግባት ሕይወትን ከማበላሸት እስከ ማጥፋት ይደርሳሉ፡፡ ሁለቱም አለን፣እጄ ገባ፣እርግጠኛ ነኝ በምንላቸው ነገሮቻችን ላይ የሚያደርሱብን ስውር ጥቃት አንድ ነው፡፡

መተት እና ዓይነ ጥላ በዕድላችን፣በእውቀታችን፣በትምህርታችን፣በእጮኝነት እና በትዳር ሕይወታችን እንዳንጠቀም ከጥንስሱ ጀምሮ እስከ ድግሱ ድረስ የመደንቀር፣የማበላሸት ሥራን ይሠራሉ፡፡ ሁለቱም አሉኝ በምንላቸው ነገሮች እንዳንጠቀም የመጠርቀም ሥራን ይሠራሉ፡፡ ሁለቱም ተስፋ በጣልንባቸው ከመቶ ፐርሰንት በላይ እርግጠኛ በሆንባቸው ነገሮቻችን ላይ፣አጋንንታዊ የበላይ በመሆን በግልጽና በስውር፣የማይታይ ምስማር በመሆን ጠስቀይ ይይዙብናል፡፡ ሲላቸው በራሳቸው ሲላቸው በሰው እያደሩ፣የእኛን ነገር ገና ከጅምሩ እየገረገሩ ያበላሹብናል፡፡ መተት እና ዓይነ ጥላ የሰው ልጅ ዳግም የማያገኝውን፣ተመልሶ የማይኖረውን ውድ ሕይወቱን በማባከን፣የያዘውን በማስጣል ብሎም በመንጠቅ አንድ ናቸው፡፡

መተት እና የዓይነ ጥላ አጋንንት የሚለያቸው ወይም አንድ የማያደርጋቸው ደግሞ አለ፡፡ ይህም መተት በደጋሚዎች ወይም በጠንቋዮች በመጎተት ሰውን የሚቆራኝ አጋንንት ነው፡፡ መተት በሰው እድል የሚቀና፣በሰው መልካም ሕይወት በብግነት የሚኖር ሰው በሚበላ በሚጠጣ፣በቁስ ወዘተ በማስደገም የሚያቆራኘው አጋንንት ነው፡፡

ዓይነ ጥላ በደጋሚዎች የሚጎተት አጋንንት አይደለም፡፡ እራሱን ችሎ፣ክፋቱን ተንኮሉን ጠቅልሎ ወደ ሰው ሕይወት የሚገባ አጋንንት ነው እንጂ በደጋሚዎች የሚቆራኝ አይደለም፡፡ ዓይነ ጥላ የሰውን ልጅ ከማኅፀን ጀምሮ በጽንስ ጊዜ በመቆራኘት አብሮ የሚያድግ፣የሰውን ሕይወት የሚያጠወልግ አጋንንት ነው፡፡ መተት ግን ድንገት ወደ እኛ ሕይወት በሰው ክፋት የሚመጣ አጋንንት ነው፡፡

ዓይነ ጥላ የማንም አጋንንታዊ ድግምት የማያዘው በራሱ የክፋት መንገድ የሚራመድ ክፉ መንፈስ ነው፡፡ በእርግጥ መተት ገና በማኅፀን ባለ ጽንስ ላይ ቢደገምም መተትን ወደ ሰው ሕይወት ለማስገባት ገፊ አካላት ያስፈልጋል፡፡ ዓይነ ጥላ ግን ዕድላችን ላይ በመቅናት ሰተት ብሎ የሚገባ ነው፡፡ መተት በሰው ቅናት የሚገባ አጋንንት ሲሆን ዓይነ ጥላ እራሱ መንፈሱ በእኛ በመቅናት የሚገባ ነው፡፡

ዓይነ ጥላ በውስጣችን ከገባ በኃላ እራሱን እየቀያየረ በሕመም እየተመሰለ ይቀመጣል፡፡ መተትም ውስጣችን ከገባ ደዌ ሆኖ ይቀመጣል፡፡ ልዩነታቸው ዓይነ ጥላ አንዴ ውስጣችን ከገባ እንደ ግል ይዞታው ተደላድሎ ይቀመጣል፡፡ መተት ግን ውስጣችን ከገባ በኃላ እድሳት የሚባል አጋንንታዊ ሥርዓት አለው፡፡

እድሳት ማለት አንድ ሰው ላይ በመልካም ነገሩ መተት ሲመተትበት፣የሚያስመትተው ሰው በደጋሚው ወይም በመታቹ በኩል ለአጋንንቱ ግብር ያቀርብለታል፡፡ ለምሳሌ ገንዘብ፣በግ፣ደም ወዘተ ያቀርባል፡፡ ይህንን ያስደገመ ቀን ያቀረበውን ግብር በየ ዓመቱ ሊያቀርብ አጋንንታዊ ውል ይገባል፡፡ ይህንን የሚያደርገው የሰውን እድል ስለወሰደ በዛም ስለሚጠቀምበት ከሰው የወሰደው ዕድል፣እውቀት፣የትዳር፣የሥራ እድል ወዘተ በአጋንንት ተጠብቆ እንዲቆይለት እንዲጠቀምበት የሚያደርገው ነው፡፡

ብዙ ጊዜ መተት የተመተተባው ሰዎች ከአጋንንቱ በቀላሉ መላቀቅ የሚያቅታቸው በአጋንንቱ እና በሚደገምበት ሰው መሃል ያለው አስደጋሚው ሰው በየዓመቱ ወይም በየወራቶቹ በተደገመበት ሰው ስም ለአጋንንቱ ስለሚገበር የተመተተበት ሰው ሲታደስበት አጋንንቱ እንደ አዲስ ወደ ውስጡ ይገባል፣ጤና ያጣል፣የጀመራቸው ነገሮች በአስገራሚና ለማመን በማያስችል ሁኔታ ይበላሻል ወዘተ፡፡

አንድ ሰው በተለይ መተት የተመተተበት ሰው መተቱ ሲታደስበት የሚያሳየው ጠባይ አለ፡፡ ይህም በድንገት ጭው የሚል ስሜት መሰማት፣ያለ ምክንያት ከፍተኛ ድንጋጤ ውስጥ መግባት፣መረበሽ፣መጨናነቅ፣ፍርሃት መሰማት፣የሆነ የማናውቀው ነገር ውስጣችን ሲገባ መሰማት፣እራስን ስቶ መውደቅ/ይህ መንፈሱ ውስጣችን ሲገባ ነው/ በጠራራ ፀሐይ ብርድ ብርድ ማለት፣ውልብ ብሎ ሰውነታችንን የሚከብድ ስሜት መሰማት፣በድንገት የልብ ምት መጨመርና ዝብርቅረቅ የሚል ስሜት መሰማት፣ከፍተኛ ድንገተኛ የሰውነት ድካምና የመክበድ ስሜት መሰማት፣ሰላም ማጣት፣ድንገተኛ የባሕርይ ለውጥ ማሳየት፣ያለ ምክንያት ብስጭት ብስጭት ማለት፣ማዞር መቅለሽለሽ፣ጭንቅላት እና ልብ ላይ ጭንቅ የሚል ስሜት መሰማት፣ጩኽ ጩኽ የሚል ስሜት ከውስጥ መግፋት፤እጮኛሞች እና ባለ ትዳሮች ከሆኑ ድንገት የማስጠላት እና የመጥላት ስሜት ውስጥ መግባት፣መሳደብ፣እንለያይ ማለት፣የትዳር አጋርንና ልጆችን መጥላት፣ያለ ጥፋት መምታት ወዘተ ሊከሰቱብን ይችላል፡፡ ስለዚህ የተመተተበት ሰው መተቱ ሲታደስበት እንኳን ለሰው ለራሱም የማያውቃቸው የሚይጨበጡ የባሕርይ ለውጦችን ያሳያል፡፡

ለምሳሌ በመጠጥ የተመተተበት ሰው በስንት ጸሎት እና ጸበል መጠጡን ከተወ የታደሰበት ቀን ንጉልያው እስኪዞር ድረስ ጠጥቶ ይሰክራል፡፡ በእጮኛውና በትዳሩ ላይ በመቅናት የተመተተበት ሰው ከሆነ የታደሰበት ቀን ከእጮኛውና ከትዳር አጋሩ እና ከልጆቹ ጋር ያለ ምክንያት ከፍተኛ ጠብ ውስጥ ይገባል፡፡ በእውቀቱ የተመተተበት ሰው ከሆነ የታደሰበት ቀን በዛን ሰሞን ደንዝዞ ፈዞ ይከርማል፡፡ በገንዘቡ የተመተተበት ሰው ገንዘቡ ከኪሱ ለመውጣት የሚያጨበጭቡ ይመስል ያለ ምክንያት ይወጣል፡፡ ግን በምን እንዳወጣው፣ገንዘቡን የት እንዳሰረሰው፣ምን ቁም ነገር ላይ እንዳዋለው አይውቅም፡፡ ሌላም ሌላ …. በአጠቃላይ እድሳት ማለት ከአጋንንቱ ጋር በሰው ሕይወት እና እድል ላይ ውል ማራዘም ማለት ነው፡፡ ይህ ማለት በሰው ሕይወት ላይ በአጋንንት ስውር ምስጢር መቆመር ማለት ነው፡፡

ተወዳጆች ሆይ መተት ከዓይነ ጥላ አንዱ የሚለይበት መተት በምንበላው ምግብ፣ በምንጠጣው መጠጥ፣በምንለብሰው የውስጥ እና ውጭ ልብስ/በላብ በወዝ/  በምንይዘው ቁስ ወዘተ ስለሚደገም በቀላሉ ሕይወታችን ሊደረመስ፣ጤናችን ሊቃወስ ይችላል፡፡ ሌላው መተት ከዓይነ ጥላ የሚለይበት ምክንያት መተት አደገኛና ገዳይ መሆኑ ነው፡፡ ምንክያቱም መተት በመርዝ መልክ ሊሠራ ስለሚችል የተመተተበትን ምግብ የበላ ወይም መጠጥ የጠጣ ሰው በድንገት ሊሞት ይችላል፡፡ በተለይ ወደ ሆድ በሚገቡ ነገሮች አጋንንቱ በሰውነታችን ሕዋሶች በመሰራጨት፣ከፍተኛ ጉዳት






#የቤተሰብ ዛር
ከቤተሰብ ወርዶ ለልጅ ልጅ የሚተርፍ የባዕድ አምልኮ የዛር መንፈስ ቁርኝት!

#የዛር መንፈስ ማለት በአብዛኛው ጊዜ ፈቅደን ወደን ከ ፈጠረን አምላካችን ይልቅ ክፉ የዛር መንፈስ ያዘዝከኝን አደርግልሃለሁ ያዘዝኩህን አድርግልኝ ብለን ቃል በመገባባት ከራሳችን ጋር እንደንጉስ አክብረን የምናዋሃደው መንፈስ ሲሆን።

#የዛር መናፍስት ከሰው ልጅ ማህበራዊ ኑሮ በመቆራኘት የሰው ልጅ ስጋውን ለብሰው ከደሙ ጋር ተዋህደው ህይወታቸውን የሚመሩ ረቂቃን መናፍስት ናቸው።

#የዛር መናፍስ ከአያት እንዲሁም ከአባት እናቶቻችን ዘንድ  በደም ሐረጋችን በመውረድ ልጅን እንዲሁም የልጅ ልጅን ትልቅ ፈተና ውስጥ የሚጥሉ የከፉ መናፍስት ናቸው።

#የዛር መናፍስት ከሰው ልጅ ጋር ከመላመዳቸው የተነሳ የየእለቱ የሰው ልጅ እንቅስቃሴ አብረው ስያከናውኑ ወዳልሆነ መንገድ ሲመሩ ሃገርንም ስያተራምሱ የሚኖሩ መናፍስት ናቸው።

#የዛር መናፍስቶ የተለያየ ነገድ ሲኖራቸው በየአከባቢው እና በየሀገሩ የተለያዩ ስሞችን እራሳቸውን በሚገልጽ መንገድ በመጠራት ሲመለኩ ይኖራሉ።

#የዛር መናፍስት የዓይነጥላ እና የመተት ምልክትን በመላበስ ራሳቸውን ደብቀው የሰው ልጅን በጥርጣሬ ከወዳጅ ዘመዶቹ እንዲጋጭ የማድረግ ብቃትም አላቸው።

#የዛር መናፍስት በተለያዩ የጥበብ ሰዎች በተለያዩ አባዎራዎች በተለያዩ ባልቴቶች እንዲሁም በተለያዩ ህጻናቶች በመቆራኘት ስራቸውን ስያከናውኑ ይኖራሉ።

#የዛር መናፍስት በ ተለያዩ መንገዶች ካልተገሰጹ እንዲሁም ካልተወገዱ እስከ ሰባት ትውልድ ድረስ የመውረድ አቅም እንዳላቸው ሊቃውንት ያትታሉ።

#የዛር መናፍስት ወደው ፈቅደው ላመለክዋቸው ሰዎች እና ልጆቻቸውን ከጥቅማቸው ይልቅ ጉዳታቸውን በማመዘን ለተለያዩ አካላዊ እና ስነልቦናዊ ችግር የሚዳርጉ መናፍስት ናቸው።

#የዛር መናፍስት በሰዎች ዘንድ በመላክም ሌሎች ሰዎችን የማጥቃት ክህሎትም አላቸው። ይህ ማለት ጉዳዩ አድርግልኝ ላድርግልህ ነውና!በገቡት ቃል መሰረት የተለያዩ እንስሳት በመስዋዕትነት በማቅረብ ጠላታቸውን እንድያጠቃላቸው በታዘዙበት ቅጽበት የተላከበት ሰው በጸሎት እና በሕገ እግዚአብሔር ያልጸና እንደሆነ በዛር መናፍስት የመጠቃት እድሉ እጅግ ሰፊ ነው።

#የዛር መናፍስት የሚፈጥሩት ችግር፦

፦ትዳር እንዳትይዙ ትልቅ እንቅፋት ይፈጥራሉ።
፦በሰዎች ዘንድ መጠላትን ይፈጥራሉ።
፦የሰውነት ጠረን ፣የአፍ ጠረን፣- ሆድ ውስጥ መንፋት የመንቀሳቀሰ ምልክት ጨጒራን በመመሰል ትልቅ ሁከት ይፈጥራሉ።
፦ሴቶች ላይ የማህጸን ህመም፣የወገብ ህመም፣ ህልመ ሌሊት፣ፍራቻን በመጫር የህይወት ስጋት ይሆናሉ።
፦ወንዶች ላይ ህለመ ሌሊት፣ድክመተ ወሲብ እና ትዳር ማጣትን ያስከትላሉ።
፦ትልቅ የስራ ዕድል መዝጋት፣ብር አለመበርከት፣ማዛጋት ፣ማንጠራራት፣እጅ እና እግር ፓራላይዝድ አልያም ሸምቅቆ በመያዝ ችግር ይፈጥራሉ።
፦በስኳር፣በደም ግፊት ፣በሪህ በመመሰል የክኒን ሱሰኛ አድርገው ሲጫወቱብን ይኖራሉ።
፦ራስ ህመም፣በአስም፣በመካንነት ችግር ይፈጥራሉ።
፦በጣም የባሰ እንደሆነ ደግሞ ማስጎራት ፣አመድ ማስቃም ፣ጫት ፣ቡና ማሰኘት ፣የአልጋ ቁራኛ አድርገው ማሰቀመጥ የመሳሰሉት ችግሮች የመፍጠር ኃይል አላቸው።

#የዛር መናፍስት እንዴት ከእኛ ዘንስ ማራቅ እንችላለን?
#በመጀመርያ ወደ ቤተ አምልኳችን  በመሔድ የተለያዩ መፍትሔዎች በታላላቅ አባቶቻችን የ እግዚአብሔር መፍትሔ መሻት።

#በመቀጠል በራስ ጊዜ ሳንሰለች በጸሎት በጾም በስግደት ስጋችንን በማድከም ያ ክፉ ያለውድ ከቤተሰብ የወረደቅ መንፈስ ማስወገድ እንችላለን።

#ይህ ሁሉ አድርገው አማራጭ እና መፍትሔ ያጡ እንደሆነ በየአከባብያችሁ ወደሚኖሩ ከ እግዚአብሔር ዘንድ ጥበብ እና ፀጋ ወደተሰጣቸው አባቶች ጎራ በማለት የ እግዚአብሔር ቃልን በመጥራት የእጽዋቶችንም ኃይል በመጠቀም አስቸጋሪ እና አሰልቺ የሆነ የዛር መንፈስን እንገስጸው እናስወግደውም።

1ኛ መፍትሔ ጧት ጧት
#ከበተሰብ የወረደ ዛርን እንዴት እናስወግደው?

#የምድር እንቧይ ሥር ቀጠል
#የደድሆ ሥር ቅጠል
#የጭቁኝ ሥር ቅጠል
#የፌጦ ፍሬ
#የደማካሴ ሥር ቅጠል

እነዚህ እጽዋቶች ሮብ እና ዓርብ በመቁረጥ አንድ ላይ በመጨቅጨቅ ጧት ጧት በአዲስ እቃ በመዘፍዘፍ ለ ፯ ቀን ያክል ሙሉ ሰውነትን  መታጠብ የዛር መንፈስ ያስወግዳል።እንዲሁም ሙሉ ግቢውን ጧት ጧት ለ ፯ ቀን መርጨት።ከራስ አልፎ ጎረቤት ላይ ቢኖርም ይወገዳል።

2ኛ መፍትሔ ማታ ማታ
#ጤና አዳም ሥር ቅጠል
#ቀጠጥና (የአህያ ጀሮ) ሥር ቅጠል
#የጊዜዋ ሥር ቅጠል
#የእንቧጮ ተቀጽላ ሥር ቅጠል

እነዚህን በማድረቅ ከደረቁ በኃላ አንድ ላይ በማቀላቀል ማታ ማታ ሊተኙ ሲሉ ከተቀላቀለው በሾርባ ማንኪያ አንድ በመለካት በፍም እሳት ለ ፯ ቀን ሙሉ ሰውነትዎን እየታጠኑ መተኛት።
ቤተሰብ ሙሉውን ይህ ድርጊት በየእምነቱ እጽዋቱ ላይ በመጸለይ ቢጠቀም ከፈጣሪው ዘንድ ሙሉ መፍትሔ ያገኛል።

የቀደምት አባቶቻችንን እውቀት እና ጥበብ ሳይበረዝ እንደወረደ ይቀርባል። የአያቶቻችን የእጽዋት ጥበብ፣ በህይወትዎ ላይ ለሚያጋጥሙ ችግሮችና መፍትሔዎቻቸው፣ ክፉ መናፍስትን እንዴት ማራቅ እንደምንችል፣ የብራና መጽሐፍት ጠልሰም እና ጥቅማቸው በዚህ ጥበባዊ ድህረ ገጽ ይዳሰሳል።

#አምደብርሃን ይትባረክ !!!

#አድራሻችን_ቁ/1 ምዕራብ ጎጃም ቡሬ ከ አደባባይ ወደ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን መሄጃ...

#አድራሻችን_ቁ/2 አ/አ ከ አየር ጤና ወደ አለም ባንክ መሄጃ በ ቤተል መገንጠያ በኩል ኪዳነምህረት ቤተክርስቲያን ፊት ለፊት  እንገኛለን

👉 የስራ ሰአት ከሰኞ -ቅዳሜ ከ2:30 እስከ 11:00 ሰአት  ለበለጠ መረጃ (ለሐሳብ አስተያየተዎ )
📞#0918487073 
📞#0920253444
📞#0918834904  ይደውሉልን

✅ቴሌግራም መልክት የምቀበልበት
@merigetaamedeberhan

✅ቴሌግራም መልክት የምቀበልበት
@mergetaamedeberhane

✅ፌስቡክ ገፃችን
https://www.facebook.com/profile.php?id=100076378898155

✅የቴሌ ግራም ቻናላችን
https://t.me/mergeta_amdebrhan

✅የቴሌ ግራም ቻናላችን
t.me/mergeta_amdebrhane

✳️የቲክቶክ ቻናላችን
http://tiktok.com/@mergetaamdebrhan

👉 ❗️❗️እውቀቱ ሳይኖራቸው በተመሳሳይ ፅሁፍ ኮፒ እያደረጉ ከሚያጭበረብሩ ሌቦች ተጠንቀቁ ሌባው በዝቷል ❗️❗️




ከላይ ለተፃፈው ችግር መፍትሔ የሚሆኑ እፅዋቶች ናቸው


#ሰላም
#ፍቅር
#ጤና ለእምየ ኢትዮጵያ እንዲሁም ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ይሁን።

ዛሬ ስለ ......................
              #ፍርሃት
              #ዓይነ ጥላ
              #ድንጋጤ
              #መንቀጥቀጥ እና መፍትሔዎቻቸው የምናይ ይሆናል።
           
#ፍርሃት እንዲሁም ዓይነ ጥላ ከልጅነት  ጀምሮ እስከ  እውቀት ስነ ልቦናዊ፣ማሕበራዊ፣እንዲሁም አካላዊ  ችግሮችን መፍጠር የሚችል በአብዛኛው ሰው የሚገኝ በሽታ ነው።

#ፍርሃት ወይንም ዓይነጥላ የሚባለው ችግር በዙርያችን ባሉ ለሰዎች ቅርብ የሆኑ ቁራኛ ሁነው ሰዎችን ለማሰቃየት የተዘጋጁ ፣ህይወትን የሚያጨልሙ፣ በክፉ መናፍስቶች የሚከሰት በሽታ ነው።

#ፍርሃት እንዲሁም መንቀጥቀጥ የአጋንንት ሴራ እንዲሁም የክፉ መናፍስት ተንኮል ከሰው ዘንዳ ያላቸው ቅናት እና ተንኮል የሚያንጸባርቁበት እንዲሁም የምያሸማቁቅበት ክስተት ነው።

#የፍርሃት እና የዓይነ ጥላ ምልክቶች፦ብዙ ጊዜ አጋንንት በቅናት መንፈስ ሰዎችን በመተናኮል በየትኛውም መንፈሳዊ እንቅስቃሴዎቻችን የዘወትር ፈተናዎች የሆኑት ጥንተ ጠላቶቻችን ውግያቸው እጅግ በረቀቀ ስልታቸው ከሰዎች ዘንዳ በመላመድ የየእለት ተግባራችንን በመላመድ እንዳናስተውላቸው ወጥመዳቸውን በማጥመድ ለብዙ ፈተናዎች ይዳርጉናል።

ከዚህም የተነሳ የፍርሃት እና የዓይነ ጥላ መናፍስቶች የሚፈጥሯቸው ችግሮች ከስር በትንሹ አስቀምጫቸዋለሁ።

የሰዎች ፍራቻ
የስራ ፍራቻ
የትዳር ፍራቻ
የትምህርት ፍራቻ
የመብረቅ ፍራቻ
የወሲብ ፍራቻ
የብቸኝነት ፍራቻ
የአይጥ ፍራቻ
የጭለማ ፍራቻ
የእባብ ፍራቻ
የእሳት ፍራቻ
የሞት ፍራቻ.....ወዘተ

#እነዚህ እና የመሳሰሉት ፍራቻዎች ትልቅ የስነ ልቦና ቀውስ መሆናቸውን የተለያዩ ምሁራኖች በተለያዪ መንገድ ግንዛቤ ሲሰጡ ይስተዋላል።
ወደ መንፈሳዊ ሕይወት ስንገባ ግን ከላይ የተጠቀሱት ችግሮች የሚፈጥሩ ቀናተኞች  እንዲሁም የሰው ልጅ ወደ ፈጣሪው መቅረቡ የሚያንገበግባቸው ክፉ መናፍስት መሆናቸው አስረግጦ ያስረዳናል።

#ውድ ቤተሰቦቼ በየእምነታችሁ ጽኑ ጊዜው የፈተና እና የመናፍስት ውግያ የበዛበት ዘመን ነውና!እምነታችሁም አጠንክሩ !መናፍስትንም መርምሩ!የጥልቁ ዓለም ተላላኪዎችንም አጋልጡ!

#የፍርሃት መናፍስቶች፦
ወደ ቤተ ክርስትያን ፣ወደ ገዳም፣ወደ ጸሎት ቦታ ለመቅረብ በምትፈልጉበት ጊዜ ብዙ ፈተናዎች ሊደርስባችሁ ይችላልና ተስፋ አትቁረጡ።
ለምሳሌ፦እንቅልፍ ማብዛት፣ድብርት፣የወር አበባ፣ህልመ ለሊት፣ፍርሃት፣ጭንቀት የመሳሰሉት ምልክቶች ሊታዩባችሁ ይችላል እና በጸሎት ያሸንፉ።

#ዓይነ ጥላ እና የፍርሃት መናፍስት፦
አእምሮን በመቆጣጠር ፣የልብ ምትን በመጨመር፣ የሆድ ሽብር በመፍጠር፣የሆድ ቁርጠት በማብዛት፣የእግር እና እጅ ቁርጥማት፣የወገብ ሕመም፣የወር አበባ ማብዛት፣ከፍተኛ የራስ ህመም በመፍጠር ትልቅ ማሕበራዊ ቀውሶችን ሊፈጥሩ ይችላሉ ።

#ጸሎት
#ስግደት
#ንስሀ
#እምነት
#ጥበብን በማጠንከር ፍርሃትን ዓይነ ጥላን ማስወገድ እንችላለን እና በእምነታችን እንጠንክር።

#ጥበባዊ የፍርሃት እና የዓይነ ጥላ መፍትሔዎች

#የምድር እንቧይ ሥር
#የአቶች ሥር
#የሴት ቀስት ሥር
#የሐረግ ሬሳ ሥር

#እነዚህን ዕጽዋቶችን በንጽህና አድርቀው አድቅቀው በመፍጨት እንዲሁም ነፍተው በትንሿ የሻይ ማንኪያ ከሁሉም አንድ አንድ በመለካት በንፁሕ ሩብ ኪሎ ማር በመለወስ ጧት ጧት ለ ሰባት ቀን ይውሰዱ።
ፍርሃትዎ ይጠፋል የዓይነ ጥላ መናፍስትንም ያስወግዳል።
ተፈትኖ ያለፈ የአባቶች ሁነኛ ጥበብ ነው።

እንዲሁም ከዚህ በፊት የላኩላችሁ በከርቤ ዕጣን ተጸልዮ ማታ ማታ የሚታጠንም ትልቅ መፍትሔ የሰጣቸው ሰዎች ምስክር ናቸውና።
ሳምንቱን አብራችሁ ማታ ማታ ተጠቀሙ።

#አምደብርሃን ይትባረክ !!!

#አድራሻችን_ቁ/1 ምዕራብ ጎጃም ቡሬ ከ አደባባይ ወደ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን መሄጃ...

#አድራሻችን_ቁ/2 አ/አ ከ አየር ጤና ወደ አለም ባንክ መሄጃ በ ቤተል መገንጠያ በኩል ኪዳነምህረት ቤተክርስቲያን ፊት ለፊት  እንገኛለን

👉 የስራ ሰአት ከሰኞ -ቅዳሜ ከ2:30 እስከ 11:00 ሰአት  ለበለጠ መረጃ (ለሐሳብ አስተያየተዎ )
📞#0918487073 
📞#0920253444
📞#0918834904  ይደውሉልን

✅ቴሌግራም መልክት የምቀበልበት
@merigetaamedeberhan

✅ቴሌግራም መልክት የምቀበልበት
@mergetaamedeberhane

✅ፌስቡክ ገፃችን
https://www.facebook.com/profile.php?id=100076378898155

✅የቴሌ ግራም ቻናላችን
https://t.me/mergeta_amdebrhan

✅የቴሌ ግራም ቻናላችን
t.me/mergeta_amdebrhane

✳️የቲክቶክ ቻናላችን
http://tiktok.com/@mergetaamdebrhan

‼️ማስጠንቀቂያ የምፅፈውን ኮፒ በማድረግና አስመስለው ድምፃቸውን የሽማግሌ በማስመሰል መሪጌታ ነኝ እያሉ የሚያጭበረብሩ ሌቦች ስላሉ በተቻላችሁ ሀቅም ጥንቃቄ እንድታደርጉ ለማሳሰብ እወዳለሁ !!!

Показано 13 последних публикаций.