Фильтр публикаций


" የ12ኛ ክፍል ፈተና ከአንድ ወር / ከአንድ ወር ተኩል በኃላ ለመስጠት ዝግጅት እየተደረገ ነው " - ብርሃኑ ነጋ (ፕሮፌሰር)

የትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕሮፌሰር) የዘንድሮው የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከአንድ ወር / ከአንድ ወር ተኩል በኃላ እንደሚሰጥ ጠቁመው " ይሄ አራተኛው ነው በአዲሱ የፈተና አሰጣጥ ፈተና የሚሰጥበት " ብለዋል።

ትምህርት ሚኒስቴር ባለፉት ዓመታት የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከትምህርት ቤቶች ወጥቶ ተማሪዎችን ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ አስገብቶ ፈተና እንዲሰጥ እያደረገ መሆኑ አስታውቀው ትምህርት ሚኒስትሩ ስለዘንድሮው የ2017 ዓ/ም ፈተና 150 ሺህ ተማሪዎች ፈተናቸውን በኦንላይ እንዲወስዱ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል።

ብርሃኑ ነጋ (ፕሮፌሰር) ፥ " እንደ ከዚህ ቀደሙ አድካሚ በሆነ ከቦታ ቦታ ልጆችን እያዘዋወሩ ከመሄድ ባለፈው ዓመት 29 ሺህ ተማሪ ነበር ኦንላይን ፈተና የሰጠነው ዘንድሮ ደግሞ 150 ሺህ ተማሪ ኦንላይን ፈተና ለመስጠት እየተዘጋጀን ነው " ያሉ ሲሆን ብሔራዊ ፈተና የሚሰጥበትን ቀን ቆርጠው ባይናገሩም ፈተናው ከአንድ ወር / ከአንድ ወር ተኩል በኃላ እንዲሰጥ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ጠቁመዋል።

Via @mussesolomon


ባለሁለትና ባለሦስት እግር ተሽከርካሪዎች ወደ አገር ውስጥ እንዳይገቡ ተወሰነ

በነዳጅ የሚሠሩ ባለሁለትና ባለሦስት እግር ተሽከርካሪዎች ወደ አገር ውስጥ እንዳይገቡ መወሰኑን፣ የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡

በተለምዶ ባጃጅ የሚባሉት ባለሦስት እግር ተሽከርካሪዎችና ባለሁለት እግር ሞተር ብስክሌቶች ወደ አገር ውስጥ ማስገባት እንደማይቻል የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ደኤታ አቶ በሪሁ ሐሰን ተናግረዋል፡፡

ሚኒስትር ደኤታው ይህንን ያሉት ሚያዝያ 2 ቀን 2017 ዓ.ም. አሃድ ቢዝነስ ግሩፕ፣ በአገር ውስጥ የተመረቱ በኤሌክትሪክ የሚሠሩ ባለሁለትና ባለሦስት እግር ተሽከርካሪዎችን ለገበያ ማቅረቡን በወዳጅነት ፓርክ በተዘጋጀ ሥነ ሥርዓት ሲያስታውቅ ነው፡፡

ኢትዮጵያ በየዓመቱ ለነዳጅ እስከ ስድስት ቢሊዮን ብር እንደምታወጣ የተናገሩት አቶ በሪሁ፣ ‹‹በታዳሽ ኃይል ላይ ያለንን ዕምቅ አቅም ተጠቅመን ከውጭ ከሚገባውን ደረጃውን ያልጠበቀ፣ ነዳጅ ላይ ጥገኛ ከመሆንና አዙሪት ውስጥ ከመግባት ይልቅ፣ በኤሌክትሪክ የሚሠሩ ተሽከርካሪዎችን እንደአማራጭ መውሰድ አለበት "ብለዋል።

Via @mussesolomon


ቻይና የክብደት መጠናቸው ከ50 ኪሎ ግራም በታች የሆኑ ዜጎቿ ከመኖሪያቸው እንዳይወጡ አሳሰበች

በቻይና ሰሜናዊ ክፍል ዝናብ የቀላቀለ ከባድ ነፋስ መከሰቱን ተከትሎ የሰውነት ክብደት መጠናቸው ከ50ኪሎ ግራም በታች የሆኑ ዜጎቿ ከመኖሪያቸው እንዳይወጡ አሳስባለች።

ከሀገሪቱ ደቡባዊ አዋሳኝ ሞንጎሊያ መነሻውን ያደረገው ነፋስ በሰዓት 150 ኪሎ ሜትር በመሸፈን ቤጂንግ፣ ቲያንጂንን እና ሄበይን ጨምሮ የቻይናን ሰሜናዊ ክፍሎች እየመታ የሚገኝ አሁን ላይ የተከሰተው ከባድ ንፋስ ባለፉት 10 ዓመታት ከተመዘገቡት የመጀመሪያው መሆኑ ተገልጿል።

የተከሰተው ከባድ ንፋስ ደረጃ 13 ሲሆን ዝናብ ፣ በረዶ እና ነጎድጓድ የቀላቀለ  መሆኑን የቻይና  የአየር ትንበያ ኤጀንሲ የገለፀ ሲሆን ይህን ተከትሎ  የሰውነት ክብደታቸው ከ50 ኪሎ ግራም በታች የሚመዝኑ ዜጎች በንፋሱ እንዳይወሰዱ በማሰብ ነው ከመኖሪያቸው እንዳይወጡ ማስጠንቀቂያው የተሰጠው።

እንዲሁም ንፋሱ የባሰ አደጋ እንዳያስከትል አስቸኳይ እርምጃዎች እየተወሰዱ እንደ ሚገኙ እና ፓርኮች እንዲዘጉ እንዲሁም ወሳኝ እና አስፈላጊ ያልሆኑ በረራዎች እንዲሰረዙም መደረጋቸው ተገልጿል።

Via @mussesolomon


ኢትዮጵያ በአህዮች ብዛት በዓለም የመጀመሪያ ደረጃን ይዛለች ።

በዓለም ላይ 50 ሚሊዮን አህዮች እንዳሉ የ2025 ሪፖርት ያመለክታል። በኢትዮጵያ 10 ሚሊዮን አህዮች እንደሚገኙ ተገልጿል።

ካለፈው አመት ጋር ሲነፃፀር ብዛቱ የጨመረ ሲሆን በዓለማችን ትንሽ አህዮች ያሉባት ሀገር ሱሪናሜ ስትሆን ሰባት አህዮች ብቻ ይገኛሉ። በአሜሪካ 52ሺህ አህዮች ይገኛሉ።

ኢትዮጵያ በ10.6 ሚሊዮን አህዮች ቀዳሚ ስትሆን ጐረቤት ሀገር ሰሜን ሱዳን በ7.6 ሚሊዮን አህዮች ሁለተኛ ሆናለች።
በ 3ኛ ደረጃ ፓኪስታን 5.8 ሚሊዮን
በ 4ኛ ደረጃ ቻድ 4.6 ሚሊዮን
በ 5ኛ ደረጃ ሜክሲኮ 3.3 ሚሊዮን በመከተል ቦታውን ይዘዋል።

Via @mussesolomon


በመዲናዋ እስከ ምሽት 4:00 ድረስ የሕዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት በማይሰጡ አሽከርካሪዎች ላይ የ5 ሺሕ ብር ቅጣት እንደሚጣል ተገለጸ

በአዲስ አበባ ከተማ እስከ ምሽት 4:00 ድረስ የሕዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት በማይሰጡ አገልግሎት ሰጪዎች ላይ የ5 ሺሕ ብር ቅጣት እንደሚጣል የከተማ አስተዳደሩ ትራንስፖርት ቢሮ አስታውቋል፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ በደንብ ቁጥር 185/2017 በተደነገገው ደንብ መሠረት ማንኛውም የሕዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት ሰጪ እስከ ምሽት 4፡00 ሰዓት የትራንስፖርት አገልግሎትን መስጠት እንደሚጠበቅበት አሳውቆ ማንኛውም የሕዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት ሰጪ ከምሽቱ 4፡00 ሰዓት በፊት የትራንስፖርት አገልግሎትን ማቋረጥ፣ ከስምሪት መስመር ውጪ አገልግሎት መስጠት፣ አቆራርጦ መጫንና የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ ካወጣው ሕጋዊ ታሪፍ ውጪ ሕብረተሰቡን ማስከፈል እንደማይቻል ቢሮው በጥብቅ አሳስቧል፡፡

Via @mussesolomon


ኢትዮጵያ በአለም አቀፍ የፓስፖርት ጥንካሬ መመዘኛ 185ኛ ደረጃ ላይ ስትገኝ አየርላንድ ቀዳሚ ሆናለች።

ኢትዮጵያ  ትላንት በዓለም አቀፍ አማካሪ ድርጅት ኖማድ ካፒታሊስት ይፋ በሆነው የ2024 የኖማድ ፓስፖርት መመዘኛ ከ199 ሀገራት ተወዳድራ 185ኛ ደረጃን ይዛለች።

አየር ላንድ አንደኛ ደረጃ ላይ ስትገኝ በፓስፖርቷ 176 ሀገር ያለ ቪዛ ያስገባሉ፤ የኢትዮጵያ ፓስፖርት 57 ሀገራት ያለ ቪዛ ወይንም በደረሱበት ሀገር አየር ማረፊያ ላይ ቪዛ ይመታለታል፤ ጎረቤት ሀገር ደበቡ ሱዳን 184ኛ  ኬንያ 134ኛ ኤርትራ ደግሞ 197ኛ ደረጃ ላይ የተቀመጠች ሲሆን አፍጋኒታስታን 199ኛ ደረጃ መጨረሻ ላይ ተቀምጣለች።

መመዘኛው ከቪዛ ነፃ የመጓዝ እድልን ብቻ ሳይሆን እንደ ግብር፣ ዓለም አቀፋዊ ገጽታ እና የግል ነፃነቶችን የመሳሰሉ ነገሮችን ከግምት ውስጥ በማስገባት በዓለም ዙሪያ ያሉ 199 ፓስፖርቶችን ጥንካሬ ገምግሟል።

ከፍተኛ ደረጃ ላይ የሚገኙት የአውሮፓ ያልሆኑ ፓስፖርቶች የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች እና ኒውዚላንድ ሲሆኑ ሁለቱም በ10ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጠዋል።

Via @mussesolomon


የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ከመመረቃቸው በፊት ለአንድ ዓመት እንዲያስተምሩ ሊገደዱ ነው።

ትምህርት ሚኒስቴር የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ከመመረቃቸው በፊት ማኅበረሰቡን ለአንድ ዓመት በቅድሚያ እንዲያስተምሩ ወይም እንዲያገለግሉ የሚያደርግ አሰራር ተግባራዊ ለማድረግ ዕቅድ መያዙን አስታወቁ ብርሃኑ ነጋ (ፕሮፌሰር)።

Via @mussesolomon


ትራምፕ ለቲክቶክ መተግበሪያ ያስቀመጡት የጊዜ ገደብ አንድ ሳምንት ብቻ ቀርቶታል።

ከጥቂት ሳምንታት በፊት የመተግበሪያውን የአገልግሎት ጊዜውን ስለማራዘም ለቀረበላቸው ጥያቄ "ይመስለኛል" የሚል ምላሽ የሰጡት ፕሬዚዳንቱ ቀጣዩ ርምጃቸው ምን ሊሆን ይችላል የሚለው በርካቶችን እያነጋገረ ይገኛል።

ቲክቶክ በአሜሪካ ምድር ከቀናት በኋላ ዳግም ይዘጋል ወይስ ዳግም የአገልግሎት ጊዜው ይራዘም ይሆን ከ ቀናት በኋላ የምናይ ይሆናል።

Via @mussesolomon


ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ለ1 ሺህ 446ኛው የዒድ አልፈጥር በዓል በሰላም አደረሳችሁ።

ዒድ ሙባረክ


Via @mussesolomon


የALX ‘Pathway Program’ን በመውሰድ፣ የአለምአቀፍ ዲግሪ እና ሙሉ ስኮላርሺፕ እድል ለማግኘት ይመዝገቡ። የዚህ ስኮላርሺፕ እድል በጥቅሉ በአመት የ85,000 አሜርካን ዶላር፣ ወይም የ11 ሚሊዮን የኢትዮጵያ ብር፣ ተመጣጣኝ ዋጋ አለው።

ALX ከ14 ታዋቂ ዓለም አቀፍ ዩኒቨርሲቲዎች ጋር የትብብር ስምምነት አለው። አብዛኛዎቹ ትምህርት ቤቶች የሚገኙት America ሲሆን፣ Europe እና South Africa የሚገኙም አሉ።

የዚህ የትብብር ስምምነት ዋና ይዘት፣ የALX Pathway ኘሮግራምን በስኬት የሚጨርሱ ልጆች፣ በእነዚህ ታዋቂ ዩኒቨርሲቲዎች ተቀባይነት እና የስኮላርሺፕ እድሎች የሚያገኙበትን መንገድ ማስፋት ነው።

የምዝገባውን ሂደት ደረጃ በደረጃ ማብራሪያ ለማየት፣ እንዲሁም ምዝገባውን በተሳካ ሁንያ ለማጠናቀቅ፣
ይህንን የቴሌግራም ቻናል ተቀላቀሉ፡- https://t.me/ALXScholarship2ndBatch

ምዝገባው ከ5 ደቂቃ በላይ አይፈጅም!


የግል ኩባንያዎች ነዳጅ እንዲያስመጡ ተፈቀደ ።

የግሉ ዘርፍ ከሽያጭ በተጨማሪ ነዳጅ ማስመጣት እንዲችል የሚፈቅደው አዋጅ ስራ ላይ ዋለ፡፡

የነዳጅ ግብይት አዋጅ ቁጥር 1363/2017 ላለፈው 11 አመት በስራ ላይ የነበረውን አዋጅ የቀየረ ሆኖ ባለፈው ጥር ነበር በፓርላማ የፀደቀው፡፡ ይህ አዋጅ በሳለፍነው ሳምንት በነጋሪት ጋዜጣ ታትሞ መውጣቱን ተከትሎ ወደ ስራ መግባቱ ነው የታወቀው፡፡

በዚህም እስካሁን በመንግስታዊው የነዳጅ አቅራቢ ድርጅት ብቻ ተይዞ የነበረውን የነዳጅ ከውጭ ገዝቶ የማስገባት ስራ ሌሎች ኩባንዎችም ማከናወን እንዲችሉ በር የሚከፍት ነው፡፡

የነዳጅ ንግድ የመንግስት የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ትግበራ አካል ሆኖ እየተሰራበት የሚገኝ መሆኑ ይታወቃል፡፡

Via @mussesolomon


የነዳጅ ዋጋን መነሻ በማድረግ ከመጋቢት 14 ቀን 2017 ዓ.ም ከምሽቱ 12 ሰዓት ጀምሮ በስራ ላይ የሚቆይ የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በሚከተለዉ መሰረት ስራ ላይ እንዲዉል በመንግስት ተወስኗል።



Via @mussesolomon


በምሽት የንግድ እና የትራንስፖርት አገልግሎት እንዲሰጥ የወጣውን ደንብ ከዛሬ ጀምሮ ተግባራዊ ይደረጋል

የአዲስ አበባ ከተማ ንግድ ቢሮ በምሽት የንግድ እና የትራንስፖርት አገልግሎት እንዲሰጥ ለማድረግ የወጣውን ደንብ ቁጥር185/2017 ከዛሬ ጀምሮ  ተግባራዊ ማድረግ መጀመሩን አስታውቋል።

ለዚህም ደንቡ በመውጣቱን  ይህ ደንብ ቀደም ብሎ የከተማ አስተዳደሩ ካቢኔ ያስተላለፈውን ውሳኔ ለማስፈጸም በመሆኑ ከዛሬ መጋቢት 10 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ ሙሉ በሙሉ ተግባራዊ መደረግ መጀመሩን ቢሮው ገልጿል።

በመንገድ ዳር ያሉ ንግድ_ቤቶች ፣ አገልግሎት ሰጭ ተቋማት እስከ ሶስት ሰዓት ተኩል የህዝብ ትራንስፖርት የሚሰጡ ደግሞ እስከ 4 ሰዓት አገልግሎት እንዲሰጡ ደንቡ ያስገድዳል፡፡

Via @mussesolomon


የመሬት መንቀጥቀጥ በሬክተር ስኬል 5.1 ተለክቷል

የአዋሽ አካባቢ ጠንካራ የመሬት መንቀጥቀጥ እንደነበር ገልጸዋል።በአዲስ አበባ በርካታ አከባቢዎች እጅግ የጠነከረ ንዝረትም ለሰከንዶች ነበር።

ከአዲስ አበባ ውጭም በርካታ ከተሞች ላይ ንዝረቱ በደምብ ተሰምቷል። የመሬት መንቀጥቀጡ ከአዋሽ በ50 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ መከሰቱን የአሜሪካ ጂኦሎጂካል ሰርቬይ ጠቁሟል።

በሬክተር ስኬልም 5.1 መለካቱን አመላክቷል።



Via @mussesolomon


በመስቀል አደባባይ ለሚከናወነው የኢፍጣር ፕሮግራም የተወሰኑ መንገዶች እንደሚዘጉ የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታወቀ!
***
ይኸውም ነገ መጋቢት 7 ቀን 2017 ዓ/ም ከቀኑ 5:00 ሠዓት ጀምሮ በመስቀል አደባባይ የሚከናወነውን የኢፍጣር ፕሮግራም ምክንያት በማድረግ፦
👉 ከኦሎምፒያ ወደ መስቀል አደባባይ (ኦሎምፒያ አደባባይ ላይ )
👉 ከጥላሁን አደባባይ ወደ ሳንጆሴፍ መብራት (ጥላሁን አደባባይ ሲሆን ከባድ ተሽከርካሪ አጎና ላይ )
👉 ከለገሃር መብራት ወደ መሰቀል አደባባይ (ለገሃር መብራት)
👉 ከቴሌ ማቋረጫ ወደ ስታድየም (ቴሌ ማቋረጫ ላይ)
👉 ከሀራምቤ መብራት ወደ መስቀል አደባባይ (ሀራምቤ መብራት ላይ )
👉 ከብሔራዊ ቤተ መንግሥት ወደ መስቀል አደባባይ (ብሔራዊ ቤተመንግሥት ላይ )
👉 ከቅዱስ ዑራኤል አደባባይ ወደ መስቀል (ባምቢስ መቅረዝ ሆስፒታል መታጠፊያ ድረስ የሚዘጋ መሆኑን በመገንዘብ አሽከርካሪዎች አማራጭ እንዲጠቀሙ የአዲስ አበባ ፖሊስ ያሳስባል።



Via @mussesolomon


የስነምግባር ጥሰት የሚፈፅሙ የአሽከርካሪ አሰልጣኞች የማስተማሪያ ፍቃድ እንደሚሰረዝ ተገለፀ።

የአዲስ አበባ አሽከርካሪና ተሸከርካሪ ፍቃድና ቁጥጥር ባለስልጣን በአዋጅ ቁጥር 1/2007 መሰረት አንድ ሰልጣኝ ሊይዝ የሚገባውን የንድፈ ሃሳብና የተግባር ክህሎት ከማስጨበጥ አንፃር ብዙሃኑ አሰልጣኞች ሃላፊነታቸውን በአግባቡ ቢወጡም፣ ውስን አሰልጣኞች እጩ አሽከርካሪዎች የሚያሰልጥኑበትን ጊዜ ከመሸራረፍ ጀምሮ ያልተገባ እና ለእንግልት የሚዳርጉ ተግባራት እንዲሁም ሌሎች የስነ ምግባር ጥሰቶች የሚፈፅሙ መኖራቸውን ቅሬታዎች ይደርሰናል ብለዋል።

ከአሽከርካሪ ዘርፍ አንፃር ተገልጋዮቻችንን ለቅሬታ የሚዳርጉ ተግባራት በአመዛኙ የአንዳንድ የማሰልጠኛ ተቋማት የሥልጠና ጥራት እና የእጩ አሽከርካሪ አሰልጣኞች የሥነ-ምግባር ጉድለት ጋር የሚያያዙ መሆናቸውን ገልፀዋል።

በድንገተኛ ምልከታና ቁጥጥር በማድረግ የማስተማሪያ ፍቃድ መንጠቅና የመሰረዝ ጥብቅ ዕርምጃ መውሰድ የሚጀመር መሆኑንም ገልፀዋል።

እጩ አሽከርካሪዎች ያልተገባ ነገር ሲገጥማችሁ በአካል በመቅረብ አልያም በነፃ የስልክ ቁጥር 7766 ጥቆማ መስጠት እንደሚሉ ተነግራል።

Via @mussesolomon


በአዲስ አበባ ብሥራተ ገብርኤል አካባቢ በሚገኘው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ካርል አደባባይ ቅርንጫፍ ላይ በዛሬው ዕለት በተፈጠረ አለመግባባት የሰዎች ህይወት ማለፉ ተሰምቷል።

በአለመግባባቱ ሳቢያ የሦስት ሰዎች ህይወት ሳያልፍ እንዳልቀረ ጉዳዩን ከተከታተሉ ሰዎች መረዳት የተቻለ ሲሆን፣ ህይወታቸው ያለፈው በባንኩ በጥበቃ ሰራተኝነት ሲያገለግሉ የነበሩ አካላት ናቸው።

ይህንን በሚመለከት የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽንን የጠየቅን ሲሆን "ጉዳዩ በምርመራ ላይ ነው" የሚል አጭር ምላሽ አግኝተናል።


Via @mussesolomon


የብሄራዊ ድህረ-ምረቃ (NGAT) መግቢያ ፈተና መጋቢት 5 እንደሚሰጥ ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል።

ትምህርት ሚኒስቴር በ2017 ዓ.ም የሶስተኛ ዙር የNGAT አመልካቾች ምዘገባ መጠናቀቁን አሳውቆ ፈተናው የሚሰጠው ዓርብ መጋቢት 5 ቀን 2017 ዓ.ም ከጠዋቱ 3፡00 ጀምሮ መሆኑንም አሳውቋል።

ተፈታኞች  በተጠቀሰው ቀንና ሰዓት በሚመደቡበት የፈተና ማዕከላት እንዲገኙ ብሏል።

ተፈታኞች ወደ ፈተና ማዕከል በሚሄዱበት ወቅት ማንነታቸውን የሚገልጽ መታወቂያ መያዝ ይጠበቅባቸዋል።

ማንኛውም ተፈታኝ ፈተናው ከመጀመሩ 3 ደቂቃ በፊት በፈተና ማዕከል መገኘት ይጠበቅበታል፡፡

የሞባይል ስልክ ይዞ በፈተና ማዕከል መገኘት ፈጽሞ የተከለከለ ነው፡፡

የፈተና ማዕከላት ምደባ በምዝገባ ፕላትፎርም የሚገለጽ ይሆናል፡፡

via @mussesolomon


የመጀመሪያው ባዮሜትሪክ ስማርት ሽጉጥ

በአሜሪካ ውስጥ ለመጀመሪያ ጊዜ ይህንን ባዮሜትሪክ “ስማርት ሽጉጥ” ገበያ ላይ ዋለ።

ይህ ሽጉጥ የጣት አሻራ እና የፊት ለይቶ ማወቂያ ቴክኖሎጂን(facial recognition) በመጠቀም የተፈቀደላቸው ተጠቃሚዎች ብቻ ሊጠቀሙት እንዲችሉ እና ከባለ ንብረቱ ውጪ መከልከል የሚችል የጦር መሳሪያ ነው።

ይህ ስማርት ሽጉጥ የሜካኒካል የተኩስ ዘዴዎችን በኤሌክትሮኒክ ስርዓት የተካ ሲሆን የሊቲየም-አዮን ባትሪ የሚጠቀም ስማርት ሽጉጡ ነው። በአንድ ጊዜ ቻርጅ ለብዙ ወራት መስራት እንደሚችል ተናግረዋል።

የስማርት ሽጉጥ እስከ አምስት የተመዘገቡ ተጠቃሚዎችን የሚፈቅድ ሲሆን ይህም ለቤተሰብ አገልግሎት መዋል እንዲችል ያደርገዋል፣ ሽጉጡ የተፈቀደለትን ተጠቃሚ እጅ ከለቀቀ፣ እራሱን በራሱ እንደሚዘጋ አሳውቀዋል።


via @mussesolomon


የኤሌክትሪክ ታሪፍ ድጋሚ የዋጋ ጭማሪ ሊደረግበት ነው።

በዚህም መሠረት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ከሚያዝያ እስከ ሰኔ ወር ድረስ በመኖሪያ ቤት ታሪፍ ላይ 0.50 ኪሎ ዋት ሰዓት የሚጠቀሙ ደንበኞች የፍጆታ ታሪፍ 0.60 ሳንቲም እንዲከፍሉ የሚደረግ ሲሆን፣

የአገልግሎት ክፍያ ተመንን በተመለከተ ለድኅረ ክፍያ አሥር ብር ከ95 ሳንቲም ሲከፍሉ፣ ለቅድመ ክፍያ አራት ብር ከ18 ሳንቲም እንደሚከፍሉ ሪፖርተር ያገኘው ሰነድ ያሳያል፡፡

የመኖሪያ ቤት ታሪፍን በተመለከተ ከ51 እስከ 100 ኪሎ ዋት የሚጠቀሙ ደንበኞች አንድ ብር ከ49 ሳንቲም፣ ከ101 እስከ 200 ኪሎ ዋት ሁለት ብር ከ67 ሳንቲም፣ ከ201 እስከ 300 ኪሎ ዋት የሚጠቀሙ ደንበኞች ሦስት ብር ከ84 ሳንቲም እንደሚከፍሉና በየኪሎ ዋቱ መጠን ክፍያው የሚለያይ እንደሆነ ሰነዱ ያስረዳል።

@mussesolomon

Показано 20 последних публикаций.